cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

መዝሙረ ማኅሌት ቁ፩ ¶ቻናል

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤት የሚከናወኑ ተግባራቶች አስመልክቶ ቆየት ያሉ ያሬዳዊ ዝማሬ በሰንበት ትምህርት ቤት ውስጥ ፣የሰንበት ት/ቤታችን ወቅታዊ ትምህርቶና የቤተክርስቲያን ወቅተዊ ጉዳዮችን ለማግኘትና ለመማማር @zemariann ይቀላቀሉን፡፡ ለማንኛውም አስተያየት @mzbot_bot

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
15 363
مشترکین
-224 ساعت
-217 روز
-15230 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

††† እንኳን ለታላቁ ነቢይና ሰማዕት ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። ††† ††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!††† ††† ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ††† ††† ቅዱስ ወንጌል ላይ ከእመቤታችን ቀጥሎ የነ ዘካርያስን ቤተሰብ ያህል ክብሩ የተገለጠለት ፍጡር ይኖራል ብሎ መናገሩ ይከብዳል:: ቅዱስ ሉቃስ ወንጌሉን የጀመረው በዚህ ቅዱስ ቤተሰብ ነውና መንፈስ ቅዱስ እንዲህ ሲል አጽፎታል:: "ዘካርያስ ካህኑና ቅድስት ኤልሳቤጥ በሰውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ" ይላቸዋል:: (ሉቃ. 1:6) *የሰውን እንተወውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ መኖር ምን ይረቅ? ለዚህ አንክሮ (አድናቆት) ይገባል! እሊህ ቅዱሳን ባልና ሚስት ግን መካኖች በመሆናቸው ልጅ ሳይወልዱ ዘመናቸው አልፎ ነበር:: እንደ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት ዕድሜአቸው የኤልሳቤጥ 90 የዘካርያስ ደግሞ 100 ደርሶ ነበር:: *ፍጹም መታገሳቸውን የተመለከተ ጌታ ግን በስተ እርጅናቸው ከሰው ሁሉ በላይ የሆነ: ትንቢት ለብቻው የተነገረለት (ኢሳ. 40:3, ሚል. 3:1) ታላቅ ነቢይን ይሰጣቸው ዘንድ መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልን ላከላቸው:: *ቅዱስ ዘካርያስ ሰው ነውና ከደስታ ብዛት በመከራከሩ ድዳ ሆነ:: ቅድስቲቷ ግን መስከረም 26 ቀን ታላቁን ሰው ጸንሳ ለ6 ወራት ራሷን ሠወረች:: በ6ኛው ወር የፍጥረት ሁሉ ጌታ በተጸነሰ ጊዜ የአርያም ንግሥት ድንግል እመቤታችን ደጋ ደጋውን ወደ ኤልሳቤጥ መጣች:: ሁለቱ ቅዱሳት የእህትማማች ልጆች ናቸው:: *የአምላክ እናቱ ስትደርስና "ሰላም" ስትላቸው መንፈስ ቅዱስ በእናትና ልጅ ወርዶ ኤልሳቤጥ በምስጋና: ዮሐንስ ደግሞ ገና በማሕጸን ሳለ በደስታ ዘለለ (ሰገደ):: ከዚህ በሁዋላ ሰኔ 30 ተወልዶ: አባቱ ዘካርያስ "ዮሐንስ" ሲለው አንደበቱ ተፈትቶለታል:: *ቅዱስ ዮሐንስ ከተወለደ 2 ዓመት ከ6 ወር በሆነው ጊዜ ሰብአ ሰገል በመምጣታቸው በእሥራኤል ምድር የሚገኙ ሕጻናትን ሔሮድስ ቁዝ አስፈጀ:: ትንሽ ቆይቶም አይሁድ ለሔሮድስ ስለ ቅዱሱ ሕጻን ነገሩት:: "ሲጸነስ የአባቱን አንደበት የዘጋ: ሲወለድ ደግሞ የከፈተ 'ዮሐንስ' የሚባል ሕጻን አለና እሱንም ግደል" አሉ:: *እናቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ ይዛው ስትሸሽ ካህኑን ዘካርያስን ግን በቤተ መቅደስ መካከል ገድለውታል:: አረጋይት ኤልሳቤጥም ሕጻኑን እያሳደገች በገዳመ ዚፋታ ለ3 (5) ዓመታት ቆይታለች:: ቅዱስ ዮሐንስ 5 (7) ዓመት ሲሞላው ግን እዚያው በበርሃ እናቱ ዐረፈች:: ከሰማይ ዘካርያስና ስምዖን ወርደው ቀበሯት:: *ሕጻኑ ዮሐንስ ሲያለቅስ ድንግል ማርያም ስንት አገር አልፋ ሰማችው:: እርሷም ስደት ላይ ነበረችና:: ከጌታ ጋር በደመና ሒደው ድንግል አቅፋ አጽናናችው:: ጌታንም "እንውሰደው ይሆን?" አለችው:: ጌታችን ግን "ለአገልግሎት እስክጠራው እዚህ ይቆይ" አላት:: ባርካው: አጽናንታውም ተለያዩ:: *ቅዱስ ዮሐንስ ከዚህ በሁዋላ በዚያ ቆላ የግመል ጠጉር ለብሶ: ጠፍር ታጥቆ ተባሕትዎውን ቀጠለ:: ለ25 (23) ዓመታትም በንጽሕና ሲኖር ከምድር አራዊትና ከሰማይ መላእክት በቀር ማንንም አላየም:: ይሕችን ዐመጸኛ ዓለምም አልቀመሳትም:: *ከዚህ በሁዋላ 30 ዘመን ሲሞላው እግዚአብሔር ከሰማይ ተናገረው:: "ሒድ! የልጄን ጐዳና ጥረግ" አለው:: ነቢያት ስለዚህ ነገር ተናግረው ነበርና:: (ኢሳ. 40:3, ሚል. 3:1) አባቱ ዘካርያስም "ወአንተኒ ሕጻን ነቢየ ልዑል ትሰመይ: እስመ ተሐውር ቅድመ እግዚአብሔር ከመ ትጺሕ ፍኖቶ" (ሉቃ. 1:76) ብሎ መንገድ ጠራጊነቱን ተናግሮ ነበርና:: *ቅዱስ ዮሐንስ በዚያ ጊዜ በኃይለ መንፈስ ቅዱስ እየገሰገሰ ከበርሃ ወደ ይሁዳ መጣ:: ያዩት ሁሉ ፈሩት: አከበሩት:: ቁመቱ ቀጥ ያለ: ጽሕሙ እንደ ተፈተለ ሐር የወረደ: ጸጉሩ የቁራ ያህል የጠቆረ: መልኩ የተሟላ: ግርማው የሚያስፈራ ገዳማዊ ነውና:: *ፈጥኖም ሕዝቡን ለንስሃ ሰበከ: ለንስሃም በርካቶችን አጠመቃቸው:: በዚህ አገልግሎት ለ6 ወራት ቆይቶ ጌታችን ወደ እርሱ ዘንድ መጣ:: ዮሐንስ ሰማይን ከነግሱ: ምድርን ከነልብሱ የያዘ ፈጣሪ "አጥምቀኝ" ብሎ ሲመጣ ደነገጠ:: የሚገባበትም ጠፋው:: *"እንቢ ጌታየ! አንተ አጥምቀኝ" አለው:: ጌታ ግን "ፈቅጄልሃለሁ" አለው: አጠመቀው:: በዚህ ምክንያት ይሔው እስከ ዛሬም "መጥምቀ መለኮት" ሲባል ይኖራል:: ቅዱስ ዮሐንስ በመጨረሻ ሔሮድስን ገሰጸው:: ንጉሡም ተቀይሞ ለ7 ቀናት አሠረው:: *ልደቱን ባከበረ ጊዜ ወለተ ሔሮድያዳ በዘፈን አጥምዳ አስማለችው:: እርሱም የታላቁን ነቢይ ራስ አስቆርጦ በወጪት አድርጐ ሰጣት:: አበው "እምሔሶ ለሔሮድስ ይብላዕ መሐላሁ - ሔሮድስ መሐላውን በበላ በተሻለው ነበር" ይላሉ:: የቅዱስ ዮሐንስ ራሱ በርራ ስትሔድ አካሉን ግን ደቀ መዛሙርቱ ቀብረውታል:: (ማቴ. 3:1, ማር. 6:14, ሉቃ. 3:1, ዮሐ. 1:6)*ርጉም ሔሮድስ አንገቱን ካስቆረጠው በሁዋላ የመጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ ራሱ የጸጋ ክንፍ ተሰጥቷት ጌታችን ወዳለበት ደብረ ዘይት ሔዳ በፊቱ ሰገደች:: ቅዱሳን ሐዋርያት በአዩት ነገር ተገርመው ራሱን እጅ ነሷት:: *ከዚሕ በሁዋላ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱስ ዮሐንስ ራስ የማስተማር ስልጣን ሰጥቶ አሰናበታት:: በመላው ዓለም ለ15 ዓመታት ስትሰብክ ኑራ ዓረቢያ ውስጥ ዓርፋለች:: ††† አስማተ-ዮሐንስ መጥምቅ (የመጥምቁ ዮሐንስ ስሞች) 1.ነቢይ 2.ሐዋርያ 3.ሰማዕት 4.ጻድቅ 5.ካሕን 6.ባሕታዊ/ገዳማዊ 7.መጥምቀ መለኮት 8.ጸያሔ ፍኖት (መንገድ ጠራጊ) 9.ድንግል 10.ተንከተም (የብሉይና የሐዲስ መገናኛ ድልድይ) 11.ቃለ አዋዲ (አዋጅ ነጋሪ) 12.መምሕር ወመገሥጽ 13.ዘየዐቢ እምኩሉ (ከሁሉ የሚበልጥ) ††† ጌታችን መድኃኔ ዓለም መጥምቁ ዮሐንስን አስቦ ይቅር ይበለን:: ጸጋውን: በረከቱንና ክብሩንም ያሳድርብን:: ††† "ጌታ ኢየሱስ ለሕዝቡ ስለ ዮሐንስ ሊናገር ጀመረ . . . ምን ልታዩ ወጣችሁ? ነቢይን? አዎን እላችሁአለሁ ከነቢይም የሚበልጠውን . . . እውነት እላቹሃለሁ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሳም . . . ነቢያት ሁሉና ሕጉ እስከ ዮሐንስ ድረስ ትንቢት ተናገሩ:: ልትቀበሉትስ ብትወዱ ይመጣ ዘንድ ያለው ኤልያስ ይሕ ነው:: የሚሰማ ጀሮ ያለው ይስማ::" ††† (ማቴ. 11:7-15) ††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር ††† ምንጭ፦✍️ ዲን ዮርዳኖስ አበበ ሰኔ ፴ ፳፻፲፮
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
መሪጌታ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ከእስር ተፈቱ። የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ  መሪጌታ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ከእስር መለቀቃቸውን የማሕበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ዘግቧል። ዋና ሥራ አስኪያጁ ሚያዚያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም ነበር ከመኖሪያ ቤታቸው ተወስደው ለእስር የተዳረጉት። ከሁለት ወራት በኋላ ዛሬ ሰኔ 25 ቀን 2016  ዓ.ም  ከእስር  መለቀቃቸውን  ከቤተሰቦቻቸው ማረጋገጥ ተችሏል። #MahibereKidusanTV
نمایش همه...
አልቦ ዘከማየ አበሳ ኃጢአት ገባሬ ወአልቦ ዘከማከ እግዚአብሔር መሐሪ
نمایش همه...
😍
🤲
👍
❤️
👏
የማይደክመው መምህር ክርስቶስ በምድር ላይ ለ33 ዓመታት ተመላልሶ በአፍም በኑሮም አስተማረ:: ከዚያም ነፍሱ ከሥጋው ስትለይ ወደ ሲኦል ወርዶ ለ33 ሰዓታት በወኅኒ ላሉ ሰላምን ሰበከላቸው:: ከትንሣኤው በኋላ ደግሞ ለአርባ ቀናት እየታየ የመንግሥቱን ነገር (ኪዳንን) አስተማረ:: ከዕርገቱ እስከ ጰራቅሊጦስ ደግሞ ለመላእክት ሥጋዌውን ገለጠ:: የክርስቶስ በአራቱ እንስሳ በሰው በላም በአንበሳና በንስር በተመሰሉ ወንጌላውያን የተጻፈው ታሪኩ በዕርገት ተጠናቀቀ:: ክርስቶስ እንደ ሰው ተወለደ ፤ እንደ ላህም ተሠዋ ፤ እንደ አንበሳ ከሙታን ተነሣ ፤ እንደ ንስር ዐረገ:: ሐዋርያት እያዩት ደመና ሠውራ ተቀበለችው:: በእርግጥ ደመና ሠውራ ስትቀበለው የመጀመርያ አልነበረም:: በተወለደ ጊዜም እውነተኛዋ ፈጣን ደመና በማሕፀንዋ ሠውራ ተቀብላው ነበር:: አሁን ደግሞ ደመና ሠውራ ተቀበለችው:: ሐዋርያት በዕርገቱ ተስፋ ነግሮአቸዋልና ደስ እያላቸው ተመለሱ:: በሃምሳኛው ቀን የነገራቸውን አጽናኝ ላከው:: በዮርዳኖስ ሲወርድ ለምስክርነት ነውና በርግብ አምሳል ነበረ:: አሁን ግን ኃይል ሊሆናቸው በነፋስና በእሳት አምሳል ወረደ:: ዛሬ እስራኤል ከግብፅ በወጡ በሃምሳኛው ቀን በሲናን ተራራ የወረደው እሳትና በጽላት ላይ የተጻፈው ሕግ የተሠጠበት ቀን ነው:: ፋሲካችን ክርስቶስ በታረደ በሃምሳኛው ቀን በሐዲስ ኪዳንዋ ደብረ ሲና በጽርሐ ጽዮን በእሳት አምሳል መንፈስ ቅዱስ ወርዶ በሐዋርያት በልባቸው ጽላት ቃሉን የጻፈበት ቀን ነው:: በዓለ ሃምሳ እስራኤል ከግብፅ ከወጡ ሃምሳኛው ቀን ነበረ:: ይህ ዕለት ሙሴ ጽላት ይዞ የወረደበት ቢሆንም ሕዝቡ ደግሞ መታገሥ አቅቶት ጣዖት ሲያመልክ ተገኘ:: በዚህ ምክንያት በዚያች ዕለት ሌዋውያ ካህናት ስለዚህ ባዕድ አምልኮ ቅጣት 3000 ሰዎች ገደሉ:: (ዘጸ. 32:28) በሐዲስ ኪዳኑ በዓለ ሃምሳ ግን ሐዋርያት በልባቸው ፅላት ወንጌል ተጻፈ:: "የሞት አገልግሎት" እንደተባለችው ኦሪት 3000 ሰው አልገደሉም:: በጴጥሮስ ስብከት 3000 ሰው አዳኑ እንጂ:: የጰራቅሊጦስ ዕለት ክርስቶስ በደሙ የዘራውን ያጨደበት የመከር ቀን ነው:: የመከሩ ባለቤት ሠራተኞችን የላከበት ቀን ይህ ነው:: ጰራቅሊጦስ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያንን ሠራ:: ኤልያስ በእሳት ሠረገላ ተጭኖ ሲያርግ መጎናጸፊያውን ለኤልሳዕ ወረወረለት:: የእኛ መምህር ክርስቶስ ግን ከኤልያስ ይበልጣል:: ኤሎሄ ኤሎሄ ብሎ ሲጮኽ አይሁድ ባልሰማ ጆሮአቸው "ኤልያስን ይጣራል መጥቶ ያድነው" ብለው እንደዘበቱት አይደለም:: የእኛ መምህር ክርስቶስ ወደ ሰማይ ለማረግ ሠረገላ አይፈልግም:: በእርግጥ የመለኮትን እሳት መሸከም የሚችል ሠረገላ ከየት ይመጣል? እያዩት ከፍ ከፍ አለ:: ልብሱን አልወረወረም:: የእኛ መምህር ክርስቶስ ለሁላችን ልብሱን ሳይሆ ሥጋውና ደሙን ሠጥቶን ሔዶአል:: :: በዐሥረኛው ቀን ደግሞ መንፈሱን ደግሞ በበዓለ ሃምሳ አደለን:: እኛ ክርስቶስ ሲያርግ እያየን አንሮጥም:: ወደ ሥጋ ወደሙ እየቀረብን እርሱ በእኛ እኛም በእርሱ ይኖራል:: ጌታ በትንሣኤው ከኃጢአት ሞት በንስሓ እንድንነሣ አስተማረን:: "አንተ የምትተኛ ንቃ ከሙታንም ተነሣ ክርስቶስ ያበራልሃል" ብሎ ከበደል በንስሓ ትንሣኤ እንድንነሣ ጠራን:: ትንሣኤውን አይተን በንስሓ ከተነሣን የሚቀረን ዕርገት ነው:: ከትንሣኤው በኋላ እያዩት ከምድር ከፍ ከፍ ያለው ጌታ ከንስሓ ማግሥት በጽድቅ ሥራ ከፍ ከፍ እያልን ከምድራዊነት እንድናርግ ይፈልጋል:: ዐርገን በቀኙ መቀመጥ ባንችል በጽድቅ ቀኙ እንዲያቆመን መንገዱ ይኸው ነው:: ጰራቅሊጦስ የቤተ ክርስቲያን የልደት ቀን ነው:: በትንሣኤው ተፀንሳ እስከ ዕርገቱ ድረስ ለዐርባ ቀናት ተሥዕሎተ መልክእ (Organ formation) የተፈጸመላት ቤተ ክርስቲያን ዛሬ የተወለደችበት ቀን ነው:: እግዚአብሔር በባቢሎን ሜዳ የበተነውን ቋንቋ የሰበሰበበትና እንዱ የሌላውን እንዳይሰማው እንደባልቀው ያሉ ሥሉስ ቅዱስ አንዱ የሌላውን እንዲሰማ ያደረጉበት ዕለት ዛሬ ነው:: ሰው ወደ ፈጣሪ ግንብ ሰርቶ በትዕቢት ለመውጣት ሲሞክር የወረደው መቅሠፍት ዛሬ በትሕትና ፈጣሪን ሲጠባበቁ ለነበሩ ሐዋርያት ፈጣሪ ራሱ ያለ ግንብ ወርዶ ራሱን የገለጠበት ዕለት ነው:: በዮርዳኖስ ወንዝ ዳርቻ በርግብ አምሳል በትሕትና የወረደው መንፈስ ቅዱስ ዛሬ በእሳትና በነፋስ አምሳል ወደ ሐዋርያቱ የወረደው ዛሬ ነው:: ርግብ ሆኖ የወረደው ሊመሰክርለት እንጂ ኃይል ሊሠጠው ስላልነበረ ነው:: ዛሬ ግን ለሐዋርያቱ ኃይል ሊሠጣቸው ፈልጎ በእሳትና በነፋስ ኃይሉን ገለጠ:: መንፈስ ቅዱስ ሲወርድ በዚያ መገኘት ከፈለጋችሁ በቅዳሴው መካከል ተገኙ:: ካህኑን "ይህች ቀን ምን የምታስፈራ ናት? ይህች ቀን ምን የምታስጨንቅ ናት? መንፈስ ቅዱስ ከመልዕልተ ሰማያት የሚወርድባት?" ሲል ታገኙታላችሁ:: ኢሳይያስ ያየውን ራእይ ማየት ከፈለጋችሁ ወደ ቅዳሴ ገስግሱ:: ሱራፊ በጉጠት ፍሕም ይዞ ኃጢአታችሁን የሚተኩስበትን ደሙን ለመቀበል ከፈለጋችሁ ወደ ቅዳሴው ገስግሱ:: "ፈኑ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ ላዕሌነ" እያላችሁ የምታዜሙበት ዕለታዊው ጰራቅሊጦስ ቅዳሴው ላይ ተገኙ:: በአዲስ ቋንቋ ትናገራላችሁ:: የእናንተ ቋንቋ ሳይቀየር የሁሉም ቋንቋ ተናጋሪ ሰምቶ ይረዳችሁዋል:: ለሐዋርያት የተሠጠኸውን ሠጥተኸን ከሐዋርያት ያገኘኸውን ያላገኘህብን ሆይ ቅዱስ መንፈስህ ከእኛ አትውሰድብን:: የማዳንህን ደስታ ሥጠን:: በእሺታም መንፈስ ደግፈን:: ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ጰራቅሊጦስ 2016 ዓ.ም. ዳላስ ቴክሳስ
نمایش همه...
ሕንፀታ ለቤተ ክርስቲያን ቤተ ክርስቲያን የሚለው የተለያየ ዓውዳዊ ፍቺ ቢኖረውም የዓለም ጌጥ፣ የምእመናን ወዳጅ፣ ለቤተ ክርስቲአያን ቅን መሪን የሚሰጥ እግዚአብሔር በዚች ቀን በእናቱ በቅድስት ድንግል ማርያም ስም በፊልጵስዩስ ከሦስት ደንጋዮች ያነፃትን ቤተ ክርስቲያን ማለታችን ነው። ቤተ ክርስቲያን አመሠራረቷ እንደ ውኃ ፈሳሽ፣ እንደ እንግዳ ደራሽ ሳይሆን፤ ለሙሴ በሲና ተራራ ደበተራ ኦሪትን በሰማያዊት ቤተ መቅደስ አምሳል እንዲሠራት ካዘዘበት ጊዜ አንሥቶ ለእግዚአብሔር መሥዋዕት የሚያቀርቡበት፣ እግዚአብሔር በቸርነት የሚገለጥበት፣ ምሕረት መንፈሳዊና ምሕረት ሥጋዊ የሚገኝበት የተመረጠ ቦታ እያዘጋጀ ሲመለክ ኑሮአል። በኋላም በጠቢቡ ሰሎሞን በተሠራው ቤተ መቅደስ መሥዋዕትን፣ ጸሎትን፣ ምጽዋትን እየተቀበለ፣ ሕዝበ እስራኤልን ከብዙ መከራ እየጠበቀ አኑሯቸዋል። ምንም እንኳን ቤተ መቅደሱ የእግዚአብሔር ታቦት ማደርያ፣ የኀዘንተኞች መጽናኛ፣ የእግዚአብሔርን መምጣት ለሚጠባብቁ ሱባኤ የሚቆጥሩበት ቢሆንም አይሁድ የቤተ መቅደሱን አገልግሎት ቀይረው ተገቢ ይልሆነ ግብር የሚሰበስቡበት፣ የሻጮች፣ የለዋጮች ቤት አድርገውት ነበር፡፡ በጸሎት እርዝመት እያመካኙ የመበለቶችን ቤት የሚበሉ፣ መንፈሳዊ ተግባርን ለታይታ የሚከውኑ ግብዞች ሆነው ተወቅሰዋል፡፡ “ጌታችን እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ በጸሎት ርዝመት እያመካኛችሁ የመበለቶችን ቤት ስለምትበሉ፥ ወዮላችሁ” ብሏቸዋል፡፡ (ማቴ. ፳፥፲፬) የቤተ ክርስቲያን ልጆች ዛሬስ በእኛ ዘመን ቤተ ክርስቲያን ምን ትመስላለች? አገልጋየቿስ? በእውኑ ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ሥራ የሚሠራባት፣ እግዚአብሔርን ደጅ የሚጸኑባት መንፈሳዊት አደባባይ ወይንስ ሌላ? ዛሬስ ቤተ ክርስቲያንን በሥጋው እንጂ በነፍሱ የማያውቃት “አገልጋይ” መኖሩን ስናይ ጌታችን ቤተ ክርስቲያን ከሻጮች፣ ከለዋጮች እንዲያጸዳት እንመኝ ይሆን? ጌታችን የወንበዴዎች ዋሻ ሆና የነበረችውን ቤተ መቅደስ ካጸዳት በኋላ ድውያነ ሥጋን በተአምራት ድውያነ ነፍስን በትምህርት እያዳነ በቤተ መቅደሱ የሚሸጡ የሚለውጡትን ገርፎ አውጥቷቸዋል። (ማቴ.፳፩፥፲፬) በኋላም በዋለበት እየዋሉ ባደርበት እያደሩ ለጊዜው በእግር፣ በፍጻሜው ግን በግብር የተከተሉት ሐዋርያትም ምሕረት ሥጋዊ፣ ምሕረት መንፈሳዊ የሚገኝባትን ቤተ ክርስቲያን በቅድስት ድንግል ማርያም ስም በፊልጵስዩስ ከተማ ሠሩ። ለሕንፀታ ቤተ ክርስቲያን መነሻው ምንድን ነው? የሚለውን ስንመልከት፦ ቅዱስ ጳውሎስና በርናባስ በአሕዛብ ውስጥ በሰበኩ ጊዜ ብዙ ሰዎች ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ። ምእመናኑም ከጣዖት ማምለክ የተመለሱና ወደ “አምልኮ ቦታ” መሄድ የለመዱ ናቸውና ወደ ቤተ ጣዖት እንዳይሄዱ ሲከለክላቸው ከከለከልከን ሌላ የምናመልክበት ቦታ ስጠን በማለት ሲጠይቁት ወደ ሐዋርያት አለቃ ወደ ቅዱስ ጴጥሮስና ወደ ሐዋርያት ሁሉ ስለቤተ ክርስቲያን መታነፅ ጉዳይ መልእክትን ላኩ፣ ሐዋርያትም ክብር ይግባውና ያለ ጌታችን ፈቃድ ምንም ምን አንሠራም። ነገር ግን የምንሠራውን እግዚአብሔር እስኪአስረዳን ድረስ ወደ እግዚአብሔር እየጸለዩና እየማለዱ አንድ ሱባኤ ይጾሙ ዘንድ ወደ ሃይማኖት የተመለሱ አሕዛብን እዘዙአቸው አሉ፤ እንዲህም አዘዙአቸው። በሱባኤውም ፍጻሜ ክብር ይግባውና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጸላቸው፤ ሐዋርያትም ሁሉ ከየአገሮችው ሁሉ እስከ ፊልጵስዩስ በደመና ሰበሰባቸው። ከከተማ በስተምሥራቅ በኩልም አውጥቶ የቤተ ክርስቲያንቱን ቦታና መሠረት ወሰነላቸው። ማኅደረ ጻድቃን፣ ጉባኤ መላእክት ቅዱሳን፣ ምስካየ ምእመናን ንጹሐን፣ ወሀቢተ ንጽሕ ለኃጥአን፣ መርዓተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንም በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ስምም ያለ እንጨት ያለ ጭቃና ያለ ውኃ ከሦስት ድንጋዮች ተሠራች። (መጽሐፈ ስንክሳር፣ ሰኔ ፳፩) ቅዱስ ያሬድ በመዝሙሩ "ሃሌ ሉያ ተቀደሲ ወንሥኢ ኃይለ ኦ ቤተ እግዚአብሔር፤ እስመ ናሁ ንጉሥኪ በጽሐ ዘያበርህ ለኪ በኃይሉ፤ ለዛቲ ቤት ሣረራ አብ ቀዲሙ ለዛቲ ቤት ሐነፃ ወልድ ለዛቲ ቤት ወፈጸማ መንፈስ ቅዱስ፤ ቤተ እግዚአብሔር ሆይ ተቀደሺ፤ ኃይልንም ልበሺ፤ ንጉሥሽ እያበራ ወደ አንቺ ደርሷልና፡፡ ይህቺን ቤት አስቀድሞ አብ ሠራት፤ ወልድ አነፃት መንፈስ ቅዱስ ፈጸማት” በማለት አብ የሠራት፣ ወልድ በቀራንዮ ያነፃት፣ መንፈስ ቅዱስ ፍጽምት ያደረጋት፣ በሥላሴ መሠረትነት የተሠራች ንጽሕት ሙሽራ እንደሆች ያስተምረናል። ክብር ይግባውና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን በመስቀል ላይ ሳለ በደሙ ፈሳሽነት አጫት የእርሱ ሙሽራ አደረጋት። ሙሽራ በሙሽርነቷ አምራ፣ ተውባ፣ ንጽሕት ሆና እንድትገኝ፣ ቤተ ክርስቲያንም የአማረች፣ የተዋበች፣ ንጽሕት፣ ክብርት የሆነች ስንዱ እመቤት ናት። ቤተ ክርስቲያን የሙሽርነት ቀለበቷን ዘወትር ከፍ አድርጋ ለዓለም ሁሉ የምታሳይ ወረት የሌለባት ድንቅ ሙሽሪት ናት። ቀለበቷም ሙሽራዋ የነገሠበት ቅዱስ መስቀል ነው። ቤተ ክርስቲያን ዘወትር በመስቀሉ አጥር ተከልላም ትኖራለች። አምላካችን በትንቢተ ኢሳይያስ "ሰንበቴን ስለሚጠብቁ ደስ የሚያሰኘኝንም ነገር ስለሚመርጡ ቃል ኪዳኔንም ስለሚይዙ ጃንደረቦች፦ በቤቴና በቅጥሬ ውስጥ ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች ይልቅ የሚበልጥ መታሰቢያና ስም እሰጣቸዋለሁ፤ የማይጠፋም የዘላለም ስም እሰጣቸዋለሁ።" (ኢሳ. ፶፮፥፬_፮) እንዳለ ንጽሕት እምንጹሐን፣ ቅድስት እምቅዱሳን በሆነችው በቅድስት ድንግል ማርያም ስም የመጀመርያዋን ቤተ ክርስቲያን ሠራት። በገነት እንበላው የነበረውን ዕፀ ሕይወት እንበላባት ዘንድ ገነት ቤተ ክርስቲያንን በእመቤታችን ስም ሠራት። ዕፀ ሕይወትም የክርስቶስ ሥጋና ደም ነው "በእንተ ማርያም ድንግል ተርኅወ ለነ ዳግመ ከፈለነ ንብላዕ እምዕፀ ሕይወት ዘውእቱ ሥጋሁ ለክርስቶስ ወደሙ ክቡር በእንተ ፍቅረ ዚአነ፤ ስለ ድንግል ማርያም ተከፈተልን፤ ከዕፀ ሕይወት እንበላ ዘንድ አደለን፤ ይኸውም እኛን ስለ መውደድ መጥቶ ያዳነን የክርስቶስ ክቡር ሥጋው ክቡር ደሙ ነው" እንዲል ቅዱስ ኤፍሬም፡፡ (ውዳሴ ማርያም ዘሐሙስ) አምላካችን እግዚአብሔር እግራችንን አጽንቶ፣ ልቡናችንን አነሣስቶ በቤተ ክርስቲያን ያኖረን ዘንድ መልካም ፈቃዱ ይሁንልን! ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር አሜን!
نمایش همه...
ወአስተርአዩ ልሳናተ እሳት እንዘ ይወርዱ ላዕሌሆሙ ለእለ አሐዱ አሐዱ ወአኀዙ ይንብቡ በሐዲስ ልሳነ ወጾሙ ዐርባ መዓልተ ለአኰቴተ ዚአሁ ትርጉም፦ የተከፋፈለ የእሳት ላንቃዎች በእያንዳንዳቸው ላይ ሲወርዱ ታዩ፤በአዲስ ቋንቋም ተናገሩ ለጌትነቱ እጅ መንሻ ሊሆን አርባ ቀን ጾሙ። ወተናገሩ በነገረ ኵሉ በሐውርት
نمایش همه...
نمایش همه...
አንድ ሚሊየን ሁለት መቶ ሺህ ወቶበት 80ሺ ብር ብቻ ያስገባዉ ፊልም -ጌታቸዉ ታደለ .Abbay TV - ዓባይ ቲቪ - Ethiopia

"በተለያዩ መስኮች ስኬታማ እና ዝነኛ የሆኑ ሰዎች የሚጋበዝቡት በሙዚቃ እና ቀልድ የታጀበ አዝናኝ ፕሮግራም! እሁድ ምሽት ከ1:00 ጀምሮ በ ዓባይ አገልግል ይጠብቁን። Sekala is a talk show hosted by artist Tigist Girma which features accomplished and well-known individuals from diverse disciplines and is accentuated by music and comedy every Sunday Evening 1፡00 (LT) on Abbay tv. Follow us on: Subscribe:

https://bit.ly/abbay_tv

Facebook:

https://www.facebook.com/AbbayTV

Instagram:

https://bit.ly/abbayTv

TikTok:

https://bit.ly/Abbaytv

Telegram:

https://t.me/AbbayNews

Website:

https://abbaytv.com/

#Abbaytv #sekela #talkshow #Ethiopia #habesha #infotainment #lemlemhailemichael #ለምለም_ሃይለሚካኤል ዓባይ ቲቪ 'የኢትዮጵያ ምርጥ'"

یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.