fa
Feedback
እውነተኛ ስሜት❤️‍🔥

እውነተኛ ስሜት❤️‍🔥

رفتن به کانال در Telegram

@Eiduka ቻናል ገራሚ #ፎቶዎች 📂 #የፍቅር_መልክቶች📜 #ቪዲዮ 📀 #ደብዳቤዎች📝 #የልብን_የሚናገሩ_ሙዚቃዎች 🎶🎶 #ሌሎችንም.......... Administrators & create 👇👇👇👇 👇👇👇 @MarH_23 @eiduka23 Join&share Be happy Be smile

نمایش بیشتر
403
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
😘አለሜ ነሽ😘 ✍️ እድል 🔥ክፍል 30 ፨ "እንቢ አልፈልግግክም ሲጀመር እኔ አንተን እንደ ወንድሜ ነው የማይክ ልክ እንደ ወንድሜ በጣም እወድካለው ግን አላፈቅርክም" ብላ ቆሌዬን ብገፈውስ። እያለ ለሊቱን ሳይተኛ ያሳለፈው ቦስ ሊነጋጋ ሲል የሞት ታናሽ ወንድን የሚወክል እንቅልፍ ወስደው። ዲና ጠዋት ተነስታ የመመረቄያ ፅሁፈ ከአዳም ጋር እየሰራች ነው። አዳም በራስዋ እንድትሰራ ቢነግራትም ዲና ግን "ከአንተ በላይ እኔ አላውቅም ሳይካሎጂ ስለ ህይወት ብዙ ያወራል ፤ያስረዳል ፤አንተ ደሞ የህይወት አስተማሪዬ ነክ ብላ እንዲያግዛት ብዙ ከጣረች በኋላ ተሳክቶላት በጋራ እየሰሩ ነው። ስአቱ ከጠዋቱ 4 ሰአት ሆኖል ግን አልታወቀቸውም። ፨ ሄዋን ከእንቅልፏ አልነቃችም ምክንያቱም ዲና መጥታ ውሀ ካርጨቻት የነጋ አይመስላትም። ዲና ዛሬ አዳምን ገና ብርሀን ሳይገፍ ሌሊት 11:35 ላይ ነው ከእንቅልፉ ቀስቅሳው እንዲያግዛት ያረገችው። አጠገባቸው የተለያዩ ጣፋጭ ኩኪሶች ከሻይ እና ብና ጋር ቀርቦላቸዋል። በተመስጦ የዲናን የመመረቄያ ፁሁፋ ሰርተው ጨርሰዋል። ፨አሁን ደሞ መመረቂያ መፅሄቷ ላይ ሰለምታረገው ፅሁፋ አዳም እንዲነግራት ዉትወታ ላይ ናት። አዳም ይህንን አባባል እራሷ መፃፍ እንዳለባት ነገራት እና "የህይወቴ ደሰታዎች የመኖሬ ትርጉሞችን አመስግናለው H /BO/ ተንከባካቢዎቼ በተለይ በተለይ ደሞ በቅርቡ ላገኘውት የህይወት መምህሪ A ብላ ፃፈች። ፨አዳም ምንድነው የፃፍሽው አላት ። ዲና ምን መሰለክ H ሄዋን ናት BO ደሞ ቦስ ተንከባካቢዎቼ ደሞ እዚህ ቤት ያሉ ስራተኖች የህይወት አስተማሪዬ A ደሞ አንተ ነክ"።ብላ ጀርባውን ደለቅ አረገችው "ኦ እረስቼው ቆይ በህይወቴ ላጋጠሙኝ ክፉ ስዎች እና ለሞቱት ቤተስቦቼ ልጨምር ብላ ፁሁፋ ላይ ጨመርችው። ፨ አዳም በግርምት እያያት "አመሰግናለው ግን ፁሁፉ አልበዛም?" አላት። ዲና "አይ አይ አልበዛም ባክህ እንደውም አንሶል" ብላ እየሳቀች ወርቀቶቾን መሰብስብ ጀመረች። ፨አዳም "እንዴ ዲናዬ ቆይ ቦስና ሄዋን እስካሁን የተኑት ውሀ ካርጨሻቸው አይነቁም ማለት ነው?" አላት ፈገግ ብሎ ከተቀመጠበት የምግብ ጠረጴዛ ሳይነሳ ሽቅብ እያያት። ዲና "እ አንተ እውነትህን ነው ቆይ አንተ ቁርስክን በደብ ብላ እኔ መጣው ቀስቅሻቸው አንተ ዛሬ ተርፈካል" ብላ ሶፉው ላይ የተቀመጠውን ስልኳን ይዞ ቀርብ ወደሚለው የቦስ ክፍል ለመጀመር ቀስ ብላ ከፍታ ገባች። ቦስ ትራስ ስር ወረቀት አየች። በከፊል ይታያል "ይህ ቀን ማለት በቃ ለእኔ" ይላል። ከዛ ቀጥሎ ያለውን ማንበብ አልቻለችም። እሱን ትታው በጆክ ውሀ ይዛ መጣች። እንደተለመደው የስልኳን ካሜራ ካመቻቸች በኋላ ቦስን በእጆ ውሀ ሞልታ እረጨችው። ፨ቦስ እንደተለመደው በርግጎ ተነሳ አይኖቹ እንቅልፍ እንዳልጠገብ ያሳብቃል። ዲና ሳቀችበት "ዛሬ ደሞ እንቅልፍ ሳትተኛ ነው እንዴ ያደርከው ወይስ ስታለቅስ ነበር። በል ተነስ" አለችው። ቦስ "ኧረ ተኝቻለው ሆሆ ስሚ ዛሬ ደሞ ውሀውን ከፍሬጅ ነው እንዴ ያወጣሽው በጣም ቀዝቃዛ ነው" አላት። ዲናም "እና የእንቅልፍ ሰአት በጨመርክ ቁጥር ቅዝቃዜው እየጨመረ ይሄዳል። በል ሄዋንም አልተነሳችም ልቀስቅሳት" ብላ ስልኳን ቦስ ልብስ ለመቀየር ወደ ቁምሳጥኑ ሲሄድላት ብድግ አርጋ ይዛው ወደ ሄዋን ሄደች። የሄዋንን የመኝታ ቤት በር ስትከፍት ሄዋን ከአልጋው ፊት ለፊት ባለው የቁም መስታወት አልጋዋ ላይ ተቀምጣ "እኔ ማን ነኝ?" እያለች እየጠየቀች ነው። በሀሳብ ተውጣለች ዲና ካሜራዋን አብርታው ነበር። ሄዋንን ሳታያት እንዳይታይ አርጋ የፊት የሹራብ ኪሷ ውስጥ አድርጋ ወደ ሄዋን ተጠጋች። ፊቷ ተቀያይሯል ያዘነች ትመስላለች ዲና በቀስታ ተጠግታ እህቴ ሄዊ አለቻት። አቤት "ደና አደርሽ" አለቻት። ዲና በግራ መጋባት ስሜት። "ምን ሆነሽ ነው ውዴ" አለቻት ሄዋን ወደ ዲና ዞር ብላ እናንተ ያልመለሳችውኝን ጥያቄ መስታወቱን እየጠየኩት ነው መስታወቱ ውስጥ ያለችው ሴት ማን ናት ብዬ"አለች። ፨ዲና በሄዋን ዞሬ እንዲ መሆን ገርሟታል ምክንያቱም ሄዋን ከእዛ ቀን ጀምሮ ማለትም ከዲና ጋር በጋራ ጥሩ ሻውር ወስደው እራሳቸውን ካፍታቱበት ቀን ጀምሮ ይህንን ነገር እርስታው አታውቅም ነበር። ፨ዲና ቀዝቀዝ ባለ ድምፅ "እህቴ ይህንን ነገር ላናወራው ተስማምተን የለ እንዴ በይ አሁን ተነሽ ቁርሳችንን እንብላ" ብላ እጆን ጎትታ ይዛት ወደ ሳሎን ሄደች። ሳሎን ቦስና አዳም እያወሩ ነበር የሚያወሩት ስለ ዲና ምርቃት ነው። "አንድ አይነት ልብስ እንልበስ ወይስ የተለያየ ይሁን ጫማችንስ ምን አይነት ይሁን" እያሉ ነበር። ዲና "እናንተ ምንድነው ቆይ እንዲ ከእኔ በበለጠ ምርቃቴ ያሳስባቹ ኧር አትጨናነቁ እንደሚሆን እናረገዋለን" አለቻቸው። ሄዋን "ደና አደራቹ" አለች። ቦስና አዳም "እንዴት አደርሽ" አሉዋት በእኩል ድምፅ። ከዛ ሄዋን ሶፉው ላይ እግሯን ስቅላ ተቀመጠች። ፨ዲና ሄዋንን "እህቴ እና ምን አይነት ልብስ ልለብሽ ወስነሻል?" አለቻት። "እኔ እንጃ" አለች።ዲና ሳቅ ብላ በቃ ፈታ በሉ እኔና ቦስ ለሁላችሁም የሚሆን ልብስ ገዝተናል። እንደምትወዱት ተስፋ አረጋለው ቆይ ይዤው ልምጣ ብላ መኝታ ቤቷ ገባች።አዳም ወደ ቦስ ዞር ብሎ እጁን እየጠቆመ "ታዲያ ይሄ ስው ምንድነው ልብስ እንግዛ ምናምን እያለ ሲያስለፈልፈኝ የቆየው" አለ።ሄዋን ሳቀችና ቦስን እያየች "አይ ቦስ ጉደኛ" አለችው። ፨ቦስ አይ የገዛነውን ልብስ ለሊላ ጉዳይ ፈልጌው ነው። ሲል ሄዋን ሰፍ ብላ ለምን አለች።ዲናም የስማች ይመስላል አይ ከዝግጅቱ በኋላ ሊጋብዘን ነው አለች። ልብሱን አሳየቻቸውና ወደዱት። ሁሉም ለኩት እና አማረባቸው ደስም አላቸው። ፨ ሴኮንዶች ተጠራቅመው ደቂቃ ሆኑ ስአታትም ተባብረው ቀናት ሆኑ። ቀናቷች አንድ ብለው ጀመረው ሁለት ሆነዋል ሁለት የተለያዩ ቀናት ዛሬ የዲና የምርቃት ቀን ነው። በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ቀን ደርሷል። ፨ ዲና ዛሬ የልፉቷን ዋጋ የምታገኝበት ቀን ነው። የዘራችውን የምታጭድበት ቀን ፤ ከመማር ወጥታ ወደ ማስተማር የምትሄድበት ፤ ታካሚ ብቻ ሳይሆን አካሚ የምትሆንበት ቀን የዲናን ደስታ ሁሉም ተጋርተዋታል ደስ ብሏቸዋል። ፨ዲና ጠዋት ተነስታ ሁሉንም ውሀ በመርጨት ቀኑን ጀምራለች። ሰአቱ12:00 ነው።ለምርቃቱ ዝግጅት በለሊት ተነስተው መዘጋጀት ጀምረዋል። ሁሉም ከእንቅልፋቸው ቀስቅሳ ቁርስ ከበሉ በኋላ ዲና ሻውር ወስዳ "በቃ ልለባብስ" ብላ ወደ መኝታ ቤት ስትሄድ። አዳም "ቆይ ቆይ ሜክ አፕ ስሪ ጠርቼልሻለው"አላት። ፨ በር ተንኳኳ "ኣ እንደውም መጣች መስለኝ" ብሎ "በሩን ክፈችው" አላት አንዶን ስራተኛ "እሺ ብላ "ከፈተችላት" ሜክ አፕ ሰሪዋ ናት እቃዎቾን ይዛ የመጣችው። ሄዋንን እንዳየቻት "እንዴ ሄዋን እንዴት ነሽ ፤በስማም በጣም ከስተሻል በሰላም ነው? ለነገሩ አዳም ነግሮኛል" ልትል "ነገሮ... "ስትል አዳም ፈጠን ብሎ "እ ኬብሮን አንቺ ጉረኛ" ብሎ ተጠመጠመባት እና "ኬብሮንዬ እንዴት ነሽ?"። ብሎ ስላም ብሏት "ነይ እስቲ ውጪ መስራት

ልጋብዝክ" ብሎ ይዞት ወጣ። ካፌ ቁጭ ብለው ሳለ አዳም "በላ እነግርካለው ያልከኝን ንገረኝ" አለው። ቦስ ትንሽ ፀጥ ካለ በኋላ ሁሉንም ነገረው ከዲና ፍቅር እንደያዘው እሷ ስለእሱ ምን እንደምታስብ እንደጨነቀው ።አዳም ተደሰተ "እና ታገቢኛለሽ ብለክ ልጠይቃት ነው ጓዴ ቆይ መቼ ፍቅር ጀመራቹ " አለው።ቦስ "አይ አሁን ዘመናዊ አሰራር መጥቷል ፍቅርኛዬ ሁኚ ብዬ ነው የምጠይቃት ከዛ ፈጣሪ ካለ በፍቅር ከቆየን በኋላ ለትዳር ስዘጋጅ ታገቢኛሽ ብዬ እጠይቃታለው ይህ የታገቢኛለሽ ሳይሆን የፕሮጀክት ጥያቄ ነው" አለው። አዳም "ወይጉድ አይ ዘመን" አለና ተገርሞ "በል ተነስ ነገ በሰፊው እናወራለን አሁን ቤት እንመለሰሰ" ብሎት አስነሳውና መኪና ውስጥ ገብቶ ቦስ ማሽከርከር ጀመር። አዳም በጣም ተገርመ ቦስን እያየ በመንገድ ሲስቅ ሲገርም ሲዝናና ነበር ማመን አልቻልም። ለነገሩ እንደተፋቀሩ ሁኔታቸው ያሳብቃል ዲና እንደሆነች ገና ስታየው ነው ፍቅር የያዛት እና እጅ ሰጥታ ተማርካ ለአዳም የተናዘዘችው ቦስ ግን ቃል አውጥቶ ሲናገር የመጀመሪያው ነው።በእዛ ቤት በጋራ 4 ወራትን አስቆጥረዋል።ሁሉም እርስ በእርስ ተግባብተዋል። አዳም ዲናን ቦስን እያየች ስትፈዝ፤ ቦስ ዲናን እያየ ሲፈዝ ፤ ቦስና ዲና ረዥም ደቂቃዎች ሲተያዩ አዳም አይቷል ሄዋን እና ሰራተኞችም ጭምር እና ይህ ነገር ይፋ ሊወጣ ነው። ✨ ይቀጥላል..... @Hayitiye 🦋

😘አለሜ ነሽ😘 🔥ክፍል 29 ✍ እድል " " ከምሽቱ 4ሰአት ሆኖአል ዶክተር ሉሊት የእጅ ሰአቷን አየች። "ሰዎች በሉ 4 ሰአት ሄኗል ወደ ቤት ልሄድ" አለች። ዶክተርም "ኦ ስአቱ ሳይታወቀን ሄደ በሉ በቃ እኔም ልሄድ" አሉና ተነሱ አዳም እንዲያድሩ ቢጠይቃቸውም አሻፈረኝ ብለው በእየ ግላቸው መኪና ወደየ ቤታቸው ሄዱ። ሰራተኞቹም ደከመን ብለው ተኙ። አዳም ፣ ሄዋን ፣ ዲና እና ቦስ ቀሩ። ዲና "በሉ ተነሱ እኛም እንተኛ" አለች። ቦስም "አዎ እኔም ልተኛ ቅርብ ሰአት ከእንቅልፌ ብነሳም በድጋሜ በሀይለኛው ነው የመጣብኝ ደና እደሩ" ብሏቸው ወደ መኝታው ሄደ። አዳም ፈገግ ብሎ "ዩኒቨርስቲ እያለንም ከዶርም ልጆች ማለቴ" አለና ያዘነ ፊት እያሳየ "ከሞቱት ጓደኖቻችን እና ከእኔ ውስጥ እሱ በጣም እንቅልፋም ነበረ " አለ ቦስ የሀዘን ፈገግታ አሳይቶ "ነብሳቸውን በገነት ያኑርልን ፣ነብስ ይማር" አለ። አዳም "አሜን አሜን እኔ እምላቹ ለምን ነገ መቃብራቸው ጋር አንሄድም?" አለ። ቦስ "አዎ እንሄዳለን ጥሩ ሀሳብ ነው"። ብሎ ወደ መኝታው ሄደ። ዲና "እኔም እሄዳለው ሄዋንም እንደዛው አደል ሄዋን?" አለች እና ወደ ሄዋን አይኖቾን አዞረችአቸው ሄዋንም ፈገግ ብላ "አዎ እንሄዳለን ደስ ይለኛል"። ብላ ፈገግ አለች። አዳም የአደጋውን ቅፅፈት እና የጓደኛቹን ጨዋታ አስታውሶ ሳቅ እና ሀዘን የተቀላቀለበት ፊት አሳየ። ዲና "በሉ ደና እደሩ ውዶቼ" ብላ ወደ መኝታ ቤቷ ገብታ ተኛች። አዳምና ሄዋን ብቻቸውን ቀሩ ሄዋን አዳም ወደተቀመጠበት ሶፋ ሄዳ ተቀመጠች። እጆቹን በእጇ ያዘቻቸው። "ለምን አዘንክ" አለችው። "ጓደኞቼ ትዝ ብለውኝ ነው። በጣም እንዋደድ ነበር በጣም ግን የተረገመ ቀን በመኪና አደጋ ምክንያት አጣናቸው። ከእዚህ ውስጥ ደሞ ቦስ አንዱ ነበር። እኔና ቦስ ቀናችን ባለመሆኑ ሳንሞት ቀረን። ከጊዜያት በኋላ ቦስ ወደ ውጭ ሄደ። እናም ተለያየን አሁን ግን ቦስ አጠገቤ ነው" አላት። ሄዋን "ውይይይ በጣም ያሳዝናል" አለች። የሄዋን ድምፅ በጣም እየጮኸች ስለምታወራ ሰው እንደሚረብሽ እሙን ነው ለእዛ ብሎ አዳም "እንቅልፌ መጣ አንቺም ተኚ ነገ ጓደኞቻችን ጋር እንሄዳለን"ብሎ ከተቀመጠበት ተነሳ። ሄዋን "እሺ ግን ትንሽ ስላቆምክልኝ ታሪክ ንገረኝ" አለችው። ሄዋን ጠይቃው እንቢ ማለት በጭራሽ የማያውቀው አዳም እሺታውን ገልፆላት ተቀመጠ። ከዛም ሄዋን አዳም ደረት ላይ ተለጥፋ ታሪኩን ለመስማት ተመቻቸች። አዳም ለሄዋን ድምፁን ቀነስ በማረግ ካሳለፉት ጣፋጭ ታሪክ ውስጥ እሷ ከ ዩኒቨርስቲ ስትመጣ ቤት ውስጥ ስላሳለፉት ጊዜያት እየነገራት በእዛው እንቅልፍ ወሰዳት። አዳም ድምጿ ሲጠፋ እና ትንፋሾ ሲረዝም እንደተኛች አውቆ ላለመቀስቀስ እሱም እዛው ተኛ። ሙሉ ሊቱን ሄዋን አዳምን ተንተርሳ አለፈ። ሁለቱም በህይወታቸው ውስጥ ከተኙት እንቅልፍ ውስጥ ይህቺ ናዋ ጣፋጭ ናት። ተደስተዋል። ዲና ጠዋት ስተነሳ ሳሎን ባየችው ነገር ተደሰተች። ወደ መኝታ ቤቷ በመመለስ ስልኳን አምጥታ ፎቶ አነሳቻቸው። ከዛም ስልኳን ቪዲዮ ላይ አድርጋ አዳም እና ሄዋን እንዲታዩ ካመቻቸች በኋላ ውሀ በጆክ አምጥታ ልርጫቸው ስትል ቦስ ትዝ አላት ቀረፃውን ከቦስ ብጀምር ብላ በማሰብ የስልኳን ካሜራ እንዳበራችው ቦስ ጋር ሄደች። ቦስ መኝታ ቤቱን አልዘጋውም በቀስታ ገብታ ስልኳን አመቻችታ ቦስን የሚያሳያት ቦታ አርገችው። ቦስ አሁንም አልነቃም በቀስታ ሄዳ ውሀውን ሞላ አድርጋ በእጆ ይዞ እረጨችው። ቦስ ከተኛበት በርግጎ ተነሳ ዲና ሳቆን ለቀቀችው ቦስ ዲናን ሙሉ መኝታ ቤቱ አሯሯጣት በመከራ ያዛት እና በትራስ ተደባደብ። ዲና "ቆይ ቆይ አንዴ ስማ አዳምና ሄዋን ሳሎን ተቃቅፈው ተኝተዋል ና ለእነሱም ይህ ነገር ይድርሳቸው ደሞ እየቀረፅኩክ ነበር በኋላ አሳይካለው። አሁን ቀረፆ ሁለት ይጀመር"። ብላ እጁን ይዛ ሳሎን ወሰደችው። ከዛም ቅድም ካሜራውን ያስቀመጠችበት ቦታ አመቻችታ አስቀመጠችው። በጆክ ከያዘችው ውሀ ለቦስም በመዳፏ አረገችለት። ቦስና ዲና እኩል አዳምና ሄዋንን እርጯቸው። ሁለቱም በጣምም ተደናግጠው በርግገው ተነሱ። ከድንጋጤው በኋላ ሳቃቸውን ለቀቁት ከዛም ውሀ በመርጫጨት ሳሎኑን ውሀ በውሀ አረጉት በጣም ደስ በሚል መልኩ ጠዋቱን ቀደሱት። ዲና ከእዛ ቀን በኋላ የደስታ ምንጫቸው ሆነች። ሁሌም ጠዋት ጠዋት የሚሆነውን ቀርፃ ታስቀምጣለች ሁሉም ግን ይህንን አያውቁም። ቦስም ቢሆን አንድ ቀን የመጀመሪያ ቀን ብቻ ቀርፃ ያስቀመጠች ነው የሚመስለው። ሶስቱም ዲናን ጠዋት ተነስተው ውሀ ሊረጩዋት ያቅዳሉ ግን ሁሌም አይቀድሞታም አይሳካላቸውም ፣ ሁሉም የቤቱ ነዋሪ ዲናን በፍቅር ይወዳታል።ዲና ሙሉ ለሙሉ ወደ ትምርቷ ተመልሳለች። ከ2 ቀን በኋላ ትመርቃለች የዲናን ምርቃት ቦስ በጉጉት እየጠበቀ ነው። ምክንያቱም ያኔ ቀለበት (ፍቅረኛዬ ትሆኛለሽ ወይ የሚል ጥያቄ ሲያቀርብላት) ከተስማማች ቀለበት ሊያርግላት ፈልጓል። ይህንን ጉዳይ ለአዳም ሊያማክረው ፈልጓል ግን ፈርተቷል። "ለአዳም ለመናገር እንዲ ከፈራው እንዴት ነው ዲናንሰ ፍቅረኛዬ ሁኚ ብዬ የምጠይቃት መድፈር አለብኝ"ብሎ እራሱን አደፋፈረ። ዛሬ ሁሉም ተሰብስበው የዲና ምርቃት የት ይከበር እያሉ እየተወያዩ ነው። ሰራተኞቹ እቤት ይሁን ይላሉ እነ አዳም ደሞ ሆቴል በእዚህ መሀል ቦስ አጠገቡ የተቀመጠውን አዳም "ጓደኛዬ" አለው አዳም "ውዬ ወዳጄ" ሲለው። "የማማክርክ ጉዳይ አለ ይህንን ስንጨረስ" አለው። አዳምም "እሺ ጥሩ ይህንን ስንጨርስ እናወራለን ክፉ ነገር እንዳልሆነ ተስፋ አረጋለው " አለ አዳም። ቦስም "አታስብ ጥሩ ነው በቃ በኋላ እናወራለን" ብለው ወደ ጋራ ወሬያቸው ሲመለሱ ሄዋን "ዛሬ ደሞ የምትንሾካሾከው ከ ቦስ ጋር ነው"? አለች።ወደ አዳም እያየች። ኧረ አልተንሾካሾክንም" ብሎ ሳቀ። ዲና "ስሙ ኧርረልብስ እኮ አልገዛውም ማነው የሚያጋዛኝ" ስትል ቦስ ፈጠን ብሎ "እኔ እኔ አጋዛሻለው" አላት። ዲና ውስጦ በደስታ ተሞላ።"እሺ አሁን እንሄድ" አለች። ቦስ "ይቻላል እሺ"አላት። ከዛም ወደ አዳም ጆሮ ጠጋ ብሎ በቃ በኋላ እናወራለን ብሎት ከዲና ጋር ተያይዘው ወጡ። ዲና ገበያው ቦታ ስትደርስ ብዙ ልብሶች አየች። ሁሉም በጣም ያማምራሉ። ቦስ የመረጠችውን አንድ ልብስ ገዝታ ሌላ እሱ እንደሚመርጥላት ነገራት።"ሁለት ልብስ ምን ይሰራልኛል" ስትለው ማታ እኔ ስጋብዝሽ ታረጊዋለሽ አላት። ዲና እሺ በቃ ብላ በጣም የተዋበ ልብስ ገዛች።ለቦስ ለሄዋን እና ደሞ ለአዳም ቦስ የመረጠላትን ቀሚስ ዲና በጣም ወደደችው። "በቃ ለምርቃት ፕሮግራሙ ይህንን አረገዋለው" ስትለው አይ አይሆንም ማታ ነው የምለብሽው አላት። ዲና ግራ ገብቷት "ከምርቃት ስነስርአቴ የሚበልጥ ነው ግብዣው" አለችው።አዎ አላት ዲና ሳቅ ብላ "እሺ እስቲ እናያለን ና በል እንሄድ" አለችው። ቦስ "አይ ቆይ አንዴ እዚህ ጠብቂኝ አልቆይም" ብሏት ሄደ።ቆየት ብሎ መጣ "የት ሄደክ ነው" አለችው ግን ሊነግራት አልፈለገም። ከዛም ወደ ቤት ተመለሱ። እንደ ተመለሱ ቦስ አዳምን "ና እስቲ

ከልብ ወደሽኝ ይሆን እንዴ😔❤️

😍😍😍😘😘😘💋💋💋

Wdedkush ymilugn leloch wndoch hula altaysh algn chrsh ksu lela😊😔😔😔😔❤️❤️❤️❤️

#ንዋይ_ደበበ😍❤️ ያይኔ አበባ 🌸🌹 misteyewe tenafkeshale

❤️❤️አፈቅርሀለዉ❤️❤️ አ=አልችልም ካንተ ተለይቶ መኖር😔😔 ፈ=ፍቃደኛ ነኝ ዘላለም ሳፈቅርህ ልኖር☺️☺️ ቅ=ቅመሜ ነህ የሂወቴ ቀመር😘😘 ር=ርሀቤ ነህ መቼም የማልጠግብህ❤️❤️ ሀ=ሀሌታዬ ሁሌም ኑርልኝ በልቤ ዘልቀህ🥰🥰 ለ=ለመሆን እጥራለዉ መመኪያ ኩራትህ😍😍 ዉ=ዉሸት አይደለም ከልቤ ነዉ ስናፍቅህ❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️😘😘😘😘😘😘😘😘😘😘😘😘😍😍😍😍😍😍😍😍🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹 @Hayitiye 🦋

አ💖ፈ💖ቅ💖ር💖ሻ💖ለ💖 ሁ💖 ━━━━━━━━━━━━ ❤️አ =አንድ ነገር ቀረኝ ከጥፋት መታቀብ 💖ፈ =ፈልጌው አደለም አላበዛም ሰበብ 💗ቅ =ቅንነትሽ ደስታ ስሜትን ይስባል 💔ር =ርሀብን ያስታግሳል ጥምንም ያስቆማል 💛ሻ =ሻማ ሁነሽኛል በጨለመው ጎኔ 💞ለ =ለማንም አልፈቅድም እንዲለዩሽ ከ #እኔ 👈 💘ሁ =ሁሌም ወድሻለሁ ትናፍቂኛለሽ እስከማይሽ በአይኔ😢💔 @Hayitiye 🦋

ነይ ነይ 😍ኧረ ነይ አንቺ ሳቂታ😁 የምን ዝምታ 😢ሞልቶ ጨዋታ ነይ ማታ ማታ😎 ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​ ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌🥀💐💃🕺💃🕺💐🥀 @fonkeya12 ❤️❤️❤️❤️❤️📍📍📍📍 💐FOR COMMENT💐🤗@Hayitiye 😃 SHER📥 🥀F🥀A🥀T🥀A🥀​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​ ​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​​ ‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌

ዝምተኛ ልቦች አምነው የወደዱ ወደው የተካዱ ተክደው የራዱ ፍርሃት አንሸራቶ ቁልቁል የጣላቸው የብቸኛ ልቦች የትነው መውደቂያቸው? የትነው መድረካቸው? ማነው አጃቢያቸው? እንዴት ነው ምታቸው? የተካዱ ልቦች አጋር የራቃቸው የሚያቀነቅኑት ምንድን ነው ዜማቸው? የተመረኮዙት እምነት ታጥፎባቸው ድንገት የወደቁ ፍቅር ያዳጣቸው ምስጢር የሚያጋሩት ሰው የበረዳቸው ብቸኝነት ሰርጎ ብቻ ያስቀራቸው ዝምተኛ ልቦች ምን ይሆን ቋንቋቸው? ከየት ነው ጥሪያቸው? በየት ነው ጉዟቸው? የት ነው መድረሻቸው? እንደ ሰብአሰገል ጠቅሶ የሚመራቸው የቃተቱ ልቦች የታል ኮከባቸው መቼም ከአምላክ ትንፋሽ ከውሃ ከአፈሩ ከእምነት እና እውነት ከፍቅር ሲሰሩ ዝምተኛ ልቦች ጥንቱን ሲፈጠሩ ተገፍትረው ወድቀው ደቀው እንዳይቀሩ በተስፋ ጸንተው ነው ዘላለም ሊኖሩ። © [ ጌትነት እንየው ] @Hayitiye 🦋🦋

ሰብስብ ብለው ተቀመጡ። አዳም ታሪኩን መናገር ጀመረ "አንድ ቀን ዩንቨርሲቲ ጊቢ ውስጥ ብጥብጥ ተነሳ። ሀይለኛ ብጥብጥ ያን ጊዜ ሁለቱም በናፍቆት ሊሞቱ ነበር። ትምህርት ለምኔ በሚል መርሀ ግብር ዩንቨርስቲዎችን እና ሌሎች የመማሪያ ተቋማትን ለማፍረስ የተደራጁ ሰዎች የተማሩትን ስዎች በመጨፍጨፍ ላይ ነበሩ። ያልተማረው ህብረተሰብ የገነባውን ሀገር የተማረው ህብረተሰብ አፈረስው የሚል ፁሁፋ ተሸክመው የሚዞሩ በእየኮሊደሩ ላይ ይህንን የሚፅፋ ሰዎች የዩንቨርሲቲ ጊቢያችንን ሞሉት ።እሱም እሷም ስጋት እና ናፍቆት አላስቆም አላስቀምጥ ብሏቸው ከ 15 ቀን በኋላ ሁሉም ተረጋጋ እሱ ጠዋት ሴቶች ዶርም ድረስ መጥቶ አገኛት ተቃቀፉ በናፍቆት እሪ አሉ"። "ከዛም ሁለት ቀን ክላስ ቀጥተው ሲዝናኑ ቆዩና ወደ ትምርታቸው ተመለሱ። የእነሱ ፍቅር የዩንቨርስቲው መነጋገሪያ እና ምሳሌ መስጫ ሆኖ ነበር አስተማሪዎች ፣ተማሪዎች ፣ ዘበኞች ፣የምግብ ቤት እና የ ፅዳት ሰራተኞች በፍቅራቸው ሁሌም ይገረማሉ "። አለ አዳም። ወሬውን ሊቀጥል ሲል ዶክተር እና ዶክተር ሉሊት መጡ። ሁሉም ሰላም ተባባሉና የጋራ ጨዋት ያዙ ስለ ስራ እና ቢዝነስ ፤ስለ አስቂኝ ነገሮች ሲያወሩ እራት ቀረበ እንደንተለመደው ስራተኞች ጨምረው በጋራ እራት በሉ ሁሉም ችግራቸውን ተወት አርገው መሳሳቅ ጀመሩ። አዳም፣ ሄዋን ፣ዲና ፣ቦስ፣ ሲታዩ ከሰአታት በፊት ከባድ ሀዘን ውስጥ የነበሩ አይመስልም። አዳም ለምን ቀን ዶክተር የመጡ ዕለት ዲናና ዶክተር ሲያዩኝ እንደ ደገጡ የሚል ሀሳብ ውስጡ ይመላለሳል። ግን ውስጡ ነው ፊቱ እየሳቀ ነው። ሄዋንም አዳም ምኔ ነው የሚለው ሀሳብ አለባት ፣ ዲና ፣ቦስ ፣እና እነ ዶክተር ፣ ሰራተኞቹ ፣ዘበኛው ደሞ ከግል ችግራቸው ባሻገር ስለ እነ እሱ ይጨነቃሉ። ዲናና ቦስ በተጨማሪም ያልተነገሩት ፍቅር አለባቸው።ግን ሁሉን ትተው እየተደሰቱነው። ✨ይቀጥላል..... @Hayitiye 🦋🦋🦋

😘አለሜ ነሽ😘 🔥ክፍል 28 ✍ እድል " " አዳም ወደ ሄዋን ተጠጋ።ፊቷ ልክ እንደ ቲማቲም ቀልቶ ፤ አልቅሳ አይኖቿ ኮስ አክለው፤ ፀጉሯ ተንጨባሮ ያረገችውን ሹራብ አውልቃ የስረኛውን ቦዲ ከ አንገቱ አንስታ እስከ ሆዶ ቀዳው ነበር። ሄዋንን እንደዚህ ሆና ማየት የማይችለው አዳም በድንጋጤ ደንዝዞ ቀር።ሄዋን በፍቅር አይን እያየችው አልጋውን መታ መታ እያርገች "ና ናተቀመጥ እዚህ ጋር" አለችው። የሰማት አይመስልም ሄዋን በድጋሜ ጮክ ብላ "አዳም ና እዚህ ቁጭ በል እያለኩህ አደል?" አለችው። አዳም አሁን ከፍዘቱ በፍጥነት ነቅቶ ፈጠን ብሎ ተቀመጠ። ሄዋን እራሷን አመቻችታ የአዳም ታፋዎች ላይ ጋደም አለች። አዳም ምንም ማለት አቃተው ብቻ ዝም ብሎ ከአይኑ እንባ ይፈሳል ከአዳም የፈስስው እንባ ሄዋን አይን ላይ ቁልቁል ወርዶ አረፈ። ሄዋን በቀስታ ከተጋደመችበት ተነስታ ጥምጥም ብላ አቀፈችው። አዳምም ጥብቅ አድርጎ አቅፎት ማልቀስ ጀመር። ለቅሶው ድምፅ አወጣ የሄዋንም ለቅሶም እንደዛው።"ምኔ ነክ እባክህ ንገረኝ እባክህ ፣ ሰላሜ ነክ እሱን አውቃለው፣ ደስታዬ ነክ እሱንም አውቃለው ግን እኔ ላንተ ምንክ ነኝ ?? ቢያንስ ምኔ እንደነበርክ ንገረኝ ለእኔ ክፉ ከነበርክም ንገርኝ ግድ የለኝም"። እያለች ከእቅፉ ሳትወጣ ለመነችው ይበልጥ ጥብቅ አረጋ እያቀፈችው። አዳም ሊነግራት ፈለገ ግን ዶክተሩ ያለውን አስታወስ። ዝም ብሎ አቀፋት ሄዋን ከ እቅፉ ወጥታ በእጆ ግጥም አርጋ ጉንጩን ያዘችው። ቅድም ቦስ እንዲ ጥብቅ አርጎ ይዞኝ አይን ለአይን ተገጣጠምን ግን የእሱን ዐይን ሳየው ልክ እንዳንተ ልቤ አልመታም ለምን እንዲ ሆነ ተወው በቃ እንደማትነግረኝ አውቃለው። በቃ ዝም ብለክ እቀፈኝ ብላ ለረዥም ስአት ተቃቅፈው ቆዩ። አዳም ሄዋንን ከእቅፉ አወጣትና ዐይን ዐይኗን እያያት "ዛሬ በጣም ልንደሰት ነው የሚገባን ጥሩ ዜና ሰምቻለው እባክሽ ሄዋን አትናደጂ ለእኔ ስትይ የምንደሰተው ላንቺ ነው የኔ አለም" አላት። አዳም ወዲያው ደነገጠ ሄዋንም እንደዛው። ሄዋን ፈገግ ብላ የመጨረሻ ቃልክን ድገምልኝ እባክህ አለችው። አዳም ግራ ገብቶት ፀጥ አላት። ሄዋን እንዲደግምላት በጉጉት አይን አይኑን ማየት ጀመረች። የሄዋን መኝታ ቤት በር ተንንኳኳ ዲና ነበረች። ስትገባ አዳም እና ሄዋን እጅግ በጣም ተጠጋግተው ነበር የተቀመጡት። ውስጧን በጣም ደስ አላት።ፈገግ ብላ ወደ እነሱ ተጠግታ ጠጋ እንዲሉላት በእጆ ፈልቅቃቸው መሀላቸው ገብታ አቀፈቻቸው። በሶስቱም ውስጥ ደስተኝነት ይታያል ትንሽ ደስተኝነት ብዙ ሀዘን። ትካዜ ፣ ፍቅር ፣ ጭንቀት ብዙ ነገሮችን በውስጣቸው እያስተናገዱ ፊታቸው ላይ ፈገግታ ነግሷል። ዝብርቅርቅ ያለ ስሜታቸውን ወደ ጎን ገሸሽ አርገው ተቃትፈው ብዙ ደቂቃዎችን አስቆጠሩ ። መተቃቀፍ ጭንቀትን ያስረሳል ዲና ከእቅፍቸው ወጣችና "በሉ ዛሬ ሀዘን የለም ደስታ ብቻ ነው እባካቹ ተነሱና ነቃ በሉ አሁን የምነግራችሁ ትእዛዝ ነው። አዳም ተነስና ሻውር ውስድ በል ተነስ" አለችውና እጁን እንዲነሳ ጎተተችው አዳም "እሺ" ብሎ ተነስቶ ሄደ። ዲና ሄዋን ጎን ተቀመጠች የሄዋንን እጅ ያዘቻቸው እና በይ አንቺም ተነሽ የዐይኖችሽን እብጠት ለመቀነስ ሻይ ቅጠል አይንሽ ላይ አደረግልሻለው ከዛ ይለቅሻል ምርጥ ልብስ አለብስሻለው ከዛ በፊት ግን ሻውር ውስጂ እንደውም ዛሬ እኔ እና አንቺ ትንሽ ገንዳ ውስጥ ጊዜ እናሳልፈለን አሁኑኑ ገንዳውን በጥሩ መልኩ አሳምረዋለው የእኔ ውድ እህት" አለቻት። ሄዋን መስማማቶን በአገጯ ምልክት ሰጥቻት። ዲና ወዲያው ሄዳ ሻውሩን አስተካክላ ሄዋን እና እሷ ገንዳ ውስጥ ገብተው ጥሩ ጊዜ አሳለፉ። ሄዋን ጥሩ ሀሳብ ላይ ሆነች። ድብርቷ ለቀቃት ዲናምተደስተች። ብዙ ነገሮችን አወሩ ሄዋን በዲና ቀልዶች በጣም ስትስቅ እና ስትዝናና ቆየች። ዲናም በእርሷ ቀልድ እንደ አዲስ እንደሰማቻቸው ሳቋን ስታቀልጠው ነበር። ሁለቱን ጆሮውን ጥሎ ለሰማቸው ሁነኛ የኮሜዲ ፊልም እያዩ አልያም ደሞ ሰው እየኮርኮራቸው የሚስቁ ወይ ደሞ እርስ በራሳቸው እየተኮራካሩ ይመስላል። ሻውር ቤቱ ላይ የራሳቸው የሳቅ ድግስ አዘጋጅተው እየተዝናኑ ነው። በህይወታችን ውስጥ ምንም አይነት ሀዘን ላይ ብንሆን የሚያስቅ ነገር አይተን አለመሳቅ ወይም ምንም አይነት ደስታ ላይ ሆነን የሚያስለቅስ ነገር ካለ አለማልቀስ አይቻልም። ህይወት እንዲ ናት በህይወታችን ውስጥ ሳቅ ፣ለቅሶ፣ ሞት ፣ፍቅር ፣ መወለድ እና ሊሎችም የህይወት ግዴታዎች ናቸው። ለእዛም ነው ዲናና ሄዋን ከሀዘናቸው ወጥተው እንዲ በሳቅ የታጀብት ምንም ነገር መርሳት ባንችልም መተው ግን እንችላለን ። ይህ የህይወት ግዴታችን ነው። አለ አደል ልክ እንደ ትዛዝ ነገር አለ አዳም የሄዋንን እና የዲናን ከልክ ያለፈ ሳቅ ሰምቶ። ሊጠራቸው ፈልጎ ነበር። ግን ደሞ ሊያቆርጣቸው አልፈለገም። ወደ መኝታ ቤቱ ሄደ እና የእራስጌ መብራት የሚቀመጥበትን አነስተኛ ሳጥንን ቁልፍ ከፍራሹ ስር በማውጣት ከፈተው። ባለ ላዳው የሰጠውን የጠበቃ ኤርሚያስ ማስታወሻዎችን አገኘው። ካቆመበት ማንበብን ቀጠለ። እንዲ ይላል "ጊዲዬን ማለት በጋለ ፍቅር ላይ ውሀ የሚቸልስ ሰው ነው። እሱ ይቅርታን አያውቅም ፤እሱ በድሎ አይርካም፤ መርዝ አስቃይቶ ይገላል ጌዲዮን እጅግ በጣም አሰቃይቶ ይገላል"። ይላል አዳም "ቆይ እኔ ነኝ ልክህን የማሳይክ ብቻ ፈጣሪ ልቦና ይስጥህ "አለ። ከዛም ሄዋን ስትጠራው ሰምቶ ሩጦ ከመኝታ ቤት ወጣ። "አቤት"ብሎ ሲወጣ የሄዋንን ውበት አይቶ ፈዞ ቀረ። አጭር ከስውነቷ ጋር የተጣበቀ ልብስ በግብዳ ጫማ ፀጉሯን ተፈርዛ እና ዲና በጥሩ ሁኔታ ያልበዛ ያላነሰ ሜክአፕ ቀብታት በጣምምም አምሮባታል። አዳም በመፈዘዙ ዲና በጣም ተዝናንታለች። ሄዋን ልቦ በሀሴት ሞልቷል። አዳም ወደ ሄዋን ጠጋ ብሎ "በጣም አምሮብሻል"። አላት ቅድም እንደዛ ተንኳታ እብድ የመሰለችው ሄዋን አበባ መስላ ሲያያት ተደምሟል ። ዲና በበኩላ እንደ ሄዋን ባዘንጥም ጥሩ ልብስ ለብሳለች። አዳም ዲናን አየት አርጎ አንቺ ነሽ አደል መቼስ እንዲ ያሳመርሻት አንቺ ግን ምነው ሳዘንጪ ነገሩ በየት በኩል ሙሉ ፕሮጀክትሽን እሷ ላይ አፈስሰሽ አለ። ዲና ሳቀችና "ኧረ ተው አንተ ልጅ ልጅቷ ከልቧ ቆንጆ ስለሆነች ነው ያማረባት ይልቅ አድንቀሀት ማለፍ ብቻ አያዋጣም ትፈርምልክ ? አለችው። አዳም ፍገግ ብሎ "ልቤ ላይ ብትፈርምልኝ ደስ ይለኛል አለ ሄዋን አዳም ለዲና ይህንን ሲላት በጩከት ባለመሆኑ አልስማችም። "የእራት ስአት እስኪደርስ እና እነ ዶክተር እስኪመጡ ያንን የፍቅር ታሪክ ንገርኝ" አለችው ሄዋን።አዳም ይቻላል ነይ አላት። ዲና እኔም መስማት እፍልጋለው ብላ ሶፋ ላይ ተቀመጡ። ቦስ መጣ ዲና "እንዴ ቦስ የት ነበርክ?" አለችው ቦስም "ተኝቼ መነሳቴ ነው" አለ።ሄዋንን አይቶት "እንዲ ስትሆኚ ነው የሚያምርብሽ" አላት።ሄዋን "አመሰግናለው ቦስዬ ና አዳም አንድ የፍቅር ተከታታይ ታሪክ እየነገርን ነው ስማ በጣም ደስ ይላል" አለችው ቦስ "እሺ ደስ ይለኛል" ብሎ ተቀመጠ። ሶፋው ላይ

😘አለሜ ነሽ😘 🔥ክፍል 27 ✍ እድል " " ዲና ለአዳም ቀዝቀዝ ባለ ድምፅ "ሄዋንን መኝታ ቤት አስተኝቻታለው" አለች። አዳም ደንገጥ ብሎ "ምን ሆና አመመማት አደል አሟት ነው የተኛችው? ሲል ዲና "አይ አይ እንቅልፏ ስለመጣ ነው ያስተኛዋት" አለችው ዶክተርም ከዲና ወሬ ቀጠል አድርገው "አዳም ና ቁጭ በል እባክህ ቦስ አንተም ቁጭ በል መነጋገር አለብን" አሉ። አዳም በሩጫ ወደ ሄዋን ክፍል እየሄደ ዶክተሩ ጠርተውት "አልሰማከኝም አዳም" አሉት። አዳም እርምጃውን ገታ አድርጎ "እሺ እሺ መጣው አንድ ጊዜ ሄዋንን ልያት" አላቸው ዲና "እንዴ ተኝታለች እኮ አትቀስቅሳት" አለችው። አዳም ፈጠን ብሎ "እሺ አልቀሰቅሳትም አይቻት ብቻ ነው የምመጣው" ብሎ ሄደ። የመኝታ ቤት በሩን በቀስታ ከፍቶ ገባ። ሄዋን አልጋዋ ላይ ተኝታለች። እሷን ሲያያየት ሁሌም እንደሚፈዝ እና ወደ ትዝታዎች እንደሚነጉድ እሙን ነው። አደጋው የተፈጠረ ዕለት ያለውን ጊዜ አስታወሰ ጠዋት ሄዋን ቁርስ ሰርታ ቁርሳቸውን በሉ። ከዛም አዳም የስራ ስልክ ተደውሎለት ሊወጣ ሲል ሄዋን "አዲዬ" አለችው "ወዬ ማሬ" አላት። ሄዋን አይናይኑን እያየችው ወገብን በፊቱ በኩል ጥብቅ አድርጋ አቅፋ "ዛሬ ማታ እራት ቤት ውስጥ በጥሩ ሁኔታ ሰርቼ ምርጥ የሻማ እራት ላዘጋጅ ፈልጌ ነበር። ግን ብር ያስፈልገኛል ባልነግርክ እና ስርፕራይዝ ባረግክ ደስ ይለኝ ነበር ግን በድንጋጤ ትሞትብኛለክ አለችና ሁለቱ አይኖቹን በተራ ሳመቻቸው። አዳምም ግንባሯን ስሟት ፍቅር አረግሻለው፤ አፈቅርሻለው፤ ህይወቴ ነሽ ፤ሁሉ ነገሬ ነሽ ፤በተለይ በተለይ ደሞ አለሜ ነሽ፤ አንቺ አንቺ አንቺ ማለት ሄዋኔ አለሜ ነሽ" እያለ አቅፎ አሽከረከራት። ሄዋን እኔም አፈቅርሀለው አለሜሜሜሜሜሜሜ ብላ ጮከች። ከዛም ከንፈሯን በመዝለል ፊቷን ምንም ቦታ ሳያስቀር ሳማት እሷም ልክ እንደሱ እያፈራረቀ ፊቱን ከሳመችው በኋላ እጁን እና ልቡ ያለበትን ቦታን ሳመችው። ከዛም ብሩን ሰጥቷት ሄደ ሄዋን አዳም ከ በር እስኪወጣ ድርስ በአይኗ ሸኘችው። አዳም ከስራ ወጥቶ ወደቤት እየተመለሰ ሳለ ስልኩ ጠራ ጊዲዮን ነበር። "ሄሎ" አለው።ጌዲዮን በሞቀ ድምፅ "ስማ እሳቱ ጠበቃ አዳም እንዳትፈታተነኝ ነግሬክ አልሰማም አልከኝ ስለዚህ ለእዚህ ድፍረትክ ትንሹን ቅጣትክን ማለቴ ሽልማትክን ልስጥህ አሁን በዋትሳፕ ቪዲዮ እደውልልካለው እና አንሳውና ሽልማቱን እየው ትወደዋለክ ሀሀሀሀሀሀሀሀ" ብሎ ስልኩን ዘጋው። አዳም ስልኩን አወጣ እና ዳታውን አበራ። ወዲያው ስልኩ ቪዲዬ ጠራ አነሳው።ጊዲዬን ፊቱን እያሳየው ካላገጠበት በኋላ ሄዋን አስፓልት ልትሻገር መኪና ስታሳልፍ አያት። ከዛም ጊዲዬን ሹፌሩን "በል ግጫት ሀሀሀሀሀሀ የአደጋው ቦታ ድረስ የሚያመጣክ ሰው ሀሀሀሀሀሀሀሀ" አለ።አዳም አይሆንምምምምም ብሎ ጮከ። ከዛም ሹፌሩ በፍጥነት ነድቶ እግርኛው መንገድ ላይ ወጥቶ ሄዋንን ገጫት።አዳም ፈዞ ቀረ እራሱን ሳተ ከደቂቃዎች በኋላ ሲነቃ በሰዎች ተከቦል። "ሄዋኔ ሄዋን ጋር ውሰዱኝ፤ ሄዋንን በመኪና ገጩብኝ ፤የመኪና አደጋ የደረስበት ቦታ ካወቃቹ ንገሩኝ አለና ከወደቀበት ብድግ" አለ። ወዲያው "የሆነ የመኪና አደጋ ደርሶል ተብሏል በእርግጠኝነት ያ ነው ሴት ናት የተገጨችው ተርጋጋ እንወስድሀለን ብለው እጅና እጁን ያዙት አንደኛው ወደ አዳም ጆሮ ጠጋ ብሎ "ጌዲዮን ስላምታን ከ እኛ ጋር ልኮልሀል" አለው። ከዛም ወደ በሀይሩፍ መኪና ይዘውት አደጋ ቦታው ወስዱት እስኪደርስ ግን ከማንም ጋር ምንም ነገር አላወራም። ቦታው ላይ ሲደርስ ሄዋንን በቃሬዛ አንስተው አንፖላንስ ውስጥ አስገብተው ሊወስዶት ሲሉ ደርሰ አዳም እኔ አብሬያት እሄዳለው ቆይ ቆይ እያለ እየጮከ በለቅሶ ታጅቦ እሩጦ አንፖላንስ ውስጥ ገባ። አዳም ከትዝታው ባነነ። የባነነው ክፍሉ ስትገባ ያላያት ዲና ጀርባውን ደለቅ ስታርገው ነው። አዳም እያለቀሰ ነበር ዲና አዳምን ስታየው እጅክ በጣም አሳዘናት ከዛ ና አዳም እንሄድ ማውራት አለብን ብላ እጁን ይዛው ከክፍሉ ወጣች። ዲና አዳምን ወደ መናፈሻው ይዛው ሄደች። ከዛም ቀና ብላ እያየችው "ሄዋን ድንገት ከእንቅልፏ ከነቃች የምናወራውን እንዳትሰማ ነውእዚህ የሆነው" ብላ ወደ ዶክተር እና ቦስ ወሰደችው። ዶክተር ለአዳም ስላምታ አቅርበውለት ወደ ጉዳያቸው ገቡ። "እ ምን መሰላቹ ሄዋን ስላለፈ ህይወቷ መጠየቋ ጥሩ ነገር ነው። ማለቴ ያው አይምሮዋ ለማስታወስ በሚጥርበት ጊዜ የማስታወስ እድሉ ከፍተኛ ነው። ነገር ግን ተሳስታቹ ስላለፈ ህይወቷ አይምሮዋ ሰርቶ በእራሱ ሳይመልስላት እናንተ ከመለሳችውላት ትንሽ ታስታውሳለች ግን በድጋሜ የመርሳት በሽታ ይይዛታል። በድጋሚ ከያዛት ደሞ እስከ መጨረሻው አታስታውስም ስለዚህ ተጠንቀቁ" አሉ ። አዳም "መቼ ነው የምታስታውሰው ታድያ እስከመቼ ነው እንዲ የምንቀጥለው " አለ። ዶክተሩ "በቅርቡ በቅርብ ሙሉ ለሙሉ ታስታውሳለች"። አሉት አዳም በጣምምም ተደሰተ በጣም ዲናና ቦስም እንደዚያው ሁሉም በጣም ተደሰቱ አዳም መጣው ብሎ ወደ ኩሽና ሄዶ ዛሬ ለየት ያለ ምግብ እንዲያዘጋጁ ለስራተኞች ነግሯቸው ወደ ፓርኩ ተመለሰ። ዛሬ ሁላችንም እዚህ እናሳልፍ ለሰራተኞቹ ምግብ እንዲያዘጋጁ ነግሬያቸዋለው"አላቸው። ቦስና ዲና ጥሩ ጥሩ ሀሳብ ነው አሉ በአንድ ድምፅ። ዶክተርም "እሺ ጥሩ ግን እኔ አንድ የምጨርሰው ስራ አለኝ እሱን ጨርሼ እመጣው" ሲሉ አዳም እሺ በቃ ሲመጡ ዶክተር ሉሊት ከተመቻት ይዘዋት ይምጡ" አላቸው። ከዛም ዶክተር እሺ በሉ ልሄድ በኋላ እንገናኛለን ብለው ሄዱ። አዳም በጣምምም ተደስቷል ያለ እርፍት እየሳቀ ነው። አንዶ ስራተኛ በሀይል ድምፅ "አዳም አዳም ሄዋን እየጠራችክ ነው"። አለችው። አዳም "ለምን እሺ መጣው" ብሎ እየሮጠ ወደ ሳሎን ከዛ ወደ ሄዋን መኝታ ቤት በር ጋር ሄዶ አንኳኳ። "ክፈተው" አለች ሄዋን አዳም በሩን ከፈተው ሄዋንን ሲያያት በጣም ደነገጠ። ✨ይቀጥላል..... @Hayitiye 🦋

ቤት እየመጡ ስለሆነ አሁኑኑ ኑ ፍጠኑ"። አለች። አዳም ደንግጦ "ምነው ችግር አለ?" ሲላት እኔም አላውቅም ከደቂቃዎች በፊት ደውለውልኝ ስልክ ሲደውሉልክ ስላላነሳክ እኔ ጋር ደውለው ስለተፈጠረው ነገር ነግሬያቸው ነው እንደሚመጡ እና አንተን አግኝቼክ እንድትመጣ እንድነግርክ ነግረውኝ ነው ይልቅ ቶሎ ኑ በቃ ቻው" ብላ ስልኩን ዘጋችው። አዳም መኪናውን እንዲነዳው ለቦስ ነግሮት ቦስ እያከነፈ መኪናውን ወደ ቤት ነድቶ ደረሱ። ዘበኛው ክላክሱን ሰምቶ የመኪና ማስገቢያ በር ከፈተላቸው። ቦስ መኪናውን ቦታ አስይዞ ካቆመ በኋላ ወደ ቤት ገቡ። ቤት ሲደርሱ ዶክተር እና ዲና እያወሩ ነው። የዲና ፊት ደስታ አይታይበትም።የ ዶክተርም ፊት እንደዛው አዳም እና ቦስ ደነገጡ። አዳም ምን ሆናቹ ነው ሄዋንስ አለ። ✨ይቀጥላል....... @Hayitiye 🦋🦋

😘አለሜ ነሽ😘 🔥ክፍል 26 ✍ እድል " " ሁሉም በጭንቀት ተውጠው ቤቱ በዝምታ ነገሰ።ሄዋን ሁሉንም በአትኩሮት ምላሽ የሚፈልጉ ዓይኖቿ ማየት ቀጥላለች። ከረጅም ዝምታ በኋላ ዲና "እህቴ ሄዊዬ እኛ እኮ ሁሉንም ነገር ማወቅ እስካለብሽ ድረስ ነግረንሻል"። አለቻት ሄዋን ንዴት እና ጩከት በተቀላቀለበት ድምፅ። በቃቹ በቃ አሁንስ በጣም አበዛችውት ቆይ ልታሳብዱኝ እየሞከራቹ ነው እንዴ?። ምንድነው ችግራችሁ እ ሲላቹ ጆሮ ለጆሮ ትንሾካሾካላቹ ፤ ሲያሰናቹ የምትጠይቃችውን ጥያቄ አዛብታቹ ትነግሩኛላቹ ፤ እና ደሞ ስላለፈ ማንነቴ ስጠይቃቹ ለምንድን ነው ለመመለስ ግራ የሚገባቹ፤ ያለፈ ህይወቴ የሚነገር አደለም?፤አሳፋሪ ነው?" ስትል።አዳም ጮክ ባለ ድምፅ "በጭራሽ አንቺ ማለት በጣም ጥሩ እና ማንም ለመሆን የሚመኘው አይነት ሰው ነሽ፤ አንቺ ማለት የፍቅር ምሳሌ ነሽ፤ አንቺ ማለት ሄዋን ለሰዎች አስፈላጊ ከሆኑት ስዎች መካከል ነሽ፤ በተለይ ለእኔ አዎ አንቺ ማለት የኔ" ሲል ዲና አዳም ዝም በል ብላ ጮከች። ሄዋን "እ ጨርሰዋ ቆይ ለምንድን ነው ያስቆምሽው? ለምን አለች" እና ሄዋን እንባ ያርገዙ ዓይኖቿ ፊቷን አጠቡት። ተንስቅስቃ አለቀስች አዳም አደንዝዞ ቀረ። ቦስ ሄዋንን ሄዶ አቅፎ አስገብቷ ደርቱ ላይ ልጥፍ አርጋት። አዳም ከፍዘቱ ሲነቃ በሩጫ ወደ ውጭ ወጣ። ዲና ልትከተለው ፈለገች ግን ብትከተለው ሄዋንን ይበልጥ ማናደድ ይሆናል ብላ ራሷን ገታ አረገች። ሄዋን በቦስ እቅፍ ውስጥ ሆና ለብዙ ደቂቃዎች ካለቀሰች በኋላ ቀና አለችና።"አንተስ ስለ እኔ አታውቅም? ወይስ እንደ እነሱ ልትነግረኝ አትፈልግም እባክህ ልለምንክ ስለ እኔ የምታውቀውን ንገረኝ"። አለችው። ቦስ አለቀሰ። ሄዋንን በሁለት መዳቹፎ ጉንጮቿን ያዛቸው። የቦስ አይኖች ከሄዋን አይኖች ጋር ተገጣጠሙ። ሄዋን የቦስን አይኖች እየተቁለጨለጨች በደፈረሱ ዓይኖቿ እያየችው። አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ? አለችው እንደ በረዶ በቀዘቀዘ ድምፅ። ቦስም በዓይኖቹ እንድትቀጥል ምልክት ሰጣት። የሄዋን እንባዎች በቦስ የእጅ መዳፎች እና በሄዋን ጉንጮች መሀል ፈሰሱ። ሄዋን በአሳዛኝ ድምፅ። ለምድነው አዳምን ሳየው ደስ የሚለኝ ፤ማለቴ ሁላቸውንም ሳያቹ ደስ ይለኛል ግን ደሞ እሱን ሳየው አለችና ጉንጮቿ ላይ ያሳርፈውን የቀኝ እጁን አንስታ ልቧ ላይ አድርጋው እሱን ሳየው እዚህ ጋር ነው ደስታዬ፤ ለምንስ ነው አንተ ስታቅፈኝ ያልተሰማኝ የደስታ ስሜት እሱ ባለፈው ሲያቅፈኝ የተስማኝ አንተ ስታቅፈኝ ደስ ብሎኛል።ግን ልቤ አልመታም። እባክህ ንገረኝ እባክህ ባለፈው ህይወቴ ይህ ሰው ምን አይነት ቦታ ነው ያለው? በሚነግርኝ የፍቅር ታሪክ ውስጥ እኔና እሱን ሁሌም ተክቼ እንደሳልኩኝ ነው። ንገርኝ ልለምንክ ብላ ሁለቱን እጆቹን ጥብቅ አድርጋ ይዛቸው ተንበረከከች። የቦስ እና የዲና ዐይኖች በእንባ ታጠበቡ እና የሄዋን ዐይኖችም በእንባ ታጥበዋል። ቦስ ከሄዋን ጋር አብሮ ተንበረከከና "አታልቅሽ አታልቅሽ ሄዋን እባክሽ ልለምንሽ። ለጊዜው ልነግርሽ እና ላስርዳሽ የምፈልገው ጥሩ ሰው እንደሆንሽ በተጨማሪም እኔ ድጋሜ ብፈጠር እንኳን እንዳንቺ ጥሩ ልሆን እንደማልችል ብቻ ነው"። አላት። ዲና ወደ ሄዋን ተጠግታ ሄዋንን ጥምጥም አድርጋ አቀፈቻት ። ሄዋንም ዲናን የበለጠ ጭምቅ አድርጋ አቀፈቻት። "እኔም እኔም" አለች ዲና ። ደጋግሜ ብፈጠርም አንቺን መሆን አልችልም ጥሩ ሰው ነሽ። እባክሽ አታልቅሺ ለቅሶ አደለም መከፋት አይገባሽም"። አለቻት። ሄዋንም በደከመ ድምፅ "ታዲያ ጥያቄዬን መልሱልኛ" አለች። ዲና "እሺ እህቴ አሁን እርፍት አድርጊ "አለች እና እንድትነሳ እረድታት ወደ መኝታ ቤቷ እየወሰደቻት ሳለ ሄዋን ዲናን "እህቴ" አለቻት። ዲና "ወዬ" ስትላት። "አንቺ ባታስቆሚው ኖሮ እኮ እሱ ለእኔ ምኑ እንደሆንኩኝ ሊነግርኝ ነበር ግን ለምን አስቆምሽው ለምን"አለቻት።ዲና የሄዋንን ጥያቄ ምን ብላ እንደምትመልስ ጨነቃት። ከዛም ነይ እህቴ እረፍት አርጊ ብላ ወደ መኝታ ቤት ወስዳት አልጋዋ ላይ አስተኛቻት። ሄዋን አልጋዋ ላይ ሆና ማልቀሷን አላቆመችም። ዲና የሄዋንን ፀጉር እያሻሸች ልክ እንደ እናት አባብላ አስተኝታት ወጣች። ወደ ሳሎን ስትመለስ ቦስ የለም። ከሳሎን ወጥታ ግቢው ውስጥ አየችው የለም ግራ ገባት "ወዴት ሄዶ ይሆን?" አለች ለእርሷ ዘበኛውን በጩከት ጠርታው እየከነፈ መጣ "አቤት" አላት። ዲና "እእእእ ቦስን አይተከዋል" አለችው። ዘበኛው "አዎ አይቼዋለው ከአዳም ጋር ነው የሄዱት አዳም መናፈሻው ጋር ቁጭ ብሎ እያለቀሰ ነበር። ከዛም ቆይቶ ቦስ መጣና ተያይዘው በአዳም መኪና ወጡ አላት ዲና "ኡፍፍፍፍ ተመስገንን አምላኬ" አለች። ዘበኛው ግራ በማጋባት ስሜት ድፍረት ካልሆነብኝ ቆይ እንዲ የመሆናቹ ሚስጥር ምንድነው? አዳምስ ለምንድነው ሄዋን ስለ ወደ ፊት ህይወቷ ከጠየቀቻችው ጥሩ እንደሆነች ብቻ ንገሩዋት" ያለን አላት። ዲና ዘበኛውን እያየችው "አዎ አዎ አዳም ያላችው አድረጉ እባካቹ። አሁን ምንም ልነግርክ አልችልም። ጊዜው ሲደርስ አዳም እራሱ ይነግራችዋል"። አለችና ወደ ቤት ገባች። ቤት ገብታ በጣም ተቁነጠነጠች" ምን ላድርግ ልደውልላቸው? ወይስ ዝም ብዬ ልቀመጥና ልጠብቃቸው " አለች። እንዲ ከእራሷ ጋር እያወራች ስልኳ ጠራ። አነሳችው ዶክተር ነበሩ ። "ሄሎ ዶክተር እንዴት ኖት" አለች። ዶክተር በተረጋጋ ድምፅ "ደና ነኝ ሁሉ መልካም ነው። ዲና አዳም እና ሄዋን እንዴት ናቸው?። የአዳም ስልክ ይጠራል ግን አይነሳም ከደቂቃዎች በፊት ደውዬ ነበር በተደጋጋሚ ነበር የደወልኩት ግን አይነሳም አንቺም የምታነሽ አልመሰለኝም በጣም ተጨንቄ ነበር"። አሉዋት። ዲና በተቀዛቀዘ ድምፅ "አይ ዶክተር ምን ሰላም አለ። ዛሬ ሄዋን ስለ ማንነቷ እንድንነግራት ጠየቀችን በተለይ ደሞ ማወቅ የፈለገችው ስለ አዳም ነው"። ስትላቸው ዶክተር ምን ቆይ መጣው መጣው ይህንን በዝርዝር መስማት እፈልጋለው። በቻልሽው አቅም አዳም ጋር ደውለሽ አልያም ደሞ በፅሁፍ ብቻ በሆነ ነገር አግኝውና አንቺ ጋር እንዲመጣ ንገሪው። እኔም እየመጣው ነው።"በይ ፍጠኝ ዲና ፍጠኝ እባክሽ" አሉና ስልኩን ዘጉት። ዲና ወደ አዳም ስልክ ደወለች ጥሪው ሊያልቅ ሲል ተነሳ። ያነሳው ቦስ ነበር።"ሄሎ" አላት። ዲና "እናተ ምን ሆናቹ ነው ቆይ አስጨነቃችውኝ እኮ እሺ አሁን የት ነው ያላችውት " አለችው። ቦስ በተረጋጋ ድምፅ አትጨነቂ ትንሽ ነው የራቅነው መኪና ውስጥ ተቀምጠን እያወራን ነው። አዳምን ለማረጋጋት እየሞከርኩኝ ነው ግን የተሳካልኝ ይመስለኛል ፈታ ብሏል "። አላት። ዲናም "እሺ ጥሩ በል ስልኩን ለአዳም አሁኑኑ ስጠው"ብላ ትዛዛዊ የሚመስል መልክቷን አስተላለፈች። ቦስ ፈገግ ብሎ በእጁ የያዘውን ስልክ ወደ አዳም ላከው። አዳም ስልኩን ከ ቦስ የተቀበለው እና ጆሮው ላይ አረገው "ዲናዬ" አላት አዳም "ወዬ አዳም እንዴት ነክ አሁን ከቅድሙ ተረጋጋክ?" አለችው። አዳምም "አዎ ተረጋግቻለው እድሜ ለጓደኛዬ" አላት። ዲና "እሺ ጥሩ እንደዛ ከሆነ ዶክተር ወደ

••●🍃የፀጥታ ጩኀት••●🍃 . . ከዝምታው ክርታስ የጩኀት ጥልቅ ወጀብ... ከልቤ ላይ ሲደርስ ዞሮ ሲያናውጠኝ ደርሶ ሲያቃጥለኝ ላዬ በድን ሆኖ ውስጤ ተበታትኖ የማይገባኝ ሀሳብ የማላቀው ሂሳብ ድንገት ሲያስጨንቀኝ የውስጤን ትኩሳት ያንጀቴን ፍም እሳት ተንፍሼው እንዳልወድቅ ወይ ነግሬ እንዳልፀድቅ መደበቂያ ዋሻ ካንገት ቃል መሸሻ ማብረጃ እንዲሆነኝ ሳቅ ነው የሚቀድመኝ። @Hayitiye @Hayitiye