የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
رفتن به کانال در Telegram
5 082
مشترکین
-11024 ساعت
-1 9137 روز
-2 77030 روز
آرشیو پست ها
👉 በማይሰበረው፣ በፈርጣማውና በኃያሉ የኢትዮጵያ ክንድ ፊት ደፍሮ የሚቆም ማንም የለም‼️
♦️ "ስትራቴጂካዊ ማፈግፈግ⁉️"--የክ/ዘመኑ ኮሜዲ ድራማ‼️
በርካታ ፀረ-ሠላም ኃይሎች፣ እብሪተኞችና ሀገር አፍራሽ ተላላኪዎች፤ ክንዱ እንደ እሳት ከሚፋጀው የኢትዮጵያዊያን የቁርጥ ቀን ልጅ ጋር ሊሳፈጡ ሞክረዋል። መጨረሻቸው ግን አላማረም- ንፁሐንን ጭምር ለእሳት ማግደው እነርሱም የእሳት እራት ነው የሆኑት። ዛሬም በተሰበረ መስታወት ውስጥ ራሱን ነብር አድርጎ እየተመለከተ ያለው ድመቱ ጃዊሳ፤ "ተው ይቅርብህ፣ ትጥቅህን አስረክበህ እጅ ስጥ" ተብሎ ቢመከርም፤ "አሻፈረኝ" በማለቱ በጀግኖቻችን የሁለት ቀናት ትንሽዬ ተመጣጣኝ ቁንጥጫ ብቻ፤ ለዘረፋ ካሰፈሰፈባቸው የአማራ ክልል ከተሞች፤ እንደ በጋ ጉም ከመቅፅበት ተበትኗል‼️
ከሞት ያመለጠውና እግሩ ወደመራው ቦታ የፈረጠጠው ጃዊሳ፤ በሚያስቅ ሁኔታ "ስትራቴጂካዊ ማፈግፈግ አድርጌያለሁ" እያለ ራሱንና ጀሌውን በማሞኘት ላይ ይገኛል። ርግጥ ማፈግፈጉ ወደ ሠማይ ቤት ከሆነ ያስኬዳል። አሊያ ግን እየሞቱ ማፈግፈግ የሚባል ነገር የክፍለ-ዘመኑ ኮሜዲ ድራማ ብቻ ነው የሚሆነው። ለማንኛውም አሁንም ስላልረፈደ፣ ከአማራ ከተማዎች በለስ ቀንቶት ከሞት ያመለጠው ዘራፊ ቡድን፤ እጁን በሠላም በመስጠት ከመሞት መሰንበትን ቢመርጥ የሚበጀው ይመስለኛል። እየፈረጠጡ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የማያውቁትን "ስትራቴጂካዊ ማፈግፈግ" ማውራት፤ በራስ ላይ ከመቆመር ውጭ፣ በሕይወት መሰንበትን አያስገኝም። በእሳት ፊት መቆም የእሳት እራት መሆንን እንደሚያስከትል፤ አሁንም ቢሆን ጃዊሳው ደጋግሞ ሊገነዘበው ይገባል-የዕለቱ ምክሬ ነው‼️
#የኢትዮጵያ_ክንድ
#ለተጨማሪ_መረጃዎች
በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች “አንዳንድ የዞን እና የወረዳ ከተሞችን መቆጣጠራቸውን አቶ ተመስገን ጥሩነህ አረጋግጠዋል
በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች “አንዳንድ የዞን እና የወረዳ ከተሞችን መቆጣጠራቸውን” እንዲሁም በተወሰኑ ቦታዎች “ወንጀለኞችን ከማረሚያ ቤት ማስለቀቃቸውን” የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መመሪያ ዕዝ ዋና ሰብሳቢ አቶ ተመስገን ጥሩነህ አስታወቁ።
አቶ ተመስገን “ዘራፊ ኃይል” ሲሉ የጠሯቸውን አካላት፤ “የክልሉን መንግስት በማፍረስ ወደ ፌደራል ስርዓት የመሄድ” ፍላጎት እና ግብ ያላቸው መሆናቸውን ተናግረዋል።
አቶ ተመስገን ጥሩነህ ይህን የተናገሩት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ቀጣይ ስራዎችን በተመለከተ ዛሬ ሐምሌ 30 ፤ 2015 ከተደረገ ስብሰባ በኋላ በሰጡት ማብራሪያ ነው። የዕዙ ሰብሳቢ በዚሁ ማብራሪያቸው ፤ በጎጃም አካባቢ ላይ የተከሰቱ የጸጥታ መደፍረሶች ፤ በርካታ “ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እና አስተዳደራዊ ችግሮችን በህብረተሰቡ ላይ ፈጥሯል” ብለዋል። በዚሁ አካባቢ “የመንቀሳቀስ መብትን የሚገድቡ ሁኔታዎች” መስተዋላቸውን አክለዋል።
የብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት ዋና ዳይሬክተሩ “ኢ-መደበኛ” ሲሉ የገለጿቸው አደረጃጀቶች፤ “አንዳንድ የዞን ከተሞችን እና የወረዳ ከተሞችን በመቆጣጠር፤ የመንግስት አገልግሎት መስጫ ተቋማትን፤ የጸጥታ አካላት እንዲሁም አንዳንድ ቦታ ላይ ወህኒ ቤቶችን ወይንም ደግሞ ማረሚያ ቤቶችን ሳይቀር በመፍታት ወንጀለኞችን እስከማስለቀቅ የደረሱባቸው ወረዳዎች አሉ” ብለዋል።
የኢፌድሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 30 ቀን 2015 ዓ.ም
"እኛ የምንሸነፈው በነፍሳችን ልናጸናት በቆምንላት ኢትዮጵያችን ፍቅር ብቻ ነው"
የምንወጣ የምንወርደው፣የነፍስ ዋጋ የምንከፍለው፣ የትኛውንም ፈተና የምንጋፈጠው ስለ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያ ብቻ ነው።
አዕምሮውን በመንደር አጥብቦ፣በዕውቀት ሳይሆን በስሜት ልቡን ያሳበጠ፣የስህተቱ ምንጭ የሴረኞች "የጨፍን ላሞኝህ" ሀሳዊ ትርክት መሆኑ በደንብ ይገባናል።በሙያዊ ዲሲፕሊን በሰከነና ጥበብ በተሞላበት የግዳጅ አፈጻጸማችን ሁሉንም ወደ ትክክለኛው ቦታ መመለስ እንደሚቻልም እናውቃለን።
ማንም በነዳው ቁጥር በአጉራ ዘለልነት እኛ ላይ ቃታ ለመሳብ የሚዳዳው የትኛውም ሃይል በአሳፋሪ ድርጊቱ ብናዝንም የመጨረሻ ውጤቱ ምን እንደሆነ ከልምዳችን አሳምረን እናውቃለን።
አሳዛኙ ነገር ከትላንቱ ምስቅልቅል ቀውስ እና ኪሳራ ካተረፈልን ችግር መማር ያልቻሉ "ጦር አውርድ" ባዮች ምን ያህል ለህዝብና ለሀገር ግድ እንደሌላቸው እየታወቀ፤ የእነዚህ እኩያን ተከታይ ጋሻ ጃግሬ መኖሩ ነው።
የፈለገውን ዓይነት ጭምብል ይልበስ በሀገር ህልውናና በህዝብ ሰላም ላይ ተረማምዶ የፍላጎቱን ቅንጣት ማሳካት አይችልም።
እኛን በእጅጉ የሚያሳዝነን የውጭ ሃይሎች ተጋላቢ ፈረሶች፣የስልጣን ጥማተኛ ጃስ ተብዬዎች ዓይናቸውን ጨፍነው በሚለኩሱት እሳት የህዝብን ሰላም ከማወክ አልፈው ማህበራዊ እረፍት ሲነሱት ነው።ያ እኛን ያመናል።
ምንም ሆነ ምን ግን በመስዋዕትነታችን ዋጋ የህዝባችንን ሰላም የሀገራችንን ህልውና አስጠብቀን ምርቱን ከግርዱ በለየ አስተውሎታዊ ግዳጅ አፈጻጸም ኢትዮጵያችንን አጽንተን ከነክብሯ እናስቀጥላታለን።
ለእኛ ከኢትዮጵያ የሚበልጥብን አንዳችም እሳቤ የለም።
ሁሉም ነገር የሚያምረው በሀገር ነውና ስለሀገር መቤዛችን የማይቆም ግዴታችን ነው።
ለማንኛውም ሁሉም በጎ ይሆናል።የሚያሳስበን የምንከፍለው ዋጋ አይደለም።የሀገርና ህዝብ ሰላም እንጂ።
በሀገርና በወገን ያሴረ ስሜት የሚነዳው አጉራ ዘለል ጊዜያዊ እውክታ ይፈጥር ይሆን እንጂ የትም እንደማያደርሰው ራሱም ጠንቅቆ ያውቀዋል።
"እኛን የሚያሸንፈን ማንም ሳይሆን በነፍሳችን ልናጸናት የቆምንላት ኢትዮጵያችን ፍቅር ብቻ ነው።"
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 29 ቀን 2015 ዓ.ም
በአማራ ክልል ያለውን የፀጥታ ችግር የሚያባብሱ እና የተለያዩ የጥፋት ተግባራትን የሚከውኑ አካላት በቁጥጥር ስር እየዋሉ ነው - የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ከትናንት ምሽት ጀምሮ በአማራ ክልል ያለውን የፀጥታ ችግር የሚያባብሱ እና የተለያዩ የጥፋት ተግባራትን የሚከውኑ አካላት በአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ እዝ በቁጥጥር ስር እየዋሉ መሆኑን የኢፌዲሪ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ አስታወቁ።
የኢፌዲሪ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት በወቅታዊ ጉዳይ ላይ መግለጫ ሰጥቷል።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በዋናነት በአማራ ክልል ላይ የሚተገበር ቢሆንም በየትኛው የሀገሪቱ ክፍል መንግስት የሚያደርገውን የህግ ማስከበር ተግባር ለማስተጓጎል የሚደረጉ እንቅስቃሴ ላይ እርምጃ ይወሰዳል ብሏል መግለጫው።
መንግስት አሁንም ለሰላም አማራጭ ቁርጠኛ መሆኑ ያነሱት ሚኒስትሩ፤ ቡድኑ ለሰላም ምንም አይነት ፍላጎት ስለሌለው ነው የአስቸኳይ ጊዜ እንዲታወጅ ያስፈለገው።
ሚኒስትሩ በመግለጫቸው፤ባለፉት ዓመታት መንግስት በመላ ሀገሪቱ ሰላምን ለማረጋገጥ በርካታ ስራዎችን ሲያከናውን ቆይቷል ብለዋል።
በመግለጫው፤ በአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያው እዝ መሰረት በቁጥጥር ስር የሚውሉ ዜጎችን ሰብዓዊ መብት እንዳይጣስ በትኩረት ይሰራል ተብሏል።
በአማራ ክልል የታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተግባራዊ በማድረግ፤ የመከላከያ ሰራዊቱ ለሚያከናውነው ኦፕሬሽን ህዝቡ ደጀንነቱን ሊያሳይ እንደሚገባ የገለጹት ዶ/ር ለገሰ ቱሉ፤ በኦሮሚያ ክልልም ያለው የሸኔ ኃይል የሰላም አማራጭን ባለመቀበሉ መንግስት እርምጃ እየወሰደበት ይገኛል ብለዋል።
የሰሜኑ ጦርነት ከተፈታ በኋላ ኢመደበኛ አደረጃጃት ወደ መደበኛ አደረጃጀት እንዲገቡ ለማድረግ ሲሰራ መቆየቱንም ሚኒስትሩ አስታውሰዋል።
በመሆኑም፣ የሰላም ስምምነቱን ያልተቀበሉ እና ጦርነትን ለግል ጥቅም ለማዋል የሚጠቀሙ አካላትን መንግስት የሰላም አማራጭን ሲሰጥ ወደ ጎን በመተው የትጥቅ ትግል እያደረጉ ይገኛል ብለዋል።
በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች በእነዚህ ቡድኖች ዘረፋ ተፈፅሟል ሲሉም ሚኒስትሩ አክለዋል።
በተለይም፣ በዚህ ግጭት የተለያዩ የግብርና ግብዓት ወደ አርሶ አደሩ እንዳይደርስ እየተደረገ ነውም ተብሏል።
#EthiopiaCheck Scam Alert በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስም ከሚፈፀሙ የማጭበርበር ድርጊቶች ራሳችንን እንጠብቅ
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስም የሚፈፀሙ በርካታ የማጭበርበር ድርጊቶች እንዳሉ ከዚህ በፊት የተለያዩ መረጃዎችን አቅርበን ነበር።
ከነዚህም መሀል ባንኩ ሽልማት የሚያስገኝ የጥያቄና መልስ መርሃ ግብር እንዳዘጋጀ፣ በሞባይል ባንኪንግ የብድር አገልግሎት መስጠት እንደጀመረ፣ የሞባይል ባንኪንግ አገልግሎት ልናስተካክልዎት ነውና የምንነግርዎትን ቁጥር ወይም ኮድ ያስገቡ፣ የባንክ አካውንት መረጃችሁን በትክክል ስላልሞላችሁ እናስተካክልላችሁ፣ ሽልማት ስለደረሶት ሽልማቱ እንዲላክልዎት ገንዘብ ያስገቡ እና ሌሎችም ተመሳሳይ መልእክቶችን በመጠቀም የማጭበርበር ድርጊቶች እንደሚፈፀሙ ይታወቃል።
አሁን ደግሞ ምስሉ ላይ በሚታየው መልኩ ባንኩ በተረጋገጠው የፌስቡክ አካውንቱ ለተገልጋዮች ገንዘብ አካውንታቸው ላይ እንደገባ የሚገልፅ መልዕክት እንደላከ በማስመሰል በቅንብር በመስራት የማጭበርበር ስራዎች እንደሚሰሩ ተመልክተናል።
ባንኩ ከዚህ በፊት ተደጋግሞ እንደገለፀው ትክክለኛ አካውንቶቹ እነዚህ ናቸው፣ ከዚህ ውጭ ያሉትን አምኖ ባለመቀበል ራሳችንን ከመጭበርበር እንጠብቅ:
ድረ-ገፅ: https://www.combanketh.et
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/combanketh
ትዊተር: https://twitter.com/combankethiopia
ቴሌግራም https://t.me/combankethofficial
#EthiopiaCheck
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 29 ቀን 2015 ዓ.ም
ማህበራዊ ሚዲይ ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጅ በመጠቀም መልዕክት የምንለዋወጥበት፣ የምንማርበት፣ አሁናዊ የአለምን ሁኔታ ካለንበት ሆነን የምንረዳበት በጎ ገፅታው የገዘፈ የሚዲያ ዘርፍ ነው።
በተቃረነ መልኩ ደግሞ ማህበራዊ ሚዲያን ለጥፋት ዓላማ የሚያውሉ፣ መልካምነትን የሚያጠለሹ፣ ያልሆነውን ሆኗል ፣ያልሞተውን ሞቷል፣ ያልተማረከውን ተማርኳል፣ በሚል የተዛባ መረጃ ለሴራ የሚጠቀሙም አልጠፉም።
ከሰሞኑም የማህበራዊ ሚዲያ ቆማሪዎች ሃምሌ 24 ቀን 2015 ዓ/ም በሰሜን ወሎ በተደረገ ጦርነት መከላከያው አልዋጋም ብሏል በዚህም ኮሎኔል ያደታ ከበደ አንዱን የደቡብ ወታደር ተኩሶ ገደለ የሚል አለፍ ሲልም ወታደሮቹ በደቡቡ ወታደር መገደል ተናደው ኮሎኔል ያደታን ገደሉት የሚል የበሬ ወለደ ሀሰት የአፍራሽ ተልዕኮ ባላቸው የማህበራዊ ሚዲያዎች ሲዘዋወር ሰንብቷል፡፡
እዉነታው ግን ይህ አይደለም፡፡ ከመነሻው ኮሎኔል ያደታ ከበደ ሳይሆን ሙሉ ስማቸው ሌተናል ኮሎኔል ከበደ አዱኛ ይባላል በሰሜን ምዕራብ ዕዝ የመገናኛ ሙያተኛ ናቸው፡፡
ሌተናል ኮሎኔል ከበደ አዱኛ በሁርሶ ማሰልጠኛ ማዕከል የሰላም ማስከበር ተልዕኮ የቅድመ ስምሪት ስልጠና በመውሰድ ላይ ይገኛሉ።
የማህበራዊ ሚዲያ ነጋዴዎች በአንድም ይሁን በሌላ መንገድ ህዝብን ከህዝብ ሰራዊቱን ከህዝብ ማጋጨት እና በሰው ህይወት የመንገድ ክፉ ሴራ ላይ መሆናቸውን የኮሎኔሉ በሀሰት ተገድሏል የመባሉ ፈጠራ ይመሰክራል።
በሁርሶ ማሰልጠኛ ማዕከል የሚገኘዉ ሌተናል ኮሎኔል ከበደ አዱኛ በቆቦ አከባቢ ሞቷል መባሉ፣ ትክክለኛ ስሙ ሌተናል ኮሎኔል ከበደ አዱኛ ሆኖ እያለ ፎቶውን ብቻ በመያዝ ኮሎኔል ያደታ ከበደ መባሉ፣ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ መገናኛ ሙያተኛ መሆኑ እየታወቀ በ37ኛ ክፍለ ጦር የሜከናይዝድ ጦር ዋና አዛዥ የሚል የሌለ ሃላፊነት መሰጠቱ የሀሠት መረጃ መሆኑን ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው።
የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ብሄርም ሃይማኖትም የለዉም። በጎሳም በሰፈርም አይከፋፈልም። ይሄኛው ወታደር ደቡብ ነው ያኛው ወታደር አማራ ነው በሚል አጠራር ተሰይሞም አያውቅም። ለወታደሩ ብሄሩም ሃይማኖቱም ሀገሩም ኢትዮጵያ ናት። ስለሆነም ነው ከምንም በላይ ለህዝብ እና ለሀገሩ ሲል ራሱን አሳልፎ የሚሰጠው፡፡
መላው ሰላም ወዳዱ ኢትዮጵያዊ ሁሉ የሌተናል ኮሎኔል ከበደ አዱኛ ሞቷል መባሉ በሚዲያ ቆማሪዎች
ዘንድ ብዙ አፍራሽ መልዕክቶችን ለማስተላለፍ የታሰበ ሴራ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል። ሰራዊቱን በብሄር እና በሃይማኖት ለመከፋፈል ያሰበ በፉፁም በቆቦ እና አከባቢው ያልነበረን ዉጊያ እንደነበረ አድርጎ ለመቀስቀስ ያለመ ከሰላም እና ከልማት ይልቅ ለጦርነት እና የህዝብን ማህበራዊ ህይወት ለማቃወስ የታቀደ የማህበራዊ ሚዲያ ሴራ መሆኑን መረዳት ተገቢ ነው፡፡
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም
በሚኒስትሮች ምክር ቤት የወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት የጸና እንደሚሆን የፍትሕ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) አስታወቁ።
የፍትሕ ሚኒስትሩ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሄደው 23ኛ መደበኛ ስብሰባ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የሕዝብን ሠላምና ደህንነት ለማስጠበቅ በሚኒስትሮች ምክር ቤት በወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 6/2015 ዓ.ም ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የሚታየውን በትጥቅ የተደገፈ እንቅስቃሴ በመደበኛ የህግ ማስክበር ስርዓት ለመቆጣጠር ወደ ማይቻልበት ደረጃ የተሸጋገረ በመሆኑ የክልሉን የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ እንቅስቃሴ በከፍተኛ ደረጃ እያወከ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በዚህም የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት መስተዳድር በመደበኛው የህግ ማስከበር ስርዓት ለመቋቋም የማይቻል የጸጥታ መደፍረስ እንዳጋጠመው መግለጹን አስታውሰዋል።
የጸጥታ መደፍረስ ተግባሩም በክልሉ ነዋሪ ጫና የፈጠረ መሆኑን በመግለጽ በህገ-መንግስቱ መነሻነት ለፌደራል መንግስቱ አስፈላጊውን የህግ ማስከበር ስራ እንዲያከናውን ጥያቄ ማቅረቡን ተናግረዋል።
በዚሁ መነሻነትም በፌደራል የጸጥታ ተቋማት እና በሚኒስትሮች ምክር ቤት ተገምግሞ አሳማኝ መሆኑን ከግምት በማስገባት የህዝብ ሰላምና ጸጥታ በመጠበቅ ህግና ስርዓትን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መደንገግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱን አዋጁ መደንገጉንም ነው የተናገሩት።
አዋጁም የሕዝብን ሠላምና ደህንነት ለማስጠበቅ የወጣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 6/2015 ዓ.ም ተብሎ የሚጠራ መሆኑን አስረድተዋል።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተፈጻሚነት በዋናነት በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አስተዳደር ውስጥ መሆኑ በግልጽ መመላከቱንም አስረድተዋል።
ነገር ግን አዋጁ በክልሉ ወይም በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለን የጸጥታ ችግር የሚያባብስ ማንኛውንም እንቅስቃሴ ለማስቆም አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በየትኛውም የሀገሪቱ አካባቢዎች ተፈፃሚነት እንደሚኖረውም አመላክተዋል።
ለአዋጁ ተፈፃሚነትም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ እንደተቋቋመም ነው ያነሱት።
ጠቅላይ መምሪያውም በኢፌዴሪ ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል የሚመራ ሆኖ ጠቅላይ መምሪያ ዕዙም ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደሚሆን ጠቅሰዋል።
የዕዙን አባላት፣ መዋቅርና አደረጃጀት በሚመለከትም በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚወሰን መሆኑንም በአዋጁ እንደተገለጸ አንስተዋል።
ጠቅላይ መምሪያ ዕዝም የሰዓት እላፊን የማወጅ፣ ለተወሰነ ጊዜ አንድን መንገድ፣ አገልግሎት መስጫ ተቋም መጓጓዣ ዘዴ እንዲዘጋ ወይም እንዲቋረጥ የማዘዝ ስልጣን ተሰጥቶታል ብለዋል።
በሀገረ መንግስቱና በህገመንግስታዊ ስርዓቱ ላይ የሚቃጡ ወንጀሎችንና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን የመጣስና አፈፃጸሙን የማደናቀፍ ወንጀል መፈጸሙ፣ መሞከሩ ወይም ለመፈጸም በዝግጅት ላይ እንደሆኑ የጠረጠራቸውን ሰዎች ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ በቁጥጥር ስር የማዋል ስልጣን እንደተሰጠውም ነው የገለጹት።
ወንጀል ሊፈጸምባቸው የሚችሉ የሚጠረጠሩ እቃዎችንና መሳሪያዎችን ለመያዝ ሌሎች ማስረጃዎችን ለማግኘት ማስረጃዎችን ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ በየትኛውም ጊዜ ማንኛውንም ስፍራ የመጓጓዣ ተሽከርካሪዎችንና ሌሎች ተቋማትን እንዲሁም መኖሪያ ቤቶችን ለመበርበር ስልጣን ተሰጥቶታልም ነው ያሉት።
በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ውስጥ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በተሰጠው ስልጣን መሰረት ደንብና መመሪያ የማውጣት ተፈፃሚ የማድረግ ስልጣን እንደተሰጠው ተናግረዋል።
በአማራ ብሔራዊ ክልል ተፈፃሚ እንዲሆን በሚኒስትሮች ምክር ቤት የታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 6/2015 ዓ.ም ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት የጸና ይሆናል ብለዋል።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአዋጁ አስፈላጊነቱን አብቅቷል ብሎ በሚያምንበት ጊዜ የአዋጁን ተፈፃሚነት ከስድስት ወራት በፊት እንዲቋረጥ ሊያደርገው እንደሚችልም አንስተዋል።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 23ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፡፡
በዚህም መሠረት ምክር ቤቱ ሳለፉቸው ውሳኔዎች አስመልክቶ የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት ያወጣው መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፦
1. ምክር ቤቱ በቅድሚያ የተወያየው የሕዝብን ሠላምና ደህንነት ለማስጠበቅ በቀረበው የሚኒስትሮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 6 /2015 ላይ ነው፡፡ በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት የሚታየውን በትጥቅ የተደገፈ ሕገወጥ እንቅስቃሴ በመደበኛ የሕግ ማስክበር ስርዓት ለመቆጣጠር ወደ ማይቻልበት ደረጃ የተሸጋገረ በመሆኑ፤ ይህ እንቅስቃሴ የክልሉን ነዋሪ አጠቃላይ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ እንቅስቃሴ በከፍተኛ ደረጃ ያወከ እና ሕገ መንግስታዊ ሥርዓቱን አደጋ ላይ የጣለ በመሆኑ፤ የሕዝብን ሠላምና ጸጥታ ለማስጠበቅ እንዲሁም ህግ እና ስርዓት ለማስከበር የአስቸኳይ ጊዜ ርምጃዎችን መውሰድ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፣ እንቅስቃሴው በአገር ደህንነት እና በህዝብ ሰላም ላይ የደቀነው አደጋ ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ መጥቷል፡፡ መንግሥት ትጥቅ አንስተው የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ሁሉ የሰላም እና ሕጋዊ መንገድን እንዲከተሉ ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪዎችን ሲያደርግ ቆይቷል፡፡
የታጠቁ ፅንፈኛ ቡድኖች እየፈፀሙ ባለው ጥቃት ምክንያት የክልሉ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ጉዳት እየደረሰ ይገኛል፡፡
የክልሉ መንግሥትም በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ያጋጠመው የጸጥታ መደፍረስ በክልሉ ከፍተኛ ሰብዓዊ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት እያስከተለ የሚገኝ መሆኑን በመግለጽ፣ ሁኔታውን በመደበኛው የሕግ ማስከበር ሥርዓት ለመቆጣጠር አዳጋች ሆኖ በመገኘቱ፣ የፌደራል መንግሥት አስፈላጊውን የሕግ ማዕቀፍ በኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት መሰረት እንዲደነግግ እና ተገቢውን ርምጃ እንዲወስድ ጥያቄ አቅርቧል። በመደበኛ የህግ ስርዓትን መሰረት አድርጎ ይህን ፈር የለቀቀ እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር አዳጋች ሁኔታ በመፈጠሩ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጅ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡
ሕገመንግስቱ እና ሕገመንግስታዊ ስርዓት ላይ የተቃጣ አደጋን በመደበኛ የህግ ስርዓት ለመቆጣጠር ባልተቻለ ጊዜ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በማወጅ ህገመንግስታዊ ስርዓትን ከአደጋ የመከላከል ስልጣን እንዳለው በኢፌዴሪ ህገመንግስት አንቀፅ 93 (1) ተደንግጓል፡፡
በመሆኑም የሚኒስትሮች ምክር ቤት በህገመንግስቱ የተጣለበትን ኃላፊነት ለመወጣት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጅ ስላለበት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 6/2015 እንዲታወጅ በሙሉ ድምጽ ወስኗል።
2. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአካዳሚክ ነጻነት እንዲረጋገጥ፣ ከፖለቲካዊም ሆነ አስተዳደራዊ ጣልቃ ገብነት ነጻ ሆነው የመማር ማስተማር እና የምርምር ሥራዎችን የሚያካሂዱ እንዲሆኑ ለማስቻል የራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ አዋጅ መውጣቱ ይታወቃል፡፡ በዚሁ መሰረትም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ሆኖ አካዳሚያዊ እና አስተዳደራዊ ነፃነቱ ተጠብቆ መንቀሳቅስ እንዲችል፣ በትምህርት ዘርፍ ለተጀመረው የሪፎርም እንቅስቃሴ ፈር ቀዳጅ ሆኖ፣ የራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ ስርዓትን ተግባራዊ እንዲያደርግ እና ለሌሎች ዩኒቨርሲቲዎችም ተምሳሌት እንዲሆን አስቻይ ሁኔታን የሚፈጥር ረቂቅ ደንብ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣት ቀን ጀምሮ በሥራ ላይ እንዲውል ወስኗል፡፡
#የኢትዮጵያ_ክንድ
#ለተጨማሪ_መረጃዎች
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም
የማሕበራዊ ሚዲያ ቁማርተኞች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ መንግስት አሳሰበ።
የመከላከያ ሠራዊት የአማራ ሕዝብ ጠላት አድርገዉ የሚቀሰቅሱ ጽንፈኞችና በሰዉ ህይወት በመነገድ ኪሳቸዉን የሚያደልቡ የማኅበራዊ ሚዲያ ቁማርተኞች ከድርጊታቸዉ እንዲቆጠቡ መንግስት አሳሰበ፡፡
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፥ የመከላከያ ሠራዊት የአማራ ክልልን ሰላምና ደህንነት ለማረጋገጥ ከየትኛዉም አካባቢ በላይ መስዋዕትነት መክፈሉና ዛሬም ጭምር እየተዋደቀ መሆኑን መገንዘብ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡
የትኛዉንም አካል ያለውን ጥያቄና ፍላጎት በሰላማዊ መንገድ ማቅረብና ለመፍትሄ መወያየት እንዲችል ትክክለኛ አማራጭ መንገድ መንግስት ዘርግቶ እያለ የግል ፍላጎትና ጥቅም በሃይል ለማሳካት የሚደረግ የትኛዉም ዓይነት ድርጊትና እንቅስቃሴ ተቀባይነት እንደሌለውም ነው ያብራሩት፡፡
በሁሉም አካባቢዎች ያሉ ጥያቄዎችና ፍላጎቶችን በምክክር ለመፍታት የሚያስችል መሰረት መጣሉና ለአንዱ ተመልሶ ለሌላኛዉ የተከለከለ ጉዳይ እንደሌለም ነው ያስገነዘቡት፡፡
በዚህም በስክነትና የወል እዉነቶች ላይ በመቆም ብቻ የተናጠል ጉዳዮች መፍትሄ እንደሚያገኙ መረዳት እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
በደቦ፣ በግርግርና በማህበራዊ ሚዲያ ጋጋታ የትኛዉም ዓይነት ጥያቄ ምላሽ ሊያገኝ እንደማይችልም ነው የተናገሩት ሚኒስትሩ፡፡
በመሆኑም ሠራዊታችን የአማራ ሕዝብ ጠላትና ጥቅሙን የማያስከብር አድርገዉ የሚቀሰቅሱ ጽንፈኞችና በሰዉ ህይወት በመነገድ ኪሳቸዉን የሚያደልቡ የማኅበራዊ ሚዲያ ቁማርተኞች ከድርጊታቸዉ መቆጠብ ይኖርባቸዋል ብለዋል፡፡
መላዉ የክልሉ ሕዝብም ከሠራዊቱ ጎን በመቆም ከዘራፊዎችና ሽፍቶች መጠበቅ አለበትም ነው ያሉት፡፡
አክለውም ፥ በተሳሳተ መንገድ ተነሳስተዉ የሠራዊቱን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ለማስተጓጓል የሚጥሩ ሃይሎችም ቆም ብለዉ ማሰብ ይኖርባቸዋል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
አሉባልታና የተሳሳቱ መረጃዎችን በመርጨት እንዲሁም የሠራዊቱን እንቅስቃሴ በማደናቀፍ በክልሉ ዉስጥ ለሚፈጠረዉ ቀዉስ እነዚህ ሃይሎችና እነሱ ያሰማሯቸዉ ቡድኖች መሆናቸዉን ከወዲሁ መገንዘብ ይገባልም ነው ያሉት።
👉 የዓይናችን ብሌን በሆነው መከላከያ ሠራዊታችን ፈፅሞ አንደራደርም‼
♦️ "የአበራሽን ጠባሳ ያየ፣ በእሳት አይጫወትም‼"
አይበገሬው መከላከያ ሠራዊታችን የኢትዮጵያ ካዝማ እና ማገር ነው። አለኝታችን፣ ብሔራዊ ኩራታችን እንዲሁም ለእኛ ሠላምና ደህንነት ሲል ሌት ተቀን በቁርና በሐሩር እየማሰነ ዳግም የማትገኝ ሕይወቱን የሚሰዋ ብርቅዬ ክንዳችን ነው። ጀግናው መከላከያ ሠራዊታችንን የነካ የመላው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ጠላት ነው‼የዓይናችን ብሌን በሆነው ሠራዊታችን ለአፍታም ቢሆን አንደራደርም‼ተሳስቶም እንኳን ቢሆን፤ ሳተናው መከላከያ ሠራዊታችንን የነካ፤ በአንድ ነገር ርግጠኛ መሆን ይችላል። ይኸውም ግብዓተ-መሬቱን በብርሐን ፍጥነት እያፋጠነ መሆኑን ነው‼
"የአበራሽን ጠባሳ ያየ፣ በእሳት አይጫወትም" እንደሚባለው፤ ከትናንት ያልተማሩ ፅንፈኞች፣ የመንደር ወጠጤዎች፣ ዘራፊዎችና ሕገ-ወጦች ሠራዊታችንን ቀና ብለው የሚያዩበት አቅምም ሆነ የሞራል ልዕልና የላቸውም። የምስራቅ አፍሪካ ኩራት የሆነው ሠራዊታችን በዘረኞች ልክ የተሰፋ አይደለም። እጅግ በጣም ይሰፋባቸዋል‼️ሠራዊታችን ውስጥ ዘረኝነት ውግዝ ነው‼️በነበልባሎቹ ጀግኖቻችን ልብ ውስጥ የገዘፉት ኢትዮጵያና ሁሉም ሕዝቦቿ ናቸው። ወገንተኝነታቸውም ለኢትዮጵያና ለሕዝቧ ብቻ እና ብቻ ነው‼️የዘረኝነት ተውሳክ የተጣባቸው ፅንፈኞችና ዘራፊዎች እንዲሁም በሕዝብ ደም የሚቆምሩ ሲራራ ቆማሪዎች፤ የዓይናችን ብሌን በሆኑት ጀግኖቻችን ከመጡ፤ አወዳደቃቸው የከፋ እንደሆነ መገንዘብ ይኖርባቸዋል። ምክንያቱም ከጥቂት ሆድ-አደሮች በስተቀር፤ በዓይኑ ብሌንና የክፉ ቀን ደራሹ በሆነው ሠራዊቱ የሚደራደር ኢትዮጵያዊ ስለሌለ ነው‼
ክብር ለሠራዊታችን፤ ክብር ለሁልጊዜ ጀግኖቻችን‼️
#የኢትዮጵያ_ክንድ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሃምሌ 25 ቀን 2015 ዓ.ም
የሠራዊቱን ሥም በማጠልሸት እና ህዝብን ከህዝብ ለማጋጨት በተሠማሩ ሃይሎች ላይ መከላከያ የሃይል እርምጃ እንደሚወስድ አሥጠነቀቀ።
የመከላከያ ሠራዊት ወቅታዊ በሆኑ ጉዳዮች ለሕዝቡ መረጃ ለመስጠትና ቀጣይ በሚወሰዱ ዕርምጃዎች ዙሪያ ባወጣው መግለጫ በርካታ ማብራሪያዎችን ሰጥቷል።
መከላከያ ሠራዊቱ አለም አቀፍ እና ቀጠናዊ ሁኔታዎች እንዲሁም ስጋቶች ሲኖሩ እንደ አመጣጣቸው የሚመክት ብቁና ድል አድራጊ ሠራዊት መሆኑና ግጭቶች ሲፈጠሩ ከሀገር ውስጥ አልፎ በውጭም ሠላም እያሰፈነ ያለ ሀገርን ከብተና የታደገ ጀግና ሠራዊት ነው ብለዋል ኮሎኔል ጌትነት አዳነ በመግለጫቸው፡፡
አሁናዊ በሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫውን የሰጡት የመከላከያ ሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተሩ ኮሎኔል ጌትነት አዳነ አሁን ላይ ፅንፈኛ ኃይሎች የሠራዊቱን ስም የማጠልሸት፣ ሕዝብን ከሕዝብ የማጋጨትና አሉባልታዎችን የመንዛት ተግባር ላይ ተጠምደዋል ብልዋል።
ሠራዊታችን በዓለም አቀፍ ደረጃ ጀግንነቱም ሆነ ህዝባዊነቱ የተመሰከረለት ነው ያሉት ኮሎኔል ጌትነት አዳነ መከላከያ ፅንፈኛ ኃይሎች በሚፈልጉት ሳይሆን ሕዝብና መንግሥት በሚሰጡት ትዕዛዝ መሠረት ሕዝባዊነቱን በተላበሰ መንገድ ግዳጁን በጥንቃቄ እየተወጣ እንደሚገኝም ገልፀዋል።
ኢትዮጵያ የውስጥ ሰላሟ እንዳይጠናከር የሚፈልጉ ኃይሎች "መከላከያ ዳር ድንበር ይጠብቅ እንጂ ለምን በክልላዊ ጉዳዮች ይገባል" የሚል ጥያቄ በማንሳት ሕዝቡንና ሠራዊቱን ለመለያየት የሚሠሩ ቡድኖች ሀገሪቱን ለማተረማመስ ባላቸው ፍላጎት በመሆኑ መከላከያ ከውስጥም ከውጭም የሚነሱ የጥፋት ኃይሎች ላይ ዕርምጃ እንደሚወስድ ዋና ዳይሬክተሩ በመግለጫቸው አንስተዋል።
የጥፋት ሀይሎች የተዘረጋውን የሠላም ጥሪ ባለመቀበል ትጥቅ አንግበው የሠላምና የልማት እንቅፋት በሆኑ በኦሮሚያ ክልል አንድ አንድ አከባቢ በሚንቀሳቀሰው የአሸባሪው ሸኔ ሀይል ላይ መከላከያ ሠራዊቱ አሳማኝ እርምጃ እየወሰደ ይገኛል፡፡
ይህን ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል እና በክልሉ የሀገር ሽማግሌዎች አባ ገዳዎችና ወላጆች ከሠራዊቱ ጋር በመሥራታቸው በርካታ ቁጥር ያለቸው የሸኔ አባላት እጅ መስጠታቸውን ኮሎኔል ጌትነት አዳነ ገልጸዋል፡፡
በአማራ ክልል ያለው ሁኔታ መሬት ላይ በተግባር ካለው ክስተት በላይ በማህበራዊ ሚዲያ ያለው ገዝፎ የታየ ሲሆን በተቋሙ ስለ ፋኖ የሚገለፀው ትክክለኛ መረጃ በተለያየ መንገድ ትርጉም እንደተሰጠው አንስተዋል፡፡
ፋኖ የረጅም ጊዜ ታሪክ ያለውና የሀገር ዕሴት የሆነ ብዙ የተዘመረለት የህዝብ ሀብት ስለመሆኑ በ1966 ዓ.ም የተማሪዎች እንቅስቃሴ ላይ የፋኖ ተሰማራ ዝማሬና በኢትዮ-ኤርትራ እንዲሁም በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በተፈጠረው ችግርም ሀገሬ ልትፈርስ ነው ሲል ከሠራዊቱ ጎን በመሆን በልኩ ዋጋ መክፈሉ አንዱ ማሳያ እንደሆነ ዳይሬክተሩ ኮሎኔል ጌትነት በመግለጫው አስቀምጠዋል፡፡
ጽንፈኛ ሃይሎች በሠራዊቱ ብቻ ሳይሆን በፋኖ ስምም በመነገድ የመከላከያ ሠራዊት አልባሳት ይዘው ወንጀል እንደሚሰሩ ሁሉ የፋኖን የተከበረ የህዝብ ዕሴት ስም ይዘው ግንባር ሳይዘምቱ በማህበራዊ ሚዲያ የሚፎክሩ ስለመኖራቸው የገለፁት ዳይሬክተሩ ይህን ተግባር በሚፈጽሙ አካላት ላይ ሠራዊቱ ምንም ዓይነት ትዕግስት እንደሌለውና እርምጃ እንደሚወሰድ ሊታወቅ ይገባል ብለዋል።
በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ የግል ፍላጎታቸውን ለማሳካት የሠራዊቱን ስም በማጠልሸትና በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ከፋፋይ ሃሳቦችን በማሰራጨት የተጠመዱ ግለሰቦችም ሆኑ ቡድኖች ላይ መከላከያ ሕጋዊ ዕርምጃ የሚወስድ መሆኑንም አሳስበዋል።
የሠራዊቱን ስም በማጠልሸት እና ጥይት በመተኮስ እንዲሁም በተለያዩ ዜዴዎች መከላከያ ሠራዊቱን የሚወጉ የሚዲያ ሞያተኞች፣ አክቲቪስቶች ፣የህግና ሥርዓት ሀዲዱን ስተው በሚመጡ የፖለቲካ ፓርቲና ፖለቲከኞች ሠራዊቱ ራሱን በመከላከል የማያዳግም እርምጃ በመውሰድ ሀገርና ህዝብ የሰጡትን አደራ በመወጣት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት እንደሚያሥከብር በመግጫው ተናግረዋል።
በቅርቡ በሰሜን ጎንደር አካባቢ የሸፈቱ ኃይሎች በሠራዊቱ ላይ ተኩስ ከፍተው እንደነበር ያስታወሱት ዳይሬክተሩ በወቅቱ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ዓመታዊ ክብረ በዓል ላይ ለመሳተፍ ወደ ሥፍራው አቅንተው በነበሩት በክቡር ፊልድ ማርሻል ላይ "ከበባ አድርገናል ፣በሄሊኮፕተር ነው ያመለጡት" በሚል የተሰራጨው ሕዝብን የማደናገር መረጃ የሐሰት ተረት ተረት ነው ብለዋል ኮሎኔል ጌትነት።
መከላከያ አይደለም የራሱን ደኅንነት ብቻ መጠበቅ የሀገሪቱን ሠላምና ደኅንነት እየጠበቀ እንዳለ የጥፋት ኃይሎች ሊረዱ ይገባልም ነው ያሉት በመግለጫው።
መከላከያ ሠራዊት የ2015 በጀት ዓመት የሥራ አፈፃፀሙን ከላይ እስከ ታች ድረስ በመገምገም በቀጣይ የሚፈፅማቸውን ግዳጆች በብቃት ለመወጣት በአስተማማኝ የዝግጁነት ደረጃ ላይ እንደሚገኝም የመከላከያ ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተሩ ኮሎኔል ጌትነት አዳነ በመግለጫቸው አንስተዋል።
ሰማዕቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ
#የመጨረሻው_ክፍል_4
በዚያች ሌሊት በአዲስ አበባ ውስጥ በየቤቱ ልቅሶና ዋይታ ሆነ» ሲል ጽሑፉን ይደመድማል። ይህም ጠላት የሰጠው ምስክርነት በካቶሊካዊው ፓፓ ቡራኬ አገራችንን የወረረውን የፋሺስት ኢጣልያን ጦር አረመኔነትና በአንጻሩ የታየውን የኢትዮጵያን ሕዝብ ጀግንነት ሲያረጋግጥ ይኖራል።
በተጨማሪም ደራሲ ጳውሎስ ኞኞ «አቡነ ጴጥሮስ እንዴት ሞቱ?» ሲል ሙሴ ፓይላክን ጠይቋቸው እርሳቸውም የሚከተለውን ተናግረዋል። «አቡነ ጴጥሮስ የተገደሉ ዕለት እዚያው ነበርኩ። መጀመሪያ በእጃቸው ይዘውት የነበረውን መጽሐፍ ቅዱሳቸውን ተሳለሙት። ቀጥለውም የያዙትን መስቀል አማትበው ሕዝቡን ባረኩ። የኪሳቸውንም ሰዓት አውጥተው ካዩ በኋላ መልሰው ከኪሳቸው ከተቱት። ወዲያው ወታደሮች በእሩምታ ተኩሰው ገደሏቸው። ይህ እንደ ሆነ አስገዳዩ ኮሎኔል ተመልካቹን ሕዝብ አጨብጭቡ ብሎ አዘዘና ተጨበጨበ።
ማታ ከአስገዳዩ ኮሎኔል ጋር ተገናኝተን ስንጫወት «በዚህ ቄስ መገደል እኮ ሕዝቡ ተደስቷል» አለኝ። «እንዴት?» ብለው «አላየህም ሲያጨበጭብ?» አለኝ። እኔም «ባታውቀው ነው እንጂ የሕዝቡ ባሕል ሲናደድም ያጨበጭባል» አልኩት።«እንዴት?» ቢለኝ እጄን እያጨበጨብኩ አሳየሁት።
እሱም አሳየኝ። «ከዚህ በኋላ የሆነው ቢሆን እኔ ትልቅ ማስታወሻ አግኝቻለሁ» ብሎ አቡነ ጴጥሮስ ሲገደሉ ይዘውት የነበረውን መስቀልና መጽሐፍ ቅዱስ፣ የኪስ ሰዓታቸውን ጭምር አሳየኝ። መጽሐፍ ቅዱሱ መሐል ለመሐል በጥይት ተሰንጥቋል። መስቀሉም ልክ በመሐከሉ ላይ ጥይት በስቶት ወጥቷል። የኪስ ሰዓታቸውንም እንዳየሁት እንደዚሁ ጥይት በስቶታል» ብለው ያዩትን መስክረዋል።»
/ትንሣኤ፣ቁጥር 58፣1978 ዓ.ም/
ምንጭ፦ ሐመር መጽሔት ግንቦት/ሰኔ ፲፱፻፺፮ ዓ.ም
ሰማዕቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ
#ክፍል_3
«ይሙት በቃ» የተፈረደባቸው ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በችሎት ፊት ለብዙ ሰዓታት ቆመው ስለዋሉና ደክሟቸው ስለነበር ለመቀመጥ ፈልገው ዳኛውን በትሕትናና በፈገግታ ጠየቁት። እንዲቀመጡም ፈቀደላቸው። በመጨረሻም የሞታቸው ፍርድ ከተነበበ በኋላ የፈረዱባቸውን ዳኞች ጸልየው በመስቀላቸው ባረኳቸው። ብፁዕነታቸው እስከመቃብር አፋፍ ድረስ የፍርሃትና የድንጋጤ ምልክት ያይደለ ከልብ የሆነ ፍጹም የክብር ትሕትና ይታይባቸው ነበር።
የአገራቸው በጠላት መወረር፣ የሕዝባቸው መገደልና መታሰር፣ የቤተ ክርስቲያናቸው መደፈር እስከ ሞት ያደረሳቸው እኒህ እውነተኛ ጳጳስ ለመገደል ሲወሰዱ ጥይት አልፎ ሌላ ሰው እንዳይጐዳ ግንብ ይፈለግ ጀመር። ሩቅ ባለመሔድ ከመካነ ፍትሑ 10 ሜትር ርቆ ግንብ ያለው መግደያ ቦታ ተገኘና ወደዚያ ተወሰዱ። ከገዳዮቹም አንዱ «ፊትዎን ለመሸፈን ይፈልጋሉን?» ሲል ጠየቃቸው። «ይህ የአንተ ሥራ ነው» ሲሉ ብፁዕነታቸው መለሱ።
ከመግደያውም ቦታ እንደ ደረሱ ወንበር ቀረበላቸውና ፊታቸውን ወደ ግንቡ ጀርባቸውን ወደ ሕዝቡ አድርገው እንዲቀመጡ ሆኑ።
ከዚያ በኋላ ስምንት ወታደሮች በስተጀርባቸው ሃያ እርምጃ ርቀው ተንበርክከው በተንጠቀቅ ቆሙ። ወዲያው አዛዡ «ተኩስ» በማለት ትእዛዝ ሲሰጥ ስምንቱም ተኩሰው መቷቸው። ግን በስምንት ጥይት ሳይሞቱ ቀሩ። መሞታቸውንና አለመሞታቸውን ለማረጋገጥ ዶክተር ተጠራ። ዶክተሩም እንዳልሞቱ አረጋገጠ። ከዚያም ሌላ ወታደር በሦስት የሽጉጥ ጥይት ራስ ቅላቸውን መትቶ ገደላቸው።
የብፁዕነታቸው አስከሬን ማንም እንዳይወስደው በአስቸኳይ ከአዲስ አበባ ውጭ ማንም በማያውቀው ቦታ በምሥጢር እንዲቀበር ተደረገ። በዚያች ሌሊት በአዲስ አበባ ውስጥ በየቤቱ ልቅሶና ዋይታ ሆነ» ሲል ጽሑፉን ይደመድማል።....
ይቀጥላል...
#ታሪክን_ወደኋላ
ሰማዕቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ
#ክፍል_2
አቡነ ጴጥሮስም የሚከተለውን መለሱ። «አቡነ ቄርሎስ ግብፃዊ ናቸው፤ ስለኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን የሚገዳቸው ነገር የለም። እኔ ግን ኢትዮጵያዊ ነኝ። ኃላፊነትም ያለብኝ የቤተ ክርስቲያን አባት ነኝ። ስለዚህ ስለአገሬና ስለቤተ ክርስቲያኔ እቆረቆራለሁ። ከዚህ በቀር ለእናንተ ችሎት የማቀርበው ነገር የለኝም። ለፈጣሪዬ ብቻ የምናገረውን እናገራለሁ። እኔን ለመግደል እንደ ወሰናችሁ ዐውቃለሁ። ስለዚህ በእኔ ላይ የፈለጋችሁትን አድርጉ። ግን ተከታዮቼን አትንኩ» አሉ።
ኢጣልያዊው ጋዜጠኛ ቺሮ ፓጃሊ «እኒህ ጳጳስ ሐቀኛ ነበሩ። ነገር ግን ለኢጣልያ ለጋስዮን ታዝዞ የመጣው አስተርጓሚ ዳኞች የሚሉትን ብቻ ከማስተርጐም በቀር ጳጳሱ የሚናገሩትን ሐቀኛ ንግግር አላስተረጐመም። እኔ እንኳን የሰማሁት በአዲስ አበባ ለሠላሳ ዓመት የኖረው የእቴጌ ሆቴል ኃላፊ የነበረው የግሪክ ዜጋ ማንድራኮስ አጠገቤ ተቀምጦ ስለነበር የተናገሩትን ሁሉ ስለገለጠልኝ ነው። እኔ እንደ ሰማሁት ፍርዱን ለመስማት በብዛት የተሰበሰቡት ጣልያኖችና ታዝዞ የወጣው የአዲስ አበባ ሕዝብ ሐቀኛ የሆነውን ንግግራቸውን ቢሰሙ ኖሮ ልባቸው ይነካ ነበር» ይላል።
ሆኖም አስተርጓሚው በጳጳሱ ላይ ተጽዕኖ ስላሳደረባቸው እውነተኛ ንግግራቸው ሳይገለጥ እንደ ቀረ ይጽፋል። ቀጥሎም ብፁዕነታቸው በፍርድ ችሎት ላይ እንዳሉ ሕዝቡ ሁሉ ስለእርሳቸው እያዘነ ሳለ መስቀላቸውን አውጥተው እየጸለዩ ሕዝቡን ባረኩ። ወዲያው የሞታቸው ሰዓት መድረሱን ዐውቀው ሰዓታቸውን ከኪሳቸው አውጥተው ተመለከቱ። በዚህ ጊዜ ሁሉ ምንም ፍርሃት አይታይባቸውም ነበር። የሞታቸውን ፍርድ ያነብ የነበረው ኢጣልያዊ ዳኛ ግን ይንቀጠቀጥ ነበር። ታላቅ ፍርሃትም በፊቱ ይታይ ነበር።
ይቀጥላል...
#ታሪክን_ወደኋላ
