fa
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

رفتن به کانال در Telegram

EEP Communication

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام EEP Communication

کانال EEP Communication (@eepcommuication) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 545 مشترک است و جایگاه 8 351 را در دسته فناوری و برنامه‌ها و رتبه 2 178 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 545 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 02 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 27 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 8 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 25.76% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 15.84% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 4 005 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 463 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 9 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
EEP Communication

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 03 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته فناوری و برنامه‌ها تبدیل کرده‌اند.

15 545
مشترکین
+824 ساعت
-227 روز
+2730 روز
آرشیو پست ها
photo content
+2

ክለቡን ወደ ቀደመ ዝናው ለመመለስ ሁሉም የስፖርት ቤተሰብ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ተጠየቀ .........///......... የኢትዮ ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ ህዝባዊ መሰረት ይዞ ወደ ቀደመ ዝናው በመመለስ በፋይናንስ አቅሙ ራሱን ችሎ ውጤታማ መሆን እንዲችል የስፖርት ቤተሰቡ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ተጠየቀ። የክለቡ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አለማየሁ መንግስቱ እንደገለጹት የስፖርት ክለቡ ያበረከታቸውን ጉልህ ሀገራዊ አበርክቶዎች አጠናክሮ ለማስቀጠልና ህዝባዊ መሠረት ያለው ክለብ እንዲሆን ለማስቻል የተለያዩ የሪፎርም ሥራዎች በመሠራት ላይ ናቸው። እየተሠሩ ካሉት ሪፎርሞች መካከል የክለቡን የፋይናንስ አማራጭ በማስፋት ራሱን ችሎ እንዲቆም ለማድረግ የአጭር፣ የመካከለኛና የረጅምና ጊዜ ዕቅድ ተነድፎ እየተሠራ መሆኑ ገልፀዋል። የስፖርት ክለቡ በኢትዮጵያ ብሎም በዓለም መድረክ በመሳተፍ የሀገራችን ክብርና ጥቅም ማስጠበቅ የሚችሉ ተተኪ ስፖርተኞችን ማፍራት እንዲቻል ከተለያዩ ስፖርት ወዳድ ባለድርሻ አካላት የፋይናንስ ድጋፍ ለማግኘት ዕቅድ መያዙን ምክትል ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል ። የስፖርት ክለቡን ሀገራዊ አበርክቶ በተለያዩ ሚዲያዎች በማስተዋወቅ ህዝባዊ ተቀባነት እንዲኖረው ለማድረግ መታሰቡንም ተናግረዋል ። የክለቡን አቅም የበለጠ በማሳደግ ውጤታማ ሆኖ እንዲቀጥል ለማድረግ የጋራ ተሳትፎና ርብርብ ስለሚያስፈልግ ሁሉም የስፖርት ቤተሰብ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ምክትል ፕሬዚዳንቱ ጥሪያቸውን አቅርበዋል ። የኢትዮ ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ በተለያዩ ዘርፎች ከ347 በላይ ስፖርተኞችን አቅፎ በመንቀሳቀስ በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ በሚደረጉ ውድድሮች ደማቅ ታሪክ እየፃፈ የሚገኝ አንጋፋ ክለብ ነው። ክለቡ የተመሰረበትን 60ኛ ዓመት ክብረ በዓል በተለያዩ አዝናኝ ስፖርታዊ ዝግጅቶች በድምቀት አክብሯል። ፐ/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 10 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

የስፖርት ክለቡን 60ኛ ዓመት ለመዘከር የተዘጋጀው ስፖርታዊ ውድድር ዛሬ ተጠናቀቀ ..........///........... ኢትዮ ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ የተመሰረተበትን 60ኛ ዓመት ለመዘከር በተዘጋጀው የስፖርት ውድድር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ማኔጅመንት ቡድን ድል ሲቀናው ዋናው የጤና ቡድን ደግሞ ሽንፈት አስተናግዷል። ጎፋ በሚገኘው የክለቡ የእግር ኳስ  ሜዳ በተካሄደው የኢትዮ ኤሌክትሪክ 60ኛ ዓመት ክብረ በዓል የማጠቃለያ ውድድር በእግር ኳስ እና በአትሌቲክስ የተለያዩ የፍፃሜ ውድድሮች ተካሂደዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የማኔጅመንት ቡድን መካከል የተካሄደው የእግር ኳስ ውድድር ጨዋታው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የበላይነት ተጠናቋል ። በጨዋታው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ማኔጅመንት ቡድን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አቻውን 3ለ0 በሆነ ሰፊ ውጤት በማሸነፍ ዋንጫ አንስቷል። በሁለተኛው ምድብ  የኦሮሚያ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና የጤና ቡድን የተገናኙ ሲሆን የኦሮሚያ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት 4ለ1 በሆነ ሰፊ ልዩነት በማሸነፍ የዋንጫ ባለቤት ሆኗል። በሴቶች የእግር ኳስ ውድድር ደግሞ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን 7ለ0 በሆነ ፍጹም የበላይነት ጨዋታውን በማጠናቀቅ ዋንጫ አንስቷል። በዕለቱ በተደረገው የሴቶችና የወንዶች አራት በመቶ የዱላ ቅብብሎሽ በወንዶች የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ በመያዝ የወርቅና የብር ሜዳሊያ ወስዷል። በሴቶች ደግሞ የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት አንደኛ በመውጣት ወርቅ ሲወስድ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሁለተኛ በመሆን የብር ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኗል። በወንዶች የ1500 ሜትር ውድድር የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት 1ኛና 2ኛ በመሆን የወርቅና ብር ሜዳሊያ ባለቤት ሲሆኑ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል 3ኛ በመውጣት የነሀስ ሜዳሊያ ተሸልሟል። በዕለቱ የኢትዮ ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ የቦርድ አባላት፣ አንጋፋ የክለቡ ተጨዋቾችና አሰልጣኞች እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 10 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

ሥርቆትን ለመከላከል አካታች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች ያስፈልጋሉ ተባለ ………/////……… በኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የሚፈጸሙ የሥርቆት ወንጀሎችን ለመከላከል ሁሉን ያካተቱ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች እንደሚያስፈልጉ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ ሪጅን ትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ጥገናና ኦፕሬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አስታወቁ፡፡ ዳይሬክተሩ አቶ አለማየሁ ዘበርጋ እንደገለፁት በሪጅኑ የጊቤ 3፣ የጊቤ 2፣ የገናሌ ዳዋ 3 እና የመልካ ዋከና የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን ከብሔራዊ የኃይል ቋት ጋር በሚያገናኙ የተለያየ የቮልት መጠን ባላቸው የማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ተደጋጋሚ ስርቆት ይፈፀማል፡፡ ስርቆቱ ከሚደጋገምባቸው አካባቢዎች መካከል ወላይታ ዞን ሶዶ ዙሪያ ወረዳ፣ ምዕራብ አርሲ ዞን ሻሸመኔ አካባቢ እና በሲዳማ ክልል አብዛኛዎቹ አካባቢዎች ተጠቃሾች መሆናቸውን ዳይሬክተሩ ጠቅሰዋል፡፡ በአቋራጭ ለመክበር የሚፈልጉ፣ በአቀባይ ተቀባይ ሰንሰለት ተሳስረው የኤሌክትሪክ ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን የሚመዘብሩ ግለሰቦችና የተሰረቁ ብረቶችን የሚቀበሉ የብረት ማቅለጫ ድርጅቶች መኖራቸው ዋነኛ የሥርቆቱ መንስኤዎች መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ ሥርቆቱን ለማስቀረትም ከጸጥታ አካላት ጋር የሚደረጉ ግንኙነቶች እንደተጠበቁ ሆነው ሁሉን ያካተተ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ የሚሰረቁት የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ለሀገር ኢኮኖሚ እና ለህብረተሰቡ የሚሰጡትን ፋይዳ በማስመልከት በቂ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ መስራት ይጠይቃል፡፡ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አሩሲ ዞን ሻሸመኔ ዙሪያ የፀጥታ አካላትን፣ የወረዳ አመራርና የቀበሌ ገበሬ ማህበሮችን እንዲሁም መስመሩ በሚያልፍባቸው አካባቢዎች ከሚገኙ ነዋሪዎችን በማሳተፍ በተሰራው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ ትልቅ ለውጥ መታየቱን ገልጸዋል፡፡ በዚህም የእኔነት ሥሜታቸውን በመድረኩ ከመግለፅ ባለፈ በውይይቱ ማግስት በርካታ ተጠርጣሪዎችን ለፍትህ አካላት በመስጠት ጉዳያቸው በህግ መያዙን ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 09 ቀን 2015 ዓ.ም

አገልግሎት ከማይሰጡ ንብረቶች ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለማግኘት እየተሰራ ነው …………///………….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተያዘው በጀት ዓመት አገልግሎት የማይሰጡ የተለያዩ ንብረቶችን
አገልግሎት ከማይሰጡ ንብረቶች ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለማግኘት እየተሰራ ነው …………///………….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተያዘው በጀት ዓመት አገልግሎት የማይሰጡ የተለያዩ ንብረቶችን በማስወገድ ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለማግኘት እየሰራ መሆኑን የተቋሙ የንብረት አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ አበበ ጉዲሳ እንዳስታወቁት ገቢው የሚሰበሰበው አገልግሎት ከማይሰጡ ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶች፣ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች፣ የትራንስፎርመር ዘይቶች፣ የዕቃ ማሸጊያ ጣውላዎች፣ ቆርቆሮዎችና መሰል ንብረቶችን በማስወገድ ነው፡፡ ተቋሙ በ2014 በጀት ዓመት አገልግሎት የማይሰጡ ንብረቶችን በማስወገድ 94 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን ሥራ አስኪያጁ አስታውሰዋል፡፡ አገልግሎት ከማይሰጡ ንብረቶች ሽያጭ የሚሰበሰበው ገቢ በየዓመቱ እያደገ መምጣቱን የተናገሩት አቶ አበበ ተቋሙ የንብረት አወጋገድ መመሪያውን የተከተለ ፈጣን የንብረት አወጋገድ ሥርዓት መዘርጋቱን በምክንያትነት ጠቅሰዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 09 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

ኢትዮ ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ ሀገራቸውን በዓለም አደባባይ ያስጠሩ ስፖርተኞችን አፍርቷል .........///........ የኢትዮ ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ የተመሰረተበትን 60ኛ ዓመት የፊታችን ቅዳሜ ጎፋ በሚገኘው የክለቡ የእግር ኳስ ሜዳ በድምቀት ለማክበር ዝግጅቱን አጠናቋል። በዓሉን አስመልክቶ የስፖርት ክለቡ ዛሬ ሜክስኮ በሚገኘው የክለቡ መሰብሰቢያ አዳራሽ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ የስፖርት ክለቡ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አለማየሁ መንግስቱ በመግለጫው ላይ እንደተናገሩት በዓሉ የክለቡን 60ኛ ዓመት ከመዘከር ባለፈ የስፖርት ክለቡን የህዝብ እንዲሆን ለማስተዋወቅ፣ የተለያዩ ስፖንሰሮችን በማሰባሰብ የክለቡን የፋይናንስ አማራጭ ለማስፋት እና የእርስ በርስ ግንኙነትን ለማጠናከር አልሞ የተዘጋጀ ነው፡፡ የኢትዮ ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ በ60 ዓመት ጉዞው በእግር ኳስ፣ በአትሌቲክስና በተለያዩ የስፖርት ዘርፎች ሀገራቸውን በዓለም አደባባይ ያስጠሩ ስፖርተኞችን ያፈራ አንጋፋ ክለብ መሆኑን አቶ አለማየሁ ገልፀዋል፡፡ አንጋፋውን የኢትዮ ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ ለመዘከር በተዘጋጀው የ60ኛ ዓመት በዓል ላይ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ የክለቡ አንጋፋ ተጫዋቾችና አሰልጣኞች እንዲሁም የክለቡ ደጋፊዎች እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡ በዓሉ በተለያዩ ውድድሮችና አዝናኝ ፕሮግራሞች ታጅቦ እንደሚካሄድም በመግለጫው ተመልክቷል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 08 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+1

በኢትዮ- ኬኒያ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዛሬ በይፋ የኤሌክትሪክ ሽያጭ ተጀምሯል ……….///…………. የኢትዮ- ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር እና የኮንቨርተር ማከፋፈያ ጣቢያ ዛሬ በይፋ የኤሌክትሪክ ሽያጭ ጀምሯል፡፡ በማስተላለፊያ መስመሩ ላይ ኃይል የማስተላለፍ የሙከራ ሥራ ከጥቅምት 29 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ ሲከናወን ቆይቷል፡፡ ዛሬ በይፋ ኃይል ማስተላለፍ የጀመረው የኢትዮ - ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር በዓመት እስከ አንድ መቶ ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ማስገባት አቅም ያለው ሲሆን ከኬንያ አልፎ ከታንዛኒያ እስከ ደቡብ አፍሪካ ላሉት ሀገራት እስከ ሁለት ሺህ ሜጋ ዋት ኤሌክትክ የማስተላለፍ አቅም አለው፡፡ የኢትዮ- ኬንያ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ኮንቨርተር ጣቢያ ፕሮጀክት ለአማካሪ ድርጅቱ፣ ለካሳ ክፍያና የተሰረቁ መሰረተ ልማቶችን ለመተካት የወጣውን ወጪ ጨምሮ ወደ አምስት መቶ ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ወጪ ተደርጎበታል፡፡ ከዚህ ውስጥ 214 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላሩ ለኮንቨርተር ስቴሽኑና ለግራውንድ ኤሌክትሮድ መስመር የግንባታ ሥራ እንዲሁም 120 ሚሊዮን ዶላሩ ደግሞ ለማስተላለፊያ መስመሩ የዋለ ነው፡፡ የኢትዮ- ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር የግንባታ ሥራ "CET" በተሰኘ የቻይና ኩባንያ የተከናወነ ሲሆን የኮንቨርተር ማከፋፈያ ጣቢያውና የግራውንድ ኤሌክትሮድ መስመሩ ደግሞ ሲመንስ በተሰኘ ኩባንያ ተከናውኗል፡፡ በኢትዮጵያ በኩል የተዘረጋው የማስተላለፊያ መስመር እና የፕሮቴክሽንና የዳታ ኮሙዩኒኬሽን መስመር (ኦፕቲካል ግራውንድ ፋይበር) 440 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን 994 የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ የብረት ታወሮች አሉት። ኢትዮጵያ የምታስተላልፈው ኃይል ያልተቆራረጠና አስተማማኝ እንዲሆን የሚያግዙ ተግባራትን ያጠናቀቀች ሲሆን በኬንያ በኩል ተመሳሳይ ሥራዎች ተሰርተው በቅርቡ ወደተግባር እንደሚገባ ይጠበቃል፡፡ የማስተላለፊያ መስመሩ ከደቡብ ህዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የወላይታ፣ ጋሞ እና ኮንሶ ዞን እንዲሁም ከኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የቦረና ዞን አቋርጦ ነው ወደ ኬንያ ኃይል የሚያስተላልፈው። ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ከሱዳን እና ከጅቡቲ ጋር የኃይል ሽያጭ እያካሔደች ሲሆን ከሶማሌ ላንድ፣ ታንዛኒያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ለማከናወን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርማለች። ባለፈው ዓመት ለሱዳን እና ለጅቡቲ ኤክስፖርት ከተደረገው የኤሌክትሪክ ኃይል 95 ነጥብ 4 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ተገኝቷል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 08 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+5

ከሁመራ - ወልቃይት - ሽራሮ ድረስ ያለው ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተጠግኗል ……...///……... በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በተካሄደው ጦርነት ሳቢያ ጉዳት የደረሰበት ከሁመራ -ወልቃይት- ሽራሮ ድረስ ያለው ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር የፍተሻና የጥገና ሥራ መጠናቀቁን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች የቴክኒክ ድጋፍ ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ተስፋዬ መንግስቱ እንደገለፁት የሽሬ - ሽራሮ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ሥራም እየተከናወነ ይገኛል፡፡ ከሽሬ እስከ ሽራሮ በተከናወነ የፍተሻ ሥራ 32 ቦታዎች ላይ የኮንዳክተር መቆራረጥ ማጋጠሙንና የፍተሻ ሥራው ከዋናው መንገድ ውጪ የሆኑ አካባቢዎችን በሚሸፍንበት ወቅትም የጉዳት መጠኑ ከዚህም ከፍ ሊል እንደሚችል ጠቁመዋል። የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ላይ የደረሰው ጉዳት ከፍተኛ እንደሆነ የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ የፍተሻና የጥገና ሥራውን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ተጨማሪ የጥገና ባለሙያዎች እንዲመደቡ ጥያቄ መቅረቡን ገልፀዋል። የሰሜን ምዕራብ ሪጅን የቴክኒካል ድጋፍ ባለሙያ አቶ አባይነህ ልጅዓለም በበኩላቸው በጥገና ሥራው ላይ ከሰሜን ምዕራብ ሪጅን በተጨማሪ የምዕራብ. የደቡብና የምስራቅ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽን ሠራተኞች እየተሳተፉ እንደሚገኙ ተናግረዋል። የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ የሚያልፍባቸው አካባቢዎች በረሃማ መሆናቸው የጥገና ሥራውን ፈታኝ ቢያደርገውም የጥገና ቡድኑ በአጭር ጊዜ ሥራውን ለማጠናቀቅ እየሰራ መሆኑን አቶ በላይነህ ጠቁመዋል። በአካባቢው ምግብ፣ መጠለያና ነዳጅ ለማግኘት አስቸጋሪ በመሆኑ የሚመለከታቸው አካላት ለችግሮቹ ትኩረት እንዲሰጡ ሥራ አስኪያጁ አሳስበዋል። ምንም እንኳ የጥገና ሥራው እየተገባደደ ቢሆንም አካባቢዎቹ ከአክሱምና ሽሬ ኃይል የሚያገኙ በመሆናቸው ወደ አክሱምና አድዋ ከተሞች በመሻገር የጥገና ሥራውን ለመቀጠል ዕቅድ ተይዟል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 07 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

በተያዘው በጀት ዓመት 23 የኦዲት ምርመራዎችን ለማከናወን ታቅዷል ………./////………. በ2015 በጀት ዓመት 23 የፋይናንስ፣ የክዋኔና ቴክኒካል የኦዲት ምርመራዎችን ለማከናወን መታቀዱን የውስጥ ኦዲት መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ገ/እግዚአብሔር መዝገበ እንዳስታወቁት በ2015 በጀት ዓመት በሚቀርቡ ጥቆማዎችና የኦዲት ይደረግል ጥያቄዎችን ሳይጨምር 23 የኦዲት ምርመራ ሥራዎችን ለማከናወን በዕቅድ ተይዞ እየተሰራ ነው፡፡ በበጀት ዓመቱ በኃይል ማመንጫ፣ በማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታዎች እና የኦፕሬሽን ሥራዎች በተያዘላቸው ጊዜና በጀት ጥራቱን በጠበቀ ሁኔታ ስለመከናወናቸው እና የኮርፖሬት ሰርቪስ ገቢን ማሳደግ እና ወጪን ከመቀነስ እንዲሁም ለሠራተኞች ምቹ የሥራ አካባቢ ከመፍጠር አኳያ ያሉበትን ሁኔታ የሚፈትሽ ኦዲት ይደረጋል፡፡ ዳይሬክተሩ እንዳሉት በኦዲት ተደራጊ በኩል የሚሰጡ ግብረ መልሶች ወቅታዊና ተገቢ ስለመሆናቸው ማረጋገጥ፤ የፋይናንሰወና ክዋኔ እንዲሁም የቴክኒካል ኦዲትን የውስጥ ዓቅም ማሳደግ ላይ ትኩረት ተሰጥቶት ይሰራል፡፡ የኦዲት ሥራ በተጨባጭ ማስረጃና በተገኘው ዉጤት ላይ መመስረት ያለበት መሆኑን ያነሱት ዳይሬክተሩ ይህን ለማድረግ ደግሞ ኦዲተሮች ሥራቸውን በሚያከናዉንበት ጊዜ የሥራ ነጻነት ሊሰጣቸው እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡ የተቋሙን ሥራዎች በአግባቡ ለመፈፀም በተቋሙ አግባብነት ያላቸው ህጎች፣ ደንቦችና መመሪያዎች በትክክል መተግበር እንዳለባቸው የገለፁት ዳይሬክተሩ በተቋሙ የስጋት አካባቢን በመለየት እርምጃ ለመውሰድ እና ለማስተዳደር በሚያስችል መልኩ መረጃዎች መደራጀት እንዳለባቸውም አመልክተዋል፡፡ የሥራ ክፍሎች ለኦዲት የሚያስፈልጉ ሰነዶችን በወቅቱና በተሟላ ሁኔታ ማቅረብ እና የስራ ኃላፊዎችና ሠራተኞችም የውስጥ ኦዲት ሥራዎችን ለማከናወን በሚደረገው እንቅስቃሴ አስፈላጊውን ትብብር የማድረግ ግዴታ እንዳለባቸው አቶ ገብረእግዚአብሔር አሳስበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 07 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

በንብረት ግምትና ዋጋ ክለሳ ሥራ ሠራተኞችን በማሳተፍ ተቋሙን ከተጨማሪ ወጪ ማዳን ተችሏል ………////………… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተከናወነው የንብረት ግምትና ዋጋ ክለሳ ሥራ የተቋሙን ሠራተኞች በማሳተፍ ተቋሙን ከተጨማሪ ወጪ ማዳን መቻሉን የንብረት ዋጋ ክለሳና አይ ኤፍ አር ኤስ ሪፖርቲንግ ፕሮግራም መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ አቶ ይርጉ ኃይሉ እንዳስታወቁት በተቋሙ አይ ኤፍ አር ኤስን ለመተግበር ፌር ፋክስ ከተሰኘ ኩባንያ ጋር የንብረት ግምትና የዋጋ ክለሳ ሥራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡ በንብረት ግምትና የዋጋ ክለሳ ሥራው የተቋሙ ሠራተኞች ከኩባንያው ጋር በመሥራት ልምድ እንዲቀስሙ በተደረሰው ስምምነት ከልምድ ልውውጡ ባሻገር ተጨማሪ ተግባራት መከናወናቸውን ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል፡፡ ከኩባንያው ጋር የተደረሰው ስምምነት የ16 ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን፣ የ86 ማከፋፈያ ጣቢያዎች፣ የ11 ሺህ የመስመር ተሸካሚ ምሶሶዎችን እንዲሁም የ684 ተሽከርካሪዎችንና የተለያዩ ማሽነሪዎችን ለመቁጠርና የዋጋ ክለሳ ለማከናወን ነበር፡፡ ይሁንና በውሉ ያልተካተቱ ተጨማሪ የ8 ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን፣ የ43 ማከፋፈያ ጣቢያዎችን፣ የ25 ሺህ 210 የመስመር ተሸካሚ ምሶሶዎችን፣ የ216 ተሸከርካሪዎችንና ማሽነሪዎችን፣ 46 ሺህ የቤትና የቢሮ ዕቃዎችን እንዲሁም የ3 ሺህ 231 ህንፃዎችን የመቁጠርና በአዲስ ዋጋ የመተመን ሥራዎች ተከናውነዋል ብለዋል፡፡ እንደ አቶ ይርጉ ገለፃ ከስምምነት ውጭ የተከናወኑ ተጨማሪ ሥራዎች በውሉ መሰረት ቢከናወኑ ኖሮ ውል ከተገባበት ገንዘብ ከእጥፍ በላይ ተቋሙን ሊያስወጣው ይችል ነበር፡፡ የንብረት ቆጠራና የዋጋ ክለሳ ሥራው ተቋሙ ከተቋቋመ ጀምሮ እስከ 2008 ዓ.ም ድረስ ያሉትን ንብረቶች በአዲስ ዋጋ በመከለስና በመተመን የተከናወነ ሲሆን ከ2009 እስከ 2013 ዓ.ም ያሉትን ደግሞ ዕቃዎች በተገዙበትና ፕሮጀክቶች በተገነቡበት ዋጋ ወደ መዝገብ እንዲገቡ ማድረግ ተችሏል፡፡ በአሁኑ ወቅትም ለአገልግሎት ዝግጁ የሆኑ የ13 ፕሮጀክቶችን መረጃ በአይ ኤፍ አር ኤስ ለመመዝገብ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 06 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+3

የጭልጋ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት የመጀመሪያ የፍተሻ ሥራ ተጠናቀቀ .........////…...... በአዘዞ - ጭልጋ ፕሮጀክት እየተገነባ የሚገኘው የጭልጋ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የመጀመሪያ የፍተሻ ሥራ መጠናቀቁን የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አስታወቁ። አስተባባሪው አቶ ዳንግብፁ መንገሻ እንደገለፁት የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈፃፀም 88 በመቶ ደርሷል። የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች የመጀመሪያ የፍተሻ ሥራ ተጠናቆ ሁለተኛው መጀመሩን የገለፁት አስተባባሪው የመቆጣጠሪያ፣ የስካዳና የኮሙዩኒኬሽን ዕቃዎች ላይ የፍተሻ ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልፀዋል። በነባሩ የአዘዞ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ የማስፋፊያ ግንባታ ላይ ሲካሔድ የቆየው የፍተሻ ሥራ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁንም ነው አስተባባሪው የተናገሩት። እንደ አስተባባሪው ገለፃ በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው የሲቪልና የኦፕሬሽን ሠራተኞች መኖሪያ ቤት የማጠናቀቂያ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። በተያያዘ ዜናም ከጭልጋ እስከ አዘዞ እየተዘረጋ ያለው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ በመፋጠን ላይ እንደሚገኝ አቶ ዳንግብፁ አስታውቀዋል፡፡ ተከላቸው በተጠናቀቀ 81 የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ የኮንዳክተር ሽቦ ዝርጋታ ሥራ መጠናቀቁን ገልፀዋል። ቀሪ 24 የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ምሰሶዎችን የመገንባትና ሽቦ የመዘርጋት ሥራን ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። በፕሮጀክቱ ዕቃዎች ላይ ተደጋጋሚ የሆኑ የስርቆት ወንጀሎች መፈፀማቸውና ለካሳ ጥያቄዎች አፋጣኝ መፍትሔ መስጠት አለመቻሉ የግንባታ ሥራው ላይ አሉታዊ ጫና ማሳደራቸውን ተናግረዋል። የግንባታ ሥራውን ሲኖ-ኃይድሮ ኮርፖሬሽን የተባለው የቻይና ኩባንያ እያከናወነ ሲሆን የጣሊያኑ ኢ.ኤል.ሲ. (ELC) ኩባንያ ደግሞ በአማካሪነት እየተሳተፈ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 05 ቀን 2015 ዓ.ም