pökä arts ™
pökä art of drawings and graphic designs - And Poetry vocal reading for any comments contact @tsebaot_melodical_habesha @pokArtsTseba @pokArtsTseba
نمایش بیشترکشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
727
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
- مشترکین
- پوشش پست
- ER - نسبت تعامل
در حال بارگیری داده...
معدل نمو المشتركين
در حال بارگیری داده...
ጦቢያ ግጥምን በጃዝ:
ምን አይነት ዘመን ላይ ደረስን ወገን !
ኢትዮጵያ ምድራዊ ገሀነም (hell pro version) የሆነችበት ዘመን የሠው ልጅ እንደ እባብ ያውም ተጨፍጭፎ ተቀጥቅጦ ተወግሮ ተቃጥሎ ተቆራርጦ ተቦጫጭቆ በጎሳ (ብሔር) ብቻ እየተለየ የሚታረድበት የሠይጣን አመት
ህገመንግስት እንጂ ህግ የሌለበት
መሪ ከነጀሌዎቹ እቃቃ በነፍስ ላይ የሚጫወትበት
ሀገር ስሟ እንጂ ክብሯ እና ልዕልናዋ ሀያልነቷ የከሰመበት
ችግኝ ዛፍ እና ቅጠላ ቅጠል ተከብረው የሠው ልጅ ነፍስ ከጥፍር ቆሻሻ የማይቆጠርበት
እናቱ ስትሰደብ የሚያንገበግበው የሌላው እናት ግን በጦርነት በርሀብ በበሽታ በዘረኝነት ጭፍጨፋ ነፍሷ ሲቀጠፍ ደንታ የማይሰጠው
እንዲህ አይነት የሰይጣን ባለሟሎች ያሉበት ጊዜ ላይ ነን ።
የምናገረው ስለ አንድ ማህበረሰብ ወይም ክልልና ከተማ ወይም ብሔር እና ነገድ አይደለም
የምጮኸው ሠው ተብሎ ስለተፈጠረው
የአዳም የልጅ ልጆች ነው ።
ጎሳ ነገድ ብሔር ክልል ሀገር (ኢትዮጵያ)
ይሔንን ሁሉ ለማለት ሰው መሆን ይቀድማል
ስለእግዚአብሔር ብላችሁ ስለ ሰው ልጅ ክብር ይኑረን
ድምፃችን እኩል ይሰማ
ዛሬ የሚጨፈጨፈው ወገንህ ሲያልቅ ነገ ወዳንተ እንደሚመጣ አትርሳ እያንዳንድህ ።
ኡኡታህን አቅልጠው እንደ ራሔል እንባህን ወደሰማይ እርጨው
ከዚያ የረጨኸው እንባ የሰማዩን ዙፋን አነቃንቆ የወረረንን ደም የተጠማና የማይጠግብ የሰይጣን መንፈስ ይዞት ይጠፋል ።
#በቃ ✋
#የዜግነት_ክብር
#ቀይ_አሻራ ❤️🔥💔
በአራቱም አቅጣጫ የሰዉ ነፍስ መጥፋት ይቁም
የተጎጂ ወገኖችን ድምፅን መስማት ያማል!!
#Ni_Gahaa!
#Kabaja_lammummaa
#በቃ
#የዜግነትክብር
#ይኣኽለና
#ናይ_ዜግነት_ኽብሪ
#Stopkillingcivilians
👉🏿#አባቴ ያ’ውና 😭❕
፡
#ይታይሀል_ጀርባው ⁉️
፡
እንደ አክርማ ስንጥቅ - የተከፋፈለ
እንደ ባድማ መሬት - ላዩ የቆሰለ
ጠኔ እንደመታው - አጥንቱ ገጠጠ
የገላው ቆዳ ተራግፎ - ዕዡ ፈጠጠ
የተተለተለ የስጋ - ርጋፊ❕
ይታይሀል ፊቱ - ያረፈበት ጥፊ❕
፡’
የቆመበት ስፍራ - በደሙ ጨቅይቶ❣️
በልብሱ ዕጣ ላይ - ቁማራቸው ደርቶ
የስድቡ ብዛት - ወርደትና ንቀት
እኔን ለመፈለግ - ያደረገው ትጋት
ፍቅሩን ነው ’ሚተርክ - የጀርባው ግርፋት
ሁሉን የሚችለው - ያ’ውል የ'ኔ አባታ❗️
፡
በቃሉ ያጽናት - ምድርም ስትርቀው 🌍
በመውደቅ መነሳት - ውርደት ስትንቀው🥺
፡
👉🏿#አባቴ ያ’ውና❗️
ፍቅሩ እየበረታ - ምህረቱን ያጸና❗️
መከራዬን ታግሎ - በመስቀል ላይ ሊሞት❤️
ሆሳህና ብዬ🌿 - ትናንት የሸኘሁት
ቀራኒዮ ሳልደርስ - ከረቅት ያየሁት
መከራውን ስገጥም
ውርደቱንም ሳዜም🌜
ጭንቀቱን ስተርክ
ጩኽቱንም ስሰብክ
ልቤ ሳይንበረከክ🔥
ስለፍቅሩ ምለሽ
ከዓለም ጋራ ስሸሽ
በውርደቱ ካባ - እኔ ከበርኩበት🌤
ስራውን ስናገር - ዝና አተረፍኩበት
በመስቀሉ መንገድ - ለዓለም ገነንኩበት
፡
ፍቅር ባዘለ ልብ - በዛለ ትከሻው
የሞቱ ፍጻሜ - እኔ ፡ ነኝ መድረሻው 🔥
፡
Repost from ጦቢያ ግጥምን በጃዝ
ምን እየሆንኩ ልጠብቅሽ?
ኤልያስ ሽታኹን
~ ~ ~ ~ ~
ቅድ ሰማይ እየሰፋሁ
ራስ ዳሽን እየገፋሁ
ወይስ
እየሰራሁ የኖኅ መርከብ
ሳፈላልግ የሰው ኮከብ..
ምን እየሆንኩ ልጠብቅሽ?
እየዘመርኩ?
እየዘፈንኩ?
እያረመምኩ?
ግራ ገባኝ እኮ
ያልለየት ድል ነው ያልለየት ምርኮ።
ምን ስሆን ልጠብቅሽ?
አባይን ስጠልቀው
ኤርታሌን ስሞቀው
ቆዳዬን እንደጨርቅ ችሎ ቢተኩሰው
ተዋነይ ጋር ልሂድ ዕፁን እንዲምሰው።
ማን ጋር ልጠብቅሽ?
ከጌታዬ ግራ ከጌታዬ ቀኙ
በየት ትመጫለሽ ወይ አፍቃሪ ሞኙ።
ካብርሃም ቤት አጋር
ወይስ
ባቢሎን ግንብ ጋር።
የት ጋር ትመጫለሽ?
በዘመን የት ዘመን?
በቦታ የት ቦታ?
ከንጉሥ የት ንጉሥ?
ከባህር ምን ባህር?
ከጫካ የት ጫካ?
ከደብር የት ደብር?
:
ከሶላት ምን ሰዓት?
ምን እያረግኩኝ ልጠብቅሽ?
ከመላእክት ጋር ስገለፍጥ
የዛፍ ቆዳ ስልጥ...
ግዙፍ ሆኜ ወይ ረቂቅ
ንፋስ ሆኜ ወይስ ደቂቅ....
ወንዝ ሆኜ ወይስ አምባ
ደስታ ሆኜ ወይስ ዕምባ...
ፀሀይ ግርጌ ወይ ጨረቃ
ግጥም ሆኜ ወይ ሙዚቃ...
ምን እየሆንኩ ልጠብቅሽ?
ገጣሚ ኤልያስ ሽታሁን
ንባብ ፀባዖት ሶልአኪያ
Repost from ጦቢያ ግጥምን በጃዝ
.....ህማማት
.....✍✍✍
አባ አይኮንኑኝ
የጦም በመብላቴ
እንቁላል በልቼ
ብትቆይ ህይወቴ
ሌሎቹን ሳያዩ
እኔን አይገዝቱ
ሰው እየቦጨቁ
በለተ ህማማቱ
ምን ነው ግን አባቴ
በኔ ላይ በረቱ???
ቀለል አርገው አይተው
አባቴ ይፍቱኛ
የጣለችው ዶሮ
ነበረች ጦመኛ
በህይወት ዘመኗ
ስትጭር ስትለቃቅም
ከጥሬ በስተቀር
አንዳች በልታ አታውቅም
ፀባዖት ሶልአኪያ