የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
رفتن به کانال در Telegram
6 203
مشترکین
-28224 ساعت
-2 9327 روز
-1 61030 روز
آرشیو پست ها
+7
ልዩ መረጃ‼️ የጥምር ጦር በቦረና ወረዳ መካነ ሠላም ሶዮ አከባቢ በፅንፈኛው ላይ እርምጃ ወስዷል።
የ11ኛ ዕዝ ኮር በደቡብ ወሎ ዞን ቦረና ወረዳ እየተንቀሳቀሰ የህዝብን ሠላም ሲነሳጨበቆየው ፅንፈኛ ቡድን ላይ እርምጃ መውሰዱን የኮሩ ዋና አዛዥ ኮሎኔል ገዳ በዳዳ ተናግረዋል።
የሀገርን ሰላምና የህዝብን ደህንነት ለማደፍረስ የጥፋት ተልዕኮ አንግቦ ሲንቀሳቀስ የነበረውና ራሱን ምሬ (ምህረት) ወዳጆ ብሎ በሚጠራው ግለሰብ የሚመራው የሽፍታ ስብስብ፣ በቦረና ወረዳ መከነ ሰላም ከተማ አቅራቢያ ሶዬ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በጀግናው ጥምር ሃይላችን በተወሰደበት ጠንከር ያለ የማፅዳት እርምጃ እንደ ቅጠል ረግፏል።
የአንድ ክፍል ጦር አዛዥ ኮሎኔል ተስፋዮ መልካሙ ዛሬ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ.ም ከንጋቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ የህዝብ መገልገያ የሆኑ የባንክ ተቋማትን ለመዝረፍና የህዝብን ምርጫ ለማደናቀፍ አቅዶ የተንቀሳቀሰው የጥፋት ቡድን፣ አስቀድሞ በተጠና በተቀናጀ ጥቃት እጁን መሳሪው ላይ ሳያነሳ ሙሉ በሙሉ ተመቷል ብለዋል። ዘገባው የኮሩ ሠራዊት ስነ-ልቦና ግንባታ ነው።
የኢፌዴሪ አየር ኃይል የምልመላ ማስታወቂያ
በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የኢፌዴሪ አየር ኃይል፤ በተዋጊ አውሮፕላን አብራሪነት እና በቴክኒሽያንነት የሙያ ዘርፎች ፍላጎት ያላቸውንና የምልመላ መስፈርቱን የሚያሟሉ ወጣቶችን መልምሎ ለማሰልጠን ይፈልጋል።
✅ አጠቃላይ መመዘኛዎች
• ዜግነት ኢትዮጵያዊ የሆኑ፤
• ለኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥት ተገዥ የሆኑ፤
• መልካም ሥነ-ምግባር ያላቸው፣
• በውትድርና ለማገልገልና ሙያው የሚጠይቀውን ሥልጠና ለመውሰድ ፍቃደኛ የሆኑ፤
• የወንጀል ጥፋት ሪከርድ የሌለባቸው ለመሆኑ ከትውልድ ቦታቸው ወይም ከሚኖሩበት አካባቢ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤
• ሙሉ ጤንነት ያላቸውና የሕክምና ምርመራ ለመውሰድ ፍቃደኛ የሆኑ፤
• ከዚህ በፊት በውትድርና ወይም በፖሊስነት ያልሰሩና የማንኛውም የፖለቲካ ድርጅት አባል ያልሆኑ እንዲሁም ትዳር ያልመሰረቱ።
✅ ለትምህርትና ሌሎች መመዘኛዎች
ለተዋጊ አውሮፕላን አብራሪነት የምልመላ መስፈርቶች
• የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ ሆነው ከ2015-2017 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስደው አጠቃላይ ውጤት 350 እና ከዚያ በላይ ያላቸው፤
• በእንግሊዝኛ፣ በሂሳብ እና በፊዚክስ ትምህርቶች አማካይ ውጤት 50% እና ከዚያ በላይ ያላቸው፤
• እድሜ ከ18-22 ዓመት፣ ቁመት አንድ ሜትር ከ65 እና ከዚያ በላይ እንዲሁም ክብደት ከ50-65 ኪሎግራም የሆኑ።
✅ ለቴክኒሽያንነት የምልመላ መስፈርቶች
• የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ ሆነው በ2015-2017 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ወስደው አጠቃላይ ውጤት 200 እና ከዚያ በላይ ያላቸው፤
• እድሜያቸው ከ25 ዓመት ያልበለጠ፣ ቁመታቸው 1.65 ሜትር እና ክብደታቸው ከ50-65 ኪሎ ግራም የሆኑ።
✅ ለአጫጭር ኮርስ ሰልጣኞች የመመልመያ መስፈርቶች
• በመጀመሪያ ዲግሪ በሜካኒካል፣ በኤሌክትሪካልና በኮምፒውተር የሙያ ዘርፎች የተመረቁ፤ እንዲሁም በተለያዩ የቴክኒክ ሙያዎች በደረጃ 4 እና በደረጃ 5 ተረምቀው የሲኦሲ ምዘና ውጤት ያላቸው፤
• እድሜ ከ27 ዓመት ያልበለጡና ቁመት 1 ሜትር ከ65 የሆኑ።
✅ የሙያ አይነቶቹን ሙሉ ዝርዝር በየምዝገባ ጣቢያዎቹ የማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ መመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
✅ መስፈርቱን የምታሟሉ ተወዳዳሪዎች የ8ኛ እና 12ኛ ክፍል ማስረጃዎቻችሁን ኦርጅናልና ፎቶ ኮፒ በመያዝ ቀርባችሁ መመዝገብ የምትችሉ ሲሆን፤ በአየር ኃይል አካዳሚ የሚሰጠውን የመግቢያ ፈተና ማለፍ ይጠበቅባችኋል።
✅ ምዝገባ የሚካሄድባቸው የክልል ከተሞች
• ትግራይ ክልል - መቀሌ
• አፋር ክልል - ሠመራ
• አማራ ክልል - ባህርዳር ፣ጎንደር ፣ ደሴ፣ ደብረብርሃን
• ኦሮሚያ ክልል - አዳማ፣ ቢሾፍቱ ፣ባሌጎባ፣ አሰላ ሻሸመኔ ፣ነቀምት፣ አምቦ፣ ጅማ ፣መቱ፣ ወሊሶ ፣ፊቼ፣ ሸገርሲቲ፤
• ሶማሌ ክልል - ጅግጅጋ
• ቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል - አሶሳ
• ጋምቤላ ክልል - ጋምቤላ
• ሲዳማ ክልል - ሃዋሳ
• ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል - ቦንጋ
• ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል - ሆስአና
• ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል - ወላይታ ሶዶ
• የድሬዳዋ ከተማ መስተዳደር - ድሬዳዋ
• ሀረሪ ክልል - ሀረር
• የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር - አዲስ አበባ
✅ ምዝገባ የሚካሄድባቸው ቦታዎች - በሁሉም የክልል የዞንና የወረዳ ፀጥታ ቢሮዎች ይሆናል።
በኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስቴር የአየር ኃይል ጠቅላይ መምሪያ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
👍👍👍👍👍👍👍
📱 TikTok tiktok.com/@ethiopian_commando
📱 Instagram
⚡️ Telegram https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
📱 YouTube https://youtube.com/@ethiopiancommando?si=0SRgdyWuN3axteCi
👍👍👍👍👍👍👍
📱 TikTok
📱 Instagram
⚡️ Telegram
📱 YouTube
🪙 TikTok coin
ለመላው ክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለስቅላት በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን 👉🇪🇹💪🙏
+2
ሰበር ዜና‼️
በአማራ ክልል ሰሜን ሽዋ ዞን ማጀቴና መራቤቴ ወረዳዎች ዙሪያ የፅንፈኛው ቡድን ሎጅስቲክስ ሃላፊ የነበረው አብርሃም ደሳለው ከነግብረ አበሮቹ በሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ በሰላማዊ መንገድ ለሠራዊቱ እጅ መሥጠታቸውን የ6ኛ ዕዝ ጋሻ ክፍለጦር ምክትል አዛዥ ሻለቃ ናስር አባጊዲ ተናግረዋል።
Ethiopian Army ኢትዮጵያዊ ወታደር
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/@ethiopiancommando?si=0SRgdyWuN3axteCi
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://youtube.com/@ethiopiancommando?si=0SRgdyWuN3axteCi
+3
የኢራን 'የማታለያ ስልት'‼
ኢራን ከአሜሪካ እና ከእስራኤል ጋር በገባችበት ከፍተኛ ወታደራዊ ውጥረት ውስጥ፣ ዘመናዊ የጦር መሣሪያዎቿን ከጥቃት ለመከላከል የምትጠቀምበት "የማታለያ ጥበብ" (Deception) የዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን መነጋገሪያ ሆኗል።
ሀገሪቱ በመቶዎች የሚቆጠሩ የፊኛ (Inflatable) ወታደራዊ ቁሶችን በመጠቀም የጠላት ድሮኖች እና ሳተላይቶች እውነተኛ ኢላማ እንዳይለዩ እያደረገች መሆኑ ተነግሯል። እነዚህ የፊኛ ታንኮች፣ ሚሳይል ማስወንጨፊያዎችና የጦር አውሮፕላኖች ከሩቅ ሲታዩ እውነተኛ ስለሚመስሉ፣ ጠላት ውድ የሆኑ ሚሳይሎችን በነዚህ ርካሽ ቁሶች ላይ እንዲያባክን ያደርጋሉ።
ከዚህም በተጨማሪ በኢራን የአየር ማረፊያዎች ላይ በመሬት ላይ የሚሳሉ የውሸት የጦር አውሮፕላን ሥዕሎች ሌላው ስልት ሆኖ ከሰሞኑ መነጋገሪያ ነበር።
ይህም የጠላት ኃይሎች በባዶ መሬት ላይ ጥቃት እንዲሰነዝሩ በማድረግ፣ እውነተኛው የጦር አቅም ሳይነካ እንዲቆይ ያስችላል። ይህ ስልት በዘመናዊ ጦርነት ውስጥ ከጉልበት ይልቅ ብልሃትና ስልታዊ አመራር ያለውን ዋጋ የሚያሳይ መሆኑ ተገልጿል።
(ዋሱመሐመድ)
==============
