🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts
رفتن به کانال در Telegram
ይህ በአቡ ጁነይድ ሳላህ አህመድ የቀረቡ የድምፅና የፅሁፍ መልዕክቶች የሚሰበሰቡበት ቻነል ነው። አላህ ጠቃሚ እውቀትን ከመልካም ስራ ጋር ያግራልን! You can contact me here @salehom100
نمایش بیشتر2 214
مشترکین
+124 ساعت
-67 روز
-3430 روز
آرشیو پست ها
📌 ንፁሕ ልብ ♡
🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ
🔗 Share Link
https://t.me/abujunaidposts/137
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
🔗 ንፁሕ ልብ
🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ
🔗 Share Link
https://t.me/abujunaidposts/137
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
📌 በተከበሩት ወራቶች ነብሳችንን ከመበደል እንጠንቀቅ!!
ምስጋና ለአለማት ጌታ ለአላህ የተገባ ነው። የአላህ ሰላምና እዝነት በተከበሩት መልእክተኛ በቤተሰቦቻቸውና በባልደረቦቻቸው ላይ ሁሉ ይሁን። በመቀጠል፤
ያለንበትን የረጀብ ወር በማስመልከት የሚፈፀሙ የቢድዓ ተግባራት ተበራክተዋል። የረጀብን የመጀመሪያ እለት፣ የመጀመሪያ ጁምዓ፣ አስራ አምስተኛውን እለት እንዲሁም ሀያ ሰባተኛውን ቀን ማክበር ቢድዓ መሆኑን፤ በሌሎች ወሮች እንደሚፈፀሙት የሰኞና ሀሙስ ወይም አያመልቢድ ፃሞች ካልሆነ ወሩን አስመልክቶ የተደነገገ ልዩ ፆምም ይሁን ሰላት እንደሌለ ገልጫለሁ። ይህ ማለት ግን ረጀብን ከሌሎች ወራቶች የሚለየው ምንም ነገር የለም ማለት አይደለም።
የረጀብ ወር፤ በሱረቱል ተዉባህ ቁጥር 36 ከተጠቆሙት የተከበሩ አራት ወራት (አሽሁሩል ሁሩም) አንዱ ነው።
አላህ እንዲህ ይላል፤
[إِنَّ عِدَّةَ الشُّهُورِ عِنْدَ اللَّهِ اثْنَا عَشَرَ شَهْراً فِي كِتَابِ اللَّهِ يَوْمَ خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالأَرْضَ مِنْهَا أَرْبَعَةٌ حُرُمٌ ذَلِكَ الدِّينُ الْقَيِّمُ فَلا تَظْلِمُوا فِيهِنَّ أَنْفُسَكُمْ] التوبة/36
« አላህ ዘንድ የወሮች ቁጥር፤ በአላህ መጽሐፍ ዉስጥ (በጥብቁ ሰሌዳ ለውሀልማህፉዝ) ሰማያትንና ምድርን በፈጠረበት ቀን (የሰየመው) ዐሥራ ሁለት ወር ነው፤ ከነሱ አራቱ የተከበሩ ናቸው፤ ይህ ቀጥተኛው ሃይማኖት ነው፤ በነርሱ ውስጥም ነፍሶቻችሁን አትበድሉ፤» አልተውባህ 36
عَنْ أَبِي بَكْرَةَ رضي الله عنه عَنْ النَّبِيِّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ : ( السَّنَةُ اثْنَا عَشَرَ شَهْرًا مِنْهَا أَرْبَعَةٌ حُرُمٌ , ثَلاثٌ مُتَوَالِيَاتٌ : ذُو الْقَعْدَةِ وَذُو الْحِجَّةِ وَالْمُحَرَّمُ , وَرَجَبُ مُضَرَ الَّذِي بَيْنَ جُمَادَى وَشَعْبَانَ) رواه البخاري ومسلم.
ከአቢ በክራህ በተዘገበ ሀዲስ የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፤ «አመት አስራ ሁለት ወራት ነው፤ ከነሱ ዉስጥ አራቱ የተከበሩ ናቸው። ሶስቱ ተከታታይ ሲሆኑ፤ ዙልቂእዳ ዙልሂጃና ሙሀረም ናቸው። ሌላው ደግሞ በጁማዳና በሻዕባን መካከል ያለው የሙደር (ጎሳዎች የታወቁበት) የ”ረጀብ” ወር ነው።»
ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።
ዙልሂጃ የታወቀው የሀጅ ወር ነው፤
ዙልቂዕዳ ደግሞ ሁጃጆች ወደ መካ የሚያቀኑበት ወር ሲሆን፤
ሙሀረምም ከሀጅ ስነስርአት በኋላ ሰዎች ወደቀያቸው የሚመለሱበት ወር ነው። አላህ ረጀብንም ከእነዚህ የረከበሩ ወራት አድርጎታል።
እነዚህ ወራት (የተከበሩ) ናቸው ስንል፤
1- እነዚህ ወረሰቶች ጦርነት የተከለከለባቸው ወራት ናቸው።
ሙስሊሞች ላይ ጥቃት ከፈፀመባቸው እራሳቸውን ለመከላከል ብቻ ካልሆነ በስተቀር ውጊያ አይፈቀድም።
2- በነዚህ ወራት አላህ ክልክል ያደረጋቸውን ነገሮች መፈፀም በሌላ ወራት ወንጀልን እንደመፈፀም አይደለም። ስለዚህም አላህ እነዚህን ወራቶች ለይቶ ነብሳችንን እንዳንበድል አሳስቦናል፤ «በነርሱ ውስጥም ነፍሶቻችሁን አትበድሉ» ።
እራስን መበደል አስከፊ መሀይምነት ነው። በአንድ ሰውና በጌታው መካከል የሚፈፀም እራስን መበደል ለአላህ መፈፀም የሚገባን ሀላፊነት አለመወጣት ነው። በራስ ላይ ከሚፈፀሙ በደሎች ሁሉ ትልቁ በአምልኮ ፍጥረታትን ከአላህ ጋር ማጋራት “ሽርክ" ነው። ሰዎች ላይ የሚፈፀም በደልም ቢሆን የሚጎዳው ሰሪዉን ነውና እራስን መበደል ነው። ለራሱ ያወቀ በማንኛውም ጊዜ ከበደል ይርቃል።
ኢባደላህ!
አላህ እነዚህን ወራቶች አክብሯቸዋልና እኛም ከፍተኛ ክብር መስጠት ይገባናል።
እነዚህ ወራቶች ሲገቡ፤ አላህ ክብርን እንደለገሳቸው ልናስታውስና ከወንጀል ለመራቅ ያለንን ቁርጠኝነት ልናድስ ይገባል። ይህ ልባዊ ኢባዳ ነው።
ወንጀልን በማንኛውም መፈፀም የተከለከለ ቢሆንም በነዚህ ወራት ግን ክልክልነቱ የበረታ ነው።
ስለዚህም ከምንም አይነት ወንጀሎች መጠንቀቅ እና ወደ አላህ መመለስ ያስፈልገናል። ከትናንሽም ይሁን ከትላልቅ ወንጀሎች በአላህ እንጠበቅ።
ሸይጣንን እናሸንፍ!
አላህ ከጥፋት ይጠብቀን..
አሚን!!
አኹኩም ፊላህ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ
http://t.me/abujunaidposts
🔖 ዓቂዳ እና መንሐጅ...
ዘጠኝ ወሳኝ ነጥቦች
🎙አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ
📌 ትኩረት የሚሹ 9 የአቂዳና የመንሐጅ ጉዳዮችን ይዳስሳል
https://t.me/abujunaidposts/88
🔖 የመንሐጅ ቅብብሎሽ...
ከኸዋሪጅ እስከ ሀዳዲያ
🎙 አቡ ጁነይድ ሳላህ አሕመድ
🍂 ከ 10 አመታት በፊት በጃሊያ አዳራሽ የቀረበ አጭር መልዕክት
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
Watch "የትዕግስት ፍሬ በነብዩላህ አዩብ ታሪክ በአቡ ጁነይድ ሳላህ አህመድ || NesihaTv" on YouTube
https://youtu.be/nPQu_7p3wRg
🔖 የረጀብ ወር እና ድንጋጌዎቹ
🎙አቡ ጁነይድ ሳላሕ አሕመድ
⌚️ የ 30 ደቂቃ አጭር መልዕክት
🔗 Share Link
https://t.me/abujunaidposts/322
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
🍂 ° መሳጭ ቲላዋ ° 🍂
ቃሪእ ኢብራሂም ዓሲሪ
📖 ٱقۡتَرَبَ لِلنَّاسِ حِسَابُهُمۡ وَهُمۡ فِی غَفۡلَةࣲ مُّعۡرِضُونَ (1) مَا یَأۡتِیهِم مِّن ذِكۡرࣲ مِّن رَّبِّهِم مُّحۡدَثٍ إِلَّا ٱسۡتَمَعُوهُ وَهُمۡ یَلۡعَبُونَ (2) لَاهِیَةࣰ قُلُوبُهُمۡۗ
[ለሰዎች እነርሱ በዝንጋቴ ውስጥ (መሰናዳትን) የተው ኾነው ሳሉ ምርመራቸው ቀረበ፡፡ ከጌታቸው አዲስ የተወረደ ቁርኣን አይመጣላቸውም፡፡ እነሱ የሚያላግጡ ሆነው የሚያደምጡት ቢሆኑ እንጂ፡፡ ልቦቻቸው ዝንጉዎች ኾነው (የሚያዳምጡት ቢኾኑ እንጅ)]
ሱረቱል አንቢያእ 1-3
#تلاوات_لا_أنساها
@abujunaidposts
Repost from NESIHA TV | ነሲሓ ቲቪ
ተውሒድ በምሳሌ አቡ ጁነይድ ሳላህ አህመድ || NesihaTv
https://youtu.be/1iEqqY8j8BI
ነሲሓ ቲቪ...
ኢስላማዊ እውቀት ለሁሉም!!
Telegram: @nesihatv
Facebook: https://www.facebook.com/nesihatv/
YouTube: https://www.youtube.com/channel/UCX2E30J71sKpnLQuGr7kt6w
የኢስላምን ውበት እናስተንትን!
በአይጥ፣ በበራሪ ወፎች፣ በቀበሮና በመሳሰሉት መሟረት ወይም ነሌላ ነገሮች ገድ ማሰብ የጃሂልያ ድ*ንቁርና ነው። አይጥ ካለ ውሸትና ሌብነት እንዳለ ምልክት ማድረግ ስህተት ነው። ጉንዳን ወይም እርግብ ቤት ውስጥ ካለ ድህነት ይመጣል የሚባለውም እንዲሁ ነው። ሙስሊም የጉጉት ወይ የቁራ ጩኸት ሰምቶ ስራ አይቀናኝም ብሎ አይመለስም። አንዳንዶች በራሪ ሲጮህ ሰው እንደሚሞት በማሰብ ይጨነቃሉ። እጃቸውን ካሳከካቸው ገብዘብ እንደሚያገኙ፣ አይናቸው ከተርገበገበ እንግዳ እንደሚመጣ ያምናሉ። እነዚህ ሁሉ በጨለማው የጃሂልያ ዘመን ነግሰው የነበሩና ኢስላም የተዋጋቸው የክህደት አመለካከቶች ናቸው፡፡
አልሐምዱሊላህ ኢስላም ጠንካራ ስነልቦና ያላብሳል። የሙስሊም እምነቱና ተስፋው ሁሉ በአላህ ነው። የነገሮች ሁሉ ባለቤት፣ ፈፃሚና አስተናባሪ አላህ አይደለምን? በሱረቱ ነምል 59–65 ያሉ አንቀፆች ማስተንተን ተውሒድን ያድሳል። ሙስሊም በመሆናችን አልሐምዱሊላህ እንበል!
قُلِ ٱلۡحَمۡدُ لِلَّهِ وَسَلَـٰمٌ عَلَىٰ عِبَادِهِ ٱلَّذِینَ ٱصۡطَفَىٰۤۗ ءَاۤللَّهُ خَیۡرٌ أَمَّا یُشۡرِكُونَ
(ሙሐመድ ሆይ) በል «ምስጋና ለአላህ ይግባው፡፡ በእነዚያም በመረጣቸው ባሮቹ ላይ ሰላም ይውረድ፡፡ አላህ በላጭ ነውን ወይስ ያ (ከአላህ ጋር) የሚያጋሩት፡፡
أَمَّنۡ خَلَقَ ٱلسَّمَـٰوَ ٰتِ وَٱلۡأَرۡضَ وَأَنزَلَ لَكُم مِّنَ ٱلسَّمَاۤءِ مَاۤءࣰ فَأَنۢبَتۡنَا بِهِۦ حَدَاۤىِٕقَ ذَاتَ بَهۡجَةࣲ مَّا كَانَ لَكُمۡ أَن تُنۢبِتُوا۟ شَجَرَهَاۤۗ أَءِلَـٰهࣱ مَّعَ ٱللَّهِۚ بَلۡ هُمۡ قَوۡمࣱ یَعۡدِلُونَ
ያ ሰማያትንና ምድርን የፈጠረና ከሰማይም ለእናንተ ውሃን ያወረደው (ይበልጣል ወይስ የሚያጋሩት) ። በእርሱም ባለውበት የኾኑትን የታጠሩ አትክልቶችን ዛፍዋን ልታበቅሉ ለናንተ ችሎታ ያልነበራችሁን አበቀልን፡፡ ከአላህ ጋር ሌላ አምላክ አለን (የለም)፡፡ ግን እነርሱ (ከእውነት) የሚያዘነብሉ ሕዝቦች ናቸው፡፡
أَمَّن جَعَلَ ٱلۡأَرۡضَ قَرَارࣰا وَجَعَلَ خِلَـٰلَهَاۤ أَنۡهَـٰرࣰا وَجَعَلَ لَهَا رَوَ ٰسِیَ وَجَعَلَ بَیۡنَ ٱلۡبَحۡرَیۡنِ حَاجِزًاۗ أَءِلَـٰهࣱ مَّعَ ٱللَّهِۚ بَلۡ أَكۡثَرُهُمۡ لَا یَعۡلَمُونَ
ወይም ያ ሰማያትንና ምድርን የፈጠረና ከሰማይም ለእናንተ ውሃን ያወረደው (ይበልጣል ወይስ የሚያጋሩት) ። በእርሱም ባለውበት የኾኑትን የታጠሩ አትክልቶችን ዛፍዋን ልታበቅሉ ለናንተ ችሎታ ያልነበራችሁን አበቀልን፡፡ ከአላህ ጋር ሌላ አምላክ አለን (የለም)፡፡ ግን እነርሱ (ከእውነት) የሚያዘነብሉ ሕዝቦች ናቸው፡፡
أَمَّن یُجِیبُ ٱلۡمُضۡطَرَّ إِذَا دَعَاهُ وَیَكۡشِفُ ٱلسُّوۤءَ وَیَجۡعَلُكُمۡ خُلَفَاۤءَ ٱلۡأَرۡضِۗ أَءِلَـٰهࣱ مَّعَ ٱللَّهِۚ قَلِیلࣰا مَّا تَذَكَّرُونَ
ያ ችግረኛን በለመነው ጊዜ የሚቀበል፣ መከራንም የሚያስወግድ፣ በምድርም ላይ ምትኮች የሚያደረጋችሁ፤ (ይበልጣልን ወይስ የሚያጋሩት) ። ከአላህ ጋር ሌላ አምላክ አለን ጥቂትንም አትገሠጹም፡፡
أَمَّن یَهۡدِیكُمۡ فِی ظُلُمَـٰتِ ٱلۡبَرِّ وَٱلۡبَحۡرِ وَمَن یُرۡسِلُ ٱلرِّیَـٰحَ بُشۡرَۢا بَیۡنَ یَدَیۡ رَحۡمَتِهِۦۤۗ أَءِلَـٰهࣱ مَّعَ ٱللَّهِۚ تَعَـٰلَى ٱللَّهُ عَمَّا یُشۡرِكُونَ
ያ በየብስና በባሕር ጨለማዎች ውስጥ የሚመራችሁ ነፋሶችንም ከዝናሙ በፊት አብሳሪ ኾነው የሚልክ (ይበልጣልን ወይስ የሚያጋሩት) ። ከአላህ ጋር ሌላ አምላክ አለን አላህ (በእርሱ) ከሚያጋሩዋቸው ሁሉ ላቀ፡፡
أَمَّن یَبۡدَؤُا۟ ٱلۡخَلۡقَ ثُمَّ یُعِیدُهُۥ وَمَن یَرۡزُقُكُم مِّنَ ٱلسَّمَاۤءِ وَٱلۡأَرۡضِۗ أَءِلَـٰهࣱ مَّعَ ٱللَّهِۚ قُلۡ هَاتُوا۟ بُرۡهَـٰنَكُمۡ إِن كُنتُمۡ صَـٰدِقِینَ
ያ መፍጠርን የሚጀምር ከዚያም የሚመልሰው ከሰማይና ከምድርም ሲሳይን የሚሰጣችሁ አምላክ (ይበልጣልን ወይስ የሚምኑበት) ከአላህ ጋር ሌላ አምላክ አለን «እውነተኞች እንደኾናችሁ፤ አስረጃችሁን አምጡ» በላቸው፡፡
قُل لَّا یَعۡلَمُ مَن فِی ٱلسَّمَـٰوَ ٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ ٱلۡغَیۡبَ إِلَّا ٱللَّهُۚ وَمَا یَشۡعُرُونَ أَیَّانَ یُبۡعَثُونَ
«በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉ ሩቅን ምስጢር አያውቅም፡፡ ግን አላህ (ያውቀዋል)፡፡ መቼ እንደሚቀሰቀሱም አያውቁም» በላቸው፡፡
[Surah An-Naml: 59-65]
በገድ የማመን አመለካከት መቀበል እምነትን የሚያበላሽ ክህደት ነው። ዒምራን ኢብኑ ሁሰይን እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፤ ‹‹ገድ ያለ ወይም እንዲባልለት ያደረገ፣ የጠነቆለ ወይም የተጠነቆለለት፣ ድግምት የሰራ ወይም እንዲሰራለት ያደረገ ከእኛ አይደለም፤ ወደ ጠንቋይ በመሄድ የሚለውን አምኖ የሚቀበል ሙሐመድ ላይ በተወረደው ክዷል፡፡››
አላህ እስከ እለተ ሞታችን በእርሱ ብቻ የምንመካ፣ ከእርሱ ብቻ የምንከጅል ትክክለኛ አማኞች እንዲያደርገን እለምነዋለው።
✍ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ
ታህሳስ 30/2015 ዓ.ል
https://t.me/abujunaidposts/466
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
ዒሳ (እየሱስ) በእየሩሳሌም
አምላክ VS የአምላክ መክዕክተኛ
ዘመንን የኃሊት በመቁጠር ከ2000 አመታት ተመልሰን እየሱስን ለካዱት የአይሁድ ፈሪሳውያን ለመሆኑ የእየሱስን አምላክነት ነው የምትክዱት ወይንስ ነብይነቱን? በማለት ጥያቄ ብናቀርብ፤
በእርግጠኝነት በጥያቄው በመገረም አይናቸውን ያቁለጨልጫሉ። ለምን ብትሉኝ፤ እየሱስን አምላክ ነኝ ሲል ሰምተውት አያውቁም!! "እየሱስ አምላክ ነው" የሚል ጥሪም ከማንም ሰው ሰምተው አያውቁም።
የዘመኑ ሰዎች አጀንዳ "ኢየሱስ እውነተኛ ነብይ ነው ወይስ አይደለም?" የሚለው ብቻ ነበር። ይህንን ለመረዳት ዛሬ በክርስቲያኖች እጅ ከሚገኘው አዲስ ኪዳን ሶስት ታሪካዊ ክስተቶችን ማቅረብ በቂ ይሆናል።
1ኛ) በማቲዮስ ወንጌል ምዕራፍ 21 አንቀፅ 10 እና 11 ላይ በወቅቱ በእየሩሳሌም ከተማ የሚኖረው መላው ህዝብ የሚያውቀው የእየሱስን አምላክነት ሳይሆን ነብይነቱን እንደነበረ በግልፅ ያሳያል። «ወደ ኢየሩሳሌምም በገባ ጊዜ መላው ከተማ ይህ ማን ነው? ብሎ ተናወጠ። ሕዝቡም፤ ይህ ከገሊላ ናዝሬት የመጣ ነቢዩ ኢየሱስ ነው አሉ» ማቲዮስ 21:10&11
የእየሱስን አምላክነት የሚሰብከው ጥሪ፤ በእየሱስ ዘመን የእየሩሳሌም ከተማ ሰዎች ዘንድ ፍፁም የማይታወቅ መሆኑ በእጅጉ ግልፅ ነው። አዎን በእየሱስ ዘመን የኢየሩሳሌም ህዝብ የሚያውቀው አምላክነቱን ሳይሆን ነብይነቱን ብቻ ነበር!
2ኛ) እንደዚሁ በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 6 እንደተጠቀሰው ኢየሱስ ወደ ገሊላ ባሕር ማዶ በተሻገረ ግዜ በጥቂት ምግብ ብዙ ሰዎች መመገብ እንዲችሉ በጌታ ፈቃድ የፈፀመውን ተዓምር ያዩ ሰዎች የመሰከሩት ነብይነቱን እንጂ አምላክነቱን አልነበረም። «ከዚህ የተነሣ ሰዎቹ ኢየሱስ ያደረገውን ምልክት ባዩ ጊዜ፤ "ይህ በእውነት ወደ ዓለም የሚመጣው ነቢይ ነው አሉ"» ዩሀንስ 6:14
ተዓምርን ሁሉ የአምላክነት መገለጫ አድርገው እንደሚያቀርቡ የዚህ ዘመን ሰዎች እንደሚሉት፤ "እየሱስ አምላክ ነው" አላሉም። ነገር ግን እውነተኛ ነብይነቱን ተረድተው መስክረዋል።
3ኛ) በሉቃስ ወንጌል ምእራፍ 7 ላይ እንደሰፈረው እየሱስ በገሊላ ምድር እየተዘዋወረ ይሰብክ በነበረበት ጊዜ በፈሪሳዊው ስምዖን ግብዣ እቤቱ በታደመ ግዜ ኃጢአተኛ የነበረችው ሴት አልቅሳ እግሩ ላይ በተደፋች ግዜ ፈሪሳዊው ስምዖን አይቶ:- «ይህስ ነቢይ ቢሆን፣ ይህች የምትዳስሰው ሴት ማን እንደ ሆነች እንዴትስ እንደ ነበረች ባወቀ ነበር፣ ኃጢአተኛ ናትና ብሎ በልቡ አሰበ» ሉቃስ 7:39
ይህ ፈሪሳዊ ያሰበውና ያሰላሰለው፤ ‘የእየሱስን እውነተኛ ነብይ መሆን ወይም አለመሆን’ እንጂ ስለ አምላክነቱ አልነበረም። ለምን ቢባል፤ እየሱስ አምላክ ነው የሚል እምነት ህይወቱን ሙሉ አልሰማም፤ በልቡም ፍፁም አላደረም።
አንዳንድ የመፅሀፍ ቅዱስ ማብራሪያዎች ላይ ይህ ፈሪሳዊ "ይህስ ነብይ ቢሆን..." ያለበትን ምክንያት ስንቃኝ ‘በዚያን ዘመን ሲነገር የነበረው የእየሱስ ነብይነት ብቻ ስለነበር ነው’ በማለት ያስረዳሉ።
አዎን! በዘመኑ እየሱስን የካዱት ሰዎች እውነተኛ ነብይነቱን አስተባብለዋል!! በዚያ ዘመን ያመኑበትም ሰዎች እውነተኛ ነብይነቱን ተቀብለዋል።
👌 ይህንን እውነታ መረዳት የእየሱስን አምላክነት ለሚያምን ሰው ከባድ ፈተና ነው። እየሱስ ያላስተማረውን እንግዳ እምነት መሰረታዊ አስተምህሮ አድርጎ ማቅረቡ ጥያቄ ውስጥ ይጥለዋል።
እኛ ሙስሊሞች ለእየሱስ ታላቅ ክብር አለን። በአምላክ ፈቃድ ብዙ ተዓምራትን ያደረገ ታላቅ የጌታ መልዕክተኛ ነብይ እንጂ አምላክ አለመሆኑን እናምናለን። ይህም የእየሱስ አስተምህሮ መሆኑ አያጠራጥርም።
የቁርአን አስተምህሮ እየሱስ ለእስራኤል ልጆች ያቀረበው ጥሪ ነብይ ነኝ የሚል እንጂ አምላክ ነኝ የሚል እንዳልነበር ያሳያል። አላህ ለህዝቦቹ ያደረገውን ጥሪ አስመልክቶ እንዲህ ይላል፤ «አላህ ጌታዬና ጌታችሁ ነው፤ ስለዚህ አምልኩት፤ ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነው» (አላቸው)፡፡ [አል ዒምራን 51]
በሌላ አንቀፅ እየሱስ አምላክ ነው የሚለው አዲስ አስተምህሮ ክህደት መሆኑን ያስተምረናል። [እነዚያ «አላህ እርሱ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ነው» ያሉ በእርግጥ ካዱ፡፡ አልመሲህም አለ፡- «የእስራኤል ልጆች ሆይ! ጌታዬንና ጌታችሁን አላህን አምልኩ» እነሆ! በአላህ የሚያጋራ ሰው አላህ በርሱ ላይ ገነትን በእርግጥ እርም አደረገ፡፡ መኖሪያውም እሳት ናት፡፡ ለበዳዮችም ምንም ረዳቶች የሏቸውም!] አልማዒዳህ 72
በመጨረሻም የእየሱስን ነብይነት ላስተባበሉት አይሁዶችም ይሁን ኃላ አምላክ ነው ላሉ ክርስቲያኖች የተላለፈውን ግልፅ ጥሪ በማስነበብ አቋጫለው። «እናንተ የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! በሃይማኖታችሁ ወሰንን አትለፉ፡፡ በአላህም ላይ እውነትን እንጅ አትናገሩ፡፡ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ዒሳ የአላህ መልክተኛ ወደ መርየም የጣላት «የኹን» ቃሉ፤ ከእርሱ የኾነ መንፈስም ብቻ ነው፡፡ በአላህና በመልክተኞቹም እመኑ፡፡ «ሦስት ናቸው» አትበሉም፡፡ ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና ተከልከሉ! አላህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ ለእርሱ ልጅ ያለው ከመኾን የጠራ ነው፡፡ በሰማያትና በምድር ያለ ሁሉ የርሱ ነው፡፡ መመኪያም በአላህ በቃ!» አን’ኒሳእ 117
ስህተትን ለማረም ጊዜው አልረፈደምና ልብ ያለው ልብ ይበል!
ሀቅን በተከተለ ሁሉ ላይ የአላህ ሰላም ይስፈን!
---------------
✍ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ
ግንቦት 16/ 2007 ዓ.ል
https://t.me/abujunaidposts/232
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
በካፊሮች በዓል እንኳን አደረሳችሁ ማለት ይፈቀዳልን?
በበአላት ሰሞን በተደጋጋሚ እገሌና እገሌ ላይክ አድርገውታል ከሚለን ፖስቶች መካከል ከፊሎቹ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክቶች ናቸው። ለጌታ መወለድ፣ ለጌታ መሰቀል፣ ለጌታ ሞቶ መነሳት (ትንሳኤና) መሰል ክስተቶች እንኳን አደረሳችሁ ሲባል ሼር ወይም ላይክ የሚያደርጉ ብዙ እህትና ወንድሞችን አስተውያለው። አንዳንዴ በስህተት ሌላ ግዜም ነገሩን እንደቀላል በመውሰድ የሚፈፀም ሊሆን ይችላል። ሆኖም እጅግ ከባድና በአኼራ ዋጋ የሚያስከፍል መዘናጋት ነው!!
በካፊሮች በአል፤ እንኳን አደረሳችሁ... እንኳን ደስ አላችሁ... እንኳን አብሮ አደረሰን ማለት እነሱን ለማስደሰትም ይሁን ለመመሳሰል ከአላህ ዲን መንሸራተት እና የካፊሮችን ኩፍር የመናገር ስነልቦና መካብ ስለሆነ
ክልክል ነው። መከባበር እና አብሮነትን ለማሳየት ከእምነታችን መንሸራተት አይጠበቅብንም። ዲን ከምንም በላይ ነውና ሸሪዓን መተላለፍ ፍፁም ጥፋት ነው!!
ፈጣሪ ወለደ ተወለደ የሚለው አስተምህሮ የጥፋትነቱ ክብደት ሰማያትንና ምድርን ሊሰነጥቅ እንደሚቀርብ ቁርአን ይነግረናል። አላህን የሚያስቆጣ ተግባር በመፈፀማቸው እንኳን ደስ ያላችሁ ማለት ከሙስሊም አይጠበቅም!!
(وَقَالُوا۟ ٱتَّخَذَ ٱلرَّحۡمَـٰنُ وَلَدࣰا * لَّقَدۡ جِئۡتُمۡ شَیۡـًٔا إِدࣰّا * تَكَادُ ٱلسَّمَـٰوَ ٰتُ یَتَفَطَّرۡنَ مِنۡهُ وَتَنشَقُّ ٱلۡأَرۡضُ وَتَخِرُّ ٱلۡجِبَالُ هَدًّا * أَن دَعَوۡا۟ لِلرَّحۡمَـٰنِ وَلَدࣰا * وَمَا یَنۢبَغِی لِلرَّحۡمَـٰنِ أَن یَتَّخِذَ وَلَدًا * إِن كُلُّ مَن فِی ٱلسَّمَـٰوَ ٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ إِلَّاۤ ءَاتِی ٱلرَّحۡمَـٰنِ عَبۡدࣰا * لَّقَدۡ أَحۡصَىٰهُمۡ وَعَدَّهُمۡ عَدࣰّا * وَكُلُّهُمۡ ءَاتِیهِ یَوۡمَ ٱلۡقِیَـٰمَةِ فَرۡدًا)
[«አልረሕማንም ልጅን ያዘ (ወለደ)» አሉ፡፡ ከባድ መጥፎን ነገር በእርግጥ አመጣችሁ፡፡ በእርሱ (በንግግራቸው ምክንያት) ሰማያት ሊቀደዱ፣ ምድርም ልትሰነጠቅ፣ ጋራዎችም ተንደው ሊወድቁ ይቃረባሉ፡፡ ለአልረሕማን ልጅ አለው ስለአሉ፡፡ ለአልረሕማን ልጅን መያዝ አይገባውም!! በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉ (በትንሣኤ ቀን) ለአልራሕማን ባሪያ ኾነው የሚመጡ እንጂ ሌላ አይደሉም]
Surah Maryam 88 - 95
ለመሆኑ አንድን ካፊር ለሀይማኖታዊ በአል እንኳን አደረሰህ ስትለው፤ ምን ማለት እንደሆነ ግልፅ አይደለምን?
እንኳን አደረሰህ...
ጌታ ተወልዶ ተሰቅሎ ሞቷል ብለህ ለማወጅ፣ ለመስቀል ለመስገድና የፈጣሪን ክብር የሚነኩ ንግግሮችን ለመናገር እንኳን በቃህ!
እንኳን አደረሰህ...
ማርያም ፈጣሪዋን ወለደችው፤ በመጠቅለያም ጠቀለለችው እያልክ ለመዘመር እንኳን በቃህ!
የኩፍር ተግባርን ለመከወን ከሆነ የደረሰው ለምንስ እንኳን አብሮ አደረሰን እንላለን?
እውቁ አሊም ኢብኑል ቀይም ረሂመሁላህ ይህ ተግባር የተከለከለ ስለመሆኑ የኡለማዎች የጋራ አቋም መሆኑን በመጠቆም እንዲህ ብለዋል፤ «ኩፍርን ብቻ በሚያንፀባርቁ የሀይማኖታቸው መገለጫዎች እንኳን አደረሳችሁ...እንኳን ደስ ያለችሁ ማለት ሀራም መሆኑ የሁሉም ሊቃውንት ስምምነት ያለበት ነው።
ለምሳሌ አንድ ሙስሊም በነሱ በዓላትና ፆም ጊዜ፤ «በአሉን የተባረከ ያድርግልህ» ወይም «መልካም የደስታ በአል ያድርግልህ» እና መሰል የደስታ መግለጫዎችን ቢያስተላልፍ፤ ተናጋሪው ከኩፍር ቢድን እንኳ ከባድ ወንጀል ነው የፈፀመው። ይህም፤ ልክ «እንኳን ለመስቀል ሰገድክ» ብሎ ደስታን እንደመግለፅ ነው!
ይህ እንደውም፤ አንድ ሰው ነብስ በማጥፋቱ፣ አልኮል በመጠጣቱ፣ ዝሙት በመፈፀሙና በመሰል ተግባራት እንኳን ደስ ያለህ ከማለት በወንጀልነት የከበደ እና አስቀያሚ ነው። ለኢስላማዊ ድንጋጌዎች ተገቢዉን ክብር የማይሰጡ ብዙ ሰዎች ይህንን ይፈፅማሉ። ምን ያክል የሚያስጠላ የግባር እንደፈፀሙም አያስተውሉም። ቢድአ፣ ኩፍር እና ወንጀሎች በመፈፀማቸው እንኳን አደረሰህ፣ እንኳን ደስ ያለህ እና መሰል የደስታ መግለጫዎችን ያስተላለፈ፤ እራሱን ለአላህ ቁጣና ጥላቻ የተገባ እንዲሆን የሚያደርግ ምክኒያት ፈፅሟል» አህካም አህሉዚማህ
የዘመናችን ፈቂህ ሸይኽ ኡሰይሚን ረሂመሁላህ እንዲህ አሉ «ካፊሮችን እንኳን አደረሳችሁ ማለት ኢብኑል ቀይም እንዳለው የዚህን ያክል ከባድ የሆነበት ምክኒያት እነርሱ የሚፈፅሟቸውን የኩፍር መገለጫዎች ማፅደቅ ስለሆነ ነው። ምንም እንኳን ለራሱ ይህንን ኩፍር መፈፀምን ባይወድም እነሱ መፈፀማቸውን ወዷልና። ሙስሊም ደግሞ የኩፍር መገለጫዎችን መውደድም ይሁን ሌሎችን እንኳን ደስ ያላችሁ ማለት አይፈቀድለትም።»
መጅሙዑ ፈታዋ ወረሳኢል አሸይኽ ኢብኑ ኡሰይሚን 3/44
በተመሳሳይ መልኩ፤ ክሪስማስም ሆነ ሌሎች በአላት ላይ ስጦታ ወይም ፓስት ካርዶችን መለዋወጥ፤ እንዲሁም ማንኛውም ደስታን መግለጫ የሆኑ ነገሮችን መፈፀም በአሉን መካፈል ስለሆነ የተከለከለ ነው!!
በዚህ ፅሁፍ መጠቆም የፈለኩት ምንም አይነት ማህበራዊ ግንኙነት ሀራም ነው የሚል መልእክት አይደለም። በተለይም ከክርስቲያን እና አይሁዶች ጋር ባለን ማህበራዊ ግንኙነቶች ላይ የተፈቀዱ ብዙ በመልካም የመኗኗር እሴቶች አሉን። ሆኖም ሀይማኖታዊ ወሰኖች የሉም ማለት አይደለም። የተፈቀደውን ስንተገብር እንደ ያልተፈቀደ ጋብቻ፣ በአላት ላይ መሳተፍ፣ ለሞቱት የአላህን ማርታ መለመንና ባጠቃላይ በዲን መመሳሰልን ግን በፍፁም አንፈፅምም። ይህንን የእምነትና የሀይማኖት ወሰን መናድ አይቻልም። ማንነታችንን ማክበር፣ ግንኙነታችንን በዲናዊ ገደቦች ማጠር ብሎም አለመሟሟት ለሌሎች ሞራል ዲንና ማንነት ከመጨነቅ ይቀድማል። ዲን ከምንም በላይ ነውና ከመሸማቀቅ እንውጣ። ይህ የዲናችን መገለጫ እንጂ እንደ ማክረርና ፅንፈኝነት የሚታይ አይደለም። በነገራችን ላይ የአንድ እምነት ተከታይ ከሌሎች ለመቀራረብ ብሎ ከራሱ እምነት ጋር የሚጣላበት ሁኔታ ድሮ ቀርቷል። ሌሎቹም ቢሆኑ ይህ በኛ ሀይማኖት አልፈቀድም እና ይቅርታ ይሉሀል።
(فَلَا تُطِعِ ٱلۡمُكَذِّبِینَ * وَدُّوا۟ لَوۡ تُدۡهِنُ فَیُدۡهِنُونَ * وَلَا تُطِعۡ كُلَّ حَلَّافࣲ مَّهِینٍ)
አስተባባዮችንም አትታዝዙ፡፡ ብትመሳሰላቸውና ቢመሳሰሉህ ተመኙ፡፡
[Surah Al-Qalam 8 - 10]
ወላሁ አዕለም
አላህ ከጥፋት ሁሉ ይጠብቀን!
____
አቡጁነይድ ረጀብ 24/1437 ዓ.ሒ / ሜይ 1/ 2016 ከጥቂት ማሻሻያዎች ጋር
https://t.me/abujunaidposts/141
👌 አጭር ወቅታዊ መልዕክት
በክሪስማስና መሰል ኢስላማዊ ያልሆኑ በዓላት ላይ መሳተፍ (Share) እናድርገው
ሙሀመድ ሀሰን ማሜ
https://youtu.be/xItMWnSa3p4
يا جامِعَ المالِ مُنذُ كانَ غَداً
يَأتي عَلى ما جَمَعتَهُ الحَرَبُ
إِيّاكَ أَن تَأمَنَ الزَمانَ فَما
زالَ عَلَينا الزَمانُ يَنقَلِبُ
إِيّاكَ وَالظُلمَ إِنَّهُ ظُلَمٌ
إِيّاكَ وَالظَنَّ إِنَّهُ كَذِبٌ
بَينا تَرى القَومَ في مَحَلَّتِهِم
إِذ قيلَ بادوا بِلىً وَقَد ذَهَبوا
يا بانِيَ القَصرِ يا مُشَيِّدَهُ
قَصرُكَ يُبلي جَديدَهُ الحِقَبُ
إِنّي رَأَيتُ الشَريفَ مُعتَرِفاً
مُصطَبِراً لِلحُقوقِ إِذ تَجِبُ
وَقَد عَرَفتُ اللِئامَ لَيسَ لَهُم
عَهدٌ وَلا خِلَّةٌ وَلا حَسَبُ
إِحذَر عَلَيكَ اللِئامَ إِنَّهُمُ
لَيسَ يُبالونَ مِنكَ ما رَكِبوا
فَنِصفُ خُلقِ اللِئامِ مُذ خُلِقوا
دُلٌّ ذَليلٌ وَنِصفُهُ شَغَبُ
فِرَّ مِنَ اللُؤمِ وَاللِئامِ وَلا
تَدنُ مِنهُم فَإِنَّهُم جَرَبُ
@abujunaidposts
ما استعبد الحرص من له أدب - ابو العتاهية - الديوان
https://www.aldiwan.net/poem10331.html
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
