fa
Feedback
ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

رفتن به کانال در Telegram

ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።

نمایش بیشتر
636
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-47 روز
-1130 روز
آرشیو پست ها
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ እንኳን #ለክብር_ባለቤት_ለጌታችን_ለአምላካችን ­#ለመድኃኒታችን_ለኢየሱስ_ክርስቶስ_ለብርሃነ_ትንሣኤው በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና  አደረሰን­።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የዚህ_ሳምንት_መዝሙር፦ ሃሉ ሉያ "#ይትፌሣሕ_ሰማይ_ወትትሐሠይ_ምድር ወይንፍሑ ቀርነ መሠረታተ ኅምዝ ወይወውዑ አድባር ወአውግር ወኵሉ ዕፀወ ገዳም ወዮምሰ ዐባይ ፍሥሓ በሰማያት #ወምድርኒ_ትገብር_ፋሲካ_ተሐጺባ_በደመ_ክርስቶስ። ትርጉም፦ ምድርና ሰማይ ይደሰቱ፣ ቀርነ መለከትም ይነፋ፤ ተራሮችና ኮረብቶችም የዱር ተክሎችም ይደሰቱ፤ ዛሬ በሰማያት ታላቅ ደስታ ሆነ፣ #ምድርም_በክርስቶስ_ደም_ታጥባለችና_ፋሲካ (ደስታን) ታደርግ። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በድጓው_ላይ።                                                          ❤ #ትንሣኤ። ❤ ትንሣኤው የዓለም ድኅነት ሆነ በረቀቀ ጥበቡ ሠላሳ ሦስት ዓመት ያህል በምድር ላይ ሥራውን ሠርቶ በፈጸመ ጊዜ በፈቃዱ ሕማማተ መስቀል ተቀብሎ ሙቶ ከተቀበረ በኋላ በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሥቷልና። ❤ በዚች ዕለት ከሲኦል በመዳን ሙታንና ሕያውን ደስ አላቸው በዚች በጌታችንና በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ መነሣት መነሣታቸውን አረጋገጡ የከበረ ቅዱስ ጳውሎስ በመነሣቱ ክርስቶስ የሙታን በኵር ሆነ እንዳለ እርሱ ለሙታን በኵራቸው ነውና። ለእርሱም ክብር ምስጋና ለዘላለሙ ይሁን አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት 29 ስንክሳር።                           ✝ ✝ ✝  ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ወተንሥአ እግዚአብሔር ከመ ዘንቃሕ እምንዋም። ወከመ ኃያል ወኅዳገ ወይን። ወቀተለ ፀሮ በድኅሬሁ"። መዝ 77፥65-66። የሚነበቡት ወንጌላት ማቴ 28፥1-ፍ.ም፣ ማር16፥1-ፍ.ም፣ ሉቃ 24፥1-13።                           ✝ ✝ ✝  ❤ #የዕለቱ_ቅዳሴ_ምስባክ፦ "ዛቲ ዕለት እንተ ገብረ እግዚአብሔር። ንትፈሣሕ ወንትሐሠይ ባቲ። ኦ እግዚኦ አድኅንሶ።" መዝ 117፥24-25 ። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 15፥20-41፣ 1ጴጥ 1፥1-13 እና የሐዋ ሥራ 2፥22-37። የሚነበው ወንጌል ዮሐ 20፥1-19። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የብርሃነ ትንሣኤ በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ❤ ❤ እንኳን #ለሰሞነ_ሕማማት_ሦስተኛ_ቀን_ለምክር፣ #ለመልካም_መዓዛ_ላለውና_ለዕንባ ቀን እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                 ❤ #ዕለተ_ረቡዕ። ❤ ይህ ዕለት የምክር ቀን ይባላል፡፡ ምክንያቱም የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሓፍት ጌታን እንዴት መያዝ እንደሚገባቸው ምክር የጀመሩበት ወይም የያዙበት ቀን ስለሆነ ነው፡፡ በዚህ ምክራቸው ላይ በጣም ትልቅ ጭንቀት ነበር፡፡ ምክንያቱም ወቅቱ የፋሲካ በዓላቸውን የሚያከብሩበት በመሆኑ ብዙውን ሕዝብም በጌታችን ትምህርት የተማረኩ፣ ተአምራቱን የሚያደንቁ ስለነበር ሁከት እንዳይፈጥር ነው፡፡ በዚህ ጭንቀት ሳሉ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ የአስቆሮቱ ይሁዳ በመካከላቸው በመገኘት የምክራቸው ተባባሪ ሆኖ ጭንቀታቸውን አስወግዶላቸዋል፡፡ ማቴ. 26፤1-5፣ ማር. 14፤1-2 የሐዲስ ኪዳን ካህናት ምእመናን በዚህ ዕለት በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ተሰብስበው ከእህልና ውኃ ተለይተው፣ መላ ሰውነታቸውን ለእግዚአብሔር አስገዝተው፣ የሞት ፍርዱን በማሰብና በማልቀስ፣ ስለዚህ ታሪክ የሚያወሳውንም በማንበብ እስከ ኮከብ መውጫ በጾም፣ በጸሎትና በስግደት ተወስነው ይቆዩና ወደ ቤታቸው ይሄዳሉ፡፡ ይሁዳ ማለት ታማኝ ማለት ቢሆንም እንደ ስሙ ግብሩ ሆኖ አልተገኘም፡፡ ስምና ግብሩ አልተባበረለትም፡፡ እኛ እንደ ስማችን ይሆን ግብራችን? ❤ መልካም መዓዛ ያለው ቀንም ይባላል፡፡ ምክንያቱም ጌታችን በዚህ ዕለት በቤተ ስምዖን ዘለምጽ ተቀምጦ ሳለ መላ ሕይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ እፍረት ከእንግዲህ በኃጢአት ተጎድቶ የኖር የነበረውን ሕይወቴን እንደዚሁ መልካም ሽቶ ዋጋው እጅግ በጣም ውድ የሆነ ከሦስት መቶ ዲናር በላይ የሚያወጣ በአልባስጥሮስ ብልቃጥ የሞላ ሽቱ ይዛ በመሄድ በጠጉሩ (በራሱ) ላይ በማርከፍከፍ ስላቀረበች ነው፡፡ ❤ የእንባ ቀንም ይባላል፡፡ ይህም ይህችው ሴት በጌታችን እግር ላይ ተደፍታ መላ ኃጢአቷን ይቅር እንዲላት በእንባዋ እግሩን አጥባዋለችና፡፡ ማቴ. 26፤6-13፣ ማር. 14፤3-9፣ ዮሐ. 12፤1 ከዚህም እያንዳንዳችን ልንማር የሚገባን ነገር አለ፡፡ ይኸውም የራሱን ኃጢአት በማሰብ ማልቀስና የተወደደ መሥዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር ማቅረብን ነው፡፡ ❤ እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ፃዕማ ወድካም አመ ከመዮም ያብጽኀነ ያብጽዕክሙ እግዚአብሔር በፍስሃ ወበ ሰላም። ❤ መልካም የሰሞነ ሕማማት የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ እንኳን #ለሰሞነ_ሕማማት_ለመጀመርያ_ቀን #ለአንጾሖተ_ቤተ_መቅደስ (ለቤተ መቅደስ መንጻት) እና መርገመ በለስ በሰላም አደረሰን።                ❤ #ዕለተ_ሰኑይ_ሰኞ። ❤ ይህ ዕለት አንጾሖተ ቤተ መቅደስ የቤተ መቅደስ መንጻት እና መርገመ በለስ የተፈጸመበት ዕለት ነው፡፡ ማር.11-11፣ ማቴ.21-18-22 ሉቃ.13-6-9፡፡ ❤ ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ "ወመሰለ ሎሙ ወይቤሎሙ አሐዱ ብእሲ በለሰ ቦቱ ውስተ አጸደ ወይኑ ወየሐውር ይንሣእ ፍሬሃ ወኢይረክብ ...፤ ይህንም ምሳሌ አለ ለአንድ ሰው በወይኑ አትክልት የተተከለች በለስ ነበረችው ፍሬም ሊፈልግባት ወጥቶ ምንም አላገኘም"። ሉቃ13፥6 በማለት በበለስ ስለተመሰለ የሰው ልጅ ሕይወት በማሰብ እንዲመለስ ንስሐ እንዲገባ በሕይወትም እንዲኖር እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ማሳሰቡን ያጠይቃል፡፡ ❤ ንስሐ አልገባም አልመለስም ያለም በለሷ እንደጠወለገችና እንደተቆረጠች ሁሉ ፍሬ ባለማፍራታቸው እንደሚቆረጡ እንዲሁም ወደ እሳት እንደሚጣሉ መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ያስረዳል፡፡ ❤ በለስ የተባለች ቤተ እስራኤል ፍሬ የተባለ ደግሞ ሃይማኖትና ምግባርን ነው፡፡ ሁላችን ቤተ እስራኤላውያን ፍሬ ሃይማኖት ወምግባር አስተባብረን ይዘን መገኘት ይገባናል፡፡ ❤ ፍሬ አልባ እንዳንሆን ጌታ ሲመጣም እንዳናፍር የመጽሐፉን ቃል ልንጠብቅና ልንፈጽም ይገባናል፡፡ በዚህ የሕማማት የመጀመሪያ ቀን ዕለተ ሰኑይ የምናስበው የምንዘክረው የሰው ልጅ ሕይወት በከንቱ በቸልተኝነት እንዳይደክም እንዳይጠወለግ እንዳይደርቅ ወደ እሳትም እንዳይጣል ማድረግ ይገባናል፡፡ ❤ እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ፃዕማ ወድካም አመ ከመዮም ያብጽኀነ ያብጽዕክሙ እግዚአብሔር በፍስሃ ወበ ሰላም አሜን። ❤ መልካም የሰሞነ ሕማማት የጾምና የስግደት ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።

መንገድንም ምራቸው ለሰይጣንም እንዳይታዘዙና እንዳያጠፋቸው አደራ አስጠብቃቸው። ልጆችህንና የልጅ ልጆችህን ከቃየል ልጆች ለያቸው አንድ ይሆኑ ዘንድ ከቶ አትተዋቸው ወደ ሥራቸውና ወደ ጨዋታቸውም አይቅረቡ" አለው። ❤ ከዚህም በኋላ ወደ ልጁ ወደ ሴትና ወደ ሔዋን መለስ ብሎ ያንን ወርቅ ከርቤና ዕጣን ከእርሳቸው ጋራ አኑረው ይጠብቁት ዘንድ አደራ አላቸው። እንዲህም አላቸው "የጥፋት ውሃ በመጣ ጊዜ ሥጋዬን ከወርቁ ከከርቤውና ከዕጣኑ ጋራ ወደ መርከብ ያስገቡ ከዚያም በኋላ በምድር መካከል ያኑሩት። ከብዙ ዘመናት በኋላም ያቺን አገር ይወርዋታል እሊህንም ወርቅ ከርቤና ዕጣን ከብዙ ምርኮ ጋር ይወስዱትና አካላዊ ቃል መጥቶ ሰው እስኪሚሆን ድረስ በዚያ ይጠበቃል።ማሕያዊት ነገሥታትም ይዘው መጥተው ይገብሩለታል ወርቁ ስለ መንግሥቱ፤ ዕጣኑ ስለ ካህነቱ፤ ከርቤውም ስለሆች ሞቱ ነው" አላቸው። ❤ ለአባታችን አዳምም ዘጠኝ መቶ ሠላሳ ዓመት ሲሆን መላልኤልም መቶ ሠላሳ አምስት ዓመት ሲሆነው በተፈጠረባት ዐርብ በዘጠኝ ሰዓት ዐረፈ። ያረፈባትም ሰዓት ከገነት የወጣባት ናት በዚያን ጊዜም የመላእክት ሠራዊት ከልጆቹ ጋራ ተሰበሰቡ። መልካም አገናነዝም ገነዙት በብዙ ሽቱዎችም መዓዛውን አጣፈጡ። ይህም በገነትና በደብር ቅዱስ ያለ ነው። ሥጋውንም በፀሐይ መውጫ በኵል በዋሻ ውስጥ አኖሩ የሚያበራ መብራትም አኖሩ ከእርሱም ጋር ወርቁን፣ ከርቤውንና ዕጣኑን አስቀመጡ ዋሻውንም በአዳምና በሔዋን በሴት ቁልፍ ቆልፈው አተሙት። የጥፍት ውኃም እስከ መጣ ድረስ ሴትና ልጆቹ ለአባታችን አዳም ሥጋ ሲያገለግሉ ኖሩ። ❤ ከዚህ በኋላም ኖኅ በአምላክ ትዕዛዝ ደብረ አራራት እስከሚደርሰው ከእርሱ ጋራ የአባታችን የአዳምን ሥጋ በመርከብ ወሰደው። ከዚያም ሴምና መልከ ጼዴቅ የእግዚአብሔር መልአክ እየመራቸው ይዘውት ሔዱ ከቀራንዮ ቦታ ደርሰው በዚያ ቀበሩት መልከ ጼዴቅም በዕጣን በቊርባን ሲያገለግል ኖረ። የእግዚአብሔር ልጅ መጥቶ ከድንግል ልጁ በተወለደ ጊዜ መድኃኒት በሆነች ሞቱ አድኖ ወደ ቀደመው ርስቱ መለሰው እርሱ ለከበሩ ደጋጎች ነቢያት ለተጋዳዮች ሰማይታትና ጻድቃን አባት ነውና ስለእርሱም የእግዚአብሔር ልጅ ወደ ዓለም መጥቶ ሰው ሁኗልና። ❤ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን የአባታችን የአዳም የእናታችን የሔዋን የቀደሙ የሁሉም አባቶች በረከት በላያችን ለዘላለሙ ይደር አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ 6 ስንክሳር።

ተአምኆ ቅዱሳን ወግጻዌ (የቅዱሳን ሰላምታ) Teamho Kidusan Wegtsawe (Yekidusa Selamta): ❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤              ❤ #ሚያዝያ ፮ (6) ቀን። ❤ እንኳን #ለክብር_ባለቤት_ለጌታችን_ለአምላካችን #ለመድኃኒታችን_ለኢየሱስ_ክርስቶስ በትንሣኤው ሳምንት #ለሐዋርያው_ለቅዱስ_ቶማስ ለተገለጠለት (ለጥንት ዳግም ትንሣኤ)፣ ለአባታችን #ለቅዱስ_አዳምና_ለእናታችን_ቅድስት_ሔዋን ለዓመታዊ መታሰቢያ በዓላቸው፣ #ለቅዱስ_ኖኅና ለንጉሥ #ቅዱስ_ዳዊት ለልደታቸው መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                                 ✝ ✝ ✝ ❤ በዚች ዕለት የክብር ባለቤት #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ_በትንሣኤ_ሳምንት_ለሐዋርያው_ቅዱስ_ቶማስ ተገለጠለት በእጆቹና በእግሮቹ ውስጥ የችንካሮቹን ምልክትም አሳየው የቶማስንም እጅ ይዞ በመለኮታዊ ጐኑ ውስጥ አኖረውና በጦር የተወጋበትን ቦታ አሳየው ቶማስም "ጌታዬና ፈጣሪዬ መነሣትህን አመንኩ" አለ። ጌታችንም "ብታየኝ አመንከኝ የሚመሰገንስ ሳያየኝ የሚአምንብኝ ነው" ብሎ መለሰለት። ❤ በትርጓሜ ወንጌልም እንዲህ ይላል ቶማስ በመድኃኒታችን ጐን ውስጥ እጁን በአስገባ ጊዜ እጁ በመለኮት እሳት ተቃጠለ በመለኮቱም ደግሞ በታመነ ጊዜ እጁ ከመቃጠል ዳነች። ❤ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በሐዋርያቶቹም ጸሎት በተጋዮች ጻድቃን በድል አድራጊዎች ሰማዕታትም ጸሎት ይልቁንም በእመቤታችን አምላክን በወለደች በክብርት ድንግል ማርያም በአማላጅነቷ ይማረን ዘንድ ወደርሱ እንለምናለን ለዘላለሙ አሜን።                                ✝ ✝ ✝ ❤ #አባታችን_ቅዱስ_አዳምና_እናታችን_ቅድስት_ሔዋን፦ ይህን አባታችን አዳምን ሳይፈጥረው አስቀድሞ በሰማይና በምድር ያለውን አዘጋጀለት። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረ መላእክትንም ስለርሱ ፈጠረ። ❤ ከዚህም በኋላ በኤዶም ተክልን አዘጋጀለት እርሱም የፍሬው ጣዕም በየራሱ ልዩ ነው የሚያሻውን ሁሉ አከናውኖ እንሆ ከምድር መካከል ይኸውም በጎልጎታ ነው። አፈር አንሥቶ በሦስት ሰዓት እርሱን ፈጠረው። ከአራት ባሕርያት ይኸውም ውኃ፣ እሳት፣ ነፋስና መሬት ነው በአርአያውና በምሳሌው ራሱን አስመስሎ ፈጠረው በፊቱም እፍ ብሎ የሕይወት መንፈስን አሳድሮ የሚናገርና የሚያስተውል የሚያውቅ አደረገው የብርሃንንም ልብስ አልብሶ ንጉሥ፣ ነቢይ፣ ካህን፣ አስተዳዳሪ አድርጎ በፈጠረው ሁሉ ላይ ሾመው። ❤ ከዚህም በኋላ አይቶ ስማቸውን ይሰይም ዘንድ አራዊትን እንስሳትን የሰማይ ወፎችን ሁሉ ወደርሱ አመጣ። አዳምም መንፈስ ቅዱስ እንዳናገረው ለሁሉም ስም አወጣላቸው። ❤ ከዚህም በኋላ በአዳም ላይ እንቅልፍን አመጣበትና አንቀላፋ ከጐኑም አንድ ዐጥንትን ነሣ ቦታዋንም በሥጋ መላው እግዚአብሔርም ሴት አድርጎ አሳምሮ ሠራት በአዳምም በፊቱ አኖራት። አዳምም ነቅቶ "ይቺ ከዐጥንቴ ዐጥንት ከሥጋዬ ሥጋ ናት ሴት (ሚስት) ትሁነኝ ብሎ ተናገረ ስሟንም ሔዋን" አላት። ❤ አዳምም በጎልጎታ ቁሞ የፈጣሪውን ቃል እየሰማ ሳለ እንሆ ከሚስቱ ከሔዋን ጋራ በፊት በኋላ ሁነው በየነገዳቸው አዳምን ስለ አከበረው መላእክት እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ደመና ተሸክማ ወሰደቻቸው በኤዶም ገነትም አኖራቸው። ❤ እግዚአብሔር አዳምንና ሔዋንን "በገነት ካለው ተክል ሁሉ ብሉ ግን ከገነት መካከል ዕፀ በለስን አትብሉ ከእርሱ በበላችሁ ቀን ሞትን ትሞታላችሁ" አላቸው። አዳምም ገነትን እያረሰና እየቆፈረ ከፍሬዋም እየተመገበ ከመላእክት ጋራ ሲያመሰግን ኖረ። ❤ የበጎ ሥራ ጠላት ሰይጣን ግን ከማዕርጉ በወደቀ ጊዜ በአዳም ጌትነትና ክብር ቀንቶ በእባብ አድሮ ወደ ሔዋን ሔደ። ያንን ዕፀ በለስንም ትበላ ዘንድ አታለላት አምላክ የመሆንንም ተስፋ አሳደረባትና አሳታት። ያንን ዕፀ በለስንም በአየችው ጊዜ አማራት በልታ ለባልዋም አበላችው ያን ጊዜ የብርሃን ልብሳቸው ከላያቸው ተገፈፈ። እነርሱም ራቁታቸውን እንደሆኑ አውቀው በበለስ ቅጠል ኅፍረተ ሥጋቸውን ሸፈኑ። ❤ እግዚአብሔርም ስሕተታቸውን አውቆ አስቀድሞ እባብን ረገመ በእርሷና በሴቲቱ ዘር መካከል ጠላትነትን አጸና። በሔዋንም ላይ "በፃር በገዐር ውለጂ ወልደሽም መመለሻሽ ወደባልሽ ይሁን እርሱም ይግዛሽ" ብሎ ፈረደባት። አዳምንም እንዲህ አለው "ስለ አንተ ምድር የተረገመች ትሁን ጥረህ ግረህ እንጀራህን ብላ አንተ አፈር ነህና ወደ አፈርነት ትመለሳለህ" አለው። ❤ እግዚአብሔርም የቁርበትን ልብስ አዘጋጅቶ አለበሳቸው ሰባት ዓመት በተድላ ከኖሩ በኋላ በምሽት ጊዜ ከኤዶም ገነት ወጡ። አዳምም በማለዳ ፀሓይ ሲወጣ ነጭ ዕጣን ቀንዓት ሰሊሖት የሚባል ሽቱ ከሎሚ ውኃ ጋር አጠነ። አዳምም በኤዶም ገነት እንደተማረ ምድሪቱን እያረሰና እየቆፈረ ኤልዳ በሚባል ምድር ኖረ። ❤ አዳምም ሔዋንን በግብር አወቃት ቃየልን ከእኅቱ ጋራ ወለደችለት ከእርሱም በኋላ አቤልን ከእኅቱ ጋራ ወለደችው ቃየልና አቤልም አድገው አካለ መጠን አደረሱ። ወደ እግዚአብሔር መሥዋዕት በአቀረቡ ጊዜ ጌታ የአቤልን መሥዋዕት ተቀበለ ስለዚህም ቃየን ተቆጣ በአቤልም ቀንቶ ገደለው። አዳምም በልጁ በአቤል ሞት እያዘነና እያለቀሰ አራት የዘመን ሱባዔ ኖረ። ከዚህም በኋላ ሴት ተወለደለት በእርሱም መታሰቢያው ጸና ከእርሱም በኋላ ብዙዎች ወንድንና ሴቶች ልጆችን ወለደ። ❤ እግዚአብሔርም ንስሓውንና ልቅሶውን አይቶ የድኅነት ተስፋ ሰጠው። "አምስት ሽህ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም ወደ ዓለም መጥቼ ከልጅ ልጅህ እወለዳለሁ ሕፃንም ሁኜ በሜዳህ ውስጥ እድሀለሁ በመስቀሌና በሞቴም አድንሃለሁ" አለው። ❤ አዳምም ከገነት በወጣ ጊዜ የወሰደውን ወርቅ አርቤና ዕጣን ለልጁ ለሴት ሰጠው እንዲህም አለው "በኋላ ዘመን የእግዚአብሔር ልጅ መጥቶ ከድንግል ይወለዳል ያን ጊዜ የጥበብ ሰዎች ይህን ወርቁን ከርቤውንና ዕጣኑን እጅ መንሻውን ያመጡለታል" እርሱም መዝግቦ በዕቃ ቤት አኖረው። ወደ ኖኅም እስኪደርስ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ ኖረ ከኖኅም የምሥራቅ ሰዎች ወደ ሆኑ የጥበብ ሰዎች እስኪደርስ ተላለፈ። እነርሱም ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም በሥጋ በተወለደ ጊዜ አምጥተው ለእግዚአብሔር ልጅ እጅ መንሻ አድርገው አቀረቡለት እመቤታችንም ከእጃቸው ተቀብላ በኋላ ለቅዱስ ጴጥሮስ ሰጠችው ቅዱስ ጴጥሮስም ለቀሌምንጦስ ሰጠው። ❤ አዳምም የሚያርፍበትን ሰዓት በአወቀ ጊዜ ልጁ ሴትን ጠርቶ "ከመሞቴ በፊት ልጆችህንና የልጅ ልጆችህን ወደእኔ አቅርባቸው" አለው። የአባቱን ቃል ሰምቶ ዕንባው በጉጩ ላይ እየፈሰሰ ወጣ አዳምም አቀረባቸው። አዳምም በአያቸው ጊዜ ከእርሳቸው ስለ መለየቱ አለቀሰ። እነርሱም ሲያለቅስ በአዩ ጊዜ ሁሉም በአንድነት ወደ እግዚአብሔር በግምባራቸው ተደፍተው አለቀሱ "ምድር እንዴት ትሸፈንሃለች ከዐይኖቻችንስ እንዴት ትሠወራለህ" አሉ። ❤ ከዚህም በኋላ አባታችን አዳም ሁሉን ልጆቹን ባረካቸው መረቃቸው። ልጁን ሴትን እንዲህ አለው "ይቺ ዓለም ድካምና ችግርን የተመላች ናትና በእግዚአብሔር እየታመንክ ዕውነትን ንጽሕናን ጠብቅ ሰይጣን ወደሚያሳይህ ምትሐቱና ወደ ነገሩ አታዘንብል። በሞትኩ ጊዜም ሥጋዬን ወስዳችሁ ሰሊክ ሚዓ በሚባል ሽቱ ገንዛችሁ በግምጃ ቤት አኑሩኝ የጥፍት ውሃ ይመጣ ዘንድ አለውና ፍጥረት ሁሉ ይሰጥማል ከስምንት ነፍስ በቀር የሚቀር የለም። ልጄ ሆይ ለወገኖችህ ቋሚ ሁነህ እግዚአብሔር በመፍራት ጠብቃቸው የዕውነት

Repost from N/a
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 “የዘንባባ ዛፍ ዝንጣፊ ይዘው ሊቀበሉት ወጡና፦ ሆሣዕና፤ በጌታ ስም የሚመጣ የእስራኤል ንጉሥ የተባረከ ነው
+9
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 “የዘንባባ ዛፍ ዝንጣፊ ይዘው ሊቀበሉት ወጡና፦ ሆሣዕና፤ በጌታ ስም የሚመጣ የእስራኤል ንጉሥ የተባረከ ነው እያሉ ጮኹ።”    ዮሐንስ 12፥13 ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በዓለ ሆሣዕና በደብራችን እንዲህ በደመቀና ደስ በሚያሳኝ ሁኔታ አክብረን አልፈናል ለብርሃነ ትንሣኤው ያድርሰን ከሚዲያና ዕቅበት ክፍል የምስል ማህደር በጥቂቱ ይህን ይመስላል።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤               ❤ #ሚያዝያ ፬ (4) ቀን። ❤ እንኳን #ለአባታች_ቅዱስ_አዳም ለተፈጠረበት ቀን (ሰው ለተፈጠረበት ቀን)፣ ለከበሩ #ቅዱሳን_ፊቅጦርና_ዳኬዎስ_ለኤሞን፣ ሌሎችም ብዙዎች ሰዎች ሴቶችና ወንዶች ደናግሎች ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚችን ከሚታሳቡት፦ #ከአበ_ምኔት_አባ_ይስሐቅ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                      ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅዱሳን_ፊቅጦርና_ዳኬዎስ_ኤሞን፦ እሊህም ቅዱሳን በታላቁ ቈስጠንጢኖስና በልጁ ዘመነ መንግሥት የጣዖታትን በረቶች አፍርሰው ጣዖታትንም ሰብረው አቃጥለው በቦታቸውም አብያተ ክርስቲያናትን ሠርተው አምላክን በወለደች በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ስም በሌሎችም በብዙዎች ቅዱሳን ስም ታቦቱን ሰይመው ነበር። ❤ ከሀዲ ዮልያኖስም በነገሠ ጊዜ የጣዖትን አምልኮ አቆመ። የጣዖቱንም ካህናቶች አከበራቸው ብዙዎች ክርስቲያኖችንም አስገደለ። የእሊህ ቅዱሳን ዜናቸው አስቀድሞ በጣዖታት ቤቶች ላይ ያደረጉት ጣዖታትን እንደሰበሩ ሁሉ ተሰማ። ይዘውም ጽኑ ሥቃይን አሠቃዩአቸው ብዙ ቀንም ሲሰቅሏቸውና ሲገርፋቸው ቆዳቸውንም በሾተል ሲሰነጥቁ ኑረው በኋላም ቸብቸቧቸውን በሰይፍ ቆረጡ። በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ። በረከታቸው ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ4 ስንክሳር።                           ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለክሙ_ለፊቅጦር_ወዳኬዎስ ወኤርሞ። ምስለ ዕድ ወአንስት ዘተጋደልክሙ በተቃድሞ። ወተዓገሥክሙ ደርገ ለመስትረ ኀፂን ሕማሞ። በአስማቲክሙ ቶሲሕቶ ስሞ። ለአበ ምኔት ይስሐቅ አነብብ ሰላም"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሚያዝያ_4።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ንፍሑ ቀርነ በዕለተ ሠርቅ"። በእምርተ ዕለተ በዓልነ። እስመ ሥርዓቱ ለእስራኤል ውእቱ"። መዝ 80፥3-4። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 8፥1፥ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 1፥11-13 እና የሐዋ ሥራ 8፥26-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 12፥1-12። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ባስልዮስ ወንድም የቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘኑሲስ ቅዳሴ ነው። መልካም የጾም ጊዜና በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ ታላቁ አብርሃ በ364 ዓ.ም ጥቅምት 4 ቀን እሑድ ዕለት ዐረፉ፡፡ ከ13 ዓመት በኋላ ታናሹ አጽብሓ በ379 ዓ.ም ጥቅምት 4 ቀን ዐረፉ፡፡ ልደታቸውም ሆነ ሞታቸው አንድ ቀን ነው የዕረፍታቸው ዓመቱ ይለያይ እንጂ፡፡ የተቀበሩበት ቦታም አንድ ነው፡፡ የንግሥና ስማቸው ኢዛናና ዛይዛና ይባላል፡፡ ከቅዱሳን ነገሥታት ከአብርሃ ወጽብሓ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን ከሚለው መጽሐፍ የተወሰደ።

ተአምኆ ቅዱሳን ወግጻዌ (የቅዱሳን ሰላምታ) Teamho Kidusan Wegtsawe (Yekidusa Selamta): ❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤             ❤ #ሚያዝያ ፬ (4) ቀን። ❤ እንኳን #ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ ሃይማኖት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ሃይማኖት እንዲሆን ላደረጉ ለቅዱሳን ለወንድማማቾች ነገሥታት ያለፈረቃም በፍቅር አንድነት በአክሱም ተቀምጠው ለነገሡ (ለገዙ) #ለአብርሀና_አጽብሐ ለመታሰቢያ በዐላቸው እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅዱሳን_ወንድማማቾች_ነገሥታት_አብርሀ_ወአጽብሐ፦ አባታቸው ታዜር እናታቸው ሶፍያ (አህየዋ) ይባላሉ፡፡ መንትዮች የሆኑት እነዚህ ቅዱሳን የተወለዱት ጌታችን በተወለደባት ዕለት በታኅሣሥ 29 ቀን 312 ዓ.ም ነው፡፡ በታላቁ አባት በአቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን እየተማሩ አድገው በእሳቸው እጅ በ330 ዓ.ም መጋቢት 29 ቀን ተጠመቁ፡፡ በእነርሱም ጊዜ አማናዊው ጥምቀትና ቊርባን መጣልን፡፡ በሀገራችን 154 አብያተ ክርስቲያናትን ያሠሩ ሲሆን 44ቱ ፍልፍል ናቸው፡፡ በተለይም ገርዓልታ ያለው ቀመር ዓርባዕቱ እንስሳ ፍልፍል ቤተ መቅደስ በሩ በራሱ ጊዜ ይከፈታል ይዘጋል እንጂ ሰው አይከፍተውም አይዘጋውም፡፡ ❤ አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን በአክሱም ሲኖሩ ከሳምንቱ ቀናት ውስጥ ቅዳሜና እሑድ ብቻ የዛፍ ቅጠሎችን ከመመገብ በቀር ሌላ ምግብ ባለመመገብ በታላቅ ተጋድሎ ይኖሩ ነበር፤ አህልም አይቀምሱም፤ በየቀኑም አምስት ሺህ ስግደትን ይሰግዳሉ፡፡ በእርሳቸውም የተጋድሎ ዘመን ደጋግ የሆኑ ቅዱሳን ነገሥታት አብርሃና አጽብሓ ነገሡ፡፡ ❤ ነገሥታቱም ሆኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃንን እጅግ በጣም ይወዷቸው ነበር፡፡ አባታችንም በእንዲህ ዓይነት ተጋድሎ ሲኖሩ ከዕለታት በአንደኛው ቀን የብርሃን እናቱ ድንግል ወላዲተ አምላክ ለአቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ተገልጣላቸው "ዲቁናና ቅስናን መቀበል ይገባሃል፣ ለጵጵስና ተዘጋጅ፣ እግዚአብሔር ይህችን ከፍ ያለችውን ማዕረግ ሰጥተሃልና የልጄ ወዳጅ ሆይ በጸሎትህና በልመናህ በስብከትህም የኢትዮጵያ ሰዎች ሁሉ ይድናሉ፣ በእጅህ ጥምቀትንና ሥጋ ወደሙን ይቀበላሉ!" አለችው፡፡ ጌታችንም እንዲሁ ተገልጦላቸው "ወደ ሊቀ ጳጳሳት ወደ አትናቴዎስ ሄደህ ከፍ ያችውን ማዕረግ ተቀብለህ የኢትዮጵያን ሰዎች አጥምቅልኝ፣ ነቢዩ ዳዊት ስለ እነርሱ "ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች" ብሎ ተናግሯልና" አላቸው፡፡ ❤ ነገሥታቱ አብርሃንና አጽብሓ ነገረ ክርስቶስን እያሰቡ ስለ ጥምቀት ልጅነት ይጨነቁ ነበር፡፡ ከሊቀ ካህናቱም ጋር በዚህ ጉዳይ ሲጨዋወቱ ሊቀ ካህናቱ ስለ አቡነ ሰላማ ነገሯቸው፡፡ ነገሥታቱም አቡነ ሰላማን አስጠርተው ስለነገረ ክርስቶስ ምሥጢር እንዲያስረዷቸው ጠየቋቸው፡፡ አባታችንም "ነቢያት በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝተው አካላዊ ቃል እግዚአብሔር ወልድ ይወለዳል ካሉበት ጀምሮ የልደቱን፣ የትምህርቱን የጥምቀቱን፣ የስቅለቱን፣ የሞቱን፣ የትንሣኤውንና የእርገቱን ነገር ሌላውንም ሁሉ ተንትነው አስተማሯቸው፡፡ ሐዋርያትም በጌታ ተሾመው ዓለምን ዞረው ማስተማራቸውን እንዲሁ ተረኩላቸው፡፡ ነገሥታቱም ይህንን በሰሙ ጊዜ እጅግ ደስ ብሏቸው ፍሬምናጦስን "ወንድማችን ሆይ! ይህን ሥርዓት በሀገራችን እንድታስፋፋ" አሏቸው፡፡ አባታችን ግን "ለዚህ የሚያበቃ ሥልጣን ያለው እንጂ ለእኔ አይቻለኝም" አሉ፡፡ ነገሥታቱም "ይህን የሚችል ማነው?" ብለው ቢጠይቋቸው "በእስክንድርያ ጳጳሳትን፣ ቀሳውስትንና ዲያቆናትን የሚሾም አባት አለ" አሏቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ነገሥቱ ወደ እስክንድርያው ሊቀ ጳጳሳት ወደ ቅዱስ አትናቴዎስ ደብዳቤ በመጻፍ "አባታችንና መምህራችን ሆይ! የምንጠይቅህን እሺ በጀ በለን ይኸውም ወደ ጽድቅ ጉዳና የሚመራንን ጳጳስ ሹምልን" በማለት ብዙ ወርቅና ብር ገጸ በረከት አስይዘው ከብዙ ሊቃውንት ጋር ፍሬምናጦስን ወደ እስክንድርያ ላኳቸው፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ አባታችን ከነገሥታቱ አብርሃና አጽብሓ ጋር ተማክረው ወደ እስክንድሪያ ሄደው በቅዱስ አትናቴዎስ እጅ በአገራችን ላይ ሊቀ ጳጳስ ሆነው ታኅሣሥ 18 ቀን ተሾሙ፡፡ ቅዱስ አትናቴዎስ ከሾሟቸውና ከመረቋቸው በኋላ ለአቡነ ሰላማና አብረውት ለነበሩ ሊቃውንት መጻሕፍተ ብሉያትን፣ መጻሕፍተ ሐዲሳትንና ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያንን፣ ታቦተ ማርያምን፣ ታቦተ ሚካኤልንና ታቦተ ገብርኤልን አስይዘው ለነገሥታቱም ደብዳቤ ጽፈው ከብዙ ገጸበረከት ጋር በታላቅ ክብር ሸኟቸው፡፡ ❤ ቅዱሳን የሚሆኑ ሁለቱ ነገሥታትም አቡነ ሰላማ ከእስክንድርያ ተሾመው መምጣቸውን በሰሙ ጊዜ "የኢትዮጵያ ሰዎች ሁላችሁ እስከ 40 ቀን ተሰብሰቡ" ብለው አዋጅ አስነገሩ፡፡ አባታችንንም በደብረ ሲናም ሄደው አገኟቸውና ከዚያች ቀን ጀምሮ ሕዝቡም ሁሉ እስከ 40 ቀን ድረስ ተጠመቁ፡፡ በዚያችም ዕለት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚያች በደብረ ሲና አገር ላይ ወረደና ሕዝቡን ሁሉ ባረኮ ተመልሶ ሲያርግ ከአባ ሰላማ በቀር ያየው አልነበረም፡፡ ወደ አክሱምም ሄደው ቅዱሳን ነገሥታቱም የአድባራት ሁሉ የበላይ የምትሆን የቅድስት ጽዮንን ቤተ ክርስቲያን በወርቅና በዕንቊ ሠሯትና አባ ሰላማ ባርከው ቀደሷት፡፡ ታቦተ ጽዮንም ከድንኳን ወጥታ ማንም ካህን ሳይሸከማት አብርሃና አጽብሓ ወዳሠሩላት ቤተ መቅደስ ራሷ በመንፈስ ቅዱስ ገብታ ተገኘች፡፡ አባታችን በእመቤታችንም በዓለ ዕረፍት ጥር 21 ቀን በውስጧ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲቀድሱ ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል በግራ በቀኝ እየተራዷቸው እርሳቸውም ከምድር ሦስት ክንድ ከፍ ብለው ሥርዓተ ቅዳሴውን ፈጽመው ለነገሥታቱና ለሕዝቡም ሁሉ አቆረቧቸው፡፡ የዚያን ዕለትም እጅግ ታላቅ በዓልን አደረጉ፡፡ ❤ እነዚህም ቅዱሳን ነገሥታት ትምህርተ ወንጌልን እየሰጡ በአክሱም ቤተ መንግሥታቸው ሳሉ ከዕለታት አንደኛው ቀን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መላእክቱን አስከትሎ መጥቶ በአክሱም "ማይ ኰኩሐ" በሚባል ተራራ ላይ ቁሞ አብርሃ ወአጽብሓን ጠርቶ "በዚህች ቦታ ላይ ቤተ መቅደሴን አንጹልኝ" አላቸው፡፡ እነርሱም "ቦታው ባህር ላይ ነው በየት እናንጽልህ?" አሉት፡፡ ጌታችንም በጥበቡ ከገነት ጥቂት አፈር አምጥቶ በባሕሩ ላይ ቢበትንበት ባሕሩ ደርቆ ሜዳ ሆነ፡፡ በዚህ ጊዜ ጌታችን "ቤተ መቅደሴን በዚህ ሥሩ" ብሏቸው ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ ጌታችንም በቆመባት ዓለት ላይ የእግሩ ጫማ ቅርጽ እስከ አሁን ሳይጠፋ በግልጽ ይታያል፡፡ ቦታውም ከዚያ ወዲህ "መከየደ እግዚእ" እየተባለ ይጠራል፡፡ ❤ አብርሃ ወአጽብሓ ከመንግሥት አስተዳደሩ ጋር ክርስትናንና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን በመላ ኢትዮጵያ በማዳረስ እጅግ ከፍተኛ አስተዋፅዖ አድርገዋል፡፡ ካህናትንና ዲያቆናትን ይዘው በመላ ኢትዮጵያ ሐዋርያዊ ጉዞ በማድረግ ሕዝቡን ሁሉ እያስተማሩ፣ ሃይማኖትን እያጸኑ፣ ሥርዓተ ጥምቀትን እያስፋፉ ብዙ አብያተ ክርስቲያናትን አንጸዋል፡፡ በሀገራችን በአራቱም አቅጣጫ ወን ጌልን አስፋፍው ሕግ ሠርተዋል፡፡ የከበሩ ቅዱሳን ነገሥት አብርሃ ወአጽብሓ በእንዲህ ዓይነት ግብር ጸንተው በመኖር እግዚአብሔርንም ሰውንም አገልግለው ለሀገራችንም ብርሃን አብርተውላት ነው ያለፉት፡፡

እያሉ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት እርሱም በሹመቱ ላይ ሁኖ እንደሚገባ በመልካም አመራር ሥራውን መራ። ❤ የሚጽፍለትም ጸሐፊ መረጡለት ስለ ምዕመናን አጠባበቅና ስለማስተማር ወደ አገሮች ሁሉና ወደ ኤጲስቆጶሳቱ መልእክት ይልክ ነበር። ❤ እርሱም ከኃጢአታቸው ተመልሰው ንስሐ እንዲገቡ ሕዝቡን ይመራቸውና ይገስጻቸው ነበር እግዚአብሔርን ይፈሩት ዘንድ። ንጽሐ ነፍስ ንጽሐ ልቡና ያለው ሆነ የዚህን ዓለም ጣዕም ያለውን ምግብ አይሻም አይመኝም ክብሩንም ቢሆን ወይም ጥሪቱን ለድኆችንና ችግረኞችን አስቦ ይመጸውታቸው ነበር እንጂ። ከእነርሱ የሚተርፈውን ለቤተ ክርስቲያን ማሠሪያ ያደርገው ነበር። ❤ ይህ አባት ሙሉ ዓመት አልኖረም በዚያ የሚያንስ ነው እንጂ። በሰላም በፍቅርም ሚያዝያ3 ዐረፈ። ከአባ ሚካኤል በረከቱ ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ3 ስንክሳር።                             ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለመርቄ_ክርስቲያናዊ_ክቡር። እንተ መጠወ ወርቆ ለእግዚአብሔር። ሶበ ፈነወ ፵ በመድሎተ ልጥር። ወሰላም በፍቁሩ መምለኬ ጣዖት ጉዝፋር። ምስለ ሰብአ ቤቱ ዘአምነ እምዝንቱ መንክር"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሚያዝያ_3።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ወኢይትቃወመከ መንበረ ዓመፃ። ዘይፋጥር ፃማ ዲበ ትእዛዝ። ወይንዕዋ ለነፍስ ጻድቅ።" መዝ 93፥14-15። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 4፥14-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 5፥5-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 19፥21-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 4፥2-12። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ባስልዮስ ወንድም የቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ። መልካም የጾም ጊዜና በዓል። በሁላችንም ይሁንልን።

ተአምኆ ቅዱሳን ወግጻዌ (የቅዱሳን ሰላምታ) Teamho Kidusan Wegtsawe (Yekidusa Selamta): ❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤             ❤ #ሚያዝያ ፫ (3) ቀን። ❤ እንኳን #ለክርቲያናዊ_ነጋዴ ሲያርፋ ሁለት አንበሶች የቀበሩትና የላከው አርባ ልጥረ ወርቅ መብዓ ከሰማይ በክብር ወርዶ ራሱ ጌታችን በእጁ ለተቀበለው #ለቅዱስ_መርቄ ለዕረፍት በዓል፣ ለኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ #ለአባ_ዮሐንስ ለዕረፍት በዓልና #ለእስክንድርያ_ሰባ_አንደኛ_ሊቀ_ጳጳሳት_ለአባ_ሚካኤል ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር በሰላምና በጤና አደረሰን።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #ለቅዱስ_መርቄ፦ ይህም ቅዱስ ከአንጾኪያ ሰዎች ወገን ነው ጉዝፋር የሚባልም ወዳጅ ነበረው ይህም ጉዝፋርም ጣዖት የሚያመልክ ከሀዲ ነው ከሃይማኖት በቀር በምንም በምን አይለያዩም። ❤ ከዕለታትም በአንዲቱ መርቄና ጉዝፋር ግዱድ ወደሚባል አገር ለንግድ ሒደው ሰው በሌለበት በበረሀ ውስጥ አምስት ቀን ተጓዙ ክርስቲያናዊ መርቄም ባለጸጋ ነው ከእርሱ ጋራም አርባ ልጥረ ወርቅ ነበር። ❤ በጎዳና በጉዞ ላይም እያሉ ለሞት የሚያደርስ ደዌን ታመመ ከዚያም ራሱን አጽናንቶ እንዲህ ብሎ ጻፈ "ከባሪያህ ልጅ ከባሪያህ መርቄ ከእኔ ያለ በጥቁር በቅሎ የተጫነ አርባ ልጥረ ወርቅ ለአንተ ይሁን ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ የክብር ባለቤት ሆይ ስለ በደሌ ይቅር ብለኸኝ መንግሥተ ሰማያትን ትሰጠኝ ዘንድ ለልጆቼ ለሚስቴም ወይም ለዘመዶቼ አይሁን ብዬአለሁ"። ይቺን ደብዳቤ ጠቅልሎ ወዳጁ ጉዝፋርን ጠራው የሚለውን ሁሉ ያደርግለት ዘንድ አማለው። ከዚያም በምሞትበት ጊዜ አትንካኝ ግን ይህን አርባ ልጥረ ወርቅ እንደተጫነ ከበቅሎው ጋራ ወስደህ የክብር ባለቤት ለሆነ ለሕያው እግዚአብሔር ልጅ ለጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ በእጁ ስጠው። ለልጆቼ እንዳትሰጥ ከእርሱ በቀር ለማንም ቢሆን አትስጥ" አለው። ጉዝፋርም እንዲህ ብሎ መለሰለት "አንተ ራስህ ሞቶ ተነስቶ ወደ ሰማይ ወጣ የምትል አይደለምን እኔ ወደ ሰማይ ወጥቼ ልሰጠው እችላለሁን?"።መርቄም እንዲህ አለው "ወደ ቤተ ክርስቲያን ሒድ ራሱ ወደ አንተ ይመጣል እጅ በእጅ ስጠው" አለው። ❤ ከዚህ በኋላ መርቄ ለመሞት ሲቃረብ ራቅ ብሎ በመቀመጥ ጉዝፋር መሞቱን ይጠብቅ ነበር። ወደርሱም መላእክት የብርሃን ልብስ ይዘው ሲወርዱ አየ ከእርሳቸውም ጋራ ጻድቃን ሰማዕታት አሉ ዳዊትም በመሰንቆ ያመሰግን ነበር መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል ወርዶ በሥጋው ላይ ሦስት ጊዜ ዞረ ያንጊዜም የመርቄ ነፍስ ከሥጋዋ ተለይታ ወደ ሰማይ እንዲህ ባለ ሁኔታ ዐረገች። ሁለት አንበሶችም መጡ ምድሩንም ቆፍረው ቀበሩት። ❤ ጉዝፋርም ተነሣ የመርቄንም ወርቅ ጭኖ ስለአየው ሁሉ እያደነቀ ሔደ። አንጾኪያም በደረሰ ጊዜ የቤተ ክርሰቲያንኑን አስተዳዳሪ ቀሲስ ታዴዎስን አግኝቶ መርቄ እንዳለው ነገረው። ቀሲስ ታዴዎስም ሊረከበው ወደ ጉዝፋር ሔደ። ግን "የክብር ባለቤት ከሆነ ከጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ለማንም አልሰጥም ወዳጄ መርቄ እንዳማለኝ እጅ በእጅ እሰጠዋለሁ እንጂ" ብሎ ከለከለው። ❤ ከዚያም ሒዶ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ቅጽር ግቢ ገባ። ቀሲስ ታዴዎስም ደጁን ከፈተለት የተጫነውንም ወርቅ አውርዶ በፊቱ አኑሮ በዚያ ቆመ። ከሌሊቱ እኩሌታ ላይ እንደ ነጐድጓድ ድምጽ ያለ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሰማ። ታላቅ ብርሃንም ወጣ ጌታችንም ከሰማይ ወርዶ በመሠዊያው ላይ ተቀመጠ መላእክትም ከእርሱ ጋር አሉ። ከመላእክትም አንዱ "ከሀዲ ጉዝፋር ከዚህ ለምን ቆምክ" አለው። እርሱም "ወዳጄ መርቄ ለክብር ባለቤት ለጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እንጂ ለሌላ እንዳይሰጥ ብሎ እንደማለው" ነገረው። መልአኩም "የክብር ባለቤት የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ጌታ ኢየሱስ ክርሰቶስ ይህ ነውና ና ስገድ" አለው። ጉዝፋርም ሰገደ ደብዳቤውንም ሰጠው እየተንቀጠቀጠም "የክብር ባለቤት ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አመንኩብህ" አለ። ❤ ጌታም ያንን ወርቅ ይመዝኑት ዘንድ አዘዘ። አርባ ልጥርም ሆነ ጉዝፋርንም ከቀሲስ ታዴዎስ ዘንድ እንዲጠመቅ አዘዘው። ከቤተሰቡ ሁሉ ጋር ተጠመቀ የተጠመቁትም ሰባ አምስት ነፍስ ሆኑ። ኃጢአተኛውን በንስሐ ተመልሶ መዳኑን እንጂ መሞቱን ለማይወድ ቸር ይቅር ባይና ሰውን ለሚወድ እግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።                               ✝ ✝ ✝ ❤ #ለኢየሩሳሌም_ኤጲስቆጶስ_አባ_ዮሐንስ፦ የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ የኦሪት ምሁራን የሆኑ አዋቂዎች ነበሩ የኦሪትን ሕግ ትምህርቶችንም እያስተማሩት አሳደጉት። ክርስቲያኖችን በጸና ልቡና የሚከራከራቸውና የሚጣላቸው ነበር መጻሕፍትን አዘውትሮ ከመመርመሩ የተነሣ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ዓለም እንደመጣና ሰውም እንደሆነ በሞቱም ዓለምን እንደአዳነ አመነ። እርሱም የባሕርይ አምላክ እንደሆነ አምኖ በኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስነት ለመሾም እስቲገባው ድረስ በበጎ ሥራው በዕውቀት አደገ። ❤ ኤልያስ የሚባለው እንድርያኖስም በነገሠ ጊዜ ከኢየሩሳሌም አገር የፈረሰውን ሕንፃ ሁሉ እንዲያንፁና በስሙ ኤልያስ ተብሎ እንዲጠራ አዘዘ። ከዚህም አይሁድ ምኵራብ ደጃፍ ላይ ታላቅ ግምብ ሠሩ ከከበረ ደንጊያም ሠሌዳ ሠርቶ በላዩም ስሙን ኤልያስን ጽፎ በመግቢያው አኖረው በዘመኑም ኢየሩሳሌም አሕዛብንና አይሁድን ተመላች ሠለጠኑባትም። ❤ ክርስቲያኖችም ሊጸልዩ ወደ ጎልጎታ ሲመጡ በአዩአቸው ጊዜ አሕዛብ ይከለክሉአቸው ነበር በዚያ ዝሁራ በሚባል ኮከብ ስም መስጊድ ሠርተው ነበርና። ስለዚህም ክርስቲያኖችን በዚያ እንዳያልፉ ይከለክሏቸው ነበር። በዚህም አባት ላይ አሕዛብ ታላቅ መከራና ኀዘን ደረሰበት ብዙ ጊዜ ደብድበውታልና በምድር ላይም ጐትተውታልና አጐሳቁለውታልና እርሱም ነፍሱን ወደርሱ ይቀበል ዘንድ የክብር ባለቤት ጌታችን ልመናውን ሰምቶ ሚያዝያ3 በሰላም ዐረፈ። የአባ ዮሐንስ በረከቱ ከእኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን።                                ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_ሚካኤል፦ ይህ የከበረ አባት በእስክድርያ ለተሾሙ አባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሰባ አንደኛ ነው። ይህ አባት ከታነሽነቱ ጀምሮ የምንኵስና ልብስ ሊለብስ ወደደ በአስቄጥስ ገዳም በአባ መቃርስ ቤተ ክርስቲያን መንኵሶ እስከ ሸመገለ ድረስ በዚያ ኖረ። በብዙ መነኰሳትም ላይ አበ ምኔት ሁኖ ተሾመ በዘመኑ ሁሉ መልካም ተጋድሎ በመጋደል እግዚአብሔርን ደስ አሰኘው። በወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ ወንበር ላይ ሊቀ ጵጵስና ለመሾም እስቲገባው ድረስ ፍጹም ተጋድሎ በመጋደል ደከመ። ❤ ከእርሱ በፊት የነበረ ሊቀ ጳጳሳት አባ ገብርኤል በዐረፈ ጊዜ ወንጌላዊ ቅዱስ ማርቆስ ወንበር ያለ ሊቀ ጳጳሳት አራት ወር ኖረ በዚች ሹመት የሚሻል ሲመረምሩና ሲመርጡ ብዙ ደከሙ። ከብዙ ድካምም በኋላ ሦስት የገዳም ሰዎችን መርጠው ስማቸውን በሦስት ክርታስ ጻፉ የክብር ባለቤት የጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስንም ስም በአንዲት ክርታስ ጽፈው እየአንዳንዳቸውን አሽገው በመሠዊያው ውስጥ አኖሯቸው። ቸር ጠባቂ ይሾምላቸው ዘንድ ኤጲስቆጶሳቱና ካህናቱ እስከ ሦስት ቀን እየጸለዩና እየቀደሱ እግዚአብሔርን በመማለድ ኖሩ። ከሦስት ቀኖችም በኋላ አንድ ታናሽ ብላቴና ጠርተው "ከእነዚህ ከሦስቱ ስሞች አንዱን አንሥተህ ስጠን" አሉት። ያም ብላቴና የዚህን አባት አባ ሚካኤል ስም ያለበትን ያንን ክርታስ አወጣ። ሁሉም እግዚአብሔር እንመረጠው አውቀው ይገባዋል ይገባዋል ይገባዋል

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ❤                   ❤ #ሚያዝያ ፪ (2) ቀን። ❤ እንኳን #ለቅዱስ_ቃይናን_ልጅ_ለቅዱስ_መላልኤል ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓል፣ ፊት እንደ ውሻ የሚመስል የሆነ በጸሎቱ ታላላቅ ተዓራትን አድርጎ አስተምሮ ሊይዞት የመጡትን ወታደሮችና ሊያስቱት የመጡ ሁለት አመንዝራ ሴቶችን #በእግዚአብሔር_አምነው ሰማዕትነት እንዲቀበሉ ላደረገ #ለቅዱስ_ክርስትፎሮስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓልና ከሐሊባ አገር ሰው ለሆነ #ለከበረ_አባት_ለቅዱስ_ስምዖን ለዕረፍቱ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ከሚታሰቡት፦ #በቅዱስ_ክርስትፎሮስ በትምህርቱና በሚታደርገው ተዓምራት አምነው ሰማዕትነት ከተቀበሉ #ከሁለት_ሴቶች_ከሁለት_መቶ_ወታደሮችና ከሌሎች ብዙ ሰዎች እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                  ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅዱስ_መላልኤል፦ መቶ ስልሳ አምስት ዓመት ኖረ ቅዱስ ያሬድን ወለደው። ቅዱስ መላልኤልም ያሬድ ከወለደው በኋላ ሰባት መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ ወንዶችና ሴቶች ልጆችን ወለደ። ❤ የቅዱስ መላልኤል መላ ዘመኑ ሁሉ ስምንት መቶ ዘጠና አምስት ዓመት ነው። ይኸውም ሚያዝያ ሁለት ቀን በእሑድ ዕለት ሞተ በማከማቻም ውስጥ ቀበሩት። የፈጣሪው በረከት በላያችን ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                                ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅዱስ_ክርስትፎሮስ፦ ይህም ቅዱስ ሰውን ይበሉ ከነበሩ ሰዎች አገር ነው በጦርነትም ማረኩት አባቱም በሐዋርያ ቅዱስ ማትያስ እጅ ያመነ ነው። ❤ በማረኩትም ጊዜ ቋንቋቸውን አያውቅም ነበር የክብር ባለቤት ወደሆነ እግዚአብሔርም ማለደ ቋንቋቸውንም ገልጦለት እንደርሳቸው ተናገረ የክርስቲያን ወገኖችን የሚያሠቃዩአቸውንም ገሠጻቸው የጦር ሠራዊቱንም የሚመራ መኰንን ጽኑዕ ግርፋትን ገረፈው። ቅዱስ ክርትፎሮስም መኰንኑን "የጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ትእዛዙ ኃይሉን ባትይዘኝና ባታስታግሠኝ አንተና ሠራዊትህ ከእኔ እጅ ባልዳናችሁ ነበር" አለው። መኰንኑም ስለ ርሱ ወደ ንጉሥ ላከ ከእርሱ የሆነውንም ነገረው። ❤ ንጉሡም ወደ ርሱ እንዲያመጡት ሁለኀት መቶ ወታደሮች ላከለት እርሱም ያለ መፍራት ያለ ማፈግፈግ አብሮቸው ሔደ። በእጁ በትር ነበረች በላይዋ በጸለየ ጊዜ በቀለችና አበበች። እነዚያ ወታደሮች ተርበው የሚበሉት እንጀራ በአጡ ጊዜ ቅዱስ ክርስትፎሮስ ጸለየ በእነርሱ ዘንድ እንጀራ በዝቶ ተትረፈረፈ እጅግም አድንቀው በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ። ወደ አንጾኪያም ደርሰው በሊቀ ጳጳሳት አባ ጳውሎስ እጅ የክርስትና ጥምቀትን ተጠመቁ። ❤ ወደ ንጉሡም ፊት በደረሱ ጊዜ ንጉሥ ዳኬዎስ ሊያስፈራውና ሊሸነግለው ጀመረ ደግሞ እጅግ መልከ መልካም የሆኑ ሁለት አመንዝራ ሴቶችን ወደርሱ ሰደደ እነርሳቸው እንደሚያስቱትና በኃጢአት እንደሚጥሉት አስቧልና። እርሱ ግን ገሠጻቸው አስተማራቸውም በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምነው በደማቸው ምስክር ሆኑ። እንዲሁም እነዚያ ሁለት መቶ ወታደሮች በንጉሡ ፊት በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመኑ ራሶቻቸውንም በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ የሰማዕትነትንም አክሊል በመንግሥት ሰማያት ተቀበሉ። ❤ ቅዱስ ክርስትፎሮስም ንጉሡን "አንተ የሰይጣንን ሥራ የምትቀበል ማደሪያው የሆንክ" ብሎ ዘለፈው ንጉሡም ተቆጥቶ በትልቅ ብረት ምጣድ ውስጥ እንዲጨምሩትና ከበታቹ እሳትን እንዲያነዱ አዘዘ። እንዲሁም አደረጉበት ነገር ግን ከጉዳት እንዳሰቡት ምንም የደረሰበት የለም። ጤነኛ ሁኖ ሰዎችን አስተማራቸው እንጂ። እጅግም አድንቀው በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ። ቅዱሱንም ከእርሷ ሊአወጡት ወደዚያች ብረት ምጣድ ቀረቡ ንጉሡም አንገታቸውን በሰይፍ እንዲቆርጧቸው አዘዘ የሕይወት አክሊልንም ተቀበሉ። ❤ ከዚያም በኋላ ታላቅ ደንጊያ በአንገቱ አንጠልጥለው ከጥልቅ ጒድጓድ እንዲጨምሩት ንጉሡ አዘዘ በጨመሩትም ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ በጤንነት አወጣው። ማሠቃየቱንም በሰለቸ ጊዜ አንገቱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ ንጉሡ አዘዘ። ቅዱሱም በእግዚአብሔር መንግሥት የድል አክሊል ተቀዳጀ። ጸሎቱ በረከቱ ከእኛ ጋር ለዘላለም ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ2 ስንክሳር።                              ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለክርስትፎሮስ_ዘተፄወወ_በጸብእ። በውስተ ሀገሩ ዘእምነ በትምእምርተ ማትያስ ረድእ። በህየ ተቀትለ በእንተ ክርስቶስ እግዚእ። ወሰላም ለእለ ሞቱ ምስሌሁ በስንዕ። ክልኤቱ አንስት ወአምዓት ሰብእ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ(አርኬ) #የሚያዝያ_2።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ሀቡ አኰቴተ ለእግዚአብሔር። ላዕለ እስራኤል ዓቢይ ስብሐቲሁ። ወኃይሉሂ እስከ  ደመናት"። መዝ 67፥34-35። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 15፥7-14፣ 1ኛ ጴጥ 3፥10-18 እና የሐዋ ሥራ 23፥6-12። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 18፥35-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ባስልዮስ ወንድም የቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘኑሲስ ቅዳሴ ነው። መልካም በዓልና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።