403
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
#ሆሳዕና_ማለት_ምን_ማለት_ነው ??
#በሆሳዕና_ለምን_ቀለበት_እናስራለን ?
#በሆሳዕና_ጌታችን_ለምን_በአህያ_ላይ_ተቀመጠ .
#በሆሳዕና_ለምን_ዘንባባ_አነጠፉ ?
................................................................
እና ሌሎች በደንብ ይነበብ ሼር!
=> ሆሳዕና ማለት ምን ማለት ነው??
ሆሳዕና ማለት፦ የዕብራይስጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ ‹‹እባክህ አሁን አድን አሁን ባርከን›› ማለት ነው፡፡በሰሙነ ሕማማት ጸሎተ ፍትሃት ጸሎተ አስተስርዮ ስለማይፈጸም ጸሎተ ፍትሃትና አስተስርዮ
የሚደረገው በዚሁ ዕለት ነው::
=> በሆሣዕና ዕለት በእጃችን እደ ቀለበት ማሰራችን የምን ምሳሌ ነው??
1.ጌታ ለአዳም የሰጠው ቃል ኪዳን ለማስታወስ፡-ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድነሃለሁ ያለውን የተስፋ ቃል ለማስታወስ፡፡
2.ጌታ ለእመቤታችን የገባላትን ቃል ኪዳን ተምሳሌት ነው።
3.ጌታ ለእስራኤላውያን የሰጣቸው ቃል ኪዳን ተምሳሌት ነው።
4.ጌታ ለአዳም ከሰይጣን ግዛት ነጻ እንዳወጣው ሁሉ እኛም ከሰይጣን ግዛት ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ከክፋት ከኃጢአት አውጣን ማረን ለንስኃ ሞት አብቃን ከቤትህ አትለየን እንደ ቸርነትህ ይቅር በለን ስንል ለጌታ ዳግም ላናጠፋ ቃል የምንገባበት ነው፡፡
=> ጌታችን በዕለተ ሆሳዕና ለምን በፈረስ ላይ አልተቀመጠም??
ትንቢቱንና ምሳሌውን ለመፈጸም ነው፡፡ "
አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ፥ እጅግ ደስ ይበልሽ ፤ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ፥ እልል በዪ፤ እነሆ፥ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው፤ ትሑትም ሆኖ በአህያም፥ በአህያይቱ
ግልገል በውርጫይቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል።(ትንቢተ ዘካርያስ 9:9)
=> በአህያ መቀመጡ፦
•ትህትናን ለማስተማር
•የሰላም ዘመን ነው ሲል
•ለፈለጉኝ ሁሉ የቅርብ አምላክ ነኝ ሲል በንጽህና በየዋህነት ለሚኖሩ ምዕመናን አድሬባቸው እኖራለሁ ሲል፡፡
•አህያዎች ትሁታን ናቸው ረጋ ብለው ነው
የሚሄዱት፤በቀላሉ ትወጣበታለህ፤በቀላሉ
ትይዘዋለህ፤እንደፈለክም ታዝዋለህ።
=> ጌታችን ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ ዘባባ የመነጠፉ ሚስጢር የምን ምሳሌ ነው???
1.ዝንባባ፡- ይስሃቅ በተወለደ ጊዜ ደስ ብሎት አብርሃምን ዘንባባ ይዞ እግዚአብሔር አመስግነዋል፡፡
2.ዝንባባ ደርቆ እንደገና ሂይወት ይዘራል፡- የደረቀ የምታለመልም አምላክ ነህ ሲሉ ነው፡፡
3.ዝንባባ የሰላም ምልክት ነው፡- የሰላም አምላክ ነህ ሲሉ ነው።
4.ዝንባባ የደስታ መግለጫ ነው፡- አንተ ደስ የምታሰኝ ሃዘናችንም የምታርቅልን አምላክ ነህ ሲሉ ነው፡፡
5.ዝንባባ እሾሃማ ነው፡- አንተ ህያው አሸናፊ አምላክ ነህ ሲሉ ነው፡፡
6.ዝንባባ እሳት አይበላውም ለብልቦ ይተወዋል እንጂ፡፡ ጌታም አንተ ባህሪህን የማይመረመር ነው ሲሉ ነው፡፡
ህዝቡ ከልብሳቸው ሌላ ስንት አይነት ቅጠንል አነጠፉለት ምን ምን??
=> ልብሳቸውን ማንጠፋቸው፡-
ለክብሩ መግለጫ ነው፡፡
ሌሎችም ሦስት አይነት ቅጠል አነጠፉለት ዘንባባ፤የቴመር ዛፍ፤የወይራ ዛፍ አነጠፉለት፡፡
=> ትልቅዋ አህያ በምን ትመሳለለች ውርን ጭለዋስ???
ትልቅዋ አህያ የኦሪት ምሳሌ ነው።
1.ትልቅዋ አህያ ሸክም የለመደች ናት ህገ ኦሪትም የተለመደች ህግ ናትና፡፡
2.የእስራኤል ምሳሌ ነው፡-ትልቅዋ አህያ ሸክም እንደለመደች ሁሉ እስራኤልም ህግ ለመፈጸም በህግ ለመራመድ የለመዱ ናቸው፡፡
3.የአዳም ምሳሌ ነው፡- አዳም ሸክም የበዛበት ነበርና።
ውርጭላዋ
1.በህገ ወንጌል ትመሰላለች፡-ምክንያቱም ወንጌል ኢየሱስ ክርስቶስ የመሰረታት የሰራት አዲስዋ ህግ ናትና፡፡
2.በአህዛብ ትመሰላለች፡-ትንሽዋ አህያ ሸክም የለመደች አይደለችም እንዲሁም አህዛብም ህግህን የመቀበል የመቀበል የለመደ አይደሉም፡፡ ለህግህ አዲስ ናቸውና፡፡
3.የእመቤታችን ምሳሌ ናት፡- የዓለም ሸክም አቅልላለችና በእመቤታችን ትመሰለላለች፡፡ እመቤታችን ድህነተ ምክንያታችን ጌታን የተሸከመች ንጽህት እንከን የሌላት እናት ናትና፡፡
።።።።#ወስበሐት_ለእግዚአብሔር ።።።።
።።።።። #ወለወላዲቱ_ድንግል ።።።።።
።።።።። #ወለመስቀሉ_ክቡር ።።።።።
Join @Hayitiye
#ሆሳዕና_ማለት_ምን_ማለት_ነው ??
#በሆሳዕና_ለምን_ቀለበት_እናስራለን ?
#በሆሳዕና_ጌታችን_ለምን_በአህያ_ላይ_ተቀመጠ .
#በሆሳዕና_ለምን_ዘንባባ_አነጠፉ ?
................................................................
እና ሌሎች በደንብ ይነበብ ሼር!
=> ሆሳዕና ማለት ምን ማለት ነው??
ሆሳዕና ማለት፦ የዕብራይስጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ ‹‹እባክህ አሁን አድን አሁን ባርከን›› ማለት ነው፡፡በሰሙነ ሕማማት ጸሎተ ፍትሃት ጸሎተ አስተስርዮ ስለማይፈጸም ጸሎተ ፍትሃትና አስተስርዮ
የሚደረገው በዚሁ ዕለት ነው::
=> በሆሣዕና ዕለት በእጃችን እደ ቀለበት ማሰራችን የምን ምሳሌ ነው??
1.ጌታ ለአዳም የሰጠው ቃል ኪዳን ለማስታወስ፡-ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድነሃለሁ ያለውን የተስፋ ቃል ለማስታወስ፡፡
2.ጌታ ለእመቤታችን የገባላትን ቃል ኪዳን ተምሳሌት ነው።
3.ጌታ ለእስራኤላውያን የሰጣቸው ቃል ኪዳን ተምሳሌት ነው።
4.ጌታ ለአዳም ከሰይጣን ግዛት ነጻ እንዳወጣው ሁሉ እኛም ከሰይጣን ግዛት ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ከክፋት ከኃጢአት አውጣን ማረን ለንስኃ ሞት አብቃን ከቤትህ አትለየን እንደ ቸርነትህ ይቅር በለን ስንል ለጌታ ዳግም ላናጠፋ ቃል የምንገባበት ነው፡፡
=> ጌታችን በዕለተ ሆሳዕና ለምን በፈረስ ላይ አልተቀመጠም??
ትንቢቱንና ምሳሌውን ለመፈጸም ነው፡፡ "
አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ፥ እጅግ ደስ ይበልሽ ፤ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ፥ እልል በዪ፤ እነሆ፥ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው፤ ትሑትም ሆኖ በአህያም፥ በአህያይቱ
ግልገል በውርጫይቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል።(ትንቢተ ዘካርያስ 9:9)
=> በአህያ መቀመጡ፦
•ትህትናን ለማስተማር
•የሰላም ዘመን ነው ሲል
•ለፈለጉኝ ሁሉ የቅርብ አምላክ ነኝ ሲል በንጽህና በየዋህነት ለሚኖሩ ምዕመናን አድሬባቸው እኖራለሁ ሲል፡፡
•አህያዎች ትሁታን ናቸው ረጋ ብለው ነው
የሚሄዱት፤በቀላሉ ትወጣበታለህ፤በቀላሉ
ትይዘዋለህ፤እንደፈለክም ታዝዋለህ።
=> ጌታችን ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ ዘባባ የመነጠፉ ሚስጢር የምን ምሳሌ ነው???
1.ዝንባባ፡- ይስሃቅ በተወለደ ጊዜ ደስ ብሎት አብርሃምን ዘንባባ ይዞ እግዚአብሔር አመስግነዋል፡፡
2.ዝንባባ ደርቆ እንደገና ሂይወት ይዘራል፡- የደረቀ የምታለመልም አምላክ ነህ ሲሉ ነው፡፡
3.ዝንባባ የሰላም ምልክት ነው፡- የሰላም አምላክ ነህ ሲሉ ነው።
4.ዝንባባ የደስታ መግለጫ ነው፡- አንተ ደስ የምታሰኝ ሃዘናችንም የምታርቅልን አምላክ ነህ ሲሉ ነው፡፡
5.ዝንባባ እሾሃማ ነው፡- አንተ ህያው አሸናፊ አምላክ ነህ ሲሉ ነው፡፡
6.ዝንባባ እሳት አይበላውም ለብልቦ ይተወዋል እንጂ፡፡ ጌታም አንተ ባህሪህን የማይመረመር ነው ሲሉ ነው፡፡
ህዝቡ ከልብሳቸው ሌላ ስንት አይነት ቅጠንል አነጠፉለት ምን ምን??
=> ልብሳቸውን ማንጠፋቸው፡-
ለክብሩ መግለጫ ነው፡፡
ሌሎችም ሦስት አይነት ቅጠል አነጠፉለት ዘንባባ፤የቴመር ዛፍ፤የወይራ ዛፍ አነጠፉለት፡፡
=> ትልቅዋ አህያ በምን ትመሳለለች ውርን ጭለዋስ???
ትልቅዋ አህያ የኦሪት ምሳሌ ነው።
1.ትልቅዋ አህያ ሸክም የለመደች ናት ህገ ኦሪትም የተለመደች ህግ ናትና፡፡
2.የእስራኤል ምሳሌ ነው፡-ትልቅዋ አህያ ሸክም እንደለመደች ሁሉ እስራኤልም ህግ ለመፈጸም በህግ ለመራመድ የለመዱ ናቸው፡፡
3.የአዳም ምሳሌ ነው፡- አዳም ሸክም የበዛበት ነበርና።
ውርጭላዋ
1.በህገ ወንጌል ትመሰላለች፡-ምክንያቱም ወንጌል ኢየሱስ ክርስቶስ የመሰረታት የሰራት አዲስዋ ህግ ናትና፡፡
2.በአህዛብ ትመሰላለች፡-ትንሽዋ አህያ ሸክም የለመደች አይደለችም እንዲሁም አህዛብም ህግህን የመቀበል የመቀበል የለመደ አይደሉም፡፡ ለህግህ አዲስ ናቸውና፡፡
3.የእመቤታችን ምሳሌ ናት፡- የዓለም ሸክም አቅልላለችና በእመቤታችን ትመሰለላለች፡፡ እመቤታችን ድህነተ ምክንያታችን ጌታን የተሸከመች ንጽህት እንከን የሌላት እናት ናትና፡፡
።።።።#ወስበሐት_ለእግዚአብሔር ።።።።
።።።።። #ወለወላዲቱ_ድንግል ።።።።።
።።።።። #ወለመስቀሉ_ክቡር ።።።።።
Join @ortodoxslijoch
የሚያፈቅሩን ሰው ማፍቀር ያለውን ደስታ ግን የታደለ ያውቀዋል።
ሁለቱም ልባቸው በሀሴት ተሞልቷል እንደተቃቀፉ እንቅልፍ
ወሰዳቸው።አዳም ከረዥም ወራት በኋላ ይህንን ሀሴት አስተናገደ።
፨ቦስ ሻውር ወስዶ ሳሎን ከዲና ጋረ ተቃቅፈው ፊልም እያዩ ነው
ቤቱ ዛሬ በመተቃቀፍ ውስጥ ያለውን ፍቅር እያስተናገደ ነው። ዲና
እነ ሄዋንን ሄዳ ልጠራቸው ፈለገች ግን ከቦስ እቅፍ መውጣት
አልፈለገችም። የዲና ስልክ ጠራ የማታውቀው ቁጥር ነው
ዘጋችው ውስጧ በፍርሀት ተርበተበተ የፈጣሪ ያለ አለች በውስጧ
።ቦስ በሁኔታዋ ግራ ተጋብቷል።
፨ ሰራተኛዋ "ቁርስ ደርሷል" አለች። ዲና እና ቦስ "እሺ
እናመስግናለን" አሉ።
በድጋሜ ስልኳ ጠራ ዲና ከቦስ እቅፍ እየወጣች ቦስዬ መጣው"
አለች። ቦስ እንዴ የት ልትሄጂ ነው እነ አዳምን ልጠሪያቸው
ነው?"አላት። ዲና "አይ ስልክ ላወራ ነው እነ ሄዋን አንተ
ጥራቸው" ብላ ወደ ውጭ ወጣች። ቦስ "ኦኬ" አለ ግን ግራ
ተጋብቷል። ጋደም ካለበት ተነስቶ ወደ አዳም ክፍል ሄደ።
፨ዲና በረንዳ ላይ ወጥታ ስልኩን አነሳችው ዲና "ሄሎ" አለች።
ድምፅ የለም ዘጋችው በድጋሜ ተደወለ። እጇ ለማንሳት
ተርበተበተ ፤እጇ በጣም ተንቀጠቀጠ አነሳችው ጎርናና ድምፅ
"ሄሎ" አላት። ዲና ዝም አለች። አስፈሪ ሳቅ ከስልኩ ሲወጣ
ተሰማት። አሁን ይበልጥ ደነገጠች። ድምፅ ማውጣት አቃታት።
ይቀጥላል
@Hayitiye 🦋
😘አለሜ ነሽ😘
✍️ እድል
✍️ክፍል 33
"""
"""
"""
"""
፨ መልዕክቱ ከጌዲዬን ነበር። "እሳቱ ጠበቃ አዳም ብዙ ደስታዎች
ስታሳልፍ ይሁን ብዬ...." ይላል ቀጣዩን ለማንበብ የግድ
የስልኩን ይለፋ ቃል ማስገባት ነበረባት። ወዲያውኑ አስገባች።
የጌዲዮን መልክቶች ወደአሉበት አመራች። የመጀመሪያ መልክቱ
ከትናት ወዲያ ነበር።
፨"ተዘጋጅ" የሚል ነበር። ቀጣዩ የትናቱ ነው ትናት በተደጋጋሚ
የፁሁፍ መልክት ልኮለታል። "ደስ ሲልክ አልወድም" ይላል። ከዛም
ከአምስት ደቂቃዎች በኋላ ደሞ "የእዛች አጭር አጎብዳጅ ምርቃት
ዛሬ ነው" ይላል።ቀጣይ ላይ ከአመሻሽ 12፡55 ላይ "ዝምታክን
በጩከት እተካልሀለው" ይላል።
፨ዲና ትናት አዳም ለምን በስልክ መልክት እንደተጨናነቀ ገባት።
ዝግጅቱ ላይ እያሉ አዳም ጭንቀት ውስጥ ሆኖ የጭንቀት ስሜቱን
ደብቆ እንደነበር እና እሷን ላለመረበሽ እንዴት ሲጥር እንደነበር
ተረዳች።እሱ ምንም ሳይል ያ እርጉም ጊዲዬን ግን ብዙ ሲል
ነበር። አዳም አሁን ይበልጥ በውስጧ ጥሩ ቦታ ኖርው ።
፨ባለፈው በተደጋጋሚ ለአዳም ሲደወልለት ሄዋን ወደ እቤት
የተመለሰች እለት እሷ የአዳምን ስልክ ይዛ ወጥታ ጊዲዮንን ነበር
አዋርታ የመጣችው። ግን ጓደኛዬ ናት ብላ ዋሽታዋለች። ዲና ያኔ
ከጌዲዮን ጋር ስታወራ አዳምን እንዳይረብሽው እና በእሱ ፋንታ
እሷን የፈለገውን መጠየቅ እንደሚችል ስትነግረው ተስማምቶ
አንድ ስምምነት አቅርቦላት ነበር። ስምምነቱም እሱ በጠራት እና
በፈለጋት ጊዜ እንድትገኝ እና ያላትን ሁሉ እንድታረግለት ነበር።
ይህንን ደሞ ለዶክተር ስነግራቸው እሳቸውንም ሄዋን ህክምና ላይ
እያለች የሆነ ጥቁርና አስፈሪ ሰው ጌዲዮን እንደሚባልና ህይወትን
የሚቀይር ብር ስቷቸው እሳቸው ደሞ በምላሹ ሄዋንን ቀስ በቀስ
የሚያሳብድ መዳህኒት እንዲያውጧት ነግሯቸው አይሆንም ሲሉት
ዝቶባቸው እንደሄደ ያኔ ዶክተርና እሷ ሲያወሩ አዳም የደረስባቸው
እለት ሄዋን ስለማንነቷ ጠይቃ ጭቅጭቅ ተፈጥሮ አዳም እሮጦ
ወጥቶ ቦስ የተከተለው እለት ዲና ስልካቸው እንቢ ሲላት አጋጣሚ
ከዶክተር ጋር ያወሩትን አስታወሰች።ያኔ ደሞ ዶክተር ቦስና አዳምን
"አሁኑኑ እቤት ተመለሱ በያቸው እኔም እየመጣው ነው" ብለው
ዶክተር የመጡበትን ቀን አስታወሰች።
፨ዶክተር ጋር ደጋግማ ደወለች ግን አይነሳም ዲና እንደፈጠጠች
ለሊቱ ነጋ ጠዋት የተለመደውን ውሀ የመርጨት ቅስቀሳዋን
ለመቀጠል ውሀ በጆክ ይዛ ቦስ ክፍል ሄደች። ቀስ ብላ ገባች እና
ካሜራዋን አስተካከለች ዲና በስልኳ መቅርፅ ትታለች በጣም
ትንሽ ተንቀሳቃሽ ካሜራ ገዝታለች። እሱን በአሰረችው ሻሽ
አመቻችታ ክፍሉ ገባች።
፨ ቦስ ጣራ ጣራውን እያየ ተመስጧል ። "ቦስ" አለችው " አይኑን
ከጣራው ሳይነቅል "ወዬ ዲናዬ" አላት። ፊቱ ፈገግ እንዳለ ነው።
ምንም እያስብክ ነው" አለችና አልጋው ጠርዝ ላይ ወደ ቦስ
ተጠግታ ተቀመጠች። ቦስ የዲናን እጅ ጎትቶ ያዘው እና ጣቶቹን
ከጣቶቿ አጣመራቸው እና ልቡ ላይ አሳረፈው። "ግማሽ ለሊቱን
እንዳልተኛው ታውቂያለሽ?" አላት። ዲና "አይ ቦስዬ አላውቅም
ግን ለምን"? አለችው። አይኗን እያየ ስለ እኛ እያስቡኩ፤ ስለ
ፍቅራችን፤ ስለእነ አዳምና ሄዋን፤ ብቻ በብዛት ግን ስላንቺ እና
ስለእኔ ፤እንዴት አርጌ ላስደስትሽ እንደምችል እያስብኩ
ታውቂያለሽ እኔ አዳምን ካንፖስ ከማግኘቴ በፊት በጣም ሀይለኛ
እና ሰዉ የምንቅ ነበርኩኝ። አዳም ግን ቀየረኝ። ስለ ስዎች ክብር
እና አንድነት እንዳውቅ እረዳኝ ፤ነብሳቸውን ይማርና ጓደኖቼ ግን
አልሰሙትም ነበር፤ ግን ሲከፋቸው ከአዳም መፅናኛ
ቃል ፍለጋ ይመጣሉ"።
፨ ከጥቄት ዝምታ በኋላ ቦስ ወሬውን ቀጠለ"እኔ ግን የአዳም
ጥሩነት ተጋባብኝ እና በአጭር ጊዜ ውስጥ አስቀያሚ የሚባሉ
ነገሮቼን ተውኩኝ።ከዛም በሁለተኛው አመት አዳም ፍቅር ያዘው ያኔ
ደሞ አፍቃሪነትን ከእሱ ተማርኩኝ።አዳም ላንቺ ብቻ ሳይሆን
ለእኔም የህይወት አስተማሪዬ ነው። ጥሩ አርገሽ ገልፀሽዋል እሱን
በማግኘቴ በጣም ተጠቅምያለው እና ደሞ አንቺን በእሱ አመካኝቶ
ፈጣሪ ሰጠኝ" አለና ጎትቶ አቅፎ ደርቱ ላይ አስተኛት።
፨ቦስ ፀጉሯን እያሻሸ "ዲናዬ እኔ ለማረግልሽ ነገር ፈፅሞ
እንዳታመሰግኝኝ እኔ ላንቺ የማረገው ሁሉ የውዴታ ግዴታዬ ነው"።
አለ።ከዲና የሚፈሱ የእንባ ዘለላዎች የቦስ ደረትን ላይ አረፉ። ቦስ
ዲናን ቀና አድርጎ "ለምን ታለቅሻለሽ።ከእዚህ በኋላ እንባሽን
ፈፅሞ ማየት አልፈልግም" አላት።ዲና "እሺ አላለቅስም እንዲሁ
እድለኝነቴ ነው በደስታ የሚያስለቅሰኝ" አለችው። ቦስ የዲናን
ፀጉሮች ሳማቸው። ጭንቅላቷን ደጋግሞ ሳማት። ሁለቱም ደስስ
አላቸው። ቦስ የዲናን እንቦዎች ጠረገላት።
፨ ዲና ቦስን "በቃ ቦስዬ ተነስና ለባብስ" አለችና ወጣች። ጠዋት
2:30 ሆኗል ዲና ሄዋን ጋር ሄደች እና ውሀ እረጨቻት ሄዋን
ፈገግ ብላ "አሁንማ በቃ ለመድኩት እኮ" አለች።
፨ ዲና ሄዋንን አቅፋ ሳመቻት እና "እህቴ ዛሬ ብታይ ደስ ብሎኛል"
አለቻት። ሄዋን "ምን ተገኘ" አለችና አልጋዋ ላይ ተመቻችታ
ተቀመጠች። ዲና በደማቅ ፈገግታ "ከደቂቃዎች በፊት ቦስን
ልቀስቅሰው ብዬ ክፍሉ ውሀ ልረጨው ሄጄ ነበር። ከዛ እሱ ግን
አልተኛም" ነበር። ስትል ሄዋን ለምን "ለምን?" አለች።
፨ ዲና የሄዋንን እጅ ልክ ቦስ ጣቶቻቸውን እንዳቆላለፉው
አቆላልፋ ያዘችውና "እንዲህ አደርጎ ይዞኝ ልቡ ላይ እጆቻችንን
ጫነው ከዛ" ስትል ሄዋን "እሺ ከዛስ እህቴ" አለቻት እየጓጓች
ከዛማ ያው ብላ የተፈጠረውን ሁሉ ነገረቻት።ሄዋን በጣምም
ተደስተች። "እንኳን ደስ አለሽ ደስ ብሎኛል ሁሌም ደስተኛ ሁኚልኝ
እህቴ "አለቻት። ዲና "እሺ እህትየዋ በይ ልብስ ልበሽና ነይ እኔ
አዳምን ልቀስቅሰው" ብላ ወደ አዳም ሄደች።
፨ክፍሉ ደረሰች እንደ ሌላ ቀኑ ለመግባት ግን ፈራች።"ንዴት ላይ
ቢሆንስ ፤ ምን አልባት ብቻውን መሆን ቢፈልግስ፤ሰውን ማውራት
ባይፈልግስ" እያለች በር ላይ ቆማ ከእራሷ ጋር ስትሞገት ሄዋን
መጣች። "እ ዛሬ አዳምን ውሀ ስረጭው እንዴት ሊሆን
እንደሚችል ለማየት ነው የመጣሁት" አለቻት። ዲና መግባቱን
ብትፈራም በሄዋን ግፊት ገባች። አዳም ተኝቷል ዲና ልትረጨው
ስትል ሄዋን ተቀበለቻት።
፨ ከዛም ዲና እንድትወጣ እና አዳምን ዛሬ በተለየ መልኩ
ልትቀሰቅሰው እንደምትፈልግ ነግራት አሶጣቻት። ዲና ወደ ሳሎን
ሄደች። ሄዋን ዲና እንደሄደች በሩን ቆለፈችው አዳም ይህ ሁሉ
ሲፈጠረ ሀገር ሰላም ብሎ ተኝቷል። ሄዋን በቀስታ ሄዳ አልጋው
ላይ ወጥታ ተጋደመች። በቀስታ ፀጉሩን መነካካት ጀመረች። አዳም
አሁን ከእንቅልፉ ባነነ ግን ህልም ስለመሰለው። በዝምታ ሄዋንን
ማየት ጀመረ።
፨ ሄዋን ጠጋ ብላ አይኖቹን ሳመቻቸው አዳም አሁንም ሰመመን
ላይ ነው። ሄዋን በቀስታ ፀጉሩን እየነካካት ለእረዥም ስአት ተያዩ።
"ሄዋኔ" አላት አዳም "ወዬ አዳም" አለችው። ከዛ ዝምምም ብሎ
ከቆየ በኋላ "አትሄጂ ዝም ብለሽ አብረሽኝ ቆዬ" አላት "እሺ
አልሄድም "አለችና ጠጋ ብላ አቀፈችው እሱም አቀፋት። ተቃቀፉ
በጣምምም ተቃቀፉ።
፨ የሚወዱትን ሰው ማቀፍ ያለውን ደስታ ሁሉም ያውቃል።
ሳታውቄ እንዴት አዳም አወቀ አብራቹ አልነበር እንዴ የምትኖሩት"
አለቻት። ዲና "እንዴ ሄዊዬ እኔ እኮ ተከራይቼ ነበር የምኖርው"
ስትላት። "እሺ በቃ ተይው" አለቻት።
፨ ዲና ሄዋንን ያቀፈቻቸውን እጇን አላቃ ወደ ፊትለፊቷ አዞረቻት።
የሄዋን አይኖች እንባ ቆጥርው እንባዋን በአንድ ቅፅፈት
አረገፈችው።ዲና ደነገጠች "በቃ አታልቅሽ እባክሽ ሁሉም ላንቺ
ብሎ ነው እንዲ የሚሆነው መዳኒትሽን በስርአት ከወሰድሽ
ትድኛለሽ" አለቻት። ሄዋን እያለቀስች "መዳኒቴን እየዋጥኩኝ አደል
እንዴ ታድያ መች ለውጥ አመጣሁ ሁላችሁም ስላሳለፋችሁት
ህይወት ታውቃላቹ እኔ ግን አላውቅም በቃ እርሽው ሄጂ ልብስሽን
ቀይሬ ስንቆይ እንዳያስቡ ሂጂ በቃ አለቻትና አጣድፋ አስወጥታት
በሩን ዘጋችው።
፨ ዲና እየተጨነቀች ሄደች። ሄዋን በሩን ዘግታ በጣም
አለቀስች። እራስዋን እንደምንም አረጋግታ ልብሷን ቀይራ ወደ
ሳሎን ሄደች። ሳሎን ማንም የለም።ቁጭ ብላ ቲቪ ማየት
ጀመርች። አዳም መጣ ። "ምን እያየሽ ነው አላት" ምንም ዝም
ብሎ ነው የዘፈን ውድድር" አለችው። "እኔን ለምን አትዳኝኝም
ልዝፈን?" አላት። ሄዋንን ለማዝናናት እየጣረ ነው። እሺ እስቲ
አለችው። ጉሮሮውን ጠራረገና
ዶሮ ውሀ ጠምቶት ተንጋሎ ይጠጣል
ከዋሉ ካደሩ መረሳት ይመጣል
አትጥፊ ብዙ ከልቤ እንዳትወጪ
እንዲህም ስላልኩሽ ቶሎ ቶሎ አትምጪ
የሚለውን ዘፈን ዘፈነላት ሄዋን ደስ አላት።ዲናና ቦስም ተመስጠው
ላለመረበሽ እና ላለማቋረጥ በዝምታ ሲያዳምጡት ቆዩ። ልክ
ሲጨርሽ ሶስቱም አጨበጨብለት። ሄዋን በጣም ደስስ አላት።
ሁላችሁም ወደእኔ ኑ አለች እና አቀፈቻቸው አራቱም ተቃቅፈው
ቆዩ ዲና አዳም እና ቦስን "እንደ እናንተ አይነት ወንድ በጭራሽ
ያጋጥመኛል ብዬ አስቤ አላውቅም ነበር ግን አሁን በአይኔ አየው"
አለች። ከዛ ቦስ ኧር ሞቀን ሀሀ አለ አዳምም ተከትሎ በጣም
አለ። ውይይ በጣም እኮ ነው የምወዳቹ የኔ ውዳች ብላ ሶስቱንም
ሳመቻቸው።
፨አዳም "በሉ በሉ ተነሱ ሰዎች እንሄድ" አላቸው። ስራተኖቹን
ተሰናብተው ወጡ። አዳም ከአለው መኪና ትልቁን መርጦ በእሱ
ተጭነው እራሱ እየነዳ ወስዳቸው። ተክለ ሀይማኖት ቤተ
ክርስቲያን አሳዳጊው የተቀበሩበት ቦታ ላይ የመቃብር ቦታውን
አሳያቸው።ሶስቱም መቃብሩ ላይ ያለውን የእሳቸውን ፎቶ
እያፈራረቁ ሳሟቸው። ትንሽ ቆይተው ከመቃቅር ቦታው ወጡ።
፨ "አሁን ጊዜው የጉብኘት ነው።ወደ ማሳደጊያ ተቋሙ እንሄዳለን
ያደኩበትን ቦታ ታያላቹ" አላቸውና ሞተሩን አስነስቶ ከነፈ።
ከደቂቃዎች በኋላ ተቋሙ ጋር ደረሰ። "በጣም ያምራል ቦታው"
አለች ሄዋን። ዲናና ቦስም ተከትለው "አዎ በጣም በስማም"
አሉ። ከዛ መኪናውን የመኪና ማቆሚያ ጋር አቁሞ ወደ ቢሮ ገባ።
ዳይሬክተሩን ግቢው ጋር ጊዜ እንዲያሳልፉ አስፈቅዶ ወጣ። እና
ተፈቀደለት እስከ ምሽት 1:30 ድርስ ከማሳደጊያውያ ልጆች ጋር
ሲጫወቱ ቆዩና ልጆቹ አዳምን በጣም ስለሚወዱት ሲያዩት ደስ
ብሏቸዋል ከዛ አመስግነው ሁሉንም ተሰናብተው ወደ ቤት
ለመመለስ ጉዞ ጀመሩ።
፨ ቤት ሊደርሱ ሲሉ አዳም መልክት ገባለት። ዲና አየችው ጌ
ይላል ጌዲዮን እንደሆነ እርግጠኛ ነበርች። ቤት ደርሰውም አዳም
ተረብሿል ደና እደሩ ብሎ ተኛ ቦስ እና ሄዋን ግራ ገብቷቸዋል ዲና
ግን ገብቷታል። ከዛም ቦስና ሄዋንም ለመተኛት ወደ የመኝታ
ቤታቸው ሄዱ። ዲና ግን እንቅልፍ በአይኖ አልዦረም። መኝታ ቤቷ
ገብታ ልትተኛ ብትሞክርም አንቢ አላት።
፨ ሳሎን መጥታ ቁጭ አለች። የአዳም ስልክ ጠረጴዛው ላይ
ተቀምጦል። አነሳችው ወዲያው መልክት ገባለት። ዲና
አነበበችው እና ደርቃ ቀረች።
ይቀጥላል
@Hayitiye
😘አለሜ ነሽ😘
✍️ እድል
🔥ክፍል 32
""""
""""
""""
""""
፨ አዳም ግራ ተጋባ ሁሉም ያልጠበቁት ድምፅ በክፍሉ ውስጥ
ነገሰ። ለስለስ ያለ የዘፈን ክላሲካል ነው "ምን እየተፈጠረ ነው?"
አለ አዳም።ዘድያው መብራቱ በራ ክፍሉ በሙሉ ዲና ፍቅረኛዬ ትሆኛለሽ፤
ታፈቅሪኛለሽ ፤ፍቅረኛሽ ልሁን ፤ስለወደፊታችን አብርን እናስብ
፤የሚሉ ፁሁፋዎች ሞልተውታል። ዲና አይኗን ማመን ተሳናት።
ክፍሉ ውስጥ ማንም የለም ክላሲካሉ ከየት እንደሚመጣ አይደለም ማወቅ
አይቻልም መገመትም አይቻልም።
፨ ሄዋን በዲና መደናበር ሳቋ መጣ ግን አልሳቀችም።አዳም በቦስ
ስራ በጣም ተገረመ። ቦስ መጣ ወደ ዲና ቀረበ ከዛም
ተንበረከከ። "ዛሬ ቀኑ ደስ ይላል ፤ግን ደሞ ያስፈራል፤ የፈራውት
እኔ ነኝ ፤እንቢ አልፈልግክም እንዳትይኝ ፤እባክሽ ካፈቀርሽኝ ብቻ
፤እሺ በይኝ አንቺ የእኔ እንድትሆኜ ነው የምፈልገው አለና ቀለበቱን
አወጣ። ዲና አለቀሰች እጇን ዘርጋችለት።ወዲያው፦ አንድ ዘፋኝ
መድረኩ ላይወጥቶ
የኔ አካል የኔ ነሽ ምን አወርስሻለው
አንጀቴ እና ልቤን ያው ትቼልሻለው
፨የሚለውን ዘፈን ከእዚህ ግጥም በኋላ ያለውን ግጥም ቀይሮ
ዘፋኑ መዝፈን ጀመረ። ልክ እንደ ትክክለኛ ዘፈኑ አስመስሎ።
የኔ አካል የኔ ነሽ ምን አወርስሻለለው
አንጀቴና ልቤን ያው ትቼልሻለው
ፍቅርሽን በህልሜ የኔ አለም
ሳወጣና ሳወርድ የኔአለም..... እያለ ዘፈነ።
፨ቦስ ዲና እሺ በማለቷ ደስስስ አለው። እጇን ይዞ ወደ ምግብ
ጠረጴዛ ወሰዳት። ሄዋን አዳምን ያኔ በድንጋጤ አቅፋ እንደያዘችው
አለቀቀችውም ነበር። እነሱም ተያይዘው ወደ ጠረጴዛው ሄዱ።
አራቱም ተቀመጡ።ቦስ ሆቴሉን በዝግ ነው ዛሬ የተከራየው። እስከ
ምሽቱ 8ስአት እንዲው ሲዝናኑ እና ሲሳሳቁ ሲጨፍሩ አመሹ።
፨ ከዛም ሲጨርሱ ሹፌራቸውን ጠርተው ቤት ሄዱ። ሲደርሱ ሰአቱ
9፡20 ነበር። ሁሉም በለበሱት ልብስ ተኙ። ጠዋት ሁሉም
አልተነሱም እስከ ቀኑ 7 ሰአት ተኝተው አረፈዱ። ዲናም አቅም
ኖሯት መነሳት ከበዳት ተዝለፈለፈች ሁሉም ድካም ላይ ነበር። 7
ሰአት ሲል ግን ሄዋን ድካሞን ጨርሳ ተነሳች ፣ ዲናም የሄዋንን
ድምፅ ከሰራተኞቹ ጋር ስታወራ ስምታ ተነሳች።
፨ ወንዶቹም ዲናና ሄዋን ውሀ ርጭተው አስነሷቸው። ሄዋን "ዛሬ
ተርፌያለው" አለች። እየሳቀች ዲና "እህ ዛሬማ አላለልሽም"
አለቻት። "ቀውስ ነሽ" አለ ቦስ አዳም ሳቅ ብሎ "ኧር ተው አሁንማ
ልእልትህ ናት አትስደባት" አለው። ዲናም "አዎ እስቲ እንደ እሱ
ንገርልኝ" አለችው። ሁሉም ተጣጥበው ሳሎን ተቀመጡ።
፨አዳም "ምሳ ዛሬ እኔ ነኝ የምሰራው ምርጥ የእንቁላል ሳንዱች ለአዲሶቹ ፍቅርኛሞች ቀለል ያለ ነው" አለ።ዲና "እንዴ ምግብ መስራት
ትችላለክ እንዴ" ስትል ቦስ ቀጠል አርጎ "እኔም ሲስራ አይቼው
አላውቅም" አለ ከዛ ሄዋን ሶፋ ላይ ዘፍ አለችና "እስቲ እንይልክ
ሙያክን በል ፍጠን" አለችው። አዳም "ጠብቁኝ በአጭር ደቂቃ
ውስጥ ምርጥ የእንቁላል ሳንዱች ከ ሻይ እና ወተት ጋር ካስፈለገ
ቡናም አለ" ሲላቸው ዲና "ኦኦኦ አንተ ምንድነው ዛሬ ደሞ ፈታ
ብለካል እኔ ሻይ ነው የምፈልገው" አለች ቦስ "እኔ ደሞ ቡና" አለ
ከዛ አዳም ሄዋንን በፍቅር አይን እያያት አንቺስ አላት ሄዋን ፈገግ
ብላ "አንተ የምትጠጣውን" አለችው። "እሺ ወተት እንጠጣለን
መጣው ዘና በሉ" አለና ወደ ኩሽና ሄደ። "ስዎች እንዴት አደራቹ"
አላቸው ስራተኖቹ ሁሉም እየተፈራረቁ "ደና አደርክ ፤እንዴት አደርክ"
አሉት። "ይመስገን ይመስገን ዛሬ ለአራታችን ቁርስ የምሰራው እኔ
ነኝ እናንተ ደሞ ለእኛ የስራችውትን ብሉ ያው እንቁላል አትወዱም
ብዬ ነው" አለና ሽርጥና ኮፍያውን አድርጎ ወደ ስራ ገባ። ስራተኖቹ
ኩሽና ያለውን የምግብ ጠረጴዛ ተጠቅመው ቁርሳቸው አቀርበው
እየበሉ በመሀል እየተነሱ ለአዳም እያጎረሱት በልተው ጨርሱ።
ሳሎን ዲና ሄዋን እና ቦስ ትናት ስላሳለፉት ነገር እና አዳም
ጨለማውን ሲያይ የተናገርውን ንግግር እያስታወሱ ሲስቁ ነበር።
፨ከሁሉም ድምፅ የሄዋን ጓልቶ ይስማል። ከዛ ደሞ ቦስና ዲና ስለ
ሄዋን ውበት እና ስዎች እንዴት ሲያይዋት እንደነበር እያስታወሱ
መሳቃቸውን ቀጠሉ።አዳም በእዛ ስአት ቁርስ አዘጋጅቶ
ጨርሶ።ከሳሎኑ አቅራቢያ ያለውን የምግብ ጠረጴዛ ተጠቅሞ
አሳመረው።
፨ "ሁላችሁም ወደ እዚህ መምጣትም ማየትም አይቻልም
አዘጋጅቼ ሳልጨርስ" አለ።ምግብን አቀራረቦ እና የሚጠጡ
ነገሮችን ከ ትኩስ እስከ ቀዝቃዛ አቀረበ። አነስተኛ ኬክም
አዘጋጅቶ ነበር እላዩ ላይ B&Dብሎ ፅፎበታል ግን እሱን
አላቀርበውም ምክንያቱም ለቦስ እና ለዲና ሰርፕራይዝ ስለሆነ።
፨ "አሁን መምጣት ትችላላቹ" አለ አዳም ያለ ማንም እርዳታ እርሱ
ስርቶ ያቀርበውን ቁርስ እየጠቆማቸው። ሼፍ መስሎ ነበር። ሁሉም
ሼፍነት ያምርብካል አሉት። የምግብ ጠረጴዛው ላይ የቀረበውን
ሲያዩ ተገረሙ። ሁሉም ተቀምጠው ቁርሳቸውን በሉ። በጣም
ጣፍጧቸው ነበር የበሉት። በልተው እንደጨርሱ አዳም ሰራተኛዋን
ጠርቶ ሰርፕራይዙን እንድታመጣው ነገራት።
፨ የነገራት በጆሮዋ ስለሆነ ሁሉም "ምን ብለካት ነው" ብለው
ጠየቁት ጠብቁ እስቲ አላቸው። ከዛም ሰራተኛዋ ኬኩን ይዛ
መጣች እና ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠችው ዲና "ኣኣኣኣ አንተ ልጅ
ጣፋጭ እኮ ነክ ወንድሜ ባትሆን ይቆጨኝ ነበር" አለችና
ከተቀመጠችበት ተነስታ ጉንጩን ሳመችው ጀርባውን መታ አርጋ
አቀፈችው።
፨ ቦስ "ጓደኛዬ በጣም አመሰግናለው ዲናዬ አንቺ ደሞ የልጁን
ጀርባ በሆነው ባልሆነው እየደለቅሽ እንጥሉን እንዳታወርጅው"
አለ። ሄዋን በጣምም ሳቀችና "አይ አንተ ልጅ" አለች። ስራተኛዋ
የኬክ መብያ አቀርበችላቸው። እና ዲና "እኔ ልቁረሰው" አለችና
ቆራርሳ ለሁሉም ሰጠቻቸው።
፨ሄዋን "ዛሬ ደሞ አብረውን አይበሉም እንዴ"? አለች።አዳም "አይ
ሄዋንዬ እነሱ ወተት እንቁላል እና ስጋ ነክ ነገር አይበሉም
አላት።ቦስ "እንዴ" ለምን አለ። ዲናም ቦስን ተከትላ "እውነትም
ለምን" አለች። አዳም "ምክንያቱን አላውቅም ለእኔም የመጀመሪያ
ቀን ስሰማ ገርሞኛል ይልቅ ዛሬ የምንሄድበት የለንም እሁድ
ስለሆነ ባለፈው እንሄዳለን የተባባልንበት ጋር እንሂድ የማሳደጊያ ጋር
ቆሙ እና የእቴቴ መቃብር ጋር"አለ። ሁሉም እሺታቸው
ገለፁለት። ሄዋን ግን "ዲና እንዴት የሰራተኞችን ፀባይ
አታውቅም። አብረው ኖረው አደል እንዴ እያለች በውስጧ
ታጉርመርም ነበር። በሀሳብ ጭልጥ አለች ቦስ ግራ ገብቶት
እያያት ነው።
፨ ሄዋን ደሞ በሀሳብ ተጉዛለች "ምን ሆነሻል ሄዊዬ" አላት
አዳም። ሄዋን አሁንም አልነቃችም። አዳም ሄዋን ጋር ሄዶ አጠገቦ
ተቀጠ እና አቀፋት ሄዋንም አቀፈችው። "ምን ሆነሻል"? አላት።
ሄዋን "ምንም አልሆንኩም በቃ ልብሴን ልቀይር እና ልምጣ" አለች።
፨ከዛም ወደ መኝታ ቤቷ ሄደች። ዲና ተከትላት ሄደች። ሄዋን
መኝታ ቤቷ ገብታ ቁም ሳጥኗን ማየት ጀመረች። ልብሷን
እየመረጠች ዲና ከኋላዋ መጥታ አቀፈቻት። "ምነው እህቴ ችግር
አለ?" አለቻት። ሄዋን "ብነግሽ አትፈችልኝ ምን ይስራልሻል"
አለቻት። ዲና "እንዴ ሄዊዬ ምን ማለትሽ ነው ቆይ እባክሽ ንገሪኝ"
አለቻት። ሄዋን "ኡፍፍፍፍፍ በቃ አንቺ ስለ ስራተኞቹ ጠባይ
ወይ አልነገርሽኝ አላውቀው .....🥺
የለኝም ጥፋት የማውቀው...😔
ያንቺስ የጉድ ነው....😞
ድንገት ተነስቶ መለየት ሆኖብኝ...
ግራ መጋባት እረ አቤት አቤት...😭
ሁሉም ስላንቺ ጠየቀኝ ምን
ልበላቸው ጨነቀኝ መላው ጠፋኝ....😣😣
ግራ ተጋባ ህይወቴ ጨለማ...😓
ወርሶታል ቤቴ ፍቅሬ አካላቴ...🥺🥺
🥺🥺🥺🥺😔😔😔
@Hayitiye
አንድ ቀን ❶
አንድ አላት ዉለታ የሁሉ መነሻ
እልፉን ለመቃኘት ጅማሮ መጥቀሻ
አንድ ነው የሁሉ የቀን መዳረሻ
እንላለን ደግሞ
መቼ ተፈጠርኩኝ ከምድር መች መጣሁ
መቼ እንዲህ አድርጌ መቼስ አበቃለሁ
አዲስ ህይወት ኖሮኝ መቼስ አገባለሁ
አግብቼ እየኖርኩ እራሴን እተካለሁ
መቼስ ኖሬ ኖሬ መቼስ እሞታለሁ
ብለን ስንጠይቅ ዉስጣችን ልናዉቀዉ
መቼም የአምላክ ፍቃድ እኛ የማናውቀው
የኋላችን እንጂ ወደፊት ባዳ ነው
እናም ስንፈልግ ዝምታን ልንገታዉ
ብለን እናልፋለን ሁሉም አንድ ቀን ነው
✍ እድል
@Marsilas_23
@Hayitiye
፨ በጣም ውብ ሆቴል ነበር። የሚገባ እና የሚወጣ ምንም አይነት
ሰው የለም። ዲና ምንድነው ሰው የለም እንዴ አለች። አዳም አለ
ኑ እንግባ አለና ይዦቸው ገባ። ሆቴሉ ጨለማ ነው።ሄዋን እና ዲና
በፍርሀት ሊሞቱ ምንም አልቀራቸውም ሄዋን አዳም ጋር ልጥፍ
አለች። ዲና ደንዝዛ ቀረች ማንም አልያዘችም።
፨ አዳም "ጌዲዮን አውሬው" አለ።ድምፁን ከፍ አድርጎ ጓደኛዬንም
ወሰድከው አንተ አውሬ" አለ። አሁንም ምንም አይነት ድምፅ
አይወጣም አዳምም ፀጥ አለ።
ዲናም ወደ አዳም ጠጋ ብላ የአዳምን ክንድ አጥብቃ ያዘችው።
በግራ እና በቀኝ ሁለቱም አዳምን አጥብቀው ያዙት። አዳም
በድጋሜ ጮክ ብሎ "ይህ ስራክ አልጠፉኝም፤ ሰይጣንነትክ
መቼም፤ አይጠፍኝም የሰው ደስታ እንደማትወድ አውቃልው አለ።
አሁንም ምንም አይነት ድምፅ የለም......
ይቀጥላል...
@Hayitiye
😘አለሜ ነሽ😘
✍️እድል
🔥ክፍል 31
"""
"""
"""
"""
፨አዳም ከስራተኖቹ አንዷን ጠርቶ ሻይ እንድታፈላ አዘዛት። ከዛም
የፈላ አለ ብላ አመጣችላቸው። ቦስ አዳም እና ሄዋን ሻይ
እየጠጡ ለዲና ምን አይነት ስጦታ እንደገዙ እየተነጋገሩ ነው።
አዳም የገዛውትን ስጦታ አልናገርም አለ። ቦስም ቢሆን እኔም የአዳም አይነት አቋም ነው ያለኝ
አለ።
፨ ሄዋን ምን እንደገዙ ብትጠይቃቸውም አልነገሯትም። አዳም
ለሄዋን "አንቺም መግዛት የምትፈልጊውን ስጦታ መግዛት
ትችያለሽ። ስልኬን ተጠቅመሽ እዘዢ አጠቃቀሙን እኔ አሳይሻለሁ
እቃውን ምረጪ" ብሎ የድህረገፁን ሽያጭ ዌብሳይት እየከፈተ ስልኩን ይዞ ከሄዋን ጎን ተቀምጦ
አጠቃቀሙን አሳያት.....በጣም የሚያማምሩ የአንገት ሀብል፣ የእጅ
ጌጥ፣የእግር አንባር እና ቀለበት በአንድ ላይ ያለበትን መረጠች እና አዘዘች።
፨ሄዋን አዳምን እያየችው "በጣም ጥሩ ጥበብ ነው" አለችው።
አዎ ልክ ነሽ አለና ፈገግ አለ።ቦስ እስቲ ምን መረጥሽ አላት ሄዋን
አአ አላሳይም ብላ ሳቀች። ዲና ድምፆን ከፍ አርጋ "ተዘጋጁ
ልመጣ ነው" አለች። ሁሉም "እሺ ፍጠኝ" ብለው ተንጫጩ ዲና የመኝታ ቤቷን በር ከፍታ ኬብሮምን አስከትላ ስትወጣ ሁሉም አፉቸን ከፍተው ቀሩ ዲና በጣም አምሮባታል ልዕልት መስላ
ነበር። ሄዋን "የእኔ ውድ እህት በጣምም እኮ ነው ያማረብሽ"
አለቻት። ዲና "አመስግናለው ውዴ። እ ወንዶች ምነው አፋችሁን
ዘጋቹ" አለች።
፨ቦስ እና አዳም በአንድ ድምጽ አንደኛ ነሽ አሉዋት። ዲና "ኦኦ በጋራ ነው አድናቆታችሁ በሉ በቃ ልሂድ" አለችና ሁሉንም ስማቸው
ኬብሮንን አመስግናት እና ተሰናብታት "እንዳታረፍዱ እሺ" ብላ
ወጣች። እሺ አሏትና ሄዋን በር ድርስ ሽኝታት ተመለሰች።
ስትመለስ "በይ ሄዋን አሁን ያንቺ ተራ ነው" አላት አዳም።ቦስም
"እውነት አንቺ ደሞ ምን እንደምትመስይ ማየት ነው" አላት።
ሄዋን "እስቲ እናያለን" ብላ የዲና ክፍል ከኬብሮን ጋር ገባች።
እንደገቡም ሄዋን ኬብሮንን "ስለ እኔ የምታውቄው ነገር ካለ ንገሪኝ"
ብላ ጠይቃት ለምናት ነበር። ኬብሮን ግን ምንም የምታውቀው
ነገር እንደሌለ ነገረቻት እና ወደ ሜክ አፕ ስራ ገባች።
፨ለ40 ደቂቃዎች ያክል ተቸግራ እና ተጠባ ሄዋንን ልእልት
አስመሰለቻት።ከዛም ሄዋን "ልብሴ እዚህ ስለሆነ ለብሼ ልውጣ"
ብላ ልብሷን ለበሰች።አዳምና ቦስም ፀጉር አስተካካይ ቤት
በመጥራት ተስተካክለው ዘንጠው ነበር።
፨ኬብሮን ከሄዋን ላይ አይኗን መንቀል አልቻለችም። የሄዋንን
ውበት ዛሬ በደንብ ያየችው ይመስላል። ሳሎን ሄዳ እነ አዳምን
አየቻቸው "ዋው ኧረ ስዎች በጣም አምሮባችዋል። ካይን ያውጣቹ
ቱቱ" አለች።እና ፈገግ አለች። ሁለቱም አናመሰግናለን ። አሁን
ደሞ ሄዋንን ለማየት ተዘጋጁ አለችና።ሄዋን እባክሽ ነይ ወደዚህ
አለች።
፨ሄዋን ደርጃውን ስትወርድ የታኮ ጫማዋ ድምጽ ይስማል።
በመጨርሻ ያዩትን ማመን ከበዳቸው። "የፈጣሪ ያለ" አለ አዳም
ያየውን ማመን ተስኖት። ቦስ "ሄዋን" አለ። ክው ብሎ እጃቸውን
አፍቸው ላይ ጭነው በጣም ተደመሙ።"ልቅም ያልሽ ቆንጆ ነሽ"
አለ። ቦስ ሁለቱም እጇን ሳማቸው ። ከዛም ወደ ዝግጅቱ ሄዱ።
በጣም ቀውጢ ነበር። ሴት፣ ወንድ ፣አሮጊት፣ ሽማግሌ ጎልማሳ
ህፃን ሁሉም ሄዋንን አይቶ ያልፈዘዘ የለም።
፨ ዝግጅቱ ላይ "በጣም ቆንጆ ነሽ" የሚሉዋት በጣም ብዙ
ናቸው። ሁሉም አድናቆታቸውን ገለፁላት። ዲና ስታያት ማመን
ተሳናት ለጓደኞቿ እየዞረች አስተዋወቀቻት "እህቴ ናት"" ስትል ግራ
ገባቸው ምክንያቱም ቤተስብ እንደሌላት ያውቃሉ። ቢሆንም
ሄዋንን ለመተዋወቅ ገና ሲያዩዋት ሁሉም ስለጓጓ ተዋወቋት
የረበሻቸው ነገር ድምጿ ነበር።
፨ ወንዶች ሄዋንን ከበዋት አልተው አልዋት። እሷም ከእነሱ ጋር
ጨዋታዋን አደራችው። ዲናም ከጓደኞቾ ጋር ጨዋታ ጀምራች።
ፕሮግራሙ ተጀመረ በድምቀት እየተከበር ነው ሁሉም
ተደስተዋል ዲና ሰቃይ ተማሪ በመሆኗ ስጦታ ተሰጥቷታል።
በጣም ደስተኛ ነበረች። የምርቃት ዝግጅቱ ላይ የተለያዩ ማርግ
ላይ ያሉ ባለ ስልጣናት እና አስተማሪዎች ሁሉም ተገኝተው
ታድመው ነበር፠
ሁሉም ተደስቱ ዝግጅቱ ሲያልቅ ቤት ወደተዘጋጀው ድግስ ሄዱ።
ዲና ቤት ውስጥ ያለውን ድባብ ማመን አለቻለችም። የአዳም
የማታውቃቸው ጓደኞች እና የቦስ ወዳጆች ተስብስበዋል
በየምግብና የመጠጡን ብዛት ማንም ቆጥሮ አይጨርስውም ዲና
ጮከች በህይወቷ ያሳለፈቻቸው ጥቃቅን ደስታዎች ተጠራቅመው
ቢሰፈሩ እንኳን ይህንን አያክልም።
፨ የደስታ እብደት አበደች።በጣምም ተደስታ ስጨፍር ቆየች።
የስጦታ መስጠት ሰአት ደረሰ። መጀመሪያ ሄዋን ነበር የሰጠቻት
ከዛ ደሞ ቦስ የሚያምር ስልክ ሰጣት የአዳም ተራ ሲደርስ ወደ
እሷ ተጠግቶ እጇን ይዞ "እስካሁን ላረግሽልኝ መልካምነት ይህ
ሁሉ ነገር ያንስብሻል የሰው ፍቅር በቁስ አይቀየርም ግን ይሄን
ስሰጥሽ ውለታሽን አስቤ አደለም" ብሎ ከረባቱን አውልቆ አይኖን
አስራት የተጋረደውን ነጭ መጋረጃ ገፈፈው። ሁሉም ሰው
አጨበጨበ ዲና ግራ ገባት። "አይኔን ፍታልኝ በጉጉት አትግደለኝ"
አለችው። ሳቅ ብሎ ፍታላት ዲና ያየችው እውነት አልመስልሽ
አላት። የሆነ ጊዜ ከስልኳ ላይ ያለውን የመኪና ፎቶ "ሲያምር" ብላ
አሳይታው ወሬዋ ሁሉ ሰለዚህ መኪና ነበር።
፨ዲና አዳምን ጥምጥም ብላ አቀፈችው። አለቀስች ከዛ እንባዋን
እየጠረገች እኔ ያለቀስኩት መኪናዋን ስለሰጠከኝ ሳይሆን
የሚችለውን "የፈለኩትን ነገር የሚያረግለኝ ወንድም ፈጣሪ
ስለሰጠኝ ነው" አለች ጮክ ብላ። ዲና መኪናዋ ውስጥ ልገባ
ቁልፉን ስትለው ሳቅ ብሎ እስካሁን አላየውትም እያለሽኝ ነው
አላት። ዲና እህ አዎ በላ አሳየኝ ስጠኝ ስትለው የመኪናውን በር
ጠቆማት አሁን አየውት እዚህ ተስክቶ ነው እንዴ አለች።
፨ ከዛም መኪናዋ ውስጥ ገብታ ትንሽ ቆየች። እና ወጣች ከዛም
ስራተኖቹ በጋራ አዋጥተው ስጧት። በጣም አመስግናቸው ብላ
ሁሉንም ሳመቻቸው። ቦስ በተደጋጋሚ ሲደወልለት ስለነበር
አስቸኮይ ስራ አለብኝ "በቃ ልሄድ ነው" ብሎ 10:50 ላይ
ሄደ።ዲና ቅር አላት በጣም ከፋት "ከእኔ ምርቃት ዝግጅት
የሚበልጥ ምን ተገኘ" አለች በውስጧ።
፨ ግን እየቆየ ሲሄድ ድብርቷ ለቀቅ አድርጓት ዘና አለች። ከምሽቱ
2:35 ላይ ዝግጅቱ አልቆ እንግዶች በእየ ቤታቸው ሄዱ። እነሱም
ቤት ውስጥ ገቡ። ዲና ንድድ ብላ "ቆይ ቦስ ግን ከእኔ ዝግጅት
የሚበልጥ ምን አግኝቶ ነው ደሞ እሱን ብሎ ጋባዥ ማታ
እጋብዛችዋለው ብሎ አልነበር ቆይ ታዲያ አሁንስ ለምን ቀረ? "
አለች። ስልኩን ሞከረችው አይስራም አዳም "በቃ አትናደጅ ነይ
እኔ ልጋብዝሽ ሄዋን አንቺም ልብስሽን ቀይሪ ማታ ለግብዣው
ልናደርገው የነበረውን ልብስ ቀይረን እንውጣ ቦስ ይቆያል"
አላቸው።ሄዋን "እሺ" አለች። ዲናም ተከትላ "ተስማምቻለው"
አለችና ሁሉም ለባብሰው ለእራት ልብስ እንዲሆን የገዙትን ልብስ
ለብስው ወጡ።
፨ አዳም ያለ ማቆረጥ የፁፍ መልክት ይገባለታል። ዲና ምን
እንደሆነ ስትጠይቀው "ምንም አደለም" ስራ ነው። ይላታል በማታ
እንዴት ብላ ብጠይቀውም መልሷን ሳይመልስላት ወደ ስልኩ
ለገባው መልክት ምላሽ ብቻ ስጥቶ ስልኩን ይዘጋዋል። ሄዋን
ምንም አላለችም አልጠየቀችውምም በትልቁ መኪና ሹፌራቸው
ነው ወደ ሚሄዱበት ያደረሰቻቸው።
የኔ ዉድ አንተኮ ከብዙ እድሎች ይበልጥ እኔ ዘንድ የተወደድክ ነህ..አለም ላይ ካለው ፀጋ በላይ ለልቤ የጣፈጥክ ነህ።..ባንተ አወቅኩኝ አለማወቅን..አወቅኩኝ አለመኖርን..አወቅኩኝ ትንሽነቴን... ለካስ .....ለካስ ልታስደስተኝ ነው ያስከፋከኝ...ከፍ ልታረገኝ ነው ዝቅ ያደረከኝ።...ለካስ....ከሰው ያጣላከኝ ከራሴ ልታስታርቀኝ ነዉ።..ከሰውም ያራቅከኝ ከራሴ ልታገናኘኝ ነዉ።....
ባንተ እራሴን አጣሁ..እራሴንም አገኘሁት።....ባንተ....ሁሉን ነገር አጣሁ..ሁሉንም አገኘሁ።..የሌለኝን ነጠቅከኝ..ሊኖረኝ የሚገባዉን ሰጠከኝ።....የእኔ ውድድድድድ ሽንፈት .....አፈቅርሀለሁ♥️
#እድል የእናቷ ልጅ
@Marsilas_23🥀
@Hayitiye
👉 # ትርጉም አልባ ቅኝት 🤷♀
መፃፍ ትርጉም የለው ማዜምም እንደዛው
ማንባት ማላዘኑ ፍቅሬን ካላመጣዉ
ማልቀሴ መጮሁ ወደኔ ካልገፋዉ
መጠጣት መስከሩ ራስን መርሳቱ
ግጥምን በዜማ አጣፍጦ መስራቱ
መልሴን ካልሆነልኝ ደስታ ለስሜቴ
በእጄ ካላስገባዉ በደጄ በቤቴ
ቁስሌን ሊያስታዉሰኝ ከሆነ ስያሜው
ትርጉም አልባ ቅኝት ሆነኝ ጥበብ ቅኔዉ
✍ eidu
@Hayitiye
በጣም "ነበር" ምወዳት
ሰው እንዴት በበአለ ልደቱ በጠዋት ተነስቶ ማልቀስ ይቃጣዋል ። ያውም ወንድ ልጅ ሆኖ ፤ በቃ እንባ እንባ ይለኛል ፤ ልክ አንድ ልጇን እንዳጣች እናት ወገብህ ላይ ነጠላህን አስረህ ፣ ቃላት እንደጉድ እያዥጎደጎድክ እሪሪሪሪሪሪሪሪሪ በል ይለኛል ። ግን ማልቀስ እንዴት ነው? ፣ እንባስ አይንን ከሚያክል ግድብ እንዴት ነው አምልጦ ሚወጣው? ፣
ከልብ ካለቀሱ እንባ አይገድም ይባላል ፤ ከልቤ ያለቀስኩበት ጊዜ አስታውሳለው ፣ ከአይኔ እንባ የፈሰሰበትን ጊዜ ግን አላስታውስም ፤ታዲያ እኔ በጨጓራ ነው እንዴ ምኖረው? (ምናልባት ለመጨረሻ ጊዜ ያለቀስኩት ይቺን አለም ስቀላቀላት ሳይሆን አይቀርም)
ያዘንኩባቸው ጊዜያት ግን አሁን ድረስ ሳስታውሳቸው እንዳዲስ ያሳዝኑኛል ፤ ማልቀስ ግን አልችልም ፣ በቃ አልችልም ፤ ውሀው እንደ ደረቀ ዥረት ፣ የኔም የእምባ ቧምቧ ደርቋል ፣ ልቤ በቢላ እንደተወጋ እየደማ እንኳን አይኔ ቅርር እንኳን አይልበትም ፣ ምን አለመታደል ነው ፣ ከአበቦች መሀል አበባ ሆነህ ሳለ እንደ እሾህ መታየት።
ሰው በሙሉ የሀዘኑ መግለጫን እንባ እያደረገ የኔ አይነቱ በነሱ ፊት አረመኔ ድንጋይ ተደርጎ ይወሰዳል። ስንት አዞ ባለበት ያንተ እንባህ ስላሎረደ ብቻ አውሬ ተደርገህ ትቆጠራለህ።
በጣም ነበር ምወዳት ፣
ስለምታምነኝና ስለማምናት ሌሎች ከሚወዷት በላይ እወዳት ነበር። ጓደኝነት በመተማመን ላይ ሲመሰረት ከምድር ከፍ ይላል ፤ መተማመኑ ሲቋረጥ ደግሞ ጓደኝነቱ እንዳይተርፍ ሆኖ ከተሰቀለበት ይከሰከሳል።
የአንድን ሰው እምነት ሰብረህ ከምትጎዳው በላይ ፣ እምነቱን እየጠበክለት ያ ሰው እምነቱን እንደሰበርክበት ሲያስብ የምትጎዳው ጉዳት ይበልጥ ያቆስላል። ከዛ የሚከፋው ደግሞ ዳግመኛ ሌላ ሰው እንዳያምንብህም ፣ እንዲያምንብህም ማድረግ እንዳትችል ያደርግሀል።
በጣም ነበር ምወዳት ፣
"ከልቤ አምንህ ነበር " ነበር ያለችኝ ። የቱ ጋር እንደዋሸዋት አልገባኝም ። እኔን ግን ምን ያክል እንደጎዳችኝ አልገባትም። በ"ነበር " ውስጥ "ከዚ ቡኋላ አይኖርም" የሚል ቃል በውስጡ እንዳለ አልገባትም።
በእርግጥ ላይኖርም ይችላል ምክንያቱም እኔ አሁንም እወዳታለው ግን.....
በጣም ነበር እኮ ምወዳት
"የእውነትህን ስትምል በማነው ምትምለው?" ብላ ጠየቀችኝ
"የማያምነኝ አይመነኝ እንጂ በማንም አልምልም ፣ ግን ላንቺ በእናቴ ሞት እምልልሻለው" ነበር ያልኳት
ለማንም እኮ በእናቴ ምዬ አላውቅም ። ደስ የማይላትን ነገር ላላደርግ 'እናቴ ትሙት' ብዬ ነበር የማልኩላት። እና የትኛው ቃል ከብዶኝ ነው እናቴ እንድትሞት ምፈቅደው?
በፍፁም ቃሌን አላጠፍኩም ፣ ከዛም ብሶ ውሸታም ቀጣፊ እስከሚያስብለኝ ድረስ መካዴን አደለም ሰው ሆኜ እሬሳ ብሆን እንኳን እንዴት አይገባኝም።
በጣም ነበር ምወዳት
"እንዴትም ብንጣላ አኮርፍሽ ይሆናል እንጂ አልለይሽም" ብዬ ቃል ገብቼ ነበር።
ግን ይሄን ቃሌን እንዳልጠብቅ ቃሉን የማይፈፅም ከንቱ ሰው አደረገችኝ ፣ ማነው አላምንህም እየተባለ እታመናለው የሚል?
በሁለት ባላ እንደተወጠረ ገመድ ሆኛለው ፣ አንደኛው ቃሌ አንዱን እንዳፈርስ ይገፋፋኛል ፣ አንደኛው ደሞ ቃሌን እንድጠብቅ ያስገድደኛል ።
መተውም አለመተውም ግዴታ ሲሆን ከምጥ የከፋ ምጥ ይሆናል። ልክ መውለድም አለመውለድም የመጨረሻ ምርጫ ሲሆን ፣ ልክ ጥፍርህን በፒንሳ እየጎተቱ ' ድምፅህን እንዳታሰማ' እንደመባል አይነት ስሜት ላይ ገብቻለው።
በጣም ነበር ምወዳት
ከዚ ቡኋላ አምንሀለው ብላ በእናቷ ብትምልልኝ እንኳን እንደምታምነኝ አላምናትም ፤ መፅሀፍ ቅዱስ ብትመታልኝ እንኳን በፍፁም አላምናትም ፤ ልክ ሳይተማመኑ እንደሚኖሩ ሁለት ሌቦች መኖርን እመርጣለው ፤ ግን በማንም የማይተካ ልቤን ከሷ ውጪ ለማንም አልሰጥም ፣ ይሄን ደሞ ማንም እንዲያምነኝ አልሻም ፤ ብቻ ግን......
በጣም እወዳት ነበር ..........................
ወደፊትም መውደዴን ሳታምነኝ እወዳታለው።
ነገ ሁሉ ዛሬ መሆኑ አይቀርም ፣
ዛሬ ሁሉ ደሞ ትናንት መሆኑ የማይቀር ነገር ነው።
@Hayitiye
@Hayitiye 🦋
ከተመቸሽ ቦታ ላሳይሽ" ብሎ ይዞት ወጣ።
፨ ኬብሮን "ምን ሆነክ ነው አዳም ሄዋንስ ለምንድነው
እንደማታቀኝ ሆና ዝም ያለችኝ" አለችው። አዳምም "እየውልሽ
መቼስ ስለ አደጋው ነግሬሻለው እና በአደጋው ምክንያት" ብሎ
ዶክተሩ ያለውን ሁሉ ነገራት ኬብሮን በጣም አዘነች።
፨ ኬብሮን የአዳምና የሄዋን የ ዩኒቨርስቲ ጓደኛቸው ናት ያን ያክል
ባይቀርቦትም ግን ጊቢ ውስጥ ሰላም ይባባላሉ። በሜክ አፕ
ባለሙያነት የተሰማራችው የዩንቨርስቲ ትምርቷን በህመም
ምክንያት አቁማ ነው።ከአዳም እና ከሄዋን ጋር አልፎ አልፎ
በፌስቡክ ታወራለች። በጣም ጓበዝ ሜክ አፕ ስሪ እንደሆነች
በዝናም ስምቷል እሷም ነግራዋለች። ለእዛም ነው የዲና ምርቃት
ሲደርስ ዲናንና ሄዋንን እንድታሳምራቸው ከፌስ ብክ ስልኳን ወስዶ
የደወለላት ።ስለ ሄዋን አደጋም በወሬ ሰምታ ስትጠይቀው የመኪና
አደጋ እንደደርስባት ብቻ ነግሯት ነበር።
፨ ለኬብሮን ሁሉንም አስርድቷት ቤት ገቡ። አደም "ውጪ
አይመችም አለች። በቃ ውስጥ ትስራሽ እና ሄጂ አሁን 1 ስአት
ተኩል ነው 30 ደቂቃ ቢፈጅባት ነው ብላለች። በስልክ ስናወራ
በቃ 2 :15 ሲል ከእቤት ትወጫለሽ። በይ ቶሎ በይ" አላት።
ሁሉም የአዳም እንዲ ያለ ማቆርጥ ማውራት ግራ ገብቷቸዋል
እሺ በይ እንሂድ አለች ሜክአፕ ሰሪዋ በቃ እሺ ብላ ዲና ወደ
መኝታ ቤቷ ወሰደቻት። ሄዋን ልምጣ? አለች። ዲና "አይ
ስርፕራይዝ ነው። ሁላችውም አምሮብኝ ታዩናላቹ" ብላ ኬብሮንን
ይዛ ወደ ክፍሏ ወስደቻት የክፍሏን በር ዘጋችው። ዲናን ለማየት
ሁሉም በጉጉት እየጠበቀ ነው። በተለይ በተለይ ቦስ።
ይቀጥላል...
@Hayitiye
