fa
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

رفتن به کانال در Telegram

EEP Communication

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام EEP Communication

کانال EEP Communication (@eepcommuication) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 539 مشترک است و جایگاه 8 340 را در دسته فناوری و برنامه‌ها و رتبه 2 161 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 539 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 28 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 1 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -4 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 24.98% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 16.34% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 882 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 539 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 8 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
EEP Communication

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 29 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته فناوری و برنامه‌ها تبدیل کرده‌اند.

15 539
مشترکین
-424 ساعت
-147 روز
+130 روز
آرشیو پست ها
photo content
+8

በጣቢያው ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት መከፈቱ ማኅበራዊ መስተጋብርን ያሳድጋል ……..///…… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በግልገል ጊቤ 1 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ የተከፈተው የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት ለጣቢያው ሠራተኞችና ለአካባቢው ማኅበረሰብ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ደሳለኝ ንጉሳ እንደገለጹት በጣቢያው ከኬጂ 1 እስከ ኬጂ 3 የሚያስተምር የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት በተያዘው በጀት ዓመት ሥራ ጀምሯል። ትምህርት ቤቱ ከመከፈቱ በፊት የጣቢያው ሠራተኞችና የአካባቢው ማኅበረሰብ ልጆቹ ከ5 ኪሎ ሜትር በላይ ተጉዘው ሶኮሩ ከተማ ድረስ በመሄድ ይማሩ እንደነበረ አንስተዋል፡፡ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቱ መከፈት የጣቢያው ሠራተኞች ልጆቻቸውን ያለሀሳብ በቅርበት እንዲያስተምሩ በማድረግ የሥራ ውጤታማነትን እንደሚያሳድግ ኃላፊው ገልጸዋል። የአካባቢው ማኅበረሰብም ለልጆቹ በአቅራቢያው የቅድመ መደበኛ ትምህርት በማግኘቱ ከጣቢያው ጋር ያለውን መስተጋብር እንደሚያሳድገው ኃላፊው አብራርተዋል። የትምህርት ቤቱ የወላጅ መምህራን ኮሚቴ አባል እና የጣቢያው የኦፕሬሽን ቴክኒሽያን አቶ ታሪኩ ተስፋዬ በበኩላቸው የጣቢያው የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት ከወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት ባገኘው ፍቃድ 52 የሚደርሱ ተማሪዎችን ተቀብሎ እያስተማረ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ቀደም ሲል የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ሩቅ ቦታ በመሆናቸው አብዛኛው ወላጅ ልጆቹን ለማስተማር ይቸገር እንደነበር ያስታወሱት አቶ ታሪኩ አሁን ግን በጣቢያው የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት በመከፈቱ የጣቢያው ሠራተኛና የአካባቢው ማኅበረሰብ ልጆቹን ያለምንም ችግር እንዲያስተምር ዕድል እንደተፈጠረለት ጠቁመዋል። ትምህርት ቤቱ በአካባቢው ካለው የትምህርት ፍላጎት አንጻር በቀጣይ የትምህርት ዘመን የመቀበል አቅሙን ለማሳደግና የጥራት ደረጃውን ለማሻሻል ማቀዱን አቶ ታሪኩ ገልጸዋል። የትምህርት ቤቱ መምህርት አየሁሽ ታምራት በበኩሏ ትምህርት ቤቱ ሥራ የጀመረው ዘንድሮ ቢሆንም የመማር ማስተማሩ ሂደትና የጣቢያው ድጋፍ አበረታች መሆኑን ገልጻለች። ትምህርት ቤቱ ከዚህ በላይ እንዲያድግና በግብዓት የተሟላ እንዲሆንም የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርባለች። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 16 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

የሰው ኃይል የማሟላትና የአቅም ግንባታ ሥራዎች እየተሰሩ ነው ……….///………. በጊቤ II የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የሰው ኃይል የማሟላትና የአቅም ግንባታ ሥራዎች በትኩረት እየተሰሩ መሆኑን የጣቢያው የሰው ኃይል አስተዳደርና የንብረትና ጠቅላላ አገለግሎት ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ታምራት ቸኮል እንደገለፁት መዋቅራዊ የሰው ኃይል ዕቅድ የሚጠይቀውን የሰው ኃይል በዕድገት፣ በዝውውርና በቅጥር ከማሟላት ባሻገር የጣቢያውን የሥራ እንቅስቃሴ ለማሳለጥ የሚያግዙ የአጭር እና የረጅም ጊዜ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠናዎች እየተሰጡ ነው፡፡ ተቋሙ ከዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመነጋገር በሳምንቱ መጨረሻ ቀናት ባመቻቸው የትምህርት ዕድል በመጀመሪያ ዙር በኤሌክትሪካል እና ኮምፒውተር ኢንጂነሪግ የትምህርት መስክ 38 ሠራተኞች በመጀመሪያ ዲግሪ መመረቃቸውንና በሁለተኛ ዙር ከ40 በላይ ሠራተኞች ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ መሆናቸውን ገልፀዋል። እንደ ሥራአስኪያጁ ገለፃ በቴክኒክና ሙያ የትምህርት መስክ ከወልቂጤ ኮሌጅ ጋር በመነጋገር በቲቪኢቲ ከደረጃ አንድ አስከ አራት 20 ሠራተኞች ትምህርታቸውን አጠናቀው ተመርቀዋል፡፡ ተቋሙ ከቮይት ኃይድሮ ካምፓኒ ባገኘው የሥልጠና ዕድል በሁለት ዙር ሠራተኞቹ የሥራ ላይ ስልጠና እና የልምድ ልውውጥ በማመቻቸት ሙያቸውን እንዲያሳድጉ ማድረጉን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል። ምቹ የሥራ አካባቢ ለመፍጠር የጣቢያውን መንገድ የማደስ ሥራ መጀመሩን እና ሠራተኛው ተረጋግቶ እንዲሰራ ለማገዝ የመኖሪያ ቤት ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል። 420 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው የጊቤ II የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ካሉት 227 የሥራ መደቦች ውስጥ ከ55 በመቶ በላይ የሚሆነው የተሸፈነው በአካባቢው ማህበረሰብ ነው፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 16 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+7

የማከፋፈያ ጣቢያውን ግንባታ በተያዘው በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ……….///……… የማሻ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታን በተያዘው በጀት ዓመት መጨረሻ ለማጠናቀቅ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፕሮጀክቱ የሲቪል ሥራዎች ተቆጣጣሪ አስታወቁ። ተቆጣጣሪው አቶ ፍቃዱ ቂጤሳ እንደገለፁት በአሁኑ ወቅት የማከፋፈያ ጣቢያው የመቆጣጠሪያ ክፍልና የኦፕሬተሮች መኖሪያ ቤት ግንባታ፣ የትራንስፎርመሮች ተከላ፣ የስዊች ያርድ እና ሌሎች የብረት ተከላ ሥራዎች ተጠናቀዋል። የማከፋፈያ ጣቢያው የጠጠር ምንጣፍ ሥራ 85 በመቶ እንዲሁም የውስጥ አጥር ሥራ 80 በመቶ መጠናቀቁንም አቶ ፍቃዱ አንስተዋል። የሰርኪዩት ብሬከሮች ተከላ፣ የውስጥ ለውስጥና ጣቢያውን ከዋናው መንገድ የሚያገናኝ የኮንክሪት አስፓልት መንገድ፣ በመቆጣጠሪያ ክፍሉ የሚገኙ እና ሌሎች የፖወር ኬብሎችን የማገናኘት ሥራዎች በቀጣይ እንደሚከናወኑም ነው የገለፁት። እንደ አቶ ፍቃዱ ገለፃ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው የሲቪል ሥራ 91 በመቶ እንዲሁም የኤሌክትሮሜካኒካል ሥራ 75 በመቶ የተጠናቀቀ ሲሆን አጠቃላይ የማከፋፈያ ጣቢያው የግንባታ ሥራ 79 በመቶ ላይ ደርሷል። ቀሪ የሲቪልና የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎችን ማጠናቀቅ እንዲሁም የፍተሻና ሙከራ ሥራዎችን በተያዘው በጀት ዓመት መጨረሻ በማከናወን ለአገልግሎት ዝግጁ ለማድረግ እየተሰራ እንደሆነም ተቆጣጣሪው ተናግረዋል። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው እያንዳንዳቸው 31 ነጥብ 5 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው ሁለት ትራንስፎርመሮች እንዲሁም አንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ገቢና ስድስት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት። ፕሮጀክቱን እያከናወነ የሚገኘው የሲኖ ሀይድሮ ኮርፖሬሽን ሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ሀይማኖት አዳነ በበኩላቸው የማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ በተያዘው መርሃ ግብር መሠረት አጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ለማድረግ ድርጅታቸው ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። የማሻ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ የግንባታ ሥራ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር በማሻ ከተማና በዙሪያው በሚገኙ ወረዳዎች የሚስተዋለውን የኃይል መቆራረጥ ለመቅረፍ እና በአካባቢው የተለያዩ የግብርና ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎችን ለማስፋፋት ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል። ለፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ ከ6 ነጥብ 56 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ እና ከ6 ነጥብ 97 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት የተያዘ ሲሆን የፋይናንስ ወጪውም ሙሉ በሙሉ በዓለም ባንክ የሚሸፈን ነው ተብሏል። የማከፋፈያ ጣቢያውን የግንባታ ሥራ ሲኖ ሃይድሮ በተባለ የቻይና ኩባንያ እየተከናወነ ሲሆን በአማካሪነት ደግሞ ኢ ኤል ሲ የተባለ የጣሊያን ኩባንያ እየተሳተፈበት ይገኛል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 15 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

ጣቢያው 987 ነጥብ 9 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል አመንጭቷል ……….///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግልገል ጊቤ 2 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት 6 ወራት 987 ነጥብ 9 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨቱን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ሹመት በላቸው እንደገለፁት የኃይል ማመንጫ ጣቢያው በ2016 በጀት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት አንድ ሺህ 67 ነጥብ 6 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ለማመንጨት አቅዶ 987 ነጥብ 9 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ በማመንጨት የዕቅዱን 92 ነጥብ 54 በመቶ አሳክቷል። አፈፃፀሙ ከዕቅድ አንጻር ያነሰው በበጀት ዓመቱ መጀመሪያ በማቀዝቀዣ ማሽኖች ላይ ያጋጠሙ ችግሮችን ለመፍታት የጥገና ሥራዎች ሲከናወኑ በተፈጠረ ክፍተት ነው ብለዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በበጀት ዓመቱ ቀሪ ወራት ከጣቢያዉ ደህንነት እና እየተሰሩ ካሉ ሥራዎች አንጻር ከዚህ የላቀ አፈጻጸም ማስመዝገብ አልያም የታቀደውን የኃይል ምርት ማሳካት ይቻላል፡፡ የግልገል ጊቤ 2 ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ2016 በጀት ዓመት 1 ሺህ 908 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል የማመንጨት ዕቅድ ይዟል፡፡ በ2002 ዓ.ም ተመርቆ በይፋ ስራ የጀመረው የኃይል ማመንጫ ጣቢያው 420 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም አለው። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 15 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

ጣቢያው በበጀት ዓመቱ ለማመንጨት የያዘውን ዕቅድ የሚያሳካ ውሃ በግድቡ ውስጥ መኖሩን ገለጸ ……….///……… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግገል ጊቤ 1 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በበጀት ዓመቱ 969 ጊጋ ዋት ስዓት ለማመንጨት የያዘውን ዕቅድ ለማሳካት የሚያስችል የውሃ መጠን በግድቡ ውስጥ መኖሩን አስታወቀ። የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ ንጉሳ እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ለማመንጨት ካቀደው 572 ነጥብ 8 ጊጋ ዋት ሰዓት ውስጥ 93 ነጥብ 2 በመቶውን አሳክቷል፡፡ በበጀት ዓመቱ ያመነጨው የኤሌክትሪክ ኃይል ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከሞላ ጎደል ተመሳሳይ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል። ጣቢያው አሁን ካመረተው በላይ የማምረት አቅም ቢኖረውም ግድቡ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ወራት ዘግይቶ በመሙላቱና በሐምሌ ወር ውስጥ አንዱ ተርባይን ውሃ ለመያዝ ሲባል እንዲቆም በመደረጉ አፈጻጸሙ ዝቅ ማለቱን ሥራ አስኪያጁ አብራርተዋል። እንደ አቶ ደሳለኝ ገለፃ አሁን ላይ ጣቢያው ያሉት ሦስቱም ተርባይኖች በሙሉ አቅማቸው እየሰሩ በመሆኑና በግድቡ ውስጥ በቂ የውሃ መጠን ስላለ በበጀት ዓመቱ ቀሪ ወራት ለማመንጨት የተያዘውን ዓመታዊ ዕቅድ ለማሳካት አስቸጋሪ አይሆንም። የጊቤ አንድ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ውሃ የሚሞላበት ከፍታ ከባህር ጠለል በላይ 1 ሺህ 671 ነጥብ 09 ሜትር ሲሆን አሁን ላይ ውሃው ከባህር ጠለል በላይ 1 ሺህ 666 ነጥብ 79 ሜትር ላይ ይገኛል። በ1996 ዓ.ም ተመርቆ አገልግሎት መስጠት የጀመረው የጊቤ አንድ የውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ 184 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም አለው፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 14 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ የሥራ መደቡ መጠሪያ - ገንዘብ ያዥ(ካሸር) የመመዝገቢያ ቦታ - ኮተቤ ብረታ ብረት ፋብሪካ ፊት ለፊት በሚገኘው የተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት፤ ማሳሰቢያ፡- በተቋሙ የጀነሬሽን ኮንስትራክሽን ህንፃ ቁጥር 13 በር ላይ በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ የማይመለስ የትምህርት ማስረጃ እና የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት () ኮፒ በማስገባት መመዝገብ ይችላሉ፡፡ ዝርዝር መረጃው ተያይዟል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 13 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

ጣቢያው በ6 ወራት ውስጥ ከአምስት መቶ ሰላሳ ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል አመንጭቷል ..........///......... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጊቤ 1 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ውስጥ 532 ነጥብ 8 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ ማመንጨቱን የጣቢያው ኃላፊ አስታወቁ። ኃላፊው አቶ ደሳለኝ ንጉሳ እንደገለፁት ጣቢያው በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ 6 ወራት ለማመንጨት ካቀደው 572 ነጥብ 8 ጊጋ ዋት ሰዓት ውስጥ 532 ነጥብ 8 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ በማመንጨት የዕቅዱን 93 ነጥብ 2 በመቶ አሳክቷል። በበጀት ዓመቱ ጣቢያው ያመነጨው ኃይል ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከሞላ ጎደል ተመሳሳይ መሆኑን ጠቁመዋል። እንደ ኃላፊው ገለፃ ጣቢያው ከዚህ በላይ የማምረት አቅም ቢኖረውም በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ወራት ግድቡ ባለመሙላቱና በሐምሌ ወር አንዱ ተርባይን ውሃ ለመያዝ ሲባል እንዲቆም በመደረጉ አፈጻጸሙ ከዕቅዱ ሊያንስ ችሏል። በበጀት ዓመቱ 969 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ ለማመንጨት ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን ኃላፊው ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት ጣቢያው ያሉት ሦስቱም ተርባይኖች በሙሉ አቅማቸው እየሰሩ በመሆኑና በግድቡ ያለው የውሃ መጠን በበጀት ዓመቱ ቀሪ ወራት ለማመንጨት የተያዘውን ዓመታዊ ለማሳካት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። በ1996 ዓ.ም ተመርቆ አገልግሎት መስጠት የጀመረው የጊቤ አንድ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ 184 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም አለው፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 13 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ በማለት ልባዊ ምኞቴን እገልፃለሁ፡፡ ተቋማችን ከተለያዩ ታዳሽ የኃይል ምንጮች ከ5 ሺህ ሁለት መቶ ሜጋ ዋት በላይ ኃይል የማመንጨት አቅም ፈጥሯል። ከ189 በላይ የማከፋፈያ ጣቢያዎችን እና ከ20 ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ ርዝማኔ ያላቸው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን በመገንባት የሀገራችንን የኃይል ፍላጎት አሟልቶ "የአፍሪካ የኃይል ማዕከል ለመሆን" በትጋት እየሰራ ይገኛል፡፡ የሦስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ነድፎ ተግባራዊ ማድረግ ጀምሯል። ይህ ሀገራዊና ተቋማዊ ትልም እንዲሳካና የተገነቡ መሰረተልማቶች ለታለመላቸው ዓላማ እንዲውሉ ለማድረግ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪዬን አቀርባለሁ። በዓሉ የሰላምና የደስታ እንዲሆንላችሁ ልባዊ ምኞቴን በድጋሚ እገልፃለሁ። መልካም በዓል አሸብር ባልቻ(ኢንጂነር) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ

photo content
+5

ኢትዮ - ኤሌክትሪክ የሊጉን የመጀመሪያ ዙር ውድድር በድል አጠናቀቀ .........///........ በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ እየተወዳደረ የሚገኘው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የአንደኛ ዙር የመጨረሻ ጨዋታውን በድል አጠናቋል። ዛሬ በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም በተካሄደው ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የከተማ ተቀናቃኙን አዲስ አበባ ከተማን አንድ ለባዶ አሸንፏል። የአጥቂ ስፍራ ተጫዋቹ አቤል ሀብታሙ ብቸኛዋን ጎል ሲያስቆጥር በሊጉ ያስቆጠራቸውን የጎል ብዛት ሰባት አድርሷል። በጨዋታው የተሻለ እንቅስቃሴ ማድረግ የቻለው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በርካታ የጎል ዕድሎችን መፍጠር ቢችልም ተጨማሪ ጎል ግን ማስቆጠር አልቻለም። ለክለቡ ብቸኛዋን ጎል ያስቆጠረው አቤል ሀብታሙ የጨዋታው ኮከብ በመሆን የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል። በመጀመሪያው ዙር 11 ጨዋታዎችን ማሸነፍ የቻለው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በአንድ አቻ ወጥቶ በሁለት ተሸንፎ በ31 ነጥብ እና በ16 ንፁህ ጎል ተከታዩን ንብ ክለብን በሰባት ነጥብ በመብለጥ ከሊጉ አናት ላይ ተቀምጧል። ሁለተኛው ዙር ጨዋታ የካቲት 30 ቀን 2016 ዓ.ም የሚጀመር ሲሆን ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከቀናት ዕረፍት በኋላ ወደ ልምምድ የሚመለስ ይሆናል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 10 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

ማከፋፈያ ጣቢያው የትራንስፎርመር ፍተሻና ሙከራ እያከናወነ ነው ........///........ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጊቤ 1 እና 2 ማከፋፈያ ጣቢያ በብልሽት ምክንያት አገልግሎት መስጠት አቁሞ የነበረው ትራንስፎርመር ተቀይሮ የፍተሻና ሙከራና ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የፕሮጀክቱ ሱፐርቫይዘር ገለፁ፡፡ ሱፐርቫይዘሩ አቶ አብርሃም በላይ እንዳስታወቁት በጊቤ 1 እና 2 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ካሉት ሁለት ትራንስፎርመሮች በአንዱ ላይ ብልሽት አጋጥሞ ነበር። 250 ሜጋ ቮልት አቅም ያለው 400 በ230 ኪሎ ቮልት ፓወር ትራንስፎርመር በመበላሸቱ ምክንያት በጣቢያው አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ጫና ፈጥሮ መቆየቱን ተናግረዋል። አሁን ላይ የትራንስፎርመር ቅየራው ተጠናቆ የፍተሻና ሙከራ ሥራ መጀመሩን አብራርተዋል። በፕሮጀክቱ የኢንጅነሪንግ ሱፐርቪዥን ባለሙያ አቶ አሊ ካሚል በበኩላቸው ለትራንስፎርመር ቅየራው የሚሆነው የሲቪልና ኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የራስ ኃይል ኮንስትራክሽን መምሪያ መከናወኑን ገልጸዋል። ከአንድ ዓመት በላይ የወሰደው ሥራ በመጠናቀቁ ትራንስፎርመሩን አገልግሎት ለማስጀመር ዝግጅት መጠናቀቁን አስረድተዋል። የትራንስፎርመር ቅየራው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር በጣቢያው ላይ ያለውን ጫና በመቀነስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተናግረዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 09 ቀን 2016 ዓ.ም