Ambara - አምባራ
رفتن به کانال در Telegram
Ambara = “The High Place of Greatness” “የከፍታና የታላቅነት ስፍራ” ☞ ታሪኮች ☞ ግጥሞች ☞ ሀሳቦች ☞ የጉዞ ማስታዎሻዎች ☞ ተስፋዎች @Adwa1888 [አምባዬ ጌታነህ] ለስራ ከፈለጋችሁ ደግሞ ታችኛውን ተጠቀሙ @Rich_poet
نمایش بیشتر3 546
مشترکین
-124 ساعت
-227 روز
-6730 روز
آرشیو پست ها
3 545
ውድ የ @Ambara1 ቤተሰቦቼ 🙏
ቻናላችን ወደ ከፍተኛ ደረጃ እንዲደርስ ድጋፋችሁ ያስፈልገናል።
በዚህ ሊንክ ቻናሉን Boost በማድረግ ቻናላችንን ከፍ እናድርግ፦
https://t.me/Ambara1?boost
እያንዳንዱ ድጋፍ ቻናላችንን ወደ አዲስ ደረጃ ያደርሰዋል፣ እና ተጨማሪ አስደናቂ ባህሪያትን ይከፍታል።
ከልብ እናመሰግናለን ❤️
@Ambara1
3 545
+1
የቬትናም 🇻🇳 ጉዞ ማስታዎሻ📝
ክፍል -2-
(አምባዬ ጌታነህ)
አዲስ አበባ በሚያማምሩ የመንገድ ዳር የመብራት ባውዛዎቿ የምሽቱን ማራኪ ውበት ገልጣ አለስስት እያሳየች መንገደኛንም አሽከርካሪንም የምታማልል ኮረዳ መስላለች። ይህንን የአዲስ አበባን አዲስ መልክ ጠግበን ሳንጨርስ የተሳፈርንበት ራይድ በፍጥነት ቦሌ አለምአቀፍ የመንገደኞች መግቢያ በር አደረሰን። እንደደረስን የተጓዡን ሰው ብዛት ሳይ ሁሉም ህዝብ ከሀገር የሚወጣ ያህል ስለተሰማኝ ደነገጥኩ። "ኢትዮጵያ ማን ቀረ ታዲያ?" በማለትም ለብቻዬ አጉተመተምኩ።
የሻንጣ ጋሪውን እየገፋ ወደ ኢንተርናሽናል ተርሚናሉ የሚጋፋው ሰው ብዛት ቀላል አይደለም። የእኔ የጉዞ ጓደኞቼ አብረውን ሊሸኙን ከመጡ ወዳጆቻችንና የንግድ አጋሮቻችን ጋር አጥሩ ላይ ፎቶ ለማስታዎሻም ለሽያጭም በመነሳት ተጠምደው ሳለ። እኔ በተጓዡና በሸኚው ሰው መካከል ያለን ጥልቅ ስሜት በአርምሞ እያነበብኩና እያደመጥኩ መሀል ላይ ሻንጣዬን አስቀምጬ ቆሜያለሁ ።
አንዳንዶቹ ድጋሚ የማይገናኙ እስኪመስሉ ድረስ ለረጅም ደቂቃ ተቃቅፈው ይላቀሳሉ። ከእንደገና ቸው ተባብለው ሲያበቁ ሁለቱም ከእንደገና ዘወር ብለው ይተያዩና እንደ ህንድ ፊልም ፍቅረኛሞች ከያሉበት ይመለሱና ድጋሚ ይተቃቀፋሉ። ነገሩን ዝም ብሎ ለሚመለከት የእውነተኛ ስሜት ሳይሆን ራቅ ብሎ የሚቀርፃቸው ካሜራ ያለ ነው የሚመስለው። እነሱን አይቼ ተገርሜ ሳልጨርስ አለፍ ስል ደግሞ ትልልቅ ሄድ ሴት በጆሯቸው አድርገው ረጅም ሻንጣቸውን እየጎተቱ በሰላም የሚሄዱ መንገደኞችንም አያለሁ። ከእንደገና አይኔን በሌላኛው አቅጣጫ ሳደርግ ደግሞ በፈገግታ ታጅበው ቦታ እየቀያየሩ ፎቶ የሚነሱ ወጣቶችን እመለከታለሁ። በአጭሩ ወደ ውጪ ሀገር መግቢያ ተርሚናሉ አካባቢ አያሌ ተፅፎ የማያልቅ ትዕይንት በምሽቱ እየተከናወነ ነበር። እኔ ከሀገር ወጥቼ ስለማላቅና የመጀመሪያ የኢንተርናሽናል ጉዞዬ ስለሆነ በንቃትም በግርምትም በፍጥነትም በመደነቅም ነው ሁሉንም የምመለከተው።
እኔ እስከዛች እለት ድረስ ሰው የዛን ያህል ብዛት ወደ ውጪ የሚወጣ ሰው ያለ አይመስለኝም ነበር። ለካ እኔ አልወጣም ማለት የሚወጣ ሰው የለም ማለት አይደለም። ይገርማል!
ጉዟችንን በሚመሩን መሪዎች አማካኝነት አነስተኛና ዋና ዋና ነጥቦች ላይ ያተኮረ ኦረንቴሽን ከተሰጠንና መጠፋፋት እንዳይኖር ማስጠንቀቂያ አዘል መልዕክት ከተቀበልን በኋላ
ሻንጣችንን ይዘን መንገደኞች ወደ ሚገቡበት በር ዘለቅን። በተሰጠን መመሪያ መሠረትም አለ አይደል ልጅ ሆነን ገበያ ስንሄድ እንዳንጠፋ የእናታችንን ቀሚስ ይዘን እንደምንከተለው እኔም የቡድናችንን ታላላቅ መሪዎች የእግር ዱካ በመከተል ረጅሙን ተርሚናል ቀበቷችንና ጫማችንን እያወለቅን አንዱን ስናልፍ ሌላኛው እየተቀበለን ከብዙ ፍተሻና አድካሚ ቆይታ በኋላ አለፍን ስል ሌላ ፍተሻ ደግሞ ጠበቀን። ከቁመታችን የሚልቁ ረጃጅም ዘመናዊ የ X-Ray መፈተሻዎችን ካለፍን በኋላ የኢሚግሬሽን አገልግሎት ደረስን።
ሁላችንም በሰልፋችን ፖስፖርታችንንና ትኬታችንን በእጃችንን ይዘን የማለፊያ ፈቃድ ከሚሰጡን የመስኮት ደንበኛ መኮንኖች ፊት ቆሜ ተራዬን እየጠበኩ ነው።
ተራዬ ደርሶ ወደ መስኮቱ ጠጋ ብዬ ለአንዱ ተቆጣጣሪ ፓስፖርቴን ሰጠሁት። እሱም ፓስፖርቴን አገላብጦ ከተመለከተ በኋላ ፊቴን ደጋግሞ ተመለከተኝ። አስተያየቱ ያስፈራል። "ለመሆኑ Travel history አለህ?" ብሎ ጠየቀኝ ብዙም ስላልገባኝ ዝም ስለው የእንግሊዘኛ ዲዳ ስለመስልኩትና የተናገረውን እንዳልሰማሁት በመገመት በአማርኛ (የጉዞ ታርክ አለህ?) ብሎ ጠየቀኝ ይህን ጊዜ ፈጠን ብዬ ኮራ ጀነን ብዬ በኩራት "አዎ" አልኩት። እሱም ኮስተር ብሎ የት የት? አለኝ "አርባምንጭ ፣ ላሊበላ! ሰውዬው አላቆመም ቀጠላና ሌላስ ሲለኝ "ኮምቦልቻም ሄጃለሁ "ስለው። አጠገቡ የነበረው ሌላኛው ተቆጣጣሪ "ትቀልዳለህ"ብሎ ኮስተር አለ። "ኧረ ማርያምን የምሬን ነው አልኩት" አጠገቤ የነበሩት ጓደኞቼ መቆም አቅቷቸው በድካም እስኪቀመጡ ድረስ ነው የሳቁት! እኔ እኮ ብዙ ጊዜ አርባምንጭ ስመላለስ በጣም ነበር የተጎረርኩት። የጊቢ ጓደኞቼ ላይ እንዴት መልክ እንደሰራሁ እኔ ነኝ የማቀው።አሁን ግን አልገባኝም። በዚህ መሀል አንዱ ከመካከላችን ያለ ይህን ጥያቄ ቀድሞ የተጠየቀው ጓደኛዬ በግራ መጋባት የመለስኩት እንደሆነ ስለገባው "አይ ይህ የመጀመሪያ ጉዞው ነው ከዚህ በፊት ከሀገር ወጥቶ አያቅም ዋልያ ነው" ብሎ በቀልድም መልክ እውነቴን ተናገረ። በዚህ ጊዜ ነው የጉዞ ታሪክ ከሀገር ውጪ የሆነ በረራ እንደሆነ የገባኝ እንጂ በአውሮፕላን የተሳፈረ ሁሉ ትራቭል ሂስትሪ አለው ማለት እንዳልሆነ ተረዳሁ። ከዛም እሱን በጉዞ አዘጋጆቻችን አማካኝነት ጨራርሰን የምንበርበትን ሰአት መጠባበቅ ጀመርን።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ስሙ ለምን በ ባለም አቀፍ ዝነኛ እንደሆነ የገባኝ በዚህ ጊዜ ነበር። እጅግ ዘመናዊ የሆነ የአቬሽን ስርአት ያለው አየር መንገዱም ጥራቱን የጠበቀ መሆኑን እያስተዋልኩም ነበር። በ ውስጡ ሌላ ከተማ ያለ እስኪመስል እጅግ በርካታ እንቅስቃሴዎች ያሉበት ሱቅና ካፌዎች ተከፍተው በሞቀ ገበያ ውስጥ መሆናቸውን ለሚያይ የአየር መንገድ ውስጥ ያለን ሳይሆን መርካቶ ላይ ያለን ነው የመሰለኝ። እጅግ ፅዱና ማራኪ እይታዎች የተሞሉበት፣ የመንገደኛ መተላለፊያ የደረጃ አሳንሱሮቹ ፅዳት፣ ፈጣን አገልግሎት የሚሰጡበት የአየር መንገዱ ሰራተኞች ለቀልጣፋ አገልግሎት የሚሰጡት ስብዕና ጎንበስ ቀና በማለት በትህትና የሚያናግሩበት ስርአት ሰዎች ከወዲያና ከወዲህ የሚንሸራሸሩበት አያሌ እንቅስቃሴዎች የተሞሉበት ነው። እኛ እንድንጠብቅ በተነገረን የመጠበቂያ ቦታ ተቀምጠን እስክንጠራ ዙሪያ ገባውን በጥሞና እየተመለከትኩ ነው ። በመጨረሸ መዳረሻችን ሲጠራ ትኬታችንን እያሳየን የመጨረሻውን የማለፊያ በር በድል አልፈን ወደ አውሮፕላኑ የሚወስደን ባስ ውስጥ ገባን። ከተወሰኑ ደቂቃ ጉዞዎች በኋላ መነሻውን ቦሌ አዲስ አበባ መዳረሻውን ደግሞ ቬትናም ሀኖይ ወዳደረገው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት ወደ ሆነው ET 637 የአውሮፕላን ቁጥር ደረስን።
ይቀጥላል.....
ክፍል 2 ን እንዴት አገኛችሁት ሀሳባችሁን አስቀምጡልኝ እንዲሁም በጉዞ ወቅት የተመለከታችሁት ነገርስ ምንድነው ?! የመጀመሪያ ከሀገር ውጪ በረራችሁ መዳረሻውስ የት ነበር?! @Rich_poet
ይህ የጉዞ ማስታዎሻ ለብዙ ሰው እንዲደርስ ሼር እንድታደርጉልኝ በትህትና እጠይቃለሁ።
@malefia
@malefia
3 545
+1
የቬትናም 🇻🇳 ጉዞ ማስታዎሻ📝
ክፍል -1-
(አምባዬ ጌታነህ)
ፀሐይ በምዕራብ ሰማይ ስር እየወረደች የሰማይን ቀለም በቀይ ፣ በብርቱካናማና በወርቃማ ቀለሞች የተቀባ ውብ ስዕል ስታስመስል ፤ ባህሩ ደግሞ እነዚህን ውብ ቀለሞች ተቀብሎ ሲያንፀባረቅ የመርከቡ አናት ወንበር ላይ ተቀምጬ ስመለከት ልቤ ወደ ሌላ ዓለም ተጓዘ።
የምሽቱ ጨለማ በእርጋታ እየተሸፈነ፣ አየሩ እየቀዘቀዘ ፣ የባህሩ ሽታ ከነፋሱ ጋር ተቀላቅሎ የሚሰጠውን የተፈጥሮ ሽታ በአፍንጫህ እየማግህ፤ በመርከቡ ቀላል እንቅስቃሴ እንደልብህ እያሰብህ ቀስ በቀስ ወደ መንፈስ መነጠቅ መግባት። በዚያ ከሀሳብ ጫና ርቀህ ከእንደገና ወደዋናው የተፈጥሮ ማንነትህ የምትመለስበትና የምትገናኝበትን መስመር ተፈጥሮ ራሷ ትሰጣለች።
ይህ እየሆነ ደግሞ ለሊቱ የውበቱን መጋረጃ ይከፍትና በከዋክብት የተሞላውን ሰማይ እያንዳንዱ ኮከብ የሚያወጡትን የእሳት ራት መሳይ ትንሽ ብርሃን ከታች ያለው ባህር ተቀብሎ በባህሩ እያንፀባረቀ ሰማይና ውሃ አንድ ሆነው የሚፈጥሩት የማይሰማ የማይወራ በዝምታና በማየት ብቻ የሚደመጥ ውብ ጥበብን እነሆ ሲሉ ይታያሉ። የውሃው ለስላሳ ምት ፣ የለሊቱ ዝምታ ፣ አንድ ላይ ተቀላቅለው ደግሞ በጆሮ ተንቆርቁሮ ነፍስ ላይ እንደሚዘልቅ ሙዚቃ ይሰማሉ። የሰው ልጅ ሆኖ ከዚህ በላይ ስጋውን የሚያሳርፍበት፣ ከድካም ገለል የሚልበት ፣ ልቡን የሚያረጋጋበት ፣ የአእምሮውን የፈጠራ አቅም የሚፈትሽበት ፣ አስተሳሰቡን የሚያበራበት ፣ ሕይዎቱን ከእንደገና ለማስተዋል የሚመርጠው የተሻለ ቦታ ሌላ የት ይኖራል?!
ጨረቃ በባህሩ ላይ ተፈጥሯዊ ነፃነቷን ተጠቅማ በብርሃኗ ለመርከቡ መንገድ ሰርታ ኮምፓስ ስትሆን ፣ እንደ ተፈጥሮ የተዘጋጀ መንገድ ስትመስል ፣ መርከቡ በዚያ መንገድ ላይ እየተጓዘ መመልከት መቻል ና በእንዲህ አይነት ምሽት ውስጥ ራስን ማግኘት በህልም ውስጥ ያለ የህይዎት ቅኝት ውስጥ ያስመስላል። የተከፈተው ዐይን የሚያየውን ውብ ዓለምም ለመቀበል የውስጥን ዕምነት ይፈትሻል። ምክንያቱም እዚህ ስዓት ይቆማል ሐሳብም በተፈጥሮ እየፀዳ አእምሮም እንደሚያየው አረንጓድ የተራራ ላይ ኩታ መለምለም እያማረው ከተፈጥሮ ጋር በጥልቅ እየተገናኘ ወደፊቱን ከትላንት በተላቀቀ ንፁህ ማንነት እየፈጠረ አምላኩን ከልብ በመነጨ ንፁህ ፍቅር እያመሰገነ ስለሚያኖር።
አምባዬ ጌታነህ ✍️
መስከረም 6/2018 ዓ.ም
Vietnam🇻🇳 Halongbay
ለዚህ ፔጅ አዲስ የሆናችሁ ፔጄን Subscribe አድርጉና ድርሰቶቼ ይድረሳችሁ። ከላይ ያለውን የጉዞ ማስታዎሻስ ከ 10 ስንት ነጥብ ትሰጡታላችሁ?
እንኳን
✍በአምባዬ ጌታነህ
@malefia
@malefia
@malefia
Join🔗 & Share➡️📇
ስለጉዞው ማስታዎሻ ያላችሁን ከ 10 ነጥብ
📨 @Rich_poet በዚህ ዩዘርኔም አስቀምጡልኝ
3 545
#መርጦ_መራመድ
※
✍️አምባዬ ጌታነህ ( @Richpoet1 ⚡️)
.
አዬህ ...
ከሃሳብህ ዘግነህ ~ በቃል የዘራኸው
በዓለም ልዩ ሚስጥር
እንደ ሼማ ክሮች ~ ተፈትሎ ተፈትሎ
በጊዜ ዑደት ውስጥ
ስጋ ለብሶ መጣ ~ ‘ሂ‘ወትህ ነኝ’ ብሎ!
…
በዓለም ዕልፍኝ ሳለህ
የሚያሰጋህ ቢኖር
ነፍስን ነው መሞገት ~ ራስን ነው መፍራት፣
የማታ የማታ
አይቀልህምና ~ ማጨድ እንደ መዝራት
በምርጫህ ነው ማትረፍ...
የሃሳብህ ቅኝት
ሁሌም በቀኝ ይሁን ~ ሁሌም ወደ መልካም፣
ጊዜ ዥንጉርጉር ነው
በወጡበት ስሜት ~ መውረድ አይለካም!
…
አሁን ለምሳሌ...
ብዙ የሆንክለት
የጉዞህ ኦሜጋ
እንክርዳድ ቢበዛው የድካምህ ፍሬ
‘እጄ አመድ አፋሽ ነው’ ~ ከማለትህ በፊት
በጥሞና መርምር
‘አመድ’ ሃሳብ ነበር
ሳያጠል ያለፈው የህሊናህ ወንፊት።
…
ስለዚህ ወዳጄ
እስኪ ዕድሉን ስጣት
የመልካም መንገድን
ከልቦናህ ጋራ ~ ነፍስህ ትነጋገር፣
ማለፊያ ሚሆንህ
ድልድይ ብታገኝም
ባልተጠና እርምጃ ~ አይቀልም መሻገር።
፨
@malefia
@malefia
@malefia
3 545
ቆይ በኋላ ማለት
ቆይ ለነገ ማለት ለምን አስፈለገ፣
በምን ይታወቃል
ማን እንደሚቀድም ከእኛና ከነገ።
@malefia
@malefia
@malefia
Join🔗 & Share➡️📇
Comment
📨 @Richpoet1
3 545
በእምነታችንበፈጣሪ ፈቃድ የሙሴ ብትሩ ባህርን ገመሰ በአንዲት ወንጭፍ ጠጠር በዳዊት ፊት ወድቆ ጎልያድ አነሰ። አዎ! ባህሩም ተገምሷል ጎልያድም ወድቋል ግን ምንድን ልልህ ነው የሙሴ ብትሩ ባህር ምን ብትገምስም አትበልጥም ከሙ፣ ጎልያዶች ሁሉ በእምነታችን እንጂ በጠጠር አይወድቁም ትልሀለች ነፍሴ። @malefia @malefia @malefia Join🔗 & Share➡️📇 Comment 📨 @Richpoet1
3 545
ያ.....ልፋ.....ል! ( ያልፋል )
በአምባዬ ጌታነህ💰
የሕይወትህ መርከብ
በማዕበል ሲናጥ በወጀብ ሲፈተን
ሀያል ነጎድጓድ ድምፅ በአይምሮህ ሲበተን
፡
ያን የጭንቀት ምሽት በህልምህ ቀዝፈኸው
የድልህን ዜማ
በተስፋ ብዕርህ "ያልፋል" ብለህ ፃፈው።
@malefia
@malefia
@malefia
Join🔗 & Share➡️📇
Comment
📨 @Richpoet1
3 545
🦋ፊዮር🦋
በ አምባዬ ጌታነህ✅
፡
የት ቦታ በምን አመክንዮ መፍገግ እንዳለባት ታውቃለች! ህይወት ለእሷ ሳቅን በረከትን በመትረፍረፍ የምታድላት ውብ ሴት ነች። ባገኘኋት ቁጥር ከሳቅና ከደስታ ከሙላትና ከበረከት ውጪ የምታውቀው ቃል የለም! ምስጋናዋ አያልቅም። የምታመሰግንበት ምክንያት ብዙ ነው። ብዙ ነገሯ ለየት ያለ ነው። ታውቂያለሽ ልዩ ሴት እኮ ነሽ ስላት! ፈገግታዋን እስከ አፅናፍ ዓለም ትለግሰኝና
ልዩ አድርጎ በምክንያት የፈጠረኝ ልዑል እግዚአብሔር ይመስገንትለኛለች! አበቦችን አብዝታ የምትወደው ናታይ ፊዮር! ስሟም አበባ ማለት አይደል! የሆነ አብሯት የሚመጣ ሰላምማ አለ። እርጋታንና ጥሞናን አላብሳ ስጋን ከነብስ የምታስታርቅ ሰው! በአረንጓዴ የተከበበ ጫካ ላይ የተሰሩ ቅንጡ ቤቶች ልቧን በሀሴት የሚወስዷት ናታይ ፊዮር የከተማ ጫጫታ ያመነናት ሴት ያስመስላታል። ይህ ከተፈጥሮ ጋር አለፍ ያለ ፍቅሯን ባየሁ ጊዜ እጄን አፌ ላይ ከመጫን ያለፈ አንዳች ቃል ማውጣትን አፌ ይሰንፋል! ከእርሷ ጋር ውቡ መግባቢያ ብቸኛው ነገር ፈገግታና ሳቅ ብቻ! ድካምንና መሰልቸትን የምታስረሳ ፍጡር! "ናታይ ፊዮር" እርሷ በሳቀች ጊዜ ዓለም ሀሴትን ትጎናፀፋለች። እርሷ ፈገግ ስትል ዓለም የመከፋት ዘመኗ ያበቃል። እርሷ ስታመሰግን እግዜር ቸርነትንና ምህረትን ለዓለም ያድላል! ሁሉም ነገር እርሷ ጋር አሁን ይሆናል! የሰውን ልጅ ዕድሜ በሰላም የምታረዝሜ የልቤ ሰው ናታይ ፊዮር! ማለፊያ ውብ ታሪኮችን የሰበሰበች ማህደሬ ነችና እየተወዳጃችሁም ለሌሎችም እያጋራችሁ! @malefia @malefia @malefia Join🔗 & Share➡️📇 Comment 📨 @Richpoet1
3 545
ፊዮር
በሳቋ የሚለመልሙ አእላፍ የነፍስ እፀዋቶች አሉ። ስትስቅ ሁሉንም ነገር የምታስረሳ ደግ ልባም ሴት ናት። አብዝሀኛውን ጊዜ ከአእምሮዋ ይልቅ ልቧን የምትሰማ በጎ ነገሮችን የምታዳምጥ ህይዎትን ቀለል አድርጋ በእያንዳንዱ ሰከንድ የምትስቅ የምትደሰት ልጅ ናት። ብዙ ሰዎች ከእርሷ ጋር ሲያወሩ የጠፋባቸውን ደስታ ሰላም ውሳጣዊ ሀሴት ያገኙታል! እርሷ ሁልጊዜ በሳቋ ያበበች በምትጠቀማቸው ቃላቶች ነፍስ የምትዘራ ቆንጆና አስተዋይ ልጅ ናት! ናተይ ፊዮር ትባላለች! ትርጉሙም የኔ አበባ ማለት ነው።ናተይ ፊዮር አዲስ አበባ እትብቷ የተቀበረ ነገር ግን ነፍሷ በዓለም በውብ ከተሞች የተሳሰረ በሀሳብም በስሜትም የተራቀቀች በሀያዎቹ መጀመሪያ የእድሜ ክልል ላይ የምትገኝ አስደሳች ህይዎትን ለመኖር በራሷ ወስና በ እያንዳንዱ ነገር ዘና በማለት ህይዎትን ቀለል አድርጋ የምትኖር ባለ ደግ ልብ ነች! ፊዮር በውስጧ ባስቀመጠችው ውብ ዓለም የምትኖር ነገሮችን ቀለል አድርጋ የምትመለከት ልቧ ለመልካም ነገሮች ብቻ ክፍት የሆነ ፣ ጆሮዋ ተፈጥሮን ከነ ገፀ በረከቶቿ የሚያዳምጥ ዐይኖቿ ጨረቃን ከነ ደቀመዝሙሮቿ ከዋክብት በምሽት የአምላክን የሰማይ ላይ ገቢረ ተውኔት በመመልከት ሀሴት አድርጋ ቀስ ብላ ትንፋሿን ወደ ውስጥ በመሳብ በእርጋታ ታስወጣለች! በዚህን ጊዜ በዐይነህሊናዋ የምትፈልጋቸውን ተጨማሪ አስደሳች ታሪኮችን እየፈጠረች ታስገባለች! ፊዮር የራሷን ህይዎት በእራሷ በመፃፍ የምትታወቅም ልጅ ናት።
ለመደሰት ቻናሉን ጆይን ያድርጉ ለማስደሰት ደግሞ ሼር በማድረግ በቅንነት ያዳርሱ
👇👇👇👇👇
@malefia
@malefia
@malefia
Join🔗 & Share➡️📇
Comment
📨 @Richpoet1
3 545
ፀሐይ ቀይ ሐምራዊ ሆና ወደ መጥለቂያዋ ስታሽቆለቁል በፈገግታ እየተመለከተ "እኔምልሽ ፂዮን "አለ "ወይዬ ባሩክ" አለች በፈገግታዋ ወጋገን ፊቱን በደስታ እያለበሰች። "አያሌ ምሽቶችን በደስታ አሳልፈናል። ጊዜን በፍቅራችን ሚዛን አስቀምጠን በህልሞቻችን ማዳወሪያ አዳውረን አሁን ያለንበትን ጊዜ ሳስብ እነዚያን ከአንቺ ጋር ያሳለፍኳቸውን ውብ ዘመናት፣ አሁን የምንኖረውን ሳይ ህይዎትን አብዝቼ እወዳታለሁ። አንቺ በህይዎቴ ውስጥ ስላለሽ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ! አማካሪዬም ስጦታዬም ስለሆንሽ በህይዎቴ ሙሉ እንድሆን አድርገሽኛል" አለ። የቃላቶቹ ስድር የነፍሱን መሻት ለመግለፅ እንደሚታትሩ የምር ያስታውቅበታል። ከልቡ እንደሚያወራት አይኖቹ ጭምር ይነግሯታል። "እግዚአብሔር ረድቶናል። አንተም መልካም ልብ ያለህ፣ ጊዜን የምትረዳ በየቀኑ ምን ማድረግ እንዳለብህ የምታውቅ ለህይዎት ያለህ መልካም አስተሳሰብ ለእኔ ያለህ ትልቅ አክብሮትና ፍቅር ስለህልሞቻችን አብዝተህ የምታስበው ሁሉ ውጤት ነው። እናም በጋራ እግዚአብሔርን ከፊታችን በማስቀደም እዚህ ደርሰናል። ታስታውሳለህ ጅማሪያችንን አንድ ጊዜ እንዲህ ብለኸኝ ነበር "' ሞትና ጊዜ የሚባሉ መልህቆች በህይዎታችን ያስፈልጉናል።ለማያልቅ ምግብ የሚስገበገብ ሰው አይኖርም! በወንዝ ውስጥ ያለ ዓሳም ውሃ ብርቁ አይሆንም።ጊዚያችንም እድሚያችንም ዋጋ ካጣ ለመኖር ያለን ፍላጎት ይረግባል። የሚያኖረንም ፍርሃታችን ብቻ ይሆናል። የእያንዳንዱ ቀን ማለፍ የተሻለ ነገን እንድናለም የሚያደርገን ካልሆነ ምንም ያላደረግንበት ትላንት ተመልሶ ዛሬ ከሆነ የመኖራችን ትርጉም ታዲያ ምኑ ላይ ነው? "' ብለኸኝ ነበር! አለች ፂዮን ባሩክ በሀሳብ ወደ ኋላ ተመልሶ ራሱን በአዎንታ አወዛወዘላት። "ታውቃለህ ይህንን አሁን የምንኖረውን ህይዎት ቀድመህ አንተ ታውቀው ነበር። ሁሌም እዚህ እንደምንደርስ ይህን ስኬት እንደምናሳካ እርግጠኛ ነበርኩ። ምክንያቱም ስታወራ ዐይኖችህን አይ ነበር ቃላቶችህ ተስተካክለው ነበር የሚወርዱ፤ ፍፁም በሆነ በራስ መተማመን ነው የምትነግረኝ ሁሌም አመሻሽ ላይ ልንተኛ ስንል በቃልህ ትነግረኝ ነበር። እና እሱን ድምፅህን እየሰማሁ ነበር የምተኛው እናም ደስ ብሎኝ በሀሴት ውስጥ ሆኜ ነው እንቅልፍ የሚወስደኝ" አለችና አቀፈችው። ባሩክ በፈገግታ ተመለከታት። ይቺን ምድር ፈጣሪ የሰጠን እንደፃፈነው እንድንኖርባት ነው። ህይዎት ውብ መዓዛ ያላት ዐደይ! ነች። ሰርክ በእኛ የልብ ወር ላይ የምትበቅል! ነፍሳችንን የምታስውብ! የዘመናችን ሁሉ ፍስሃ ነች። አዎ ህይዎት የመረጥነውን የምትመግበን የሞሰብ ቡፌ ናት። ህይዎት ምርጫም ናት ውብም ናት! "አለና ከተቀመጡበት ተነስተው ወደ የግል መርከባቸው በእርጋታ ገቡ። ሐይቁ የፀሐይን መልክ በቀለበት መስሎ አንዳች ትርኢት የሚያሳይ ውብ ገፅታን ተጎናፅፏል። የውቅያኖሱ ዳርቻዎች በአሸዋቸው የተዋቡ መልከዐምድርን በምሽት ያንፀባርቁ ጀመር። "እዚህ ዓለም ሌላ መልክ አላት የኔ ፂዮን"አለ ባሩክ! "ከአንተ ጋር ሲሆን ደግሞ ሌላ ውበት ነው "ብላ አንገቱ ስር ሽጉጥ አለች። የምሽቱ ነፋስ በጆሯቸው ሌላ የህይዎት ብስራት መልዕክት የያዘ ይመስል በተደጋጋሚ በጆሯቸው በእርጋታ እያንሾካሾከ ያልፋል! ባሩክና ፂዮን በመርከቡ አናት ላይ ተቃቅፈው የውቅያኖሱን የምሽት መልክ አይኖቻቸውን ከደን ከፈት እያደረጉ እጆቻቸውን አልፎ አልፎ እየዘረጉ አንዳንድ ጊዜም እየተቃቀፉ አልፎ አልፎ እየተቀመጡ በአንታሊያ ሀይቆች ይዝናኑ ጀመር!! አንታሊያ የቱርኮች ምልክት አንታሊያ ውብ ምድር! ታሪክም ፍቅርም ተፈጥሮም ሀሴትም የሚገኝባት የቱርኮች ገፀበረከት! መዝናናት በጣም ደስ ይላል! ፍቅርም በመዝናናት ይታደሳል ህይዎትም በመዝናናት ሌላ እድሜ ይጨመራል! የሰው ልጅ ሲዝናና ነው ትክክለኛ ማንነቱ የሚታወቀው" ብሎ ባሩክ የዕለት ማስታዎሻው ላይ ፃፈ!
@malefia
@malefia
@malefia
Join🔗 & Share➡️📇
Comment
📨 @Richpoet1
3 545
3 545
የዓለም ሁሉ መድህን
ደሙ ያረፈበት
የክርስቶስ መስቀል አፈር ትቢያ ለብሶ
ተራራን አክሎ
ከዘመናት ኋላ በንግስት እሌኒ እስኪገኝ ተምሶ።
መስቀል ምን ነበረ?
ጥበበኛ ንግስት
ቃል አክባሪ ንግስት
እንጨቱን ደምራ በእጣን ጭስ ተመርታ
በአምላክ ጠቋሚነት
በእርሱ ፈቃድነት መስቀሉን አግኝታ
ያየው ሁሉ እንዲድን
ወስዳ አስቀመጠችው
አስገንብታ መቅደስ ወደ ጎለጎታ!
እሰይ እሰይ እሰይ
የዓለም ሁሉ ፀጋ የዓለም ሁሉ ሲሳይ
(እሰይ እልል በሉ
ዓለም መፅናኘውን
ዓለም መዳኛውን
አግኝቷል መስቀሉን!
እሰይ እልል በሉ
ከአልማዞች የሚልቅ
ከከበረው ሁሉ
ትልቁ የሰው ሀብት
ተገኝቷል መስቀሉ!
እሰይ እልል በሉ!!
እፎይ ማረፊያችን
ተገኘ መስቀሉ!!
አምባዬ ጌታነህ!
በሀገር ውስጥ ከሀገር ውጪም የምትኖሩ የክርስትና ሀይማኖት እምነት ተከታይ ወገኖቼ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ!
@malefia
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
