🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts
رفتن به کانال در Telegram
ይህ በአቡ ጁነይድ ሳላህ አህመድ የቀረቡ የድምፅና የፅሁፍ መልዕክቶች የሚሰበሰቡበት ቻነል ነው። አላህ ጠቃሚ እውቀትን ከመልካም ስራ ጋር ያግራልን! You can contact me here @salehom100
نمایش بیشتر2 213
مشترکین
-224 ساعت
-67 روز
-3430 روز
آرشیو پست ها
🔖 የቁርአን ወዳጆች
🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ
⌚️ የ 50 ደቂቃ ሙሀደራ
🔗 Share Link
https://t.me/abujunaidposts/147
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
ሚና የቅንነት ክበብ ለምን አስፈለገ?
ባለፉት አመታት በአላህ ፈቃድና ችሮታ በርካታ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማህበራት መመስረታቸው በእጅጉ የሚያስደስት ነው። ከነዚህ መካከል ሚና የበጎ አድራጎት ድርጅት ይገኝበታል።
እርዳታን ከማስተባበር ጋር የበጎ አድራጎት አላማና የአፈፃፀም መርሆዎችን መረዳትና ልምድ መለዋወጥ ያስፈልጋል ብለን እናምናለን። እርስዎ ይህንን ክበብ የሚቀላቀሉት ልምድ ለመለዋወጥ፣ ለመማማርና ቅንነትን ለመለማመድ ነው። ግንዛቤን የሚያጎለብቱ ሀሳቦችና ተሞክሮዎች በስፋት ይቀርባሉ። የጋራ መድረክ በመሆኑ ገንቢ ሀሳቦቻችሁም ይደመጣሉ።
ሚና የበጎ አድራጎት ድርጅት በዋናነት ህመምተኞችን እና አካል ጉዳተኞችን በመደገፍ ላይ ትኩረት ሰጥቶ የሚሰራ ድርጅት ሲሆን ኢን ሻ አላህ በቀጣይ የተጠኑ ፍሬያማ ፕሮጀክቶችን ተባብረን እናሳካለን።
አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ
የካቲት 13/2014
T.me/minacharityclub
የባጢል ሰዎች አጃቢ የፔጅና ግሩፖቻቸው አሟሟቂ እንዳንሆን!
√ እራስን ማጥራት ግዴታ ነው!
በሳንባ በሽተኞች መካከል፤ በተበከለ አየር ውስጥ ካለመከላከያ የሚኖር ሰው ስለጤንነቴ እጨነቃለው ቢለን አትቀልድ እንለዋለን።
ለፀረ ኢስላም አቡጃህሎች ጆሮውን ያዋሰ ሁሉ ሊነቃ ይገባዋል። ግሩፓቻቸውን ያሞቁ ፔጆቻቸውን በላይክ ያደመቁ ሁሉ ሊያስቡበት ይገባል። ለአላህና ለመልእክተኛው ያላቸውን ክብር፤ ለኢስላም ያላቸውን ቁርጠኛ እምነት ካስተዋሉ ከከሀዲያን ጋር ለመቀመጥ ትእግስቱ አይኖራቸውም። አራስን ማፅዳትም ተቀዳሚ ተግባራቸው ይሆናል።
( وَقَدْ نَزَّلَ عَلَيْكُمْ فِي الْكِتَابِ أَنْ إِذَا سَمِعْتُمْ آَيَاتِ اللَّهِ يُكْفَرُ بِهَا وَيُسْتَهْزَأُ بِهَا فَلَا تَقْعُدُوا مَعَهُمْ حَتَّى يَخُوضُوا فِي حَدِيثٍ غَيْرِهِ إِنَّكُمْ إِذًا مِثْلُهُمْ ) النساء/140 .
«በእናንተም ላይ በመጽሐፉ ውስጥ፤ የአላህን አንቀጾች በርሷ ሲካድባትና በርሷም ሲላገጥባት በሰማችሁ ጊዜ፣ በሌላ ወሬ ውስጥ እስከሚገቡ ድረስ ከነርሱ ጋር አትቀመጡ ማለትን በእርግጥ አወረደ፤ እናንተ ያን ጊዜ ቢጤያቸው ናችሁና፤ አላህ መናፍቃንን እና ከሐዲዎችን በሙሉ በገሀነም ውስጥ ሰብሳቢ ነውና»
ኒሳእ 140
ኢስላምን ከምንጩ መማር፤ ልብን ንፁህ በማድረግ፤ እራስን በእውቀት በማበልፀግና በአላህ በመታገዝ ማንኛውንም አይነት መደናገርና የቀልብ በሽታ መከላከል ይቻላል።
የአላህን ውዴታና ፍቅር ከፈለግን ኢስላማዊ እውቀትን ከትክክለኛ ምንጮች እናጣጥም።
ባወቅን ቁጥር ብርሀን እንደሆነና ጨለማን እንደሚገላልጥ እንረዳለን።
አዎ! ኢስላምን ከምንጩ እንረዳው፤ ያን ግዜ ለሚነሱ ሹቡሀቶች ሁሉ የኢስላም ሊቃውንት ምን ያክል የማያዳግሙ ምላሾችን እንደሰጡ በዝርዝር ማወቅ እንችላለን። እነዚህ ግሳንግስ ማወናበጃዎች ሁሉ በቁርአናዊ አስተምህሮ እንደሸረሪት ድር ሲበጣጠሱ እናስተውላለን።
ኢስላምን ስንኖረው ጉዞአችን መሰናክሎች የተደረደሩበት ነው። ስሜታችንን ተከትለን ለዱንያ እጅ ሰጥተን ከመስመር እንድንወጣ፤ አለያም ውዥንብሮችን በመስማት መደናገር ውስጥ እንድንገባ ሌት ተቀን የሚለፉ የሸይጣን ወታደሮች ብዙ ናቸው። ከኛ የሚጠበቀው፤ ጥሩ የጉዞ ጓደኞችን መቅረብና ጉዞአችንን የሚያሰናክሉ ሽፍቶችን መራቅ ነው።
አላማ ያለው ሰው ለስኬት የሚያበቁትን እርምጃዎች መሳት የለበትም፤ መርከብ በየብስ አይጓዝምና!!
Abujunaid
https://t.me/abujunaidposts/15
🗓 ሙስሊሟና የረመዳን ፆም ቀዷ
🎙አቡ ጁነይድ ሳላሕ አሕመድ
👌 አጭር ወቅታዊ ጥቆማ!
🔗 Share Link
https://t.me/abujunaidposts/155
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
የሸይኽ ቃሲምን ቤተሰቦች ለማቋቋም የቻልነውን ገቢ እናድርግ
ንግድ ባንክ
1000130553781
ናስር አሊ
@Abujunaidposts
የሸይኽ ቃሲምን ቤተሰቦች ለማቋቋም የቻልነውን ገቢ እናድርግ
ንግድ ባንክ
1000130553781
ናስር አሊ
@Abujunaid
ሸይኽ ቃሲም ሃጂ ዛሬ ለሊት የካቲት 8/2014 ወደ አኼራ መሄዳቸውን ስናሳውቃችሁ በታላቅ የሀዘን ስሜት ነው።
አላህ ማረፊያቸውን ጀነተልፊርደውስ ያድርገው። ቀብር የሚፈፀመው ኮልፌ ሲሆን ሰላተል ጀናዛ ዙህር ላይ በአወሊያ መስጂድ ይሰገዳል። ዱአ ማድረግና ቤተሰባቸውን ማፅናናትን አንዘንጋ።
©ተንቢሃት
ታላቁ አሊም ሸይኽ ቃሲም ሃጂ ዛሬ ለሊት የካቲት 8/2014 ወደ አኼራ መሄዳቸውን ስናሳውቃችሁ በታላቅ የሀዘን ስሜት ነው። አላህ ማረፊያቸውን ጀነተልፊርደውስ ያድርገው። ቀብር የሚፈፀመው ኮልፌ ሲሆን ሰላተል ጀናዛ ዙህር ላይ በአወሊያ መስጂድ ይሰገዳል። ዱአ ማድረግና ቤተሰባቸውን ማፅናናትን አንዘንጋ።
©ተንቢሃት
وفاة الشيخ قاسم حاجي رحمه الله
توفي الليلة الشيخ قاسم حاجي الليلة 14 رجب 1443هے. كان معروفا بتدريس التفسير والعلوم الأخرى في مساجد أديس وخاصة مسجد هاشم. والصلاة عليه بمسجد أوليا ظهرا إن شاء الله، فلا تنسوه من صالح دعائكم... رحمه الله وغفر له.
إنا لله وإنا إليه راجعون
اللهم اغفر له وارحمه وأسكنه الفردوس الأعلى من الجنة.
... آمن
@abujunaidposts
🔖 የረጀብ ወር እና ድንጋጌዎቹ
🎙አቡ ጁነይድ ሳላሕ አሕመድ
⌚️ የ 30 ደቂቃ አጭር መልዕክት
🔗 Share Link
https://t.me/abujunaidposts/322
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
ዛሬ ጁምዓ ረጀብ 10 ነው። ለረመዳን 50 ቀናት ብቻ ይቀራል። ዝግጅት እናድርግ!
@abujunaidposts
ዱዓ ወደ ፈጣሪ ወይስ ፍጡራን?
አላህ እንጂ ሌላ ማንም በማይችለው ጉዳይ ላይ ከአላህ ሌላ የሆነን አካል መለመን፣ እርዳታን እና ጥበቃን መጠየቅ እንዲሁም ድረሱልን ማለት … እነዚህ የተለያዩ የዱዓእ ወይም የፀሎት ክፍሎች ናቸዉ።
ኑዕማን ኢብኑ በሺር በአስተላለፉት ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ዱዓእ ለአላህ ብቻ የሚገባ አምልኮ መሆኑን እንዲህ በማለት ይገልፁልናል፤ “ዱዓእ እርሱ እራሱ አምልኮ ነው” ኢማሙ አህመድ፣ ቲርሚዚይ እና ሌሎችም ዘግበውታል
ሽርክ ማለት ለአላህ ብቻ የሚገባን ዒባዳ (አምልኮ) ለሌላ አሳልፎ መስጠት ነው፡፡
ስለሆነም ከላይ የጠቀስናቸዉን የተለያዩ የዱዓእ ክፍሎች ለነብያት፣ ለመላኢኮች (መላእክት) ፣ ለጂኖች (ለአጋንንት)፣ ለሞቱም ሆነ በህይወት ሳሉ ደጋግ የአላህ ባሮች፣ ለአላህ ወዳጆች (ወልዮች) … ወዘተ ማዋል ከትልቁ ሽርክ ውስጥ የሚመደብ ተግባር ነው፡፡
ፍጡራንን “ያ ረሱለላህ፣ ያ ዐሊይ፣ ያ ሰይዳ ፋጡማ፣ ያ ሁሰይን፣ ያ አብዱልቃድር ጀይላኒ፣ ያ ሰይዳ ዘይነብ፣ ያ ነጃሺ፣ ያ ኑርሁሰይን፣ ያ አብሬት፣ ያ ቃጥባሪ፣ ያ አልከሰዬ፣ ያ ሐጂ አሊዬ … ወዘተ እያሉ አላህ እንጂ ሌላ ማንም ሊፈፅመው በደይችለው ጉዳይ ላይ ለምሳሌ፡-
ልጅ የለኝምና ልጅ ስጡኝ ፣ ታምሜያለሁና ፈውሱኝ፣ ተርቤያለሁና ሲሳይን ለግሱኝ፣ ፣ ተጨንቂያሁና ከጭንቅ አውጡኝ፣ ፈርቼያለሁ እና ከአደጋ ጠብቁኝ፣ ከጀሀነም እሳት ጠብቁኝ፣ ለጀነት አብቁኝ፣ አማላጅ ጠበቃ ሁኑኝ… በማለት እነሱን መጠራትና መማፀን እና ድረሱልኝ ማለት በጥብቅ የተከለከለ ግልፅ የሽርክ ተግባር ነው፡፡
ይህ አይነቱ ጥሪ ሽርክ መሆኑን ከሚያመላክቱ እጅግ በጣም በርካታ የቁርአን እና የሐዲስ መረጃዎች መካከል ጥቂቶቹን ብቻ ለመጠቆም እምክራለሁ፡፡
አላህ እርሱ እንጅ ሌላ ማንም በማይችለው ጉዳይ ላይ ሌላን እርዳታ እንዳንጠይቅ ቃል ሲያስገባን እንዲህ ይላል፡-
(ﺇِﻳَّﺎﻙَ ﻧَﻌْﺒُﺪُ ﻭﺇِﻳَّﺎﻙَ ﻧَﺴْﺘَﻌِﻴﻦُ) ﺍﻟﻔﺎﺗﺤﺔ : ٥
"አንተን ብቻ እናመልካለን አንተንም ብቻ እርዳታ እንለምናለን፡፡" አልፋቲሀ:5
እንዲሁም አላህ የሰው ልጆች ከደጋሚ፣ ከመተተኛ እና ከጠንቋይ፣ ከአጋንንት እና ከሌሎች እርኩሳን አካላት ክፋት እና ሴራ በእርሱ ብቻ አንዲጠበቁ ያዛል፡፡ አላህ መልዕክተኛውን ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ እንዲሉ አዟቸዋል፦
ﻗُﻞْ ﺃَﻋُﻮﺫُ ﺑِﺮَﺏِّ ﺍﻟْﻔَﻠَﻖِ ( 1 ) ﻣِﻦْ ﺷَﺮِّ ﻣَﺎ ﺧَﻠَﻖَ ( 2 ) ﻭَﻣِﻦْ ﺷَﺮِّ ﻏَﺎﺳِﻖٍ ﺇِﺫَﺍ ﻭَﻗَﺐَ ( 3 ) ﻭَﻣِﻦْ ﺷَﺮِّ ﺍﻟﻨَّﻔَّﺎﺛَﺎﺕِ ﻓِﻲ ﺍﻟْﻌُﻘَﺪِ ( 4 ) ﻭَﻣِﻦْ ﺷَﺮِّ ﺣَﺎﺳِﺪٍ ﺇِﺫَﺍ ﺣَﺴَﺪَ ( 5 )
"በል «በተፈልቃቂው ጎህ ጌታ እጠበቃለሁ፡፡ ከፈጠረው ፍጡር ሁሉ ክፋት፡፡ ከሌሊትም ክፋት ባጨለመ ጊዜ፤ በተቋጠሩ (ክሮች) ላይ ተፊዎች ከኾኑት (ደጋሚ) ሴቶችም ክፋት" (አል ፈለቅ 1-5)
አላህ ብቻ እንጂ ሌላ ማንም በማይችለው ጉዳይ ላይ አንድ ሰው ከችግር እንዲያወጣውም ይሁን ጥቅምን እንዲያስገኝለት ሌላን አካል ድረሱልኝ ብሎ መማፀኑ ችግሩን እንደማያስወግዱለት ወይም ጉዳቱን እንደማይመክትለት ከመግለፁም ባሻገር ይህ ተግባርና እምነት ክህደት እንደሆነ ተናገሯል፡፡
ﻗﺎﻝ ﺗﻌﺎﻟﻰ : (ﻭَﻣَﻦْ ﺃَﺿَﻞُّ ﻣِﻤَّﻦ ﻳَﺪْﻋُﻮ ﻣِﻦ ﺩُﻭﻥِ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﻣَﻦ ﻻ ﻳَﺴْﺘَﺠِﻴﺐُ ﻟَﻪُ ﺇِﻟَﻰ ﻳَﻮﻡِ ﺍﻟْﻘِﻴَﺎﻣَﺔِ ﻭَﻫُﻢْ ﻋَﻦ ﺩُﻋَﺎﺋِﻬِﻢْ ﻏَﺎﻓِﻠُﻮﻥَ) ﺍﻷﺣﻘﺎﻑ : ٥ – ٦
"እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስም ለእርሱ የማይመልስለትን (ጣዖት) ከአላህ ሌላ ከሚጠራ ሰው ይበልጥ የተሳሳተ ማነው? እነርሱም ከጥሪያቸው ዘንጊዎች ናቸው፡፡ ሰዎችም በተሰበሰቡ ጊዜ (ጣዖቶቹ) ለእነርሱ ጠላቶች ይኾናሉ፡፡ (እነሱን) መገዛታቸውንም ከሓዲዎች ይኾናሉ"
(አል አህቃፍ 5-6)
ﻋﻦ ﺍﺑﻦ ﻣﺴﻌﻮﺩ ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻪ ﺃﻥ ﺭﺳﻮﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ ﻗﺎﻝ : ( ﻣﻦ ﻣﺎﺕ ﻭﻫﻮ ﻳﺪﻋﻮ ﻣﻨﺪﻭﻥ ﺍﻟﻠﻪ ﻧﺪﺍً ﺩﺧﻞ ﺍﻟﻨﺎﺭ ) ﺭﻭﺍﻩ ﺍﻟﺒﺨﺎﺭﻱ
ዓብድላህ ኢብኑ መስዑድ በአስተላለፉት ሐዲስ የአላህ መልዕክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ይላሉ ፦
“ከአላህ ውጭ ሌላን አካል ለአላህ አጋር አድርጎ መለመንን ሳይተው (ተውበት ሳያደርግ) የሞተ ሰው እሳት ገባ” (ቡኻሪ ዘግበውታል።)
ﻓﻔﻲ ﺍﻟﺤﺪﻳﺚ ﺍﻟﺼﺤﻴﺢ ﻗﺎﻝ ﺍﻟﻨﺒﻲ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ ﻻﺑﻦ ﻋﺒﺎﺱ ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻬﻤﺎ : ( ... ﺇﺫﺍ ﺳﺄﻟﺖ ﻓﺎﺳﺄﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﻭﺇﺫﺍ ﺍﺳﺘﻌﻨﺖ ﻓﺎﺳﺘﻌﻦ ﺑﺎﻟﻠﻪ ) ﺭﻭﺍﻩ ﺍﻟﺘﺮﻣﺬﻱ ﻭﻗﺎﻝ ﺣﺪﻳﺚ ﺣﺴﻦ ﺻﺤﻴﺢ
በሌላ ሐዲስም የአላህ መልዕክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፦
“መለመንን ስትፈልግ አላህን ብቻ ለምን፣ እርዳታንም ብትፈልግ በአላህ ብቻ ተረዳ” (ቲርሚዚይ ዘግበውታል)
አላህ ሁላችንንም እርሱን በብቸኝነት ለማምለክ ይወፍቀን። በተውሒድ ኖረን የምንሞት ያድርገን።
ወቢላሂተውፊቅ
T.me/abujunaidposts
🍂 ደስተኛ ኢስላማዊ ቤተሰብ
🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ
⌚️ የ 51 ደቂቃ ሙሀደራ
🔗 Share Link
https://t.me/abujunaidposts/103
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
{...فَٱللَّهُ خَیۡرٌ حَـٰفِظࣰاۖ وَهُوَ أَرۡحَمُ ٱلرَّ ٰحِمِینَ}
«አላህም በጠባቂነት (ከሁሉ) የበለጠ ነው፡፡ እርሱም ከአዛኞች ሁሉ ይበልጥ አዛኝ ነው» Surah Yûsuf: 64
__
@abujunaidposts
{ٱلَّذِینَ قَالَ لَهُمُ ٱلنَّاسُ إِنَّ ٱلنَّاسَ قَدۡ جَمَعُوا۟ لَكُمۡ فَٱخۡشَوۡهُمۡ فَزَادَهُمۡ إِیمَـٰنࣰا وَقَالُوا۟ حَسۡبُنَا ٱللَّهُ وَنِعۡمَ ٱلۡوَكِیلُ}
እነዚያ ሰዎቹ ለእነርሱ፡- «ሰዎች ለእናንተ (ጦርን) አከማችተዋልና ፍሩዋቸው» ይሉዋቸውና (ይህም) እምነትን የጨመረላቸው «በቂያችንም አላህ ነው ምን ያምርም መጠጊያ!» ያሉ ናቸው፡፡
[Surah Âl-`Imrân: 173]
___
@abujubaidposts
💎 የ ላኢላሃ ኢለላህ ትርጓሜ
💎የላኢላሃ ኢለላህ መልእክት
💎 የላኢላሃ ኢለላህ ይዘት
💎 የላኢላሃ ኢለላህ መስፈርት
💎 ላኢላሃ ኢለላህ ያለ ሰው ምን ይጠበቅበታል
💎 አምልኮን ለአላህ ብቻ ማፅደቅ እንዴት ሊረጋገጥ ይችላል?
☀️ ይህን አሳሳቢ መልእክት የተነተነ ቪዲዮ
✅በአቡጁነይድ ሳላህ አህመድ
𒊹︎︎︎መሰል አጫጭርና ጠቃሚ መልዕክቶች ለማግኘት ይቀላቀሉን☟︎︎︎ ☟︎︎︎
𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍
❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀
☀️ሁዳ መልቲሚዲያ
ቴሌግራም 👇
t.me/huda4eth
ፌስቡክ👇
fb.com/huda4eth
ዩትዩብ👇
http://www.youtube.com/c/HudaMultimedia
💎 የ ላኢላሃ ኢለላህ ትርጓሜ
💎የላኢላሃ ኢለላህ መልእክት
💎 የላኢላሃ ኢለላህ ይዘት
💎 የላኢላሃ ኢለላህ መስፈርት
💎 ላኢላሃ ኢለላህ ያለ ሰው ምን ይጠበቅበታል
💎 አምልኮን ለአላህ ብቻ ማፅደቅ እብዴት ሊረጋገጥ ይችላል?
☀️ ይህን አሳሳቢ መልእክት የተነተነ ቪዲዮ
✅በአቡጁነይድ ሳላህ አህመድ
𒊹︎︎︎መሰል አጫጭርና ጠቃሚ መልዕክቶች ለማግኘት ይቀላቀሉን☟︎︎︎ ☟︎︎︎
𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍
❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀
☀️ሁዳ መልቲሚዲያ
ቴሌግራም 👇
t.me/huda4eth
ፌስቡክ👇
fb.com/huda4eth
ዩትዩብ👇
http://www.youtube.com/c/HudaMultimedia
يا نَفسُ إِنَّ الحَقَّ ديني
فَتَذَلَّلي ثُمَّ استَكيني
فَإِلى مَتى أَنا غافِلٌ
يا نَفسُ وَيحَكِ خَبِّريني
وَإِلى مَتى أَنا مُمسِكٌ
بُخلاً بِما مَلَكَت يَميني
يا نَفسُ لا تَتَضايَقي
وَثِقي بِرَبِّكِ وَاستَعيني
يا نَفسُ أَنتِ شَحيحَةٌ
وَالشُحُّ مِن ضُعفِ اليَقينِ
يا نَفسُ توبي مِن مُؤا
خاةِ الأَخِ البَطِرِ البَطينِ
وَتَعَلَّقي بِمَعالِقِ ال
مَكروبِ ذي القَلبِ الحَزينِ
وَتَفَكَّري في المَوتِ أَح
ياناً لَعَلَّكِ أَن تَليني
فَلَتَغشَيَنّي غَشيَةٌ
يَندى لِسَكرَتِها جَبيني
وَلَتُعوِلَنَّ المُعوِلا
تُ هُناكَ حَولي بِالرَنينِ
وَلَتَجعَلَنّي بَعدَ خَل
قي طينَةً لَحِقَت بِطينِ
وَلَيَأتِيَنَّ عَلَيَّ تَح
تَ التُربِ حينٌ بَعدَ حينِ
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
