fa
Feedback
ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

رفتن به کانال در Telegram

ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።

نمایش بیشتر
636
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-47 روز
-1230 روز
آرشیو پست ها
❤ ከዚህም በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም ሒዶ ከቅዱሳን መካናት ተባረከ በዚያም በቅድስት ትንሣኤ በተሰየመች ቤተ ክርስቲያን በጳጳሱ በአባ ሚካኤል እጅ ቅስና ተሾመ። ከዚያም ወደ ምስር አገር ተመልሶ በማዕልቃ ባለች በእመቤታችን ማርያም ቤተ ክርስቲያን ቅዱሳት መጻሕፍትን እየጻፈ ተቀመጠ። ❤ በዚያም ወራት ሊቀ ጳጳሳቱ አባ ቄርሎስ ዐረፈ። የወንጌላዊው የቅዱስ ማርቆስ መንበርም ያለ ሊቀ ጳጳሳት ነበር። ስለዚህም ኤጲስቆጶሳት የአገር ሽማግሌዎችና ሕዝቡ ሁሉ ተሰበስበው ይሾሙት ዘንድ በአንድ ምክር ተስማሙ ሰይጣን ግን ክፉዎች ሰዎችን አነሣሥቶ ተቃወሙት። ሹመቱንም አልፈቀዱም። ነገር ግን መንሳዊ አባት የነበረውን የከሊል ልጅ አባ አትናቴዎስን ሾሙት። እርሱም መንጋውን በበጎ አጠባበቅ ጠበቀ። ❤ እርሱም በዐረፈ ጊዜ ኤጲስቆሳትና የሕዝቡ አለቆች ዳግመኛ ተሰበሰቡና በእጃቸው ጽፈው አባ ገብርኤል እንዲሾም ፈቀዱ ሁለተኛም በሕቡም መካከል ሁከት ተነሳ ከሌሎችም ጋር እጣ ያጣጥሉት ዘንድ ተስማሙ ስሞቻቸውንም ጽፈው በመንበሩ ላይ አኖሩ በላዩም እየጸለዩና እየቀደሱ ሦስት ቀኖች ሰነበቱ። ከዚህም በኋላ ታናሽ ብላቴና አምጥተው በውስጡ የአባ ዮሐንስ ስም ያለበትን ክርታስ አወጣላቸው። ያም አባ ዮሐንስ ተሾመ ይህ አባ ገብርኤል ግን ለማዕልቃ ቤተ ክርስቲያን ተከራካሪ አድርገው ሾሙት። ❤ በዚያም ወራትም በግብጽ ቤተ ክርስቲያን ላይ ችግር ሁኖ ነበር። ይህ አባ ገብርኤልም ወደ አባ እንጦንስ ገዳም ሒዶ በጾምና በጸሎት በሥግደትም በቀንና በሌሊት ሲጋደል ኖረ። ከቅዱሳን መነኰሳት ብዙዎች መልካም ራእይን አዩለት ከእርሷቸው በእስክንድርያ ከተማ ሊቀ ጳጳሳት ልብስን እንደሚአለብሱት ብዙዎች ከአሕዛብ የተመለሱ ክርስቲያኖችም እንደሚያጅቡት ያየ አለ። ደግሞም ይሾምባት ዘንድ ወደ አስቄጥስ ወደ አባ መቃርስ ገዳም ሲሔድ ያየለት አለ። ቁጥር የሌላቸውንም መክፈቻዎችን ሲቀበል ያዩ አሉ። ❤ ከገዳሙም ሊወርድ ብዙ ጊዜ ይሻ ነበር ነገር ግን አልተቻለውም። ከዚህ በኋላ አባ እንጦንስ በራእይ ተገልጦ እንዲህ አለው "ያለ እግዚአብሔር ፈቃድ ከዚህ ገዳም ትወርድ ዘንድ እኔ አልፈቅድም ጊዜው ሳይደርስ አትውረድ" አለው። ❤ ከሦስት ዓመት በኋላም አንዱ አረጋዊ የከበረ መልአክ እንግዲህስ አባ ገብርኤልን ወስደው በእስክንድርያ ከተማ ሊቀ ጵጵስና ይሾሙታል እያለ እንደሚያነጋግረው ራእይ አየ። በዚያችም ቀን የሀገረ እንጣፊ መኰንን መጣ ከእርሱም ጋር ብዙዎች መሳፍንቶች ነበሩ። አባ ገብርኤልን አምጥተው በእስክንድርያ ከተማ ሊቀ ጵጵስና ይሾሙት ዘንድ የሚያዝዝ የንጉሥ ደብዳቤም ከእርሱ ጋር ነበረ። ❤ ከዚህም በኋላ ያለ ፈቃዱ ወስደው በወንጌላዊው በቅዱስ ማርቆስ ወንበር ላይ ሊቀ ጵጵስናን ሾሙት። ቀን እርሱ ለኢየሩሳሌም አንድ ጳጳስና ሌሎችንም ኤጲስቆጶሳት ቀሳውስትንና ዲያቆናትንም ሾመ። ከዚህም በኋላ ሦስት ጊዜ ሜሮን አከበረ ባረከ እንደዚህም አድርጎ አንድ ዓመት ከአንድ ወር ኖረ። በዚያን ጊዜም አባ እንጦንስ ተገልጦ እንዲህ አለው "እነሆ ዕረፍትህ ቀርቦአል ከዐሥራ ስምንት ወሮች በኋላ ወደ እግዚአብሔር ትሔዳለህ የዘላለም ሕይወትንም ትወርሳለህ"። ❤ ከዚህም በኋላ በክርስቲያን ወገኖች ላይ ታላቅ መከራ ሆነ። ይህም አባት ወገኖቹን ያድን ዘንድ ወደ ጌታችን ለመነ ክብር ይግባውና ጌታችንም ልመናውን ተቀብሎ ሕዝቡን ይቅር አለ። ❤ ከዚህም በኋላ ሊቀ ጳጳሳቱ ከመንበረ ሢመቱ ወጥቶ በምስር አገር ዓመት ሙሉ ተሠወረ። ከአንድ ምእመን በቀር ማንም አላወቀበትም በቀንና በሌሊት በገድል ከመቀጥቀጡ የተነሣም መልኩ ተለወጠ ሥጋውም ደረቀ። ❤ ከዚህም በኋላ እግዚአብሔር እርሱን ለሚፈራው ለአንድ ምእመን ሥራውን ገለጠ። እርሱም ከዚያ ቦታ አውጥቶ በሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን አስቀመጠው በጸሎትና በቅዳሴ እያገለገለ ኖረ። ድኆችንም ይጐበኛቸው ነበር። የሚሹትንም ይሰጣቸው ነበር። ወደ ርሱ የሚመጡትንም ሕዝቦች ያስተምራቸውና ያጽናናቸው ነበር። ❤ በአንዲት ዕለትም ሊቀ ጳጳሳት አባ አትናቴዎስ በግልጽ ታየው እንዲህም አለው "ስለዚህ ፈጽሞ አትዘን ከዚህ ብዙ ድካምና መከራ እግዚአብሔር ያሳርፍሃልና አነሆ ምድራዊ ኑሮህን የሚፈጽም ደዌ በአንተ ላይ ይመጣል ነገር ግን ደስ ይበልህ ታላቅ የሆነ የእግዚአብሔርን ጸጋ ተቀብለሃልና። የዘላለም ሕይወትንና የማያልቅ ተድላ ደስታንም ትወርሳለህና" አለው። ❤ በዚያን ጊዜም በሚያስጨንቅ ደዌ ታሞ እየተጨነቀ ኖረ። ስለ ነፍሱም መውጣትና በእግዚአብሔር ፊት ስለ መቆሙ ይፈራና ይደነግጥ ነበር የእመቤታችን ማርያም ሥዕልም በዚያ ነበረ። ወደርሷም አዘውትሮ ይማልድ ነበረ በዚያን ጊዜም ክብር ይግባውና ራሱ እግዚአብሔር በብሩህ ገጽ "ተገለጠለት መንግሥተ ሰማያትን አግኝተሃልና ደስ ይበልህ እንጂ አትፍራ እስከ ሦስት ቀንም ከዚህ ከኃላፊው ዓለም ትወጣለህ" በማለት አረጋጋው። ይህንንም ብሎ ከእርሱ ተሠወረ በሦስተኛውም ቀን ሐምሌ 11 ቀን በሰላም አረፈ። በቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያንም በታላቅ ክብር ተቀበረ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ገብርኤል በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሐምሌ 11 ስንክሳር።                             ✝️ ✝️ ✝️ ❤ "#ሰላም_ለኢሳይያስ_ቀሲስ። ወግኍሥ ባሕታዊ ዘደብረ መቃርስ። ከመ አአምኀከ ዘልፈ በመሥዋዕተ ስብሐት ሐዲስ። አጒይይ እከይየ መንፈስ ቅዱስ። እስመ ለኃጥእ ተብህለ መሥዋዕቱ ርኵስ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሐምሌ_11።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ተፈሥሑ ጻድቃን በእግዚአብሔር። ወለራትዓን ይደልዎሙ ክቡር። ግነዩ ለእግዚአብሔር በመሰንቆ"። መዝ 32፥1-2። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ጢሞ 2፥1-9፣ 1ኛ ጴጥ 4፥12-17፣ የሐዋ ሥራ 14፥20-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ6፥20-27። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን" ❤            ❤ #ሐምሌ ፲፩ (11) ቀን። ❤ እንኳን #ለመርባስ ከሚባል አገር ሰዎች ለሆኑ #ለቅዱሳን_ዮሐንስና_ለአባቱ_ወንድም_ልጅ_ለስምዖን ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓልና #ለእስክንድርያ_ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሰባ ስምንተኛ ለሆነው #ሊቀ ጳጳሳት_ለቅዱስ_ለአባ_ገብርኤል ለዕረፍቱ በዓል በሰላሞ አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰበው፦ በአስቄጥስ ገዳም ከነበረው ከቅዱስ አባት ኢሳይያስና እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                 ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅዱሳን_ዮሐንስና_የአባቱ_የወንድም_ልጅ_ስምዖን፦ የዚህም ቅዱስ ዮሐንስ እናቱ መካን ነበረች አባቱም ልጅን ይሰጠው ዘንድ ክብር ይግባውና እግዚአብሔርን ይለምነው ነበር ከዚህም በኋላ ልጁን በሕይወቱ ዘመን ሁሉ ለእግዚአብሔር አገልጋይ ሊአደርገው ተሳለ። ❤ መጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስም እግዚአብሔር ልጅን እንደሚሰጠው በራእይ ተገልጦ ነገረው። ይህን ቅዱስም በወለደው ጊዜ ዮሐንስ ብሎ ጠራው በመጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስም ስም ቤተ ክርስቲያን ሠራ። ❤ ከዚህም በኋላ አድጎ ዐሥራ ሁለት ዓመት በሆነው ጊዜ አባቱ የበጎች እረኛ አደረገው ምሳውንም ለእረኞችና ለመንገደኞች ሁል ጊዜ ይሰጥ ነበር እርሱ ግን እስከ ምሽት ይጾም ነበር። አባቱም ይህን ነገር በሰማ ጊዜ ስለዚህ ሊአረጋግጥ ወደ እርሱ ሔደ አባቱንም በአየው ጊዜ ዮሐንስ ፈርቶ ሊሸሽ ወደደ። አባቱም "የዛሬ ምሳህን አሳየኝ" አለው ብላቴናውም "ታይ ዘንድ ግባ" አለው ወደ መጠለያውም በገባ ጊዜ አገልግሉን ትኩስ እንጀራን ተመልቶ አገኘው እጅግም አደነቀ ከልጃቸው የሆነውንም ለሚስቱ ነገራት። ❤ ከዚያችም ቀን ጀምሮ እግዚአብሔር ጸጋ እንደ አደረችበት አወቁ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት እንዲማር አደረጉት እንጂ በጎችን የሚጠብቅ እረኛ እንዲሆን አልተዉትም። ❤ ከዚህም በኋላ አባቱ ሊአጋባው ወደደ። እርሱ ግን ይህን አልወደደም። ዐሥራ ስምንት ዓመት በሆነውም ጊዜ ቅስና ተሾመ የአባቱ የወንድም ልጅ የሆነ ስምዖንም በጎቹን ትቶ መጥቶ የእርሱ ደቀ መዝሙር ሆነ። እርሱም ስለ ተአምራቱ የተናገረ ነው። እግዚአብሔር በእጆቹ ላይ ድንቆችንና ተአምራቶችን ገልጧልና። ደዌ ያለባቸውንም ሁሉ ያመጡአቸው ነበር እርሱም በዘይቱ ላይ ይጸልይና ይቀባቸው ነበር ወዲያውኑም ከደዌያቸው ይድኑ ነበር። እርሱም ወደርሱ የሚመጡትን ከኃጢአት ይርቁ ዘንድ ያስተምራቸው ነበር። ይመክራቸውና ይገሥጻቸውም ነበር። ከተአምራቱም አንዱ ይህ ነው በአንዲት መበለት የተሸከመችውን ገብስ ቀምቶ ለፈረሱ አበላት ያችም መበለት በዚህ ቅዱስ ዘንድ ከሰሰችው ቅዱስ ዮሐንስም ረገመው ያን ጊዜም ፈረሱ ሞተች። ❤ ዳግመኛም የንጉሥ የጭፍራ አለቃ ግብር ሊሰበስብ መጣ አንድ ዐይኑ የታወረች አንድ አገልጋይም ነበረው። ከእርሱም ተባርኮ ወዲያውኑም የታወረች ዐይኑ ተገለጠች በእርስዋም ደኅና አድርጎ አየ። ይህም ቅዱስ የሰዎችን ሥራቸውን በግልጽ ያይ ነበር ስለ ኃጢአታቸውም ንስሓ ይገቡ ዘንድ ይገሥጻቸው ነበር። ❤ ዜናው በንጉሥ ማርያኖስ ዘንድ ተሰማ ለእርሱም አንዲት ሴት ልጅ ብቻ ነበረችው ወደ ሆድዋም ከይሲ ገብቶ ለሞት ተቃረበች ከዚህም በኋላ ያድኗት ዘንድ ገንዘቡን ለባለ መድኃኒቶች ሰጠ ነገር ግን አልተቻላቸውም። ከዚህም በኋላ የጭፍራ አለቃው የባሪያውን ዐይን እንደ አዳነ የቅዱስ ዮሐንስ ዜና ነገረው ንጉሡም ጭፍራ ልኮ ወደርሱ ሊአስመጣው ወደደ ቅዱስ ዮሐንስም በመንፈስ ዐወቀ እርሱ ግን የመንገዱን ድካምና ባሕሩን ይፈራ ነበር ያን ጊዜም ደመና መጥታ ነጠቀችው ሰርመላስ ከሚባል አገርም ወደ አንጾኪያ ከተማ አደረሰችው። ንጉሡም ዐልጋ ላይ አቆመችው ንጉሡም ደነገጠ ቅዱስ ዮሐንስም "ወደዚህ ወዳንተ ልታስመጣኝ የተመኘኸው ምስኪን ሰው እኔ ነኝ" ብሎ ነገረው። "አሁንም ልጅህን አምጣት" አለው ልጁንም አመጣ። በላይዋም በጸለየ ጊዜ ከይሲው ሳያሳምማት ከሆድዋ ወጣ። ንጉሡም ከቤተ መንግሥቱ ሰዎች ሁሉ ጋር ከእርሱ ተባረኩ። እጅግም አደነቁ ለሚፈሩት ይህን ጸጋ የሚሰጥ የተመሰገነ እግዚአብሔርንም አመሰገኑ። ❤ እጅ መንሻውንም ብዙ ገንዘብ አቀረበለት እርሱ ግን ምንም አልወሰደም። ንጉሡም በእርሱ ዘንድ ሊያኖረው ወደደ ቅዱሱ ግን አልወደደም ንጉሡም እንዳይሔድበት ቀሚሱን ያዘ ያንጊዜም ንጉሡ ቀሚሱን እንደያዘ ደመና ነጥቆ ወሰደው ቀሚሱም ተቆርጦ በንጉሥ እጅ ላይ ቀረ ቅዱስ ዮሐንስም በዚያች ሰዓት ወደ አገሩ ደረሰ። ❤ ንጉሡም ቤተ ክርስቲያ ሠርቶ የቀሚሱን ቊራጭ በውስጧ አኖረ ቤተ ክርስቲያኒቱም እስከ ዛሬ ድረስ የፊቃር ቤተ ክርስቲያን ተባለች። የቊርባን ቅዳሴ በሚቀደስ ጊዜም ሥጋውንና ደሙን መቀበል የሚገባቸውንና የማይገባቸውን ጻድቃንና ኃጥአንን ያያቸዋል። ❤ ከሀዲው ዲዮቅልጥያኖስ የጣዖትን አምልኮ በአቆ ጊዜ ለአባቱ ወንድም ልጅ ለስምዖንም ይህን አስረድቶት ወደ እስክንድርያ ከተማ ሔዱ በመኰንኑ ፊትም ቁመው ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ታመኑ ጽኑዕ የሆነ ሥቃይም አሠቃያቸው ከዚህም በኋላ ራሶቻቸውን ሐምሌ 11 ቀን በሰይፍ አስቈረጣቸው የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበሉ ከሥጋቸውም ድንቆችና ተአምራት ተገለጡ ለበሽተኞችም ታላቅ ፈውስ ተገኘ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ሰማዕታት ዮሐንስና ስምዖን በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ትድረስን ለዘላለሙ አሜን።                               ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_ገብርኤል፦ ይህም አባት ለእስክንድርያ ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሰባ ስምንተኛ ነው። የዚህም ቅዱስ ወላጆች እግዚአብሔር ሕግ የጸኑ ደጋጎች ፈቃዱንና ትእዛዙንም የሚፈጽሙ ነበሩ። ይህንንም ቅዱስ በወለዱት ጊዜ በፈሪሀ እግዚአብሔር አሳደጉት። ❤ በአንዲት ዕለትም ቅዱሳን መነኰሳት ወደርሱ መጡ ከውስጣቸውም መልካም ገድል ያለው አንድ አረጋዊ ነበረ። እርሱም ብዙዎች ኤጲስቆጶሳት ሕፃኑን ከበው እጃቸውን እንደሚጭኑበት እንደሚባርኩትና ይሁን ይሁን ይገባዋል እንደሚሉ ራእይን አየ። ❤ ሽማግሌውም ይህን ራእይ በአየ ጊዜ ሕፃኑ ታላቅ እንደሚሆን አሰበ ለአባቱም "ይህን ሕፃን አስተምረው ለብዙዎች ሕዝቦች አለቃ ይሆን ዘንድ አለውና" አለው። አባቱም ሰምቶ እግዚአብሔርን አመሰገነው "ከዚህ ሕፃን ምን ይደረግ ይሆን" አለ። ❤ ሕፃኑ ሁለት ዓመት በሆነው ጊዜ ክብር ይግባውና በጌታችን ፈቃድ አባቱ ዐረፈ። ብህና በሚባል አገርም በገድሉ የተደነቀ የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍትን ብሉያትንና ሐዲሳትንም የሚያውቅ የእናቱ ወንድም ስሙ ጴጥሮስ የሚባል ጴጲስቆጶስ ነበረ ሕፃኑንም ወስዶ አስተማረው ከተሰጠውም ጸጋና ዕውቀቱ የተነሣ ያዩት ሁሉ ያደንቁ ነበር ዲቁናም ተሾመ። ❤ ዐሥራ ሁለት ዓመትም በሆነው ጊዜ የምንኵስናን ልብስ ሊለብስ ወደደ ይህንም ኃላፊውን ዓለም ናቀ ኢጴጲስቆጶሱ አባ ጴጥሮስም በገድል ተጸምዶ ለሚኖር ለቀሲስ አባ ጴጥሮስ ሰጠው እርሱም በጥቂት ቀኖች የምንኵስናን ገድል አስተማረው ከእርሱም ብዙ ትሩፋቶች ታዩ። ❤ ከዚህም በኋላ መምህሩ ቀሲስ አባ ጴጥሮስ በአረፈ ጊዜ ከዚያ ተነሥቶ ወደ አባ እንጦንስ ገዳም ሔደ በዚያም በጾምና በጸሎት በስግደት በመትጋት እየተጋደለጨ ያለ ማቋረጥ ብዙ ዘመናት ኖረ። ❤ ከዚህም በኋላ ወደ አስቄጥስ ገዳም ወደ አባ መቃርስ ደብር ሔደ። ደብረ ማርስ ባለች በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን አበምኔት አደረጉት። ሕንፃዋንም አደሰ።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን" ❤ ❤ #ሐምሌ_፲ (10) ቀን። ❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ_ታላቁ_ገዳም #ደብረ_ወገግን_ቅድስት_ሥላሴ_ገዳምን_ለመሰረቱት #ለአባታች
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን" ❤         ❤ #ሐምሌ_፲ (10) ቀን። ❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ_ታላቁ_ገዳም #ደብረ_ወገግን_ቅድስት_ሥላሴ_ገዳምን_ለመሰረቱት #ለአባታች_ለአቡነ_ሳሙኤል_የልደት (ለተወለዱበት)  ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን።                           ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #አቡነ_ሳሙኤል_ዘወገግ፦ "የአባታቸው ስም እንድርያስ የእናታቸው ስም አርሶንያ ይባላል። እነዚህ የበቁ ደጋግ ወላጆቻቸው የተወለዱት በሸዋ ሀገረ ስብከት ቀድሞ ጽላልሽ ዛሬ ቡልጋ በሚባለው አውራጃ ነው። የወላጆቻቸው በጎ ምግባር ተክለ ሃይማኖትን ከደብረ ሊባኖስ አነሣስቶ በቤታቸው ሄደው እንዲስተናገዱ አድርጓል። ❤ ልጅም ስላልነበራቸው ያዝኑ ነበርና አቡነ ተክለ ሃይማኖትም በጸጋ እግዚአብሔር ተገልጾላቸው "እግዚአብሔር ጣዖታትን የሚሰብር፣ አጋንንትን በጸሎቱ የሚያርቅ፣ ሕዝብን ከኃጢአት በሽታ የሚያድን፣ ፈጣሪውን የሚያስደስት ደግ ልጅ ትወልዳላችሁ" ብለው ትንቢት ነግረዋቸውል። ❤ በትንቢቱም መሰረት አቡነ ሳሙኤል ሐምሌ 10 ቀን 1248ዓ.ም ሲወለዱ መልካቸው በአራት ልዩ ልዩ ሕብረ መልክ እየተለዋወጠ አንድ ጊዜ እንደ፡በረዶ፣ አንድ ጊዜ እንደ እሳት፣ አንድ ጊዜ እንደ ልምላሜና ቢጫ ሆነው ታይተዋል። አቡነ ተክለ ሃይማኖትም በአባቱ እድርያስ በኩል የሥጋ ዘመድ ሲሆኑ የመንፈስ ቅዱስም አባት ሆኑትና በ40 ቀን ክርስትና አንስተው ስመ ክረስትናውን "ሳሙኤል" አሉት። ትርጓሜውም "እግዚአብሔር ጸሎቴን ሰማኝ" ማለት ነው። ከሕፃንነትም ጀምረው በምግባር በሃይማኖት ኮትኩተው አሳድገው ለዲቁና አብቅተው በኋላም አመንኵሰውታል..."። ምንጭ፦ ገድለ አቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ።

በዛሬው ዕለት የሰንበት ትምህርት ቤታችን ሰራተኛ አባላት አንዲሁም በተለያየ ምክንያት የራቁትንም ጨምሮ ለቤ/ክ ሕንፃ ማሰሪያ ቃል የተገባውን ገንዘብ በአካልና በስልክ በተደረገ ማሰባሰቢያ መንገድ ባደ
+1
በዛሬው ዕለት የሰንበት ትምህርት ቤታችን ሰራተኛ አባላት አንዲሁም በተለያየ ምክንያት የራቁትንም ጨምሮ   ለቤ/ክ ሕንፃ ማሰሪያ ቃል የተገባውን ገንዘብ በአካልና በስልክ በተደረገ ማሰባሰቢያ መንገድ  ባደረገው መርሐ ግብር መሰረት ከ 55,000 ብር በላይ ገቢ ማድረጉን ለማሳወቅ እንወዳለን። ። ። የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ፅ/ቤት

ሁሉ መጽናኛ ይሆን ዘንድ ወደ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉና ወደ ገዳማትም ላክሁ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛን በአባ ኪሮስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_ሚሳኤል፦ ይህም አባት አባ ኪሮስ የቀበረው የንጉሥ ልጅ ድኃ የነበረ ነው። ዜናውም እንዲህ ነው። አባ ኪሮስ በእግዚአብሔር ትእዛዝ ወደ ሳት ገዳም ሔደ። ከዚያም ደርሶ ቤተ ክርስቲያኒቱን ተሳለማት በዚያም አምላክን የወለደች የእመቤታችን የድንግል ማርያምን ሥዕል አየ። ከዐይኖቹም ዕንባ እያፈሰሰ "እመቤቴ ሆይ አስቢኝ" አላት ሥዕሊቱም "ኪሮስ ሆይ መምጣትህ መልካም ነው ከዚህም አትለፍ የአባትህን ዐፅም ትጠብቅ ዘንድ ወደ ማደሪያህ ተመለስ እንጂ" አለችው። አባ ኪሮስም ይህን ሰምቶ ከሥዕሏ ፊት ሰባት መቶ ሰግደትን ሰገደ። በዕብራይስጥም ቋንቋ "እንግዳ ነህና በቃህ በምሕረት መዝገብም ተመዝግቦልሃል" የሚለውን ቃል ሰማ። ❤ ከዚያም በአለፈ ጊዜ መነኰሳቱ መልኩ የተዋበ ሁለመናውም ያማረ እንደሆነ ተመለከቱ። እርስ በርሳቸውም እንዲህ ተባባሉ "ይህ መነኵሴ ከመንግሥት ከተማ ከግብጽ አገር የመጣ ነው ሰውነቱ በጾምና በጸሎት አልጠወለገምና"። እጅግም ነቀፉት አልተቀበሉትም።ነገር ግን ወደ ሌላ ወደሚንቁት ቦታ ሰደዱት። ❤ በዚያም መስፈርስ በሚባል ሕማም ለብዙ ጊዜ የታመመና በምድር ላይ የተጣለ ድኃ ሰውን አገኘ። በራስጌውም የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልን በግርጌው ቅዱስ ገብርኤልን በቀኙም ቅዱስ ሩፋኤልን በግራውም ቅዱስ ሰዳካኤልን አየ። እነርሱም በክንፋቸው ጋርደውት ነበር ከሰውም ያለርሱ ያያቸው አልነበረም። "በገዳዩች ፊት ሞትን የማይፈራ ጐበዝ እንዴት ነህ" ብለው ሰላምታ ሰጡት። አባ ኪሮስም አደነቀ "በልዕልና ነዋሪዎች ሆይ ከዚህ ለምን ተቀመጣችሁ" አላቸው "ይህንን ድኃ እንድንጠብቀው ከእግዚአብሔር ታዘናል" አሉት አባ ኪሮስም "እስከ መቼ ነው" አላቸው። "ከዚህ ድካም እስከሚአሳርፈው ድረስ ነው" አሉት። ❤ ከዚህም በኋላ ወደ ታመመው ደኃ ተመልሶ "በዚህ ቦታ ከኖርህ ምን ያህል ዘመን ነው" አለው በሽተኛውም "ሠላሳ አምስት ዓመት ነው" አለው ሁለተኛም "ከታመምክ ስንት ዓመት ነው" አለው "ሃያ ዓመት ነው" ብሎ መለሰ። "አበ ምኔቱና የገዳሙ መነኰሳት ይጐበኙሃልን" ብሎ ጠየቀው በሽተኛውም "አባቴ ሆይ የለም አይጐበኙኝም ፊታቸውን ከአየሁ ዓሥራ አምስት ዓመት ይሆናል" ብሎ መለሰ። ❤ አባ ኪሮስም "ና ንገረኝ አባትህ ማነው እናትህስ ማናት" አለው በሽተኛውም እንዲህ ብሎ መለሰ "አባቴ የኬልቄዶን ንጉሥ እናቴም የራሕራሕ ንጉሥ ልጅ ናት። አባቴ ኪሮስ ሆይ እውነት እልሃለሁ በአባቴ ቤት ያሉ ሰዎች ወርቁንና ብሩን ቀጭኑንም ልብስ በእግሮቻቸው ይረግጡአቸዋል"። አባ ኪሮስም "ወደዚች ገዳም ማን አደረሰህ" አለው ድውዩም "እንዳንተ ያሉ ሁለት ሰዎች ወደ አባቴ ቤት መጥተው በዚያ አደሩ። እኩለ ሌሊትም ሲሆን ፊቱ ብሩህ የሆነ ሰውም ወደኔ መጣ "ሚሳኤል ብሎ ጠርቶ ሲነጋ ተነሥተህ ከእነዚህ ቅዱሳን ጋራ ሒድ" አለኝ በእንዲህ ያለ ሥራ ወጥቼ ወደዚህ ቦታ ደረስሁ ምንም በጎ ሥራ ሳልሠራም እንደ እነርሱ ሆንሁ"። ❤ አባ ኪሮስም "እኔ አጽናናሃለሁና ወንድሜ ሆይ ስማ ስሙ በብኑዳ የሚባል አንድ እጅግ ድኃ የሆነ በበረሃ የሚኖር መነኵሴ ነበረ። የበጎ ሥራ ጠላት ሰይጣን ወደርሱ መጥቶ አሳተው እግዚአብሔርም ሥጋውን ለአንበሳና ለሰማይ ወፎች ሰጠ እርሱም በወገን የከበረ ከሮም ንገሥ በታች የሚገዛ የኬፋዝ ንጉሥ ልጅ ነበረ"። ሁለተኛም እነግርሃለሁ "የሮሜ ንጉሥ ልጅ የሆነ አንድ ድኃ ነበረ። እርሱም ከበትር ብቻ በቀር ከአባቱ ቤት ምንም ሳይዝ በቀስታ ወጣ ያንንም ሰው እኔ እጅግ አውቀዋለሁ። ከገዳም ወደ ገዳም ከተራራም ወደ ተራራ ይዞር ነበር ሞቱንም አላስተዋልኩም ሕይወቱንም አላወቅሁም"። ❤ ዳግመኛም "አንድ የንጉሥ ልጅ ድኃ ነበረ። እርሱም በሰንበታት እነጂ በሌላ ቀን ምንም ሳይቀምስ ማቅ ለብሶ በቀንና በሌሊት ለጸሎት ይተጋ ነበር። በእንዲህ ያለ ሥራም ኑሮ አረፈ የብርሃን መላእክትም ነፍሱን ወስደው በመንግሥተ ሰማያት አኖሯት። አሁንም ወንድሜ የምነግርህን ስማ። የፈጣሪህ የእግዚአብሔርን ተግሣጽ አታድንቅ የወደደውን ይገሥጻልና" ያም በሽተኛ ድኃ መነኰስ "እውነት ነው ለእኔ ይገባኛል ስለ ኃጢአቴም ይህን ተቀበልሁ" ብሎ መለሰ። ይህንንም ብሎ ዝም አለ። ❤ በዚያች ሰዓትም ያን በሽተኛ በሞት ያሰናብተው ዘንድ አባ ኪሮስ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ። ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በድንገት መጣ። እልፍ አእላፋት መላእክትም በዙሪያው ሆነው ከእርሱ ጋር ነበሩ ለጻድቃን ሞገሳቸውና ንጉሣቸው የሆነ አምላካችንን እናመስግነው ለችግረኞችም ተስፋ የሆነ አምላካችንን እናመስግነው እያሉ ይዘምሩ ነበር። በዚህ ዓለም በገድል የደከሙ በእርሱ ደስ ይላቸዋል። ❤ አባ ኪሮስም በአየ ጊዜ በምድር ላይ ሰግዶ "ጌታዬ ፈጣሪዬ ሆይ ወደዚህ ምን አመጣህ" አለ ጌታችንም "ስለ ጠራኸኝ መጣሁ" አለው። አባ ኪሮስም "ይህ ሰው ፃዕር በዝቶበታልና ያርፍ ዘንድ አሰናብተው" አለው። ጌታችንም "ምን ያህል እንደምወድህ የመላእክት ሠራዊት ያዩና ያውቁ ዘንድ ይቺን የገነት ተክል አበባ ከእጄ ወስደህ በዚህ በሽተኛ በፊቱ ላይ ጣል" አለው። አባ ኪሮስም ያንን የገነት ተክል አበባ ከጌታችን እጅ ተቀብሎ በበሽተኛው ፊት ላይ አኖረ ያን ጊዜም ነፍሱ ያለ ፃዕር በፍጥነት ወጣች መድኃኒታችንም ተቀብሎ ሳማት ከእርሱም ጋር በብርሃን ሠረገላ ውስጥ አስቀመጣት አውጥቶም በሰማያዊ ክብር አኖራት። ❤ አባ ኪሮስም እያደነቀ አለቀሰ ከዚህም በኋላ ወደ አበምኔቱ ሔዶ "እነሆ ያ ድኃ ስለ አረፈ መቃብር ቆፍረው ይቀበሩት ዘንድ ከመነኰሳቱ እዘዝ" አለው አበ ምኔቱም "ምን ግዴታ አለብኝ" አለው አባ ኪሮስም ትኩር ብሎ ተመለከተውና "ይህ የሰይጣን ሥራ እንጂ የሰው ሥራ አይደለም" አለው። ሰለ አስጨነቀውም ሰባት መነኰሳትን አዘዘለት እነርሱም ማዕጠንታቸውን ይዘው ተነሡ አባ ኪሮስም "የሚአጥኑት አሉና የረከሱ ማዕጠንቶቻችሁን አስወግዱ። በቦታቸውም ተዉአቸው ነገር ግን ቅበሩት" ብሎ አማላቸው። ❤ ያን ጊዜም አራቱ የመላእክት አለቆች ሥጋውን በከርቤና በሚዓ አጠኑ መዓዛውም ያንን በዓት "መላው እነዚህ መነኰሳትም የሚያሸተን ምንድነው ይህመነኰስ ሥራይን ያውቅ ይሆን" ተባባሉ። ከዚህም በኋላ ሥጋውን ወስደው በዚያው ገዳም በእንግዳ መቃብር ቀበሩት ከመቃብሩም ጥሩ ውኃ ፈልቆ ለበሽተኞች ፈውስ ሆነ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛን በአባ ሚሳኤል በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሐምሌ 8 ስንክሳር።                               ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለሚሳኤል ሶበ አዕረፈ እምተጽዕሮ። እደ ኪሮስ ድኅረ ቀበሮ። ለእለ መነንዎ ቅድመ ወኢሐወጹ ማኅደሮ። ያቅልል ለክሙ ይቤሎሙ ለጌጋይክሙ ፆሮ። እስመ በግፍዕክሙ ቦእኩ ለክርስቶስ ሀገሮ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሐምሌ_8።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን" ❤            ❤ #ሐምሌ_፰ (8) ቀን። ❤ እንኳን #ጌታችን_በአረጀ_መነኲሴ አምሳል ለተገለጸላቸ በጀርባቸው ላዘሉት የሚነድ መለኮት በከንፈራቸው ለሳሙ ለአባታችን #ለአቡነ_ኪሮስ ለዓመታዊ ለዕረፍታቸው በዓላቸው፣ አባ ኪሮስ ለቀበረው ለንጉሥ ልጅ ድኃ ለነበረው #ለአባ_ሚሳኤል ለዕረፍት መታሰቢያ በዓልእግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                               ✝ ✝ ✝ ❤ #አቡነ_ኪሮስ፦ ይህም ቅዱስ የታላቁ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ ወንድሙ ነበር በከተማ ውስጥ የሚሠራውን ዐመፅ በአየ ጊዜ ገንዘቡን ሁሉ ትቶ ከሀገሩ ወጣ። ጌታቸንም መርቶ ወደዚች ምዕራባዊት በረሀ አደረሰው በውስጧም ብዙ ዘመናት ብቻውን ኖረ ከሰው ማንም አላየውም በዚህ ሁሉ ዘመን የዱር አራዊትም ቢሆኑ። ❤ በአስቄጥስም ገዳም ስሙ አባ ባውማ የሚባል አንድ ቄስ ነበረ እርሱም የንጉሥ ዘይኑን ልጅ ቅድስት ኢላርያን ሥጋዋን የገነዘ ነው። እርሱም እንዲህ አለ በቤተ ክርስቲያን ወስጥ እያለሁ "አባ ባውማ ሆይ ተነሥ ወደ በረሀው ውስጥ ገብተህ ወደ ፀሐይ መግቢያ ሒድ ከቅዱሳን ሁሉ አብዝቶ ፈቃዴን የፈጸመውን የአንድ ገዳማዊ ሥጋ ትገንዝ ዘንድ የሚለኝን ቃል ከሰማይ ሰማሁ"። ያን ጊዜም ደስ ብሎኝ ተነሣሁ በበረሀውም ውስጥ ሦስት ቀን ተጉዤ ከአንድ ገዳማዊ በዓት ደርሼ ደጁን አንኳኳሁ አንድ ሽማግሌ ገዳማዊም ከፈተልኝና እርስ በርሳችን ሰላምታ ተለዋወጥን "በዚች በረሀ ሌላ ገዳማዊ አለን?" ብዬ ጠየቅሁት "አዎን" አለኝ። ሁለተኛም "ስምህ ማነው አባቴ ሆይ በዚችስ በረሀ ውስጥ ምን ያህል ጊዜ ኖርክ አልሁት" "ስሜ ስምዖን ነው በዚች በረሀ የኖርኩትም ሰባ ዓመታት ነው" አለኝ። ❤ ከእርሱ ዘንድም ወጥቼ ሦስት ቀን ተጓዝኩ ሁለተኛም ስሙ ባሞን የሚባል ገዳማዊ አገኘሁ ሰላምታም ሰጠሁትና "በዚች በረሀ ሌላ ገዳማዊ አለን?" አልሁት "አዎን አለ" አለኝ። አራት ቀንም ተጓዝኩ ወደ አባ ኪሮስ በዓት ደረስኩ "ቅዱስ አባት ሆይ ባርከኝ" እያልኩ ደጁን አንኳኳሁ "አባ ባውማ ሆይ መምጣትህ መልካም ነው" ብሎ ከውስጥ ተናገረኝ። "እግዚአብሔር ያከበረህ ሰው በሰላም በፍቅር ወደእኔ ግባ" አለኝ ያን ጊዜ ገብቼ ከእርሱ ተባረክሁ በፊቱም የእግዚአብሔርን ጸጋ ክብር አየሁ የራሱ ጠጉርና ጽሕሙ እንደ በረድ የነጣ ነበር። ❤ ከዚህም በኋላ ተቀመጥሁ በብብቻውም አቀፈኝ እንዲህም አለኝ "እነሆ ይችን ሰዓት እየጠበቅኋት በዚች በዓት ሃምሳ ሰባት ዓመት ኖርኩ" ይህንንም ሲል ጥቂት ታመመና ተኛ እየደነገጠ ያቺን ሌሊት አደረ ሲነጋም በበዓቱ ውስጥ ታላቅ ብርሃን በራ ብርሃናዊ ሰውም ገባ በእጁም የብርሃን መስቀል አለ በአባ ኪሮስ አጠገብም ተቀምጦ ሳመዉ ባረከውም አጽናናው ሰላምን ፍቅርን አንድነትን አደረገለት ከእርሱም ተሠወረ እኔም ፈራሁ "እንዲህ የሚበራ ይህን ክብር የተጐናጸፈ ይህ ማነው" አልሁት። ❤ እርሱም "ልጄ ሆይ ይህ የእግዚአብሔር ልጅ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ልማዱ ስለ ሆነ ሁልጊዜ ይመጣል ያጽናናኛልም" አለኝ። "በቀዳሚት ሰንበት ዕለትም ዘጠኝ ሰዓት በሆነ ጊዜ እስከ ሰማይ የሚደርስ ታላቅ ጩኸትን ሰማሁ ከጩኸታቸውም ኃይል የተነሣ ምድር ተናወጸች። እኔም "ይህ የምሰማው ጩኸት ምንድነው ብዬ ጠየቅሁት እርሱም ልጄ ሆይ ይህ በሲኦል የሚኖሩ የኃጥአን ጩኸት ነው ስለ ቅድስት ትንሣኤው የእሑድ ፀሐይ እስክትጠልቅ ድረስ እግዚአብሔር ያሳርፋቸዋልና ስለዚህም እግዚአብሔርን ያመሰግኑታል" አለኝ"። በዚችም ዕለት ሐምሌ ሰባት ቀን ቅዱስ አባ ኪሮስ ጩኾ አለቀሰ ዛሬ "በግብጽ አገር ታላቅ ምሰሶ ወደቀ ይኸውም የገዳማውያን አለቃ ቅዱስ አባ ሲኖዳ ነው" አለ። ❤ ከዚህም በኋላ ከደዌው ጽናት የተነሣ እሑድ ሌሊት እጅግ ደነገጠ በበዓቱም ውስጥ እነሆ ታላቅ ብርሃን በራ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ገብቶ በአባ ኪሮስ ራስ አጠገብ ተቀመጠ። አባ ኪሮስም መድኃኒታችንን "ጌታዬ ሆይ ይህን ሰው ባርከው" አለው መድኃኒታችንም "የመረጥሁህ አባ ባውማ ሆይ ጽና አትፍራም ሰላሜ በረከቴም ከአንተ ጋራ ይኑር። አሁንም ታማኝ አገልጋዬ የሆነ የዚህን የቅዱስ ኪሮስን ያየኸውንና የሰማኸውን ወደፊትም ዳግመኛ የምታየውንና የምትሰማውን ገድሉን ጻፍ" አለኝ። ❤ ከዚህም በኋላ መድኃኒታችን አባ ኪሮስን እንዲህ አለው "እነሆ አንተ ትሞታለህና አትዘን ሞትህ ሞት አይደለም የዘላለም ሕይወት ነው እንጂ። የገድልህን መጽሐፍ የሚጽፈውን ወይም የሚያነበውን የሚሰማውንም ሁሉ በምድርም መታሰቢያህን የሚያደርገውን ሁሉ በደብረ ጽዮን በሚደረገው የሽህ ዓመት በዓል ምሳ ከእኔ ጋር ይቀመጥ ዘንድ አደርገዋለሁ ከቅዱሳኖቼም ጋራ እቆጥረዋለሁ። የኃጢአቱንም መጽሐፍ ቀድጄ ስሙን በሕይወት መጽሐፍ እጽፋለሁ። ለመሥዋዕት የሚገባውንም ዕጣኑንና ወይኑን መብራቱንም መባ አድርጎ ለሚሰጥም በስምህም ለድኆችና ለችግረኞች ምጽዋትን ለሚያደርግ ዓይን ያላየውን ጆሮም ያልሰማውን በሰው ልቡናም ያልታሰበውን በጎ ዋጋ እኔ እጥፍ ድርብ አድርጌ እሰጠዋለሁ። በበኵር ቤተ ክርስቲያንም ሥጋዬንና ደሜን አቀብላቸዋለሁ በዚህም ዓለም ቤታቸውን እባርካለሁ። ልጆቻቸውን አሳድጋለሁ ከበጎ ነገር ሁሉ ምንም ምን አያጡም። አሁንም ከዚህ ዓለም ድካም ወደ ዕረፍት የዘላለም ተድላ ደስታ ወዳለበት ወደ ብርሃን ቦታ እወስድህ ዘንድ ጊዜው ደረሰ" መድኃኒታችንም ይህን ሲናገር እነሆ ነቢዩና ዘማሪው ዳዊት መጣ መሰንቆውም ከእርሱ ጋራ ነበረች። "ይቺ ዕለት በእርሷ ፈጽሞ ሐሤት እናደርግ ዘንድ እግዚአብሔር የሠራት ናት" እያለ አመሰገነባት። ❤ መድኃኒታችንም አባ ኪሮስን "እነሆ ዘማሪው ዳዊት መጥቷልና ይዘምርልህ ዘንድ የምትሻውን ንገር" አለው። ዳዊትም ቅዱስ አባ ኪሮስን "በየትኛው አውታር እንድዘምርልህ ትሻለህ ደግሞስ በየትኛው ዜማ በየትኛው ስልት በመጀመሪያው ነውን ወይስ በሁለተኛው ወይስ በሦስተኛው" አለው። ቅዱስ አባ "ኪሮስም በዐሥሩም አውታር በየስልታቸውና በየዜማቸው ልሰማ እሻለሁ" አለ። ያን ጊዜ ዳዊት መሰንቆውን አዘጋጅቶ "የጻድቅ ሞቱ በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው" አለ ዳግመኛም "ጐለመስሁ አረጀሁም የሚወድቅ ጻድቅን አላየሁም" አለ። ዳዊትም ድምፁን አሣምሮ ዘመረ መሰንቆውንም በስልት መታት። ያን ጊዜም የቅዱስ አባ ኪሮስ ነፍሱ ወጣች ኃኒታችንም ተቀብሎ ሳማት ለመላእክት አለቃ ለቅዱስ ሚካኤልም ሰጣት። ❤ እኔ አባ ባውማም የቅዱስ አባ ኪሮስን ሥጋውን ቀበርኩ ከበዓቱም በወጣሁ ጊዜ በረሀው በሰማይ ሠራዊት ተመልቶ አየሁ መድኃኒታችንም የቅዱስ አባ ኪሮስ ሥጋው ባለበት በዓት ላይ መስቀሉን አኑሮ ዘጋት። ከዚህም በኋላ መድኃኒታችን ለኔ ሰላምታ ሰጥቶኝ መላእክትና የመላእክት አለቆች በፊቱ እያመሰገኑና እየዘመሩ በታላቅ ክብር ዐረገ። የቅዱስ አባ ኪሮስን ነፍስ ከመድኃኒታችን ጋራ እንደዚህ አሳረጓት። እርሷም በተሰጣት ክብር ደስ እያላት ዐረገች። ❤ እኔም አባ ባውማ በዚያ ቦታ ብቻዬን ቀረሁ ተመልሼም ወደ አባ አሞን በዓት ደረስሁ። ከዚያም የሦስት ቀን መንገድ ተጉዤ ወደ አባ ስምዖን በዓት ደረስሁ። ከዚያም ሦስት ቀን ተጉዤ ወደ ቦታዬ ወደ አስቄጥስ ገዳም ደረስሁ። ለመነኰሳቱም ሁሉ ያየሁትንና የሰማሁትን ሁሉ የቅዱስ አባ ኪሮስን ገድሉን ስለ አባ ሲኖዳም ዕረፍት ትንቢት እንደ ተናገረ ነገርኋቸው። መነኰሳቱም ሰምተው እጅግ አደነቁ የተመሰገነ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት። እኔ አባ ባውማም የቅዱስ አባ ኪሮስን ገድሉን ጽፌ ለሚያነበውና ለሚሰማው

በብዛት መጻሕፍትን በመጻፍ ቀዳሚ በአጠቃላይ አሥራ አራት መጻሕፍትን ያበረከተ፤ ስለ አይሁድ ህግ ሲል የመንጻት ሥርዓትን የፈጸመ ፤ በገዛ ወገኖቹ ብዙ መከራ የተቀበለ ፤ ለሁለት ዓመታት በቁም እስረኝነት ላይ እያለ ወንጌልን የሰበከ ፤ በኒቆጵልዮን ከተማ ስላስተማረ ለሁለት ዓመት ከስድስት ወር በጨለማ ቤት የታሰረ ፤ በ74 ዓመቱ በ67 ዓ.ም በኦስትያ መንገድ ላይ አንገቱ ተሰይፎ ሐምሌ አምስት ሰማዕትነትን የተቀበለ ፤  ቤተክርስቲያናችን በዘወትር ቅዳሴዋ ለዓለም ሁሉ ብርሃን መሆኑን የምትመሰክርለት ታላቅ ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስ ነው፡፡ በረከቱ በሁላችን ይደርብን፡፡ 🍇ብርሃነ ዓለም አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ🍇 የትውልድ ሀገሩ ግብጽ  አባቱ ስምኦን እናቱ አቅሌሲያ የተባሉ ፤ ወላጆቹ 30 ዓመት በእግዚአብሔር ቤት ደጅ ጠንተው በመጋቢት 29 ቀን በዕለተ ሰንበት በ852 ዓ.ም የተጸነሰና  በታህሳስ 29 ቀን በ853 ዓ.ም የተወለደ ፤ ወላጆቹ ባወጡለት በመጀመሪያ ስሙ ኒኮላዎስ(ኒቆላዎስ) የሚባል ፤ በተለወደ በ3ኛው ቀኑ የእናቱን ጡት ጠብቶ ስብሐት ለአብ፤ ስብሐት ለወልድ፤ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ ብሎ ያመሰገነ ፤ እንደ ሰው ልብስ ያለበሰ ፤ ምግብ ያልበላ ፤  በገዳመ ንሂስ ገብቶ በመመንኮስ በግብጽ 300 ዓመት ወንጌልን እያስተማረ ብርሃንነቱን እየገለጠ የኖረ ፤ ወደ ኢትዮጵያ በታላቁ ጻድቁ በላሊበላ ዘመን የመጣ ፤  የሚያገለግሉት 60 ነብሮችን 60 አንበሶችን 120 እንሰሳት የታዘዙለት ፤ የረገጠው መሬት እንደምግብ ሆኗቸው 120 እንሰሳት የመገበ ፤ ወደ ሸዋ መጥቶ ምድረ ከብድ ከቅዱስ ላሊበላ ጋር የገባ ፤ ምዕራፈ ቅዱሳን በኩረ ገዳማት ዝቋላን የገደመ ፤ በጥቅምት 5 ቀን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአንተ አማላጅነት በእኔ ተማላጅነት ፤ በአንተ ፍጡርነት በእኔ ፈጣሪነት አምኖ፤ ጧፍ ዕጣን መባእ ይዞ በስምህ በታነጸው በእኔ ማደሪያ  ቤተመቅደስ የመጣውን እምርልሃለው አለው፡፡ ብሎ ቃል የገባለት ፤  ከሰይጣን ጋር መቶ ዓመት በባህር ውስጥ ተዘቅዝቆ  እሱ በመብረቅ ሰይጣን በጦር ሲዋጋ የኖረ ፤ ብዙ ተአምራትና ድንቅ ድንቅ ስራ በእግዚአብሔር ቸርነት የሰራ ፤ የሐይማኖት ሐዋርያ ፤ ወንጌልን እና ምናኔን ያስተማሩ ፤ የተባሕትዎ ህይወት የመሩ ፤ ፍጹም መናኝ ፤ በረድሄት ፈጣን በመሆኑ አቡዬ የተባለ ፤ ብዙ ገዳማትን እና መካናትን የባረከ ፤ እቲሳ ጽላልሽን ባርኮ ብዙ ጻድቃን እንደሚወጡ ተንብዩዋል ፤ ከጸሐይ በላይ ከሰማይ በታች ሰባት ዓመት የኖረ ፤ በምድረ ከብድ ሰባት ዓመት እንደ ምሶሶ ቆሞ የጸለየ ፤ ዓይኖቹን ዲያብሎስ በቁራ ተመስሎ ቢያጠፋውም ለሁለት ሳምንት ጸሎቱን የቀጠለ ፤ ቅዱስ ገብርኤል እና ቅዱስ ሚካኤል የብርሃን ዓይን ሰጥተውት ሰባት እጥፍ ያየ ፤ እንደ አብርሃም ሥላሴን በዓይኑ ያየ ፤ ዘመኑ ሲፈጸምም አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር ያደረገ እና ሞት ያልቀመሰ ፤   እንደ ሄኖክ በምድርም ላይ ያልተቀበረ ፡፡ (ዘፍ5፡24) ፤ በ562 ዓመቱ  በ1415 ዓ.ም በመጋቢት 5 ቀን በዕለተ አርብ ነፍሱ የወጣች ፤ 12 መላእክት መጥተው  አጥበው ገንዘው ተሸክመው ወደ ገነት ያስገቡ፡፡ (ማቴ16፡28)       ቅዱሳን የተሰጣቸው አምስቱ ሥልጣኖች ፩. የታመመን መፈወስ(ሐዋ፫:፪-፰) ፪. ሙታንን ማስነሳት (ሐዋ ፱:፵) ፫. ማሰርና መፍታት ፬. አጋንንትን ማውጣት ፭. ለምጽን ማንጻት ከሦስቱ ብርሃናተ ዓለም ከቅዱሳን ምን እንማራለን? ፩. ዘመናችንን ሙሉ ለዓለም ሁሉ ብርሃን መሆንን ፪. ዘመናችንን ሙሉ ያለንፍገት ማገልገልን ፫. ዘመናችንን ሙሉ ዓለምን መናቅ ፬. ዘመናችንን ሙሉ ስለ ስሙ መከራ መቀበል ፭. ዘመናችንን ሙሉ ስለ ሰማያዊ ክብር መኖር የብርሃናተ ዓለም በረከታቸው በሁላችን ይደር ምንጭ፡- ፩. መጽሐፍ ቅዱስ ፪. ገድለ ሐዋርያት ፫. ነቅዐ መጻሕፍት ፬. የእግዚአብሔር መንግስት በምድር ላይ ፩ እና ፪ ፭. የቤተክርስቲያን ታሪክ ቁ.፩ በማህበረ ቅዱሳን ፮. ተአምኆ ቅዱሳን ፯. የስብከተ ወንጌል ምዕላድ ፰. ገድለ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ፱. የመጻሕፍ ቅዱስ ጥናት ቁ.፩ ፲. የቅዱሳን ታሪክ በሊቀ ብርሃናት መርቆሬዎስ አረጋ እና ሌሎችም            ይትባረክ እግዚአብሔር አምላከ አበዊነ

Mule senbt: Sami Zkirkos: በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን "ብርሃናተ ዓለም" (ማቴ፭፡፲፬) ፭. ፲፩. ፳፻፲፫ ዓ.ም በሳሚ ዘቂርቆስ እንኳን ለብርሃናተ ዓለም ለሊቀ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ እና ቅዱስ ጳውሎስ በዓለ እረፍት ፤ ለአቡነ አሮን ፤ ለአቡነ አሞኒ ፤ ለመልአክ ክርስቶስ ፤ ለሰባ ሁለቱ አርድዕት የመመረጣቸው በዓል ፤ ለቅዱስ ይስሐቅ ሰማዕት እና ለአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ ክብረ በዓል በሠላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ የሠው ልጆችን እግዚአብሔር የመጥራቱ ፤ የመምረጡ ፤ የመቀደሱ እና  የመባረኩ የመጨረሻው ዓላማ ለዓለም ሁሉ ብርሃን እንዲሆኑ ለማድረግ ነው፡፡ ስለዚህም በእርኩሰት ጨለማ ፤ በዝሙት  ጨለማ ፤ በዘፈን ጨለማ ፤ በመዳራት ጨለማ ፤ በዘረኝነት ጨለማ ፤ በመስረቅ ጨለማ ፤ በመግደል ጨለማ ፤ በክህደት ጨለማ ፤ በጠማማነት ጨለማ ፤ ባለመታዘዝ ጨለማ ፤ በጣዖት አምልኮ ጨለማ ፤ በምዋርት ጨለማ ፤ በጥል ጨለማ ፤ በምቀኝነት ጨለማ ፤ በቅንዓት ጨለማ ፤ በትዕቢት ጨለማ ፤ በመለያየት ጨለማ ፤ በአድመኝነት ጨለማ ፤ በስካር ጨለማ ፤ በግፍ ጨለማ ፤ በሙስና ጨለማ ፤ በውሸት ጨለማ ፤ በሴራ ጨለማ ፤ በሸፍጥ ጨለማ ፤ በአስመሳይነት ጨለማ ፤ በአድርባይነት ጨላማ ፤ በመጎምጀት ጨለማ እና በመሳሰሉት የኃጢአት ጨለማዎች ለተዋጠችው ዓለም ብርሃን እንሆንላት ዘንድ እርሱ በቅዱስ አጠራር ጠርቷል ፤ አገልጋዮች እንዲሁኑ መርጧል ፤ ምሳሌ እንዲሆኑ ቀድሷል ፤ ለትውልዱ ሁሉ የበረከት ምንጭ እንዲሆኑ ባርኳል፡፡ አዳምና ሔዋንን ብዙ ተባዙ ምድርንም ሙሏት ያለው ዓለም ሁሉ በጽድቅ ፤ በደስታ ፤ በሰላም ፤ በትእግስት ፤ በቸርነት ፤ በበጎነት ፤ በእምነት ፤ በየዋህነት ፤ ራስን በመግዛት ፤ በቅድስና ፤ በንጽህና ፤ በዝማሬ ፤ በመመጽወት ፤ በቅንነት ፤ በመታዘዝ ፤ በእውነተኛ አምልኮ ፤ በትሁት ልቦና ፤ በአንድነት ፤ በመንፈስ ፤ በሕይወት ፤ በመልካም ሥራ ፤ በሥነ ምግባር ፤ በመረዳዳት ብርሃን እንድትበራ ስለፈቀደ እና ስለወደደ ነው፡፡ ይህንን የእግዚአብሔርን የፍቅር ትህዛዝ በእምነት ተቀብለው በሕይወታቸው የተገበሩ ከሰውነት ደረጃ ከፍ ብለው በመልአካዊው ደረጃቸው ቅድስናን ገንዘብ አድርገው የሚኖሩትን ቅዱሳን እንላቸዋለን፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ስለ ብርሃን እና ስለ ጨለማ በሚደንቅ ሁኔታ እኩል እኩል ከመቶ ስድሳ ሰባት ጊዜ በላይ መጻፉ ዓለም የሁለት ጽንፈኞች መኖሪያ አንደሆነች ያመላክታል፡፡ ምክንያቱም የሰው ልጆች በተሰጣቸው ነጻፈቃድ ተጠቅመው የጨለማም ሥራ ፤ የብርሃንም ሥራ ሊሰሩባት ይችላሉ፡፡ በዚህ ሁሉ ግን ቅዱሳን የጨለማውን ዓለም ገዢ ዲያብሎስ ድል በማድረግ ለዓለሙ ሁሉ ብርሃን ሆነው ያላቸውን የምድር ኑሮ በብርሃን ተመላልሰው ፤ ብርሃንን ተጎናጽፈው ፤ የብርሃን አክሊል ተቀዳጅተው በእረፍት በምስጋና ይኖራሉ፡፡ 🍇ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ🍇 በገሊላ ባሕር ዳር በቤተሳይዳ ከነገደ ሮቤል የተወለደ ፤ የዮና ልጅ እና እናቱ ባወጣችለት ስሙ ስምዖን የተባለ ፤ በቅፍርናሆም ከተማ ከወንድሙ ከሐዋርያው እንድርያስ ጋር ዓሣ በማጥመድ ያደገ ፤ በወንድሙ ጥሪ ምክንያት ጌታችን ለወንጌል አገልግሎት በ55 ዓመቱ የመረጠው  ፤ የአርስጦቡሎስን እህት ጴርቴዋን ያገባ ፤ ስለ ክርስቶስ አምላክነት በመመስከሩ ስሙ ጴጥሮስ የተባለለት በላቲን ዐለት እና በአረማይክ ኬፋ የሚል ትርጉም ያለው ፤ በወንጌላውያኑ ስሙ ቀድሞ የተጠራ ፣ የምሥጢር ሐዋርያ ( በኢያኢሮስ ቤት ፣ በደብረ ታቦር እና በጌቴሴማኔ የተገኘ) ፣ የመንግስተ ሰማይ ቁልፍ የተሰጠው ፣ በትንሣኤው ሰሞን የጌታን መነሳት አምኖ ወደ መቃብር የገሰገሰ ፣ ለብቻው ሆኖ ጌታ የተገለጠለት ፣ ስለ ክርስቶስ በመስበኩ እስራትና  እንግልት የደረሰበት ፤ በ44 ዓ.ም በሄሮድስ አግሪጳ ትህዛዝ ታስሮ በእግዚአብሔር መልአክ ረዳትነት የተፈታ ፣ ኢየሩሳሌምን በበላይነት ይጠብቃት ዘንድ ሐዋርያው ያዕቆብን የሾመ ፤ ለነገሮች ፈጣን ፤ የዋህ እና ቁጡ ፤ ጌታን ከአንተ ወደማን እንሄዳለን ብሎ ማመኑን የገለጠ ፤ ዶሮ ሳይጮህ የካደ ፤ በንስሐ ሕይወት የተመላለሰ ፤ ሐዋርያቱን የመገበ ፤ ሕጻናትን ፤ ወጣትን እና ሽማግሌዎችን በአደራ የተቀበለ ፤ በይሁዳ ምትክ ሐዋርያ እንዲመረጥ ያሳሰበ ፤ በአንድ ስብከት ሦስት ሺህ ነፍሳትን የመለሰ ፤ ቆርነሌዎስን ከእነ ሙሉ ቤተሰቡ አስተምሮ አሳምነ ያጠመቀ ፤ በጥላው ድውያንን የፈወሰ ፤ በ50 ዓ.ም በኢየሩሳሌም በነበረው የመጀመሪያ የሐዋርያት ሲኖዶስ ላይ ለቀረበ ጥያቄ መልስ የሰጠ ፤ በተለያዩ ሀገሮች እየተዘዋወረ ለ25 ዓመታት ወንጌልን ያስተማረ ፤ የሮም ክርስቲያኖችን ያበዛ ፤ የኔሮንን ባለሥልጣናት አልቢኖስና የአግሪጳን ሚስቶች የመለሰ ፤የተሰደዱትን ያጽናና ፤ የታሰሩትን ያስፈታ ፤ ለመናፍቃን ጥያቄዎች በመልዕክቶቹ የመለሰ የሁለት መልዕክታት ጸሐፊ፤ በጌታ ትህዛዝ በሐምሌ 5 ቀን 67 ዓ.ም ተመልሶ ወደ ሮም ገብቶ ቁልቁል ተሰቅሎ ለዓለም ብርሃንነቱን ያስመሰከረ ታላቅ ሐዋርያ ነው፡፡ በሞት ጨለማ ፤ በክህደት ጨለማ ፤ በግፍ ጨለማ ፤ በፍርሃት ጨለማ ፤ በለቅሶ ጨለማ ለነበሩት ለሮም ክርስቲያኖች ብርሃን ሆኖ ወደ መንግስተ ሰማያት ብዙኃኑን ያሸጋገረ ሐዋርያ ነው፡፡ ወዳጆቼ ከዚህ በላይ ብርሃንነት ወዴት ይገኛል? ከክርስቶስ በጸጋ ያገኙትን ብርሃን ሲመላለሱበት ከምናያቸው ሐዋርያት መካከል ቅዱስ ጴጥሮስ አንዱ ነው፡፡ በረከቱ በሁላችን ላይ ይደር 🦾 ጽልመተ ዓለም 🦾 በየዘመናቱ ለዓለም ሁሉ ጨለማን አውርሰው የሚሞቱ ብዙ ነገሥታት እና ንግሥታቶች በዓለም ውስጥ ነበሩ፡፡ ከእነዚህም መካከል አንዱ ኔሮን ቄሳር ነው፡፡ በሮም በ54 ዓ.ም የነገሰ ፤ ደግ ሰው የነበረ ፤ ጨካኝነትን መርጦ የአባቱን ልጅ ያስገደለ ፤ እናቱን በመርዝ የገደለ ፤ ሚስቱን አግታሽያንን ያስገደለ ፤ ሁለተኛ ሚስቱን ፓፒያንን በእርግጫ የገደለ ፤ የሮማን ከተማ በእሳት ያቃጠለ ፤ ክርስቲያኖች አቃጠሉ ብሎ በሐሰት ያስወራ ፤ የሮም ሕዝብ በበቀል ክርስቲያኖችን እንዲገድል ያደረገ ፤ ቅዱስ ጳውሎስን በሰይፍ ያሰየፈ ፤ ቅዱስ ጴጥሮስን ቁልቁል እንዲሰቀል ያደረገ ፤ ግፈኛና ሞልቃቃ የነበረ ፤ የሮማ ሕዝብ ያመጸበት ፤ ዘመኑን ሙሉ ሲሸሽ ኖሮ ሰልችቶት አሽከሩን ለምኖ በ68 ዓ.ም በአሽከሩ ሰይፍ የሞተ ለዓለም ጨለማ ጨለማ ሆኖ ሞቶ ኖሮ ሞቶ የሞተ የዓለም ጨለማ ኔሮን ቄሳር ነበረ፡፡ 🍇ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ🍇 የቂልቅያ ዋና ከተማ በሆነችሁ በጠርሴስ ከተማ ከነገደ ብንያም የተወለደ ፤ በእናቱ ዕብራዊ በአባቱ ሮማዊ የሆነ ፤ በ15 ዓመቱ ጀምሮ በኢየሩሳሌም ከገማልያ የአይሁድን ህግና ሥርዓት እስከ 30 ዓመቱ የተማረ ፤ በ30 ዓመቱ የአይሁድ ሸንጎ (ሲናድርሃም) አባል የሆነ ፤ ከቀዳሚ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ ጋር በአይሁድ ሕግ ዙሪያ የተከራከረ ፤ በ32 ዓመቱ ክርስቲያኖችን በጅምላ ለመጨረስ ወደ ደማስቆ የሄደ ፤ ጌታችን በታላቅ ብርሃን ለዓለም ሁሉ ብርሃን እንዲሆን የተገናኘው ፤ ከጌታ ጋር የተነጋገረ ፤ ለጌታ ቃል የተገዛ ፤ ለሦስት ቀናት የጾመ ፤ የጌታን ስም ይሸከም ዘንድ የተመረጠ ፤ በሐናንያ እጅ የተጠመቀ ፤ የሐዋርያው በርናባስ የተምሳሌት ርዕሱ ፤ በተወለደባት በጠርሴስ ከተማ ለዘጠኝ ዓመታት ያስተማረ ፤ በአይሁድ እና በአሕዛብ መካከል የነበረውን ልዩነት በክርስትና አንድ ያደረገ ፤ ልዩ ልዩ ሀገራት በእግር እየተዘዋወረ ከሐዋርያው በርናባስ ጋር  ያገለገለ ፤ ብዙ ደቀ መዛሙርትን ያፈራ ፤ በአዲስ ኪዳን

❤ ከዚህም በኋላ እልዋሪቆን ወደ ምትባል ታላቅ አገር እስከሚደርስ በብዙ አገሮች ውስጥ ተመላለሰ በዚያም የብርሃን እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተገልጻለት አረጋጋችው ረዳችውም በመጋቢት ሃያ ዘጠኝ እንደጻፍነው የአገሩን ሰዎች እንዲያጠምቃቸውና እንዲያስተምራቸው አዘዘችው። ❤ ከዚህም በኋላ ወደ ሮሜ ከተማ ገብቶ በውስጧ ሰበከ በስብከቱም ብዙዎች ሰዎች አምነው የክርስትናን ጥምቀትን አጠመቃቸው። በመጻፍትነት የታወቁ ዐሥራ አራት መልክቶችን ጻፈ የመጀመሪያ መልክቱም ለሮሜ የተጻፈችው ናት። ❤ መልካም ሩጫውን ከፈጸመ በኋላ ንጉሥ ኔሮን ይዞ ጽኑ ሥቃይ አሰቃየው። ራሱንም በሠይፍ እንዲቆርጡት ለሠያፊ ሰጠው ከሠያፊውም ጋር አልፎ ሲሆድ ከንጉሥ ኔሮን ዘመዶች ወገን የሆች አንዲት ብቴና አገኘችው እርሷም ክብር ይግባውና በጌታችን ያመነች ነበረች ስለእርሱ አለቀሰች። እርሱ ግን "መጎናጸፍያሽ ስጭኝ እኔም ዛሬ እመልስልሻለሁ" አላት። እርሷም መጎናጸፍያዋን ሰጠችውና ራስ ወደሚቆርጡበት ቦታ ሔደ። ለሠያፊው ራሱ በዘነገበለለት ጊዜ በመጎናጸፍያዋ ፍቱን ሸፈነ ሠያፊው የቅዱስ ጳዌሎስ ራስ ሐምሌ 5 ቀን ቆርጦ በዚያች ብላቴና መጎናጸፍያ እንደተሸፈነ ጣለው። ❤ ሠያፊው ጳውሎስን እንደገደለው ለንጉሥ ሊነግረው በተመለሰ ጊዜ ያቺ ብላቴና አገኘችው "ያ ቅዱስ ጳውሎስ ወደ አለ" አለችው። ራስ በሚቆርጥበት ቦታ ወድቋል ራሱም በመጎናጸፍያሽ ተሸፍኗል" አላት። እርሷም እንዲህ ብላ መለሰችለት "ዋሽተሃል እነሆ ጴጥሮስና ጳውሎስ በእኔ ዘንድ አልፈው ሔዱ እነርሱም የመንግሥት ልስን ለብሰዋል በራሳቸውም ላይ በእንቊ የተጌጡ አይንን የሚበዘብዙ አክሊላትን አድርገዋል። መጎናጸፍያየም ሰጡኝ። እርሷም እነኋት ተመልከታት" ብላ ለዛያ ሠያፊ አሳየችው። ከእርሱ ጋር ለነበሩትም አሳየቻቸው። አይተውም አደነቁ ስለዚህም ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ። ❤ ለዚህም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ተአምራቶች ቁጥር የሌላቸው እጅግ የበዙ ናቸው። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛን በቅዱስ ጳውሎስ በጸሎት ይማረን በረከቱም ከርእሰ ሊቃ ጳጳሳት ከአባ መርቆሬዎና ከአባ ማትያስ ከሁሉ ሊቃነ ጳጳሳት እና የቅድስት የሐዋርያት ቤተ ክርስቲያ ልጆች ጋር ይኑር ለዘለላሙ አሜን። ምንጭ፦ የሐምሌ 5 ሰንክሳር።                                                            ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለከ_ጴጥሮስ_ተልሚድ። ዘኢያቅበጽከ ተስፋ ነገረ ኑፋቄ ወካህድ፡፡ እንዘ ትረውጽ ጥቡዕ ለመልእክተ ክርስቶስ ወልደ። አመ ለሊከ ወሬዛ ቀነትከ በእድ። ወአመ ልህቀ አቅነተከ ባዕድ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሐምሌ_5።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ውስተ ኵሉ ምድር ወፅአ ነገሮሙ። ወእስከ አጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ። ወውስተ ፀሓይ ሤመ ጽላሎቶ"። መዝ 18፥4-5። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 15፥1-17።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ወበኀቤየሰ ፈድፋደ ክቡራን አዕርክቲከ እግዚኦ። ወፈድፋደ ፀንዑ እምቀደምቶሙ። እኌልቆሙ እምኆፃ ይበዝኁ"። መዝ 138፥17-18። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ተሰ 1፥4፥-13-ፍ.ም፣ 2ኛ ጴጥ 1፥1-12 እና የሐዋ ሥራ 23፥10-16። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 21፥15-20። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱሳን ሐዋርያት ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱሳን የጴጥሮሰና የጳውሎስ የዕረፍት በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ ሳውልም ከምድር ተነሣ ዐይኖቹንም ተገልጠው ሳሉ አያይም ነበር እየመሩም ወደ ደማስቆ አስገቡት በዚያም ሳያይ ሳይበላና ሳይጠጣ ሦስት ቀን ሰነበተ። በዚያም በደማስቆ ከደቀ መዛሙርት ወገን ሐናንያ የሚባል አንድ ሰው ነበረ ጌታም በራዕይ ተገለጠለትና ሐናንያ ብሎ ጠራው እርሱም "አቤቱ ጌታዬ እነሆኝ" አለ። ጌታም "ተነሥና ቀጥተኛ ወደምትባለው መንገድ ሒድ በይሁዳ ቤትም ጠርሴስ ከሚባል አገር የመጣ ሳውል የሚባል ሰው ፈልግ እርሱ አሁን ይጸልያልና" አለው። ❤ ሐናንያ ግን መልሶ እንዲህ አለ "አቤቱ ስለዚያ ሰው በኢየሩሳሌም በቅዱሳኖችህ ላይ የሚደርገውን ክፉ ነገር ሁሉ ከብዙ ሰዎች ሰምቻለሁ ወደዚህም ከካህናቱ አለቃ አስፈቅዶ የመጣ ስምህን የሚጠሩትን ሁሉ ሊአሥር ነው"። ጌታችንም "ተነሥና ሒድ በአሕዛብና በነገሥታት በእስራኤልም ልጆች ፊት ስሜን ይሸከም ዘንድ ለእኔ የተመረጠ ዕቃ አድርጌዋለሁና። እኔም ስለ ስሜ መከራ ይቀበል ዘንድ እንዳለው አሳየዋለሁ"። ❤ ያን ጊዜም ሐናንያ ሔደ ወደ ቤትም ገባ "ወንድሜ ሳውል በመንገድ ስትመጣ የታየህ ጌታችን ኢየሱስ ታይ ዘንድ የመንፈስ ቅዱስም ጸጋ ይሞላብህ ዘንድ ወደ አንተ ልኮኛል" አለው። ያን ጊዜም የሸረሪት ድር የመሰለ ከዐይኖቹም ተገለጡ። ወዲያውም አየ ተነሥቶም ተጠመቀ እህልም በልቶ በረታ። ከደቀ መዛሙርትም ጋር በደማስቆ ጥቂት ቀን ሰነበተ። በዚያው ጊዜ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ብሎ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ሰበከ አስተማረም። የሰሙትም ሁሉ አደነቁ እንዲህም አሉ "በኢየሩሳሌም ይህም ስም የሚጠሩትን ሁሉ ያሳድድ የነበረ ይህ አልነበረምን ወደዚህስ የመጣው እያሠረ ወደ ሊቀ ካህናቱ ሊወስዳቸው አይደለምን"። ❤ አጽናኝ መንፈስ ቅዱስም አደረበት እውነተኛንም ሃይማኖት ግልጽ አድርጎ አስተማረ። ለኦሪት ሕግ የሚቀና እንደ ነበረ እንዲሁ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሠራት ሕግ ወንጌል ዕጽፍ ድርብ ቅንዓትን የሚቀና ሆነ። ከዚህም በኋላ በአገሮች ሁሉ ዞሮ ሰበከ በጌታችንም ስም ሰበከ። ድንቆችንና ተአምራትንም አደረገ። ቁጥር የሌላቸው ብዙዎች አሕዛብንም አሳመናቸው ነገር ግን ብዙ ጊዜ በመገረፍ በመደብደብና በመታሠር ብዙ መከራ ደረሰበት መከራውንም ሁሉ ታግሶ በሁሉ ቦታ አስተማረ። ❤ በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ እንደተጻፈ የእግዚአብሔርን ሥራ ሲሠሩ ሲጾሙና ሲጸልዩ መንፈስ ቅዱስ "እኔ እነርሱን ለመረጥሁለት ሥራ ሳውልና በርናባስ ለዩልኝ" አላቸው። ከዚህም በኋላ ጾመውና ጸልየው እጃቸውንም በራሳቸው ላይ ጭነው ሾሙአቸው ከመንፈስ ቅዱስም ተሹመው ወደ ሴሌውቅያ ወረዱ። ❤ በደሴቱም ሁሉ ሲዘዋወሩ ጳፋ ወደ ምትባል አገር ደረሱ። በዚያም ሐሰተኛ ነቢይ የሆነ ስሙ በርያሱስ የሚባል አንድ ሥራየኛ አይሁዳዊ ሰው አገኙ እርሱም ሰርግዮስ ጳውሎስ ከሚባል ብልህ ሰው ከሆነ አገረ ገዥ ዘንድ የነበረ ነው። የእግዚአብሔርን ቃል ሊሰማ ወዶ በርናባስንና ሳውልን ጠራቸው። የስሙ ትርጓሜ እንዲህ ነበርና ኤልማስ የሚሉት ያ ሥራየኛ ሰው ይከራከራቸው ነበር ገዥውንም ማመንን ሊከለክለው ወዶ ነበር። ❤ ጳውሎስ በተባለው ሳውል ላይም መንፈስ ቅዱስ መላበት። አተኵሮም ተመለከተው "ኃጢአትንና ክፋትን ሁሉ የተመላህ የሰይጣን ልጅ የጽድቅ ሁሉ ጠላት ሆይ የቀናውን የእግዚአብሔርን መንገድ እያመጣመምኽ ተው ብትባል እምቢ አልኽ እነሆ አሁን የእግዚአብሔር እጅ በአንተ ላይ ተቃጥታለች ትታወራለህ እስከ እድሜ ልክህም ፀሐይን አታይም" አለው። ወዲያውኑም ታወረ ጨለማም ዋጠው የሚመራውንም ፈለገ አገረ ገዥውም የሆነውን አይቶ ደነገጠ በጌታችንም አመነ። ❤ ከዚህ በኋላ ሒደው ወደ ሊቆኦንያ ከዚያም ወደ ልስጥራንና ደርቤን ከተማ ወደ አውራጃውም ሁሉ ገብተው አስተማሩ። በልስጥራን ከተማም ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ እግሩ ልምሾ የሆነ አንድ ሰው ነበረ ተቀምጦ ይኖር ነበረ እንጂ ልምሾ ከሆነ ጀምሮ ቁሞ አልሔደም። ቅዱስ ጳውሎስንም ሲያስተምር አደመጠው ጳውሎስ ተመልክቶ ሃይማኖት እንዳለው እንደሚድንም ተረዳ። ድምፁንም ከፍ አድርጎ "በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተነሥና ቀጥ ብለህ ቁም እልሀለሁ" አለው ወዲያውኑ ተነሥቶ ሔደ። አሕዛብም ቅዱስ ጳውሎስ ያደረውን አይተው በጌታች አመኑ...። ❤ ከዚህም በኋላ ከሐዋርያ ፊሊጶስ ጋር ወደ ሁለት አገሮች በአንድነት ሔዱ ከዚያም በጌታችን ስም ሰበኩ የአገሩም አለቆች ያዟቸው እጆቻቸውንና እግሮቻቸው አሰሯቸው በአንገቶቻቸውም የብረት ሰንሰለቶችን አስገቡ እራሳቸውንም የሸፋን የብር ቆብን ሰሉላቸው ዳግመኛም በእጅና በሐል እጅ በጣቶችም ምሳሌ ሰሩ በእጆቻቸውና በክንዶቻቸው እያንዳንዱን የብረት እጅ ጨመሩ። ከብረቶችም ጋር ቸነከሯቸው። ❤ ሁለተኛም እስከ አንገት የሚደርስ በትከሻ አምሳል ሰሩ በፊትና በኋላም ቸነከሯቸው ደግሞም መላ አካላቸውን የሚከብና ከአካላቸው ምንም እንዳይታይ የሚሸፍን የብረት ሰሌዳ ሰሩ ከወገቦቻቸው ጋራ ቸነከሯቸው ችንካሮችም ተረከዛቸውን ነድለው ወደ ጭኖቻቸው እስከሚደርሱና እስከሚያቆስሏቸው ድረስ የብረት ጫማ ሰርተው እግሮቻቸውን ቸነከሩ። ደግሞ በመሸፈኛ አምሳል የብረት ሰናፊል ሠሩ ቀማሚዎችም መጡ አንድ መክሊት የሚመዝን እርሳስንም አመጡ ታላቅ የብረት ጋንንም ሰባት ልጥር የሰሊጥ ቅባት አመጡ። ስቡንና አደሮ ማሩን የእሳቱን ኃይል አብዝቶ የሚያነደውን ቅመሙን ከሙጫውና ከድኙ ጋር ቀላቀሉት ከዋርካና ከቁልቋል ከቅንጭብም ደም ሰባት ልጥር አንድ ወይን ሐረግንና ቅባት ያለቸውን እንጨቶች ሁሉ አመጡ። ❤ በጋን ውስጥ ያበሰሉትንና ያሟሙትን ልዩ ልዩ ቅመምን አምጥተው ከሥጋቸው እስሚጣበቅ በቅዱሳን ሐዋርያት ሥጋ ላይ ባሉት ሠሌዳዎች ውስጥ ጨመሩት። ከእግራቸው እስከ ራሳቸው ከፍ ከፍ እስከሚል ድረስ በእሳት ያቀለጡትን ያንን እርሳስ ጨመሩት። ርዝመቱ ዐሥራ አምስት ክንድ በሆነ ወፍራም የጥድ ምሰሶ ላይም አቆማቸውና ከበታቻቸው ፍሬ በሌለው በወይን ሐረግና በተልባ እሳቱን አቀጣጥለው አነደዱ። የእሳቱም ነበልባልም ከሥጋቸው በላይ ከፍ ከፍ አለ ሐዋርያትን ግን ወደ እግዚአብሔር ይጸልዩ ነበር። ❤ ከመኳንቱም በአንዱ ልብ ርኅራኄ አሳደረና እንዲፈቷቸው አዝዞ ፈቷቸው። በፈቷቸውና ሠሌዳው ከሥጋቸው ላይ ባስወገዱ ጊዜ ቆዳቸው ተገፈፈና ከብረቱ ሠሌዳዎች ጋር ወጣ። ብዙ ደምም ከሥጋቸው ፈሰሰ። ❤ ሰይጣንም በከተማው ሰዎች ልብ አደረና ሐዋርያትን ወደ እሳት ውስጥ መለሷቸው ያን ጊዜ ጌታች ወርዶ የእሳቱ ነበልባል አጠፋው። ዝናብን የተሞላች ብርሕት ደመና መጥታ ቅዱሳን ሐዋርያት ከበበቻቸው በዚያም አገር አንድ ጊዜ በደንጊያ በመወገር አንድ ጊዜም በፍላጻ በመንደፍ ብዙ ተሰቃዩ። ❤ ከዚህም በኋላ ሙታንን በአነሱ ጊዜ የከተማው ሰዎች ሁሉ አመኑ አጠመቋቸው። ቤተ ክርስቲያንንም ሠሩላቸው ካህናትንም ሾሙላቸው በቀናች ሃይማኖት እስኪጸኑ አስተማሯቸው። ከዚያም ወጥተው ጌታችን ወደ አዘዛቸው ወደ ሌላ አገር ሔዱ። ❤ ክብር ይግባውና ጌታች ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱስ ጳውሎስ ተገለጠለትና "የመረጥኩህ ጳውሎስ ሆይ ስላም ላንተ ይሁን። መታሰቢያህን የሚደርገውን፣ በስምህ ቤተ ክርስቲያን የሚሰራውንና የሚጸልየውን፣ ስለትንና መባንም የሚሰጠውን፣ በመታሰቢያህም ቀን ለድኆች የሚመጸውተውን ሁሉ ከአንተ ጋር በመንግሥተ ሰማያት አኖራቸዋለሁ" አለው። "በስምህ የታነጹትም አብያተ ቤተ ክርስቲያናት መላእክቶቼን እንዲጠብቋቸው አደርጋቸዋለሁ" ቡዙ ቃል ኪዳንም ሰጠው። በመለኮታዊ አፉ አፉን ሳመውና ከእርሱ ዘንድ ወደ ሰማያት በክብ ዐረገ።

❤ ከዚህም በኋላ ቅዱስ ጴጥሮስ ከቅዱ ዮሐንስ ጋር ጌታችን እንደአዘዛቸው ወደ አንጾኪያ ከተማ ገቡ የአገሪቱንም ሁኔታ ይጠይቅ ዘንድ ቅዱስ ጴጥሮስ ቅዱስ ዮሐንስን ላከው ሰዎችንም አግኝቶ ክፉ ነገርን ተናገሩት። ሊገድሉትም ፈለጉ እያለቀሰም ተመለሰ ሰውነቱም ተበሳጨች ጴጥሮስንም አለው "አባቴ ሆይ የእሊህ ጎስቋሎች ክፍታቸው እንዲህ ከሆነ ወደ ነገሥታቱና ወደ መኳንንቱ ገብተን በጌታችን ስም በሰበክን ጊዜ ምን እንሆ ይሆን እንዴትስ ሃይማኖትን እናስተምራለን"። ቅዱስ ጴጥሮስም "ወዳጄ ሆይ የሃያውን ቀን መንገድ በአንዲት ሌሊት ያመጣን እርሱ ሥራችንን መልካም ያደርግልናል አትፍራ አትዘን" አለው። ❤ ከዚህም በኋላ ወደ ከተማ መካከል ክብር ይግባውና በጌታችን ስም ሰበኩ የከተማውም ሰዎችና የጣዖታቱ አገልጋዮችም በእነርሱ ላይ ተሰበሰቡ ታላቅ ድብደባንም ደበደቧቸው አጎሳቋሏቸውም ግማሽ የእራስ ጠጉራቸውን ላጭተው ተዘባበቱባቸው አሥረውም በግንብ ውስጥ ጣሏቸው። ❤ ከዚህም በኋላ ተነሥተው ይረዳቸው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸለዩ ወደያውን ክብር ይግባውና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ኪሩቤልና ሱራፊል እያጀቡት ተገለጠላቸውና እንዲህ አላቸው "የመረጥኳችሁ ጴጥሮስና ዮሐንስ ሆይ በዘመኑ ሁሉ እኔ ከእናንተ ጋር እኖራለሁና አትፍሩ አትዘኑም"። ለመዘባባቻም በራሷችሁ መኳካከል ስለላጩአችሁ አታድንቁ ይህም መመኪያና ክብርን የክህነት ሥርአትና ምልክትንም ይሆናችኋል ካህን የሚሆን ሁሉ ያለዝህ ምክንያት ሥጋዬንና ደሜን ማቀበል አልችልም። ይህ መልእክት እያለው የሚሞት ካህምን ኃጢያቱም ይሰረይለታል" ይህን ካላቸው በኋላ ከእርሳቸው ዘንድ በክብር ዐረገ። ❤ ከዚህም በኋላ ቅዱስ ጳውሎስ ወጥቶ ቅዱስ ዮሐንስን ተገናኘው "የዚህ አገር ሰዎች ያደረጉብህ ምንድን ነው" አለው እርሱም "ስለ እኔ አታድንቅ የሐዋርያትን አለቃ በእኔ ላይ ባደረጉት አምሳል አድርገውበታልና" አለው። ቅዱስ ጳውሎስ አጽናናቸው እንዲህ አላቸው "እኔ በጌታችን ፍቃድ ወደ ከተማው ውስጥ ገብቼ እናንተንም አስገባቸዋለሁ"። ❤ ከዚህም በኋላ ቅዱስ ጳውሎስ ሒዶ ምክንያትን ፈጠረ ጣዖታቸውንም እንደሚያመልክ መስሎ ሐዋርያትን እንዲያቀርቡለትና ስለ ሥራቸውም እንዲይቃቸው የከተማውን መኳንን አነጋገራቸው። መኳንንቱም ወደ ቅዱስ ጳውሎስ እንዲያቀርቧቸው አዘዙ በቀረቡም ጊዜ ቅዱስ ጳውሎስ ስለሥራቸው ጠየቃቸው። እነርሱም "ድንቆችንና ተአምራቶችን የሚያደርግ ለክርስቶስ ወደ መዛሙርቶቹ እንደሆኑ ነገሩት። ዳግመኛም "እናንተ እንደርሱ ማድረግ ትችላላችሁ" አለቸው እነርሱም "አዋ በእርሱ ስም ሁሉን ሥራ መሥራት እንችላለን" አሉት። ❤ ከዚህም በኋላ ከእናቱ ማኅፀን እውር ሁኖ የተወለደውን አይኑን አበሩ። የንጉሡንም ልጅ ከሞተ በሦስት ወሩ ሥጋውን ከተባላሸ በኋላ ከመቃብር አሥነሱት። ንጉሡና የከተማ ሠዎች ሁሉ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ ጴጥሮስም ምድሩን ረግጦ ውሃን አፈለቀ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቋቸው በቀናች ሃይማኖትም እንዲጸኑ አደረጓቸው። ❤ ከዚህም በኋላ በሎዶቅያ ያሉ ምእመናን የቂሳሮስ ባሕር ከወሰኑ አልፎ ቡዙ ሰዎችን ከአትክልት ቦታዎቻቸውና ከከቡቶቻቸው እንዳሰጠማቸው ወደ ቅዱስ ጴጥሮስ ላኩ ጴጥሮስም ተወዳጅ ቅዱስ ዮሐንስን ወደ እነርሱ ላከ ዮሐንስም ወደ እነርሱም ሲጓዝ በጎዳና በግ አገኘ በጉንም እንዲህ ብሎ ላከው "ወደ ቂሳሮስም ወንዝ ሒደ የክርስቶስ ደቀ መዝሙር ወደ አንተ ልኮኛል ወደ ቀድሞው ወሰንህ ተመልሰህ ትገባ ዘንድ አንተ በእግዚአብሔር ቃል የታሰርክ ነህ ብሎሀል በለው"። ያን ጊዜ በጉ ሒዶ እንደአዘዘው አደረገ ወንዙም ሸሽቶ ወደ ቦታው ተመለሰ ቁጥር የሌላቸው ቡዙዎች የከተማ ሰዎችም ይህን አይተው በጌታ አመኑ። ❤ ከዚህም በኋላ ቅዱስ ጴጥሮስ አልፎ ወደ ሮሜ ከተማ ገባ በዚያም ሥራ መሠሪው ሲሞን ተቃወመው እርሱንም ከአየር አውርዶ ጥሎ አጠፍው ይህንንም ድንቅ ሥራ አይተው ብዙዎች ሕዝቦች አመኑ። የከተማው ገዢ የአክሮጶስ ቊባቶችም የቅዱስ ጴጥሮስን ትምህርት ተቀበሉ ሌሎችም የከበሩ ቡዙዎች ሴቶች ትምህርቱን በመቀበል ከባሎቻቸው እርቀው ንጽሕናቸውን ጠበቁ። ስለዚህም ነገር ቅዱስ ጴጥሮስ ሊገድሉት የሮሜ መኳንንት ተማከሩ። የአልታብዮስ ሚስትም እንዳይገሉት ከሮሜ ከተማ ወጥቶ እንዲሆድ ወደ ቅዱ ጴጥሮስ ላከች ምእመናን ወንድሞችም ውጣ አሉት እርሱም ቃላቸውን ተቀበለ ትጥቁንም ለውጦ ከከተማ ወጣ። በሚወጣበትም ጊዜ መስቀል ተሸክሞ ወደ ከተማ ሲገባ ጌታችንን አገኘውና "አቤቱ ጌታዬ ወዲት ትሆዳለህ" አለው ጌታዬም "ልሰቀል ወደ ሮሜ ከተማ እህሔዳለሁ" ብሎ መለሰለት። ቅዱስ ጴጥሮስ "አቤቱ ዳግመኛ ትሰቀላለህን?" አለው። ❤ ያን ጊዜም "ጎልማሳ ሳለህ ወገብህ በገዛ እጅህ ታጥቀህ ወደ ወደድከው ትሔዳለህ በሸመገልክ ጊዜ ግን እጅህን ታነሳና ሌላ ያስታጥቅሃል ወደ ማትወደው ይወስድሃል" ያለውን የጌታችንን ቃል አሰበ አስተዋለውም። ያን ጊዜም ወደ ከተማው ተመልሶ ክብር ይግባውና ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ የሆነውን ለወንድሞች ነገራቸው እነርሱም እጅ አዘኑ። ❤ ንጉሥ ኔሮንም ቅዱስ ጴጥሮስን እንዲሰቅሉት አዘዘ ሊሰቅሉት በያዙት ጊዜ ወታደሮችን እንዲህ ብሎ ለመናቸው "የክብር ንጉሥ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ላይ ሁኖ ስለተሰቀለ እኔ ቊልቊል ልሰቀል ይገባኛል"። ወዲያውንም እንደነገራቸውም ሰቀሉት። ተሰቅሎም ሳለ ለምእመናን የሕይወትን ቃል አስተማራቸው በቀናች ሃይማኖትም እንዲጸኑ አዘዛቸው ከዚህም በኋላ ሐምሌ 5 ቀን ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባታች በሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ጸሎት ይማረ በረከቱም ከእኛ ጋራ ይኑር ለዘለላለሙ አሜን።                               ✝ ✝ ✝ ❤ #ሐዋርያው_ቅዱስ_ጳውሎስ፦ ይህም ቅዱስ በተለያዩ ስሞች ይጠራ ይኸውም ልሳነ ዕረፍት፣ የክርስቶስ አንደበት፤ የዕውቀት አዘቅት፤ የቤተ ክርስቲያን መብራት፤ እንደ ስሙም ትርጓሜ መሪ አመስጋኝ ወደብ ጸጥታ ነው። ❤ ይህም ጳውሎስ አስቀድሞ በክርስቶስ ያመኑትን የሚያሳድድ ነበር፤ እርሱም ከብንያም ወገን የፈሳሪሳዊ ልጅ ነው። ወላጆቹም ሳውል ብለው ስም አወጡለት ትርጓሜውም ስጦታ ማለት ነው። ቁመቱ ቀጥ ያለ መልኩ ያማረ ፊቱ ብሩህ ቅላቱ እንደ ሮማን ቅርፍት ደበብ ያለ ዐይኑም የተኳለ የሚመስል አፍንጫው ቀጥ ያለ ሸንጎበታም ጉንጩ እንደ ጽጌ ረዳ ነበር። ❤ እርሱም ሕገ ኦሪትን አዋቂ ነበረ። ለሕጉም ቀናተኛ ሆኖ ምእመናን አሳዳጅ ነበረ። ወደ ሊቀ ካህናቱም ሔዶ መንገድ የሚያገኘው ሰው ቢኖር ወንዶችንና ሴቶችን እንደ ታሠሩ ወደ ኢየሩሳሌም ይመልሳቸው ዘንድ ለደማስቆ ከተማና ለምኵራቦች የፈቃድ ደብዳቤ ለመነ። ሲሔድም ወደ ደማስቆ ከተማ አቅራቢያ በደረሰ ጊዜ ድንገት ከሰማ መብረቅ ብልጭ አለበት በምድር ላይም ወደቀ ወዲያውም "ሳውል ሳውል ለምን" ታሳድደኛለህ የሚለውን ቃል ሰማ። ❤ ሳውልም "አቤቱ አንተ ማነህ" አለው "አንተ የምሳድደኝ የናዝሬቱ ኢየሱስ ነኝ በሾለው ብረት ላይ ብትረግጥ አንተን ይጎዳሃል" አለው። እየተንቀጠቀጠም አደነቀ "አቤቱ ምን እንዳደርግ ትሻለህ" አለው ጌታም "ተነሥና ወደ ከተማ ግባ ልታደርግ የሚገባህን ከዚያ ይነግሩሃል" አለው። ከርሱ ጋራ ቁመው የነበሩ ሰዎችም ንግግሩን ይሰሙ ነበር ነገር ግን የሚያዩት አልነበረም።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን" ❤               ❤ #ሐምሌ ፭ (5) ቀን። ❤ እንኳን #ለብርሃናተ_ዓለም_ለቅዱስ_ጴጥሮስ፣ #ቅዱስ_ጳውሎስ_በጫካኙ ንጉሥ በኔሮን ቄሳር እጅ ሰማትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው መታሰቢያ ዓመታዊ በዓል፣ #ለመላእክት_አለቃ_ለቅዱስ_ሳቁኤል_ለበዓሉ መታሰቢያ፣ #ለሰባ_ሁለቱ_አርድእት_ለመታሰቢያቸው_በዓላቸው፣ #ለአባታችን_ለአቡነ_ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ_ዓመታዊ የመታሰቢያ በዓላቸውና ለሐዋርያት (ለሰኔ) ፆም ፍቺ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ፡በዚች ከሚታሰቡ፦ በጋዛ ሰማዕት ከሆነ #ከይስሐቅና_ከደብረ_ዓሣ_ጻድቃንም ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የሐዋርያት_አለቃ_ቅዱስ_ጴጥሮስ፦ ይህም ጴጥሮስ ከቤተ ሳይዳ የነበረ ዓሣ አጥማጅም ነበረ ጌታችንም ከተጠመቀባት ዕለት ማግስት አግኝቶ መረጠው ከእርሱ አስቀድሞም ወንድሙ እንድርያስን አግኝቶ መረጠው። መድኀኒታችንንም እስከ መከራው ጊዜ ሲያገለግለው ኖሩ ፍጹም ሃይማኖት ለጌታውም ቅንዓትና ፍቅር ነበረው። ስለዚህም በሐዋርያት ሁሉ ላይ አለቃ አድርጎ ሾመው። ❤ ጌታችን ም ሰዎች ማን እንደሆነ ማንም እንደሚሉት ስለ ራሱ በጠየቃቸው ጊዜ ሌሎች "ኤርምያስ ይሉሃል ወይም ኤልያስ ወይም ከነቢያት አንዱ ነው ይሉሃል" አሉት። ቅዱስ ጴጥሮስ ግን "የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ አንተ ነህ" አለ። ጌታችንም "የሃይማኖት አለት የቤተ ክርስቲያንም መሠረት ነህ" ብሎ ብፅዕና ሰጠው "የመንግሥተ ሰማያትንም መክፈቻ ቁልፍ ሰጥቼሃለሁ" አለው። ❤ አጽናኝ የሆነ የመንፈስ ቅዱስንም ጸጋ ከተበቀለ በኋላ ተናገሪዎች ከሆኑ በዚህ ዓለም ተኲላዎች መካከል ገባ በውስጣቸውም ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ሰበከ ቊጥር የሌላቸው ብዙዎች አሕዛብንም መልሶ የዋሆች ምእመናን አደረጋቸው። ጌታችንም የማይቈጠሩ ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶችን በእጆቹ አደረገ ጥቅም ያላቸው ሦስት መልእክቶችንም ጽፎ ለምእመናን ላከቸው። ለማርቆስም ወንጌሉን ተርጒሞ አጽፎታል። ❤ ከዚህም በኋላ ወደ ሮሜ ከተማ ገባ የከተማው መኳንንት ወደሚሰበሰቡበት ወደታላቁ የጨዋታ ቦታም ሔዶ በታላቅ ድምፅ እንዲህ ብሎ ተናገረ "የሚራሩ ብፁዓን ናቸው ለርሳቸውም ይራሩላቸዋልና" የዚህንም ተከታታይ ቃሎች ተናገረ። በዚያም ከዚያ የነበሩ አራት የደንጊያ ምሰሶዎችም በሚያስፈራ ድምፅ "አሜን" አሉ የተሰበሰቡትም ይህን ቃል በሰሙ ጊዜ ደነገጡ። ከሰባ ዓመት ጀምሮ ሰይጣን ያደረበት አንድ ሰው ነበረ ከእነዚያ ድንጋዮች ቃልን ስለ ሰማ ያን ጊዜ ጋኔኑ ጣለው ከእርሱም ወጥቶ ሔደ። መኳንንቱም ፈርተዋልና ስለዚህ ነገር እያደነቁ ወደ ቤታቸው ገቡ። ❤ ከከተማ መኳንንቶችም ቀውስጦስ የሚባል አንዱ ወደ ቤቱ በገባ ጊዜ ስሟ አክሮስያ የምትባል ሚስቱ ዓለምን ስለ መተው ለድኆችም ስመራራትና የመሳሰለውን ቃል ቅዱስ ጴጥሮስ እንዴት እንዳስተማረ ነገራት። እርሷም በሰማች ጊዜ በልቧ ነቃታ "ይህ ገገር መልካምና ድንቅ ነው" አለች። ቅዱስ ጴጥሮስ ያስተማረውንም ሁሉ ያደርጉ ዘንድ በአንድነት ተስማሙ ሁሉ ያደርጉ ዘንድ በአንድነት ተስማሙ ከዚህም በኋላ ገንዘባቸውን ሁሉ ለድኆች ሰጡ ከዕለት ራት በቀር ምንም አላስቀሩም። ❤ ከጥቂት ቀኖችም በኋላ ንጉሡ ስለ መንግሥት ሥራ ከርሱ ጋራ ለመማከር በቶሎ እንዲደርስ ወደርሱ መልክትን ላከ። ቀውስጦስም ይህ በሰማ ጊዜ ገንዘብ ስላልነበረው ፈርቶ ደነገጠ ተጨነቀም። ምክንያትም አመካኝቶ ይሰወር ዘንድ ከሚስቱ ጋራ ተማከረ። እርሷ ግን "ምክንያት አታድር ነገር ግን ወደ ንጉሥ ሒድ የቅዱስ ጴጥሮስ አምላክን ጎዳናህን ያቅናልህ" አለች። እርሱም ነገሯን ተቀብሎ ወደ ንጉሡ ሔደ በመንገድም ከእግዚአብሔር የታዘዘ ብዙ በረከትን አገኘ ወደ ንጉሡም ደረሰ ንጉም በደስታና በክብር ተቀበለው። ❤ ከሦስት ዓመት በኋላም ወደ ቤቱ በተመለሰ ጊዜ ሁለቱ ልጆቹ የተመረዘ ውሃ ጠጥተው እነሆ ሞተው ነበር ሚስቱም ለእርሱ መንገርን ፈራች ብዙ ምሳሌዎችን ከመሰለችለት በኋላ ነገረችው። በሰማ ጊዜ እጅግ አዝኖ አለቀሰ። ሚስቱም እንዲህ አለችው "ጌታዬ ሆይ ልባችን የሚጽናናበትን እርሱ ያደርግልናል የቅዱስ ጴጥሮስ ፈጣሪ እግዚአብሔርን እንለምነው"። ሊጸልዩም በጀመሩ ጊዜ ቀወስጦስና አክሮስያ "የደቀ መዝሙሬ የጴጥሮስ ቃል ስለሰማችሁና ስለተቀበላችሁት ስለዚህ ልጆቻችሁን በሕይወታቸው እሰጣቸዋለሁ" የሚል ቃልን ከሰማይ ሰሙ ያን ጊዜም ልጆቻቸው ድነው ተነሱ ቀውስጦስና ሚስቱም ደስ አላቸው የተመሰገነ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት። ❤ እሊህም ከሞት የተነሱ ልጆች ለቅዱስ ጴጥሮስ ቀደ መዝሙሮቹ ሆኑ የአንዱ ስሙ ቀሌምንጦስ ነው እርሱም ቅዱስ ጴጥሮስ ያየውንና ጌታች በሥጋ ወደ ሰማይ በሚያርግ ጊዜ የገለጠለትን ምስጢር ሁሉ የነገረው ነው ሰዎች ሊያዪአቸው የማይገባቸውን መጻሕፍትን አስረከበው። ይህንም ቀሌምጦስን ሊቀ ከጵጵስና ወንድሙንም ዲቁና ሾማቸው። ❤ ከዚህም በኋላ ዳግመኛ ቅዱስ ጴጥሮስ አምላክን የወለደች የንጽሕት ድንግል እመቤታችን ማርያም ክብራን በምሳሌ አየ። በቀስት አምሳል ደመናን አይቷልና በላዪዋም የብርሃን ድንኳን ነበር በድንኳን ውስጥም አምላክን የወለደች ቅድስት ድንግል ማርያም ተቀምጣለች። በእጆቻቸው ውስጥ የነበልባል ጦሮችና ሰይፈችን ያያዙ መላክትና የመላእክት አለቆች በዙሪያዋ ነበር። እንዲህም እያሉ ያመሰግኗት ነበር። "ከእርሷ የደኅንነት ፍሬ የተገኘ የሰመረች የወይን ተክል አንቺ ነሽ ማኅፀንስሽም የእግዚአብሔር በግ የተሸከመ ንጽሕት አዳራሽ አንቺ ነሽ"። ❤ ሁለተኛም እንዲህ ይሏት ነበር " የብርሃን እናቱ ሆይ የምሕረት መገኛ ሆይ ደስ ይበልሽ የአማልክት አምላክ የፍጥረት ሁሉ ጌታ የሆነ የመድኅን ዙፋን ሆይ ደስ ይበልሽ ክብርና ምስጋናን የተመላሽ የፍጥረት ሁሉ እመቤት ደስ ይበልሽ"። መላእክት ምስጋናዋንና ሰላምታዋን ባደረሱ ጊዜ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለእርስዋ ተገልጦ ከእርሷ በቀር ማንም ሊያውቀው የማይቻል ነገርን ነገራት ወዲያውኑም ምድር ተናገወች ሊነገር የማይቻል ምሥጢራትንም ገለጠላት። ❤ ከዚህም በኋላ መድኀኒታችን ለአገሩ ሁሉ ቅዱስ ወንጌልን ይሰብክ ዘንድ ቅዱስ ጴሮስን አዘዘው ቅዱስ ጴጥሮስም መጥቶ ሔደ ኢዮጴም ወደምትባል የባሕር ዳርቻና ልድያ ወደምትባል አገር ደረሰ። በአንዲት ዕለትም በኢዮጴ ሳለ ብርሕት ደመና ዞረችው። እነሆም ሰፊ መጋረጃ ወደርሱ ወረደች በውስጧም የእንስሳት የምድረ በዳ አውሬዎችና የሰማይ አዕዋፍ አምሳል ነበር። "ጴጥሮስ ሆይ ተነሥና አርደህ ብላ" የሚል ቃልም ከሰማይ ጠራው። ቅዱስ ጴጥሮስም "አቤቱ አይገባኝም እርኲስ ነገር አልበላም ወደ አፌም ከቶ አልገባም" አለ። ያም ቃል ዳግመኛ ጠራውና እግዚአብሔር ንጹሕ ያደረገው አንተ ርኲስ ነው አትበል" አለው ያም ቃል ሦስት ጊዜ መላልሶ እንዲህ ነገረው። በየንግግሩም ወደ እሪያዎች፣ ወደ አራዊትና ወደ አእዎፍ ሥዕሎች ጣት ያመለክተው ነበር። ❤ ከዚህም በኋላ ያቺ መጋረጃ ወደ ሰማይ ተመለሰች። ቅዱስ ጴጥሮስም ስለ አየው ራእይ አደነቀ ይህም ራእይ ወደ ፈጣሪያቸው እግዚአብሔር የሚመለሱ አሕዛብን ስለመቀበል እንደሆነ አስተዋለ። ለወንድሞቹ ሐዋርያትም አሕዛብ የእግዚአብሔር ቃል እንደተቀበሉ የመቶ አለቃ ቆርኔሎስንም ከወገኖቹ ጋር እንዳጠመቀው ነገራቸው።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን" ❤             ❤ #ሐምሌ ፬ (4) ቀን። ❤ እንኳን #ለዐሥራ_ሁለቱ_ደቂቅ_ነቢያት ለመታሰቢያ በዓላቸውና ከእነርሱ አንዱ ለሆነው ለሴዴቅያስ ልጅ ለጎዶልያ ልጅ ለኩሲ ልጅ #ለነቢዩ_ለቅዱስ_ሶፎንያስ_ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከቅዱሳን_አቡቂርና_ዮሐንስ ከሥጋቸው ፍልሰት እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #ነቢዩ_ቅዱስ_ሶፎንያስ፦ እርሱም በይሁዳ ንጉሥ በኢዮስያስ ዘመን ትንቢት ተናገረ። እንዲህም አለ "እግዚአብሔር ከዚህ ዓለም ፈጽመው ይጠፋሉ አለ ከብቶችም ሰዎችም ያልቃሉ። የባሕር አሳዎች በሰማይ የሚበሩ አእዋፍም ያልቃሉ"። ❤ ዳግመኛም ስለሞአብ እንዲህ አለ "ስለዚህ ሞአብ እንደ ሰዶም ትሆናለች የሞአብ ልጆች እንደ ገሞራ ልጆች ይሆናሉ ደማስቆም እንደ እህል ታልቃለች"። እርሱም እንደ ተነበየው እነዚያ አገሮች በናቡከደነፆር ምርኮ ይጠፋሉና። ❤ ዳግመኛም ስለ ፋርስ ስለ ነነዌ ትንቢት ተናገረ እንዲህም አለ "የፋርስን ሰዎች አጠፋቸዋለሁ ነነዌም ፍርስራሽና ውኃ እንደሌለባት ምድረ አደርጋታለሁ መንጋዎችም በመካከሏ ይሠማሩባታል"። ይቺ ከተማ በመቄዶናዊው እስክንድር እጅ ጠፍታለች። ❤ ዳግመኛ ስለ ክርስቶስ መምጣት እንዲህ ተናገረ "ያን ጊዜም ሁሉ የእግዚአብሔር ስም ይጠራ ዘንድ በአንድ ሕግም ይገዙልኛ ዘንድ የአሕዛብን ሁሉ አንደበት ወደ ሕግ እመልሳለሁ"። ደግሞም እንዲህ አለ "ከኢትዮጵያ ወንዞች ማዶ መሥዋቴን ያመጡልኛል"። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በነቢዩ ቅዱስ ሶፎንያስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱ ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላዓለሙ አሜን።                              ✝ ✝ ✝ ❤ ዳግመኛም በዚች ቀን ስለ ክርስቶስ ትንቢታቸውን እንደ ፈሳሽ ውኃ ያጎረፉ #የዐሥራ_ሁለቱ_ደቂቀ_ነቢያት መታሰቢያቸው ነው። በረከታቸው ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #የቅዱሳን_አቡቂርና_ዮሐንስ_የሥጋ_ፍልሰት፦ ይህም እንዲህ ነው እሊህ ቅዱሳን የካቲት ስድስት ቀን ሰማዕት ሆኑው በሞቱ ጊዜ ምዕመናን ሥጋቸውን ተሸክመው ወስደው በእስክንድርያ በስተሰሜን ባለች በቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሥውር አኖሩዋቸው እስከ ሊቀ ጳጳሳት አባ ቄርሎስ ዘመንም በዚያ ኖሩ። ❤ እግዚአብሔር መልአክም ለቅዱስ ቄርሎስ ተገለጸለት ወደ ወንጌላዊ ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያንም ሔዶ የቅዱሳን የአቡቂርና የዮሐንስን ሥጋቸውን አውጥቶ እንዲሸከም አዘዘው። እርሱም ተነሥቶ ሔደ ከእርሱም ጋራ ቡዙ ሕዝቦች ነበሩ በደረሱም ጊዜ ጸለዩ ምድሩንም ሲቆፍሩ ሥጋቸው በውስጡ ያለበት ቦታ ተገለጠላቸው በባሕር ዳርቻ ወደ አለች ወደ ሌላዪቱም ወደ ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ክብር የቅዱሳኑን ሥጋ ተሸክመው አድርሰው በዚያ አኖሩ። በዚያም ቤተ ክርስቲያን ሠሩላቸው በዚች ቀን ታላቅ በዓል አደረጉ ከሥጋዎቻቸው ድንቆች ተአምራት ተገለጡ። ❤ አረማውያንም ተሰበሰቡ ይህን ድንቅ ተአምር በአዩ ጊዜ ጣዖቶቻቸው ትተው ክርስቲያን ሆኑ። በዚያችም ጣዖት ቤት አሸዋ በላይዋ ተከመረባት ታላቅ ኮረብታም ሆነ። የቅዱሳንም ሥጋቸው ታአምራትንና ለበሽተኞች ታላቅ ፈውስን ያደርናጋል። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን አቡቂርና በዮሐንስ በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሐምሌ 4 ስንክሳር።                               ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለከ_ሶፎንያስ_ክቡር። ዘተነበይከ በእንተ ይሁዳ ኅልቀተ ኃጥአን እምድር። እንዘ ትብል ከመዝ እንበለ ሠናይ ምግባር። ኢያድኅን ወኢይትቤዘው ብሩር። አመ ምጽአተ እግዚእ ዕለተ ፍዳ ዘድምፃ መሪር"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሐምሌ_4።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "እግዚአ ሰማዕነ በዕዘኒነ። ወአበዊነሂ ዜነዉነ። ግብረ ዘገበርከ በመዋዕሊሆሙ በመዋዕለ ትካት"። መዝ 43፥1። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 11፥32-ፍ.ም፣ 2ኛ ጴጥ 1፥19-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 10፥37-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 21፥33-46። የሚቀደሰው ቅዳሴ ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ቅዳሴ ነው። መልካም የነቢዩ የቅዱስ ሶፎንያስ የዕረፍት በዓል፤ የዐሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት መታሰቢያ በዓልና የሐዋርያት ጾም የመጨረሻ የጾም ቀን። ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን" ❤             ❤ #ሐምሌ ፫ (3) ቀን። ❤ እንኳን #ለእስክንድርያ_ሃያ_አራተኛ_ሊቀ_ጳጳስ ለአምደ ሃይማኖት መናፍቁ ንስጥሮስ በጉባኤ ኤፌሶን ተከራክሮ ረቶ ላወገዘው ለታላቁ #ለአቡነ_ቄርሎስ_ለዕረፍት መታሰቢያ በዓልና ከእርሱ በፊት ለነበረው ሊቀ ጳጳሳት ዮናክንዲኖስ ደቀ መዝሙሩ ለነበረው ለሮሜ ሊቀ ጳሳት ለቅዱስ አባት #ለአባ_ክልስቲያኖስ_ለዕረፍት መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_ቄርሎስ፦ ይህም አባት ለእስክንድርያ (ለግብጽ) ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሃያ አራተኛ ነው። ይህም ቅዱስ የእናቱ ወንድም በሆነው በአባ ቴዎፍሎስ ዘንድ አደገ፤ ጥቂት ከፍ ባለ ጊዜም ወደ አስቄጥስ ወደ መቃርስ ገዳም ላከው በዚያም አምላካውያን የሆኑ መጻሕፍትን ተማረ እግዚአብሔርም መጽሐፍትን አንድ ጊዜ አንብቦ እስከሚአጸናው ድረስ ዕውቀትንና ማስተዋልን ሰጠው። ❤ ከዚህም በኋላ ደግሞ ያስተምረው ዘንድ ለአባ ሰራብዮን ሰጠው ከእርሱም ዘንድ ያለውን ትምህርትን በፈጸመ ጊዜ ወደ ሊቀ ጳጳሳት ቴዎፍሎስ መለሰው። እርሱም እጅግ ደስ ተሰኘበት እግዚአብሔርንም አመሰገነው። ❤ ከዚህም በኋላ ሁል ጊዜ መጻሕፍትን እንዲያነብና ሕዝቡን እንዲያስተምር ለሊቀ ጵጵስና ሥራ ውስጥ ሾመው። ከትምህርቱም ጣዕም የተነሣ ዝም ይል ዘንድ ማንም አይወድም ነበር። ❤ አባ ቴዎፍሎስ በዐረፈ በኋላ በእስክንድርያ ከተማ ላይ ይህን አባ ቄርሎስነ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት በዘመኑም በትምህርቱ ቤተ ክርስቲያን በራች። ይኸው አባት ቄርሎስ የቊስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳሳት የነበረው ንስጥሮስ በካደ ጊዜ በንጉሥ ቴዎዶስዮስ ዘመን የሁለት መቶ ኤጲስቆጶሳት ጉባኤ ማኅበርን በኤፌሶን ከተማ ሰበሰበ። ይህ አባት ቄርሎስን መረጠው ሊቀ ጉባኤ አደረጉት ንስጥሮስንም ተከራከረው ስህተቱንም ገለጠለት ከስህተቱም ባልተመለሰ ጊዜ አውግዘው ከመንበረ ሲመት አሳደዱት። ❤ ይህም አባት ቄርሎስ አሥራ ሁለት አንቀጾችን ደረሰ። በውስጣቸውም የቀናች ሃይማኖትን ገለጠ። ከዚህም በኋላ ግን ብዙዎች ድንሳናትን ተግሳጻትንና መልእክቶችን ደረሰ። እሊህም በሁሉ ቦታ በመምእመናን እጆች ይገኛሉ። ❤ ይህም አባት ቄርሎስ እግዚአብሔር ቃል ከትሥብእቱ ጋራ ከተዋሐደ በኋላ በሥራ ሁሉ በምንም በምን የማይለያይ አንድ አካል አንድ ባሕሪይ እንደሆነ አስረዳ። ይህም አባት ቄርሎስ ሃይማኖታቸው ከቀና ከሦስት መቶ አሥራ ስምንት አባቶ ሃይማኖት ወጥተው ክርስቶስ ወደ ሁለት የሚከፍሉት መናፍቃንን ሁሉንም አውግዞ ለያቸው። ❤ ወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ መንበር ላይ ሠላሳ ሁለት ዓመት ኖረ መልካም የሆነ ሥራውም ፈጽሞ ሐምሌ 3 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ቄርሎስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላዓለሙ አሜን።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #የሮሜ_ሊቀ_ጳጳሳት_ቅዱስ_አባት_አባ #ክልስቲያኖስ፦ ይህ አባ ዮናክንዲዮስ በሚያርፍበት ጊዜ በእርሱ ፈንታ አባ ክልስቲያኖስን ሊቀ ጵጵስና እንዲሾሙት አዘዘ እርሱንም አባ ክልስቲያኖስን "በሮሜ አገር ነጣቂ ተኩላዎች አሉና ልጄ ሆይ ተጠበቅ" ብሎ አዘዘ። ❤ ከዚህም በኋላ አባ ዮናክንዲዮስ በዐረፈ ጊዜ ይህን አባት ክልስቲያኖስን በእርሱ ፈንታ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት። በዚያ ወራት ደግ ንጉሥ አኖርዮስ ነበር ከእርሱም በኋላ አመጸኛ ሉልያኖስ ነገሠ እርሱም ክርስቲያኖስን ከመንበሩ አሳድዶ መናፍቁን ንስጥሮስን ሊቀ ጵጵስና ሾመው። የከተማ ሰዎች ግን አባረሩት እንጂ አልተቀበሉትም በከሀዲው ንጉሥም ልብ በክርስቲያስ ላይ ቂም ነበረ ሊገድለውም ይሻ ነበር። እርሱ አባ ክልስቲያኖስ ግን በሮሜ ከተማ የሚገኙ ገዳማት በንዱ ገብቶ ኖረ እግዚአብሔርም ብዙ ድንቆችንና ተአምራቶችን በእጆቹ ያደርግ ነበር። ❤ ከዚህም በኋላ ከሀዲው ንጉሥ ወደ ጦርነት ሆደ የእግዚአብሔር መልአክ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሩፋኤልን ለክልስቲያኖስ ተገለጠለት ወደ አንጾክያ ከተማ ወደ ሊቀ ጳጳሳት ድምትርያኖስ ይሔድ ዘንድ አዘዘው "በዚያም ኑር" አለው። "ንጉሡ ከጦርነት እንደተመለሰ ይገድልህ ዘንድ በልቡ አስባልና"። ከእንቅልፉም በነቃ ጊዜ ከዚያ ገዳም ወጣ ከእርሱም ጋራም ሁለት መነኰሳት ነበሩ ወደ አንጾኪያ ከተማ ወደርሶ ቅዱስ ድምትርያኖስ አገኘው ከአመጸኛው ንጉሥም የደረሰበትን ሁሉ ነገረው እርሱም በአንጾኪያ ከተማ የሚገኙ ገዳማት በአንዱ ገዳም አኖረው። ❤ ከዚህ በኋላ ቅዱሳን ሊቃ ጳጳሳት አግናጥዮስና ዮናክንዲዮስ በሌሊት ዕራይ ለንጉሡ ተገለጡለት ከእርሳቸውም ጋራ የነበረው አንዱ እጅግ የሚያስፈራና ግሩም ነበር። እርሱም ንጉሡን እንዲህ አለው "ሊቀ ጳጳሳቱን ክልስቲያኖስን አገሩን ለምን አስተውከው እነሆ እግዚአብሔር ነፍስህን ከአንተ ይወስዳል በጠላቶችህም እጅ ትሞታለህ"። ንጉሥም ጌታዬ "ምን ላድርግ" አለው እነዚያም ሁለትም አባቶች "በእግዚአብሔር ልጅ ሕማም በመቀበሉ ታምናለህን" ብለው መለሱለት "እኔ አምናለሁ" አላቸው "ዳግመኛም መልእክትን ልከህ ልጃችን ክልስቲያኖስ ወደ መንበሩ መልሰው" አሉት። ❤ ከእንቅልፉም በነቃ ጊዜ መልክትን ጽፌ ወደ ድምትራያኖስ እንዲህ ብሎ ላከ "ስለ ሊቀ ጳጳሳት ክልስቲያኖስ በእኔ ላይ አትዘን ወደ መንበረ ሲመቱ ይመልሱት ዘንድ ሊቀ ጳጳሳት ክልስቲያኖስ ያለበትን በመላእክተኞቼ ታመላክታቸውና ታደርሳቸው ዘንድ እለምንሀለሁ"። መልአክተኞችም በሔዱ ጊዜ አገኙትና መለሱት ሕዝቡም በታላቅ ክብርና በብዙ ደስታ ተቀበሉት በዚያም ወራት ንጉሡ ከጦርነት በደና ተመለሰ ቤተ ክርስቲያንም በዕረፍትና በሰላም ኖረች። ❤ የንስጥሮስም ክህደቱ በተገለጠ ጊዜ በእርሱ ምንክያት አንድነት ያላቸው ማኅበር ተሰበሰቡ ይህ አባት ክልስቲያኖስ በደዌውና በእርጅናው ምክንያት ወደ ጉባኤው መምጣት አልተቻላቸውም ነገር ግን ንስጥሮስን ከሚያወግዝ ደብዳቤ ጋር ሁለት ቀሳውስትን ላከ። ❤ ክብር ይግባውና ጌታችንም ከዚህ ኃላፊ ዓለም ድካም ሊያሳርፈው በፈቀደ ጊዜ ዮናክንዲዮስና አትናስዮስ ተገለጡለት እንዲህም አሉት "ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሕይወት ጠርተሀልና አንተ ወደ እኛ ስለምትመጣ አስጠንቅቃቸው" አሉት። ከእንቅልፉ ነቅቶ ወገኖቹን ጠራቸው እንዲህም አላቸው "ተኩላዎች ወደዚች ከተማ ይገቡ ዘንድ አላቸውና ተጠንቀቁ"። ❤ ይህንም ከተናገረ በኋላ ዳግመኛ እንዲህ አለ "እንነሳና እንሂድ እነሆ ቅዱሳን ይሹኛልና ሁለቱ ሌሎች ናቸው በዚችም ሰዓት በዚች ዓለም በአንድነት እንወጣለን እነርሱም የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ቄርሎስና የፃን አገር ኤጲስቆጶስ ሉቅያስ ናቸው" ይህንንም ብሎ ሐምሌ 3 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን አባቶቻችን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሐምሌ 3 ሰንክሳር።                                                       ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "እነግሮሙ ስመከ ለአኃውየ። ወበማዕከለ ማኅበር እሴብሓከ። እለ ትፈርህዎ ለእግዚአብሔር ሰብሕዎ"። መዝ 21፥22-23። የሚነበቡት መልዕክታት ቲቶ 3፥18-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 3፥15-ፍ.ም የሐዋ ሥራ 20፥28-31። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 18፥15-21። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ቄርሎስ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ ቄርሎስ በዓልና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ ከዚህ በኋላ በላ መርፌው ቀዳዳው ጠባብ የሆነውነ መርፌ በአቀረበለት ጊዜ "ኃይልህ ግለጥ" ብሎ ወደ ጌታችን ጸለየ እጁንም ዘርግቶ በአለ ገመሉን ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም አንተ ከገመልህ ጋር በመርፎ ቀዳዳ ውስጥ ግባና እለፍ" አለው ገብቶም አለፈ "ሕዝቡም የፈጣሪያች የክርስቶስ ኃይል ይረዱ ዘንድ ዳግመኛ ገብተህ እለፍ" አለው። ባለ ገመሉም በመርፎው ቀዳዳ ሦስት ጊዜ ከገመሉ ጋር አልፎ ሆደ። ❤ ሕዝቡም አይተው "ከቅዱሳን ሐዋርያት አምላክ ከህያው እግዚአብሔር ልጅ ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ሌላ አምላክ የለም" እያሉ ጽምጻቸውን ከፍ አድርገው ተናገሩ። ያም ጎልማሳ ባለጸጋ መጥቶ ከሐዋርያው እግር በታች ወድቆ ሰገደና ኃጥያቴን ሁሉ ይቅ በለኝ ገንዘቤንም ሁሉ ወስደህ ለድኆችና ለምስኪኖች አከፍፍልልኝ" አለው። እንደ ለመነውም አደረገለት የሃይማኖትንም ሕግ አተምሮ የክርስትና ጥምቀትንም አጠመቀው ሥጋውንና ደሙ አቀበለው ሁሉንም በቀናች ሃይማኖት አጸናቸው። ❤ ከዚህ በኋላ ከዚያ ወጣ በሰላምም ሸኙት በቡዙ አገሮችም ውስጥ ገብቶ ሰበከ ከአይሁድና ከአረማውያን መከራ ደረሰበት ከዚህም በኋላ ሐምሌ 2 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ይሁን እኛንም በሐዋርያው ቅዱስ ታዴዎስ ጸሎት ይማረን በረከቱ ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላዓለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሐምሌ 1 ስንክሳር።                               ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለታዴዎስ_ምንዳቤ_ሕንቀት_ዘተወክፈ። እንበይነ ጥሪቱ ወብዕሉ አመ ባዕለ ዘለፈ። ለትውልድ ደኀሪ እስከ ተአምሩ ተጽሕፈ። ሰቀለ ብእሲተ በነፋስ ዘትዜሙ ዘልፈ። ወበስቊረተ መርፍዕ ካዕበ ገመለ አኅለፈ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሐምሌ_2።                            ✝️ ✝️ ✝️ ❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "ውስተ ኵሉ ምድር ወፅአ ነገሮሙ። ወእስከ አጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ። ወወስተ ፀሓይ ሤመ ጽላሎቶ"። መዝ 18፥4-5። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 13፥24-33።                            ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ሐወጸካ ለምድር ወአርወይካ። ወአብዛኅኮ ለብዕላ። ፈለገ እግዚአብሔር ምሉዕ ማያት"። መዝ 64፥9። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 9፥1-13፣ ይሁ 1፥17-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 5፥17-33። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 19፥16-30። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱሳን ሐዋርያት ቅዳሴ ነው። መልካም የሐዋርያው የቅዱስ ታዴዎስ የዕረፍት በዓልና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።