fa
Feedback
Halal memory🫀

Halal memory🫀

رفتن به کانال در Telegram

#ǫᴜʀᴀɴ & ʜᴀᴅɪs #ғᴜɴ ɪsʟᴀᴍɪᴄ ᴄᴏɴᴛᴇɴᴛ #вєѕт ɪsʟᴀᴍɪᴄ 𝑣𝑖𝑏𝑒 #ᴇᴠʀʏ ᴍᴜsʟɪᴍ ᴄᴏɴᴛᴇɴᴛ ╱◥██████◣. │∩│🪟▤│🪟│. ▓▆▇█▓🚪▓█▇.

نمایش بیشتر
9 480
مشترکین
-1124 ساؚت
-617 عوز
-26230 عوز
آرشیو پست ها
"እኔ የሆነ ሀገር ቪዛ ጠይቄ፣ ገና ሳይሰጠኝ ስለ ቋንቋቸው፣ ስለ ባህላቸው፣ ስለ አለባበስ ስርአታቸው dress Code እንዲሁም ስለ ህግና ደንባቸው ለማወቅ ጥረት አድርጌአለሁ። ቋንቋውን ለመማር ሞክሬአለሁ፤ ስለ ሀገሪቷም ብዙ ማስታወሻ ይዤ ነበር። ሆኖም ለእኔ ሳይሳካልኝ ቀርቶ ለጓደኛዬ ተሳክቶላት እሷ ተጠቅማበታለች፤ ለዚህም አመስግናኛለች። አንድ ቀን ለእኔም ይሰጡኛል፣ Inshallah ብዙ ኢትዮጵያውያን ስለሚሄዱበት ሀገር ህግና ደንብ ለማወቅ ጥረት አያደርጉም። የሄዱበት ሀገርም ረጅም ጊዜ እየኖሩ ቋንቋ ለመማር አይሞክሩም። በአውሮፓና በአሜሪካ እንዲሁም ከእንግሊዝኛ ውጪ ሌላ ቋንቋ በሚናገሩ ማህበረሰቦች ውስጥ እየኖሩ፣ ቋንቋውን የማይችሉ ብዙ አሉ። የትምህርት እድል እየተፈጠረላቸው እንኳ አይማሩም፤ ይልቁንም የልጅ እርዳታ ብር ለማግኘት ሲሉ ብቻ እንደ ሶማሌዎች 'ልጅ ይፈለፍላሉ'። የራሳቸውን ቡድን ፈጥረው ይደራጃሉ እንጂ፣ ከሰፊው ህዝብ ጋር አይቀላቀሉም፤ ማህበራዊ ህይወትም አይፈጥሩም። በጣም ቆንቋና  ይሆናሉ፤ ስለ ነገ እያሰቡ ዛሬን አይኖሩም። ሀገር ቤት ሄደው ፎቅ ለመስራት ሲሉ፣ ዋስትና ለሌለው ነገ ዛሬን ራሳቸውን ይበድላሉ። የሚገዙትን ነገር ሁሉ 'ሀገር ገብቼ እጠቀማለሁ' በሚል ያስቀምጡታል። ሰው በርግጥ ስለ ነገ ማሰብ አለበት፤ ግን ራሱን እየበደለ መሆን የለበትም። በአጠቃላይ ራሳቸውን አይጠብቁም፤ የሚዘንጡት ሀገር ሲገቡ ነው። ይሄን ታዝባችኋል ግን? "ዕድሉን ቢያገኙ ብዙ ማድረግና መለወጥ የሚችሉ ኢትዮጵያውያን ባሉበት፤ ዕድሉን አግኝተው ግን በአግባቡ የማይጠቀሙበት ብዙ ኢትዮጵያውያን አሉ።" የሰው ልጅ ከየትኛውም የዓለም ህዝብ ጋር ተግባብቶ፣ እነሱን ወዶና መስሎ፣ የሚኖርበትን ሀገር ህዝብ አክብሮና ባህሉን ለምዶ መኖር አለበት። በዚህ መንገድ ራሱን ማነፅ ይኖርበታል።"

እረ አሚን በሉ😭

~ሐያእ እና ይሉኝታ ምንና ምን ናቸው ?! ¤ .. ይሉኝታ ሰዎችን ለማስደሰት ወይም ላለማሳዘን ከራስህ ምታጎልበት ስነ ምግባራዊ ጡዘት ሲሆን ... ¤ ..ሐያእ ደሞ ለራስህ የምትሰጠውን ቦታ(ክብር) ለሌሎችም ለመስጠት የምታደርገው ጥረት ነው .. ∞ በሁለቱ መሓል ግራንድ ካንየንን የሚያህል ገደል አለ... ¤ ..ሌላው ግድንግድዬው ገደል ደሞ ምን መሰለህ ... ሐያእ ሐያእነቱ ከውስጥ የሚገፋህ ሐይል(እምነት) ኖሮ ስታደርገው ነው...ያ ካልሆነ ሐያእነቱ ቀርቶ ሪያእ (እዩልኝ) ሆኖ ቁጭ ይላል... ¤ እንደው ከጠቀመህ ማለት.. ¤ ..አንዳንዱ ስራ ቀድሞውኑ ሲሰራ ከሪያእ (ከእዩልኝ) የፀዳ መሆን ይኖርበታል... ከነዚህ 'አንዳንዶች' ውጭ ያለው ስራ ደሞ እነዚህን አጥርተህ ስትሰራ አላህ ላንተ የሚያገራልህ ወይም አንተ ላይ የሚገልጠው ነው... አሁን የምናወራለት ሐያእ ከሁለተኞቹ የሚመደብ ነው .. ¤ ስለዚህ ምን ይሁን ?... ∞∞∞∞∞ .. መንፈሳዊነታችን ላይ እንበርታ ነው የምልህ!...እዩልኝም በለው ሌላ አይነት ቀልብ የሚያጨልሙ በሽታዎች የፍቅሩ ብርሃን ሲያገኛቸው ተቋቁመው ሊዘልቁ የሚችሉ አይደሉም ... ተህሊል ሶለዋት ዚክርህን ጠንክረህ ከርር ... ከአላህ የሆኑ ውብ ምግባሮች በአንተ ላይ ሲገለጡ ትመለከታለህ..!

ቅድም የሆነ ጓደኛዬን ለደመወዝ የሚመለስ አንድ ሺህ ብር አበድረኝ ልለው አትላስ የሆነ ቤት ተገናኘን። ጉዳዬን ሳልነግረው አንድ ሁለት እያልን የውሻውን ጥፍር ለማሰራት ደህና የእንሰሳት ህክምና አጥቶ መቸገሩንና ናይሮቢ ውስዶ ሊያሰራት እንዳሰበ አጫወተኝ። የኔን የ1 ሺህ ብር ማጣት ባለመናገሬ ፈጣሪን አመሰገንኩ። ለካስ ሁሉም በየቤቱ ብዙ ችግር አለበት።

..በዑስማንዮች የግዛት ወቅት እንደ መንግስትም እንደ ህዝብም ውብ እና የሚያስገርሙ ልማዶች ነበሯቸው...ብዛቱ ለቁጥር ቢያታክትም ያስገረሙኝን ጥቂት ልበላችሁ ..~~~¿ (ሀ)..ሁሌም እንግዳ ሲመጣ ለእንግዳው ውሃ እና ቡና ይቀርቡለታል... ቀድሞ ውሃውን ከጠጣ ባለቤቱ እንግዳው እንደራበው ተረድቶ ምግብ ያቀርባል... ቡናውን ቀድሞ ከጠጣ ይህ ማለት እንግዳው እዛ ከመምጣቱ በፊት ተመግቧል ማለት ነው ( ይህ ልማድ ምናልባት አሁንም ድረስ ቱርኮች እና ኩርዶች እንደ ባህል አስቀጥለውታል) ¤ (ለ)..በዛ ወርቃማ ዘመን ሁሉም ቤቱ በር ላይ አንድ ትልቅ እና አንድ ትንሽ የበር ማንኳኪያዎች ማስቀመጥ ደንብ ነበር ...በትንሹ ከተንኳኳ ሴት ናትና የቤቱ እመቤት ሄዳ ትከፍታለች... በትልቁ ከተንኳኳ ደሞ ወንድ ነውና የቤቱ ጌታ ሄዶ ይከፍታል ..ይህ አላስፈላጊ መተያየቶችን ለመከላከል የተደረገ ነበር ... ምናልባት እስካሁን ቀጥሎ ቢሆን ተብሊጎች "ወንድ ካለ ጥሩልን" ለማለት ባልተቸገሩ ነበር😁 ¤ (ሐ)..የዑስማንይ መንግስት ረመዷን ከመግባቱ በፊት የሙዕሚኖችን ዕዳ በንግድ ቦታዎች እየተዘዋወረ የሚከፍል ቡድን ያሰማራ ነበር ... ወደ አንድ ንግድ ቦታ ያመሩና የዕዳ መዝገቡን ይጠይቃሉ... የተመዘገቡ ዕዳዎችንም አንድ በአንድ አስልተው ለአበዳሪው በመክፈል ያሰርዛሉ ... ነገር ግን አበዳሪውም ተበዳሪውም ከፋዩ ማን እንደሆነ አያውቁም ነበር ¤ (መ)..በቤታቸው በር ላይ ቢጫ ፅጌሬዳ ካስቀመጡ በቤቱ ውስጥ የታመመ ሰው አለና በዛ በኩል የሚያልፍ ሰው በሽተኛውን ሚረብሽ ድርጊት እንዳያደርግ የሚያሳውቅ ነው... ...ቀይ ፅጌሬዳ ደጃፋቸው ላይ ከተቀመጠ ደሞ በቤቱ ለትዳር የደረሰች ሴት አለችና "ጠያቂ ሆይ አርሂብ" እንደማለት ሲሆን🥰...ከዛ ውጪ ላለው ሰው ደሞ "በቤቱ አቅራቢያ ሆነህ ስሜቷን ሊጎዳ የሚችልን ቃል እንዳትናገር" እንደማለት ነው...( ለምሳሌ ሐበሻ "ቆሞ'ቀር" እንደሚለው አይነት ቃል😀) ∞ (ሚም)..ሌላው እጅግ ውቡ እና ልብ የሚነካው ልማዳቸው ደሞ በዛ ዘመን የነበሩ እድሚያቸው ከ63 አመት ያለፈ አዛውንቶች እድሚያቸውን ሲጠየቁ ...እድሜያቸው ከሰይዳችን (ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) የምድር ቆይታ ያለፈ መሆኑን መግለፅ እንደ ነውር እና አሳፋሪ ተግባር ይቆጥሩት ነበር ...እናም መልሳቸው አንድ ነበር ... "..ልጄ ሆይ!..ድንበር አልፈናል.."]ነበር

"ነገ ባይሽ ደስ ይለኛል.." "..ትንሽ አሞኛል ግን ሻል ካለኝ አገኝሃለሁ." አለች በደከመ ድምፅ "..ሻል ባይልሽም እኔን ስታዪኝ መሻርሽ ግን የማይቀር ነው.." አልኳት ሐሳቧ ላይ እንድትገፋበት
"ነገ ባይሽ ደስ ይለኛል.." "..ትንሽ አሞኛል ግን ሻል ካለኝ አገኝሃለሁ." አለች በደከመ ድምፅ "..ሻል ባይልሽም እኔን ስታዪኝ መሻርሽ ግን የማይቀር ነው.." አልኳት ሐሳቧ ላይ እንድትገፋበት .. ሳቅ አለች.. "..ራስህን እንደ ነብዩላህ ዩሱፍ ቀሚስ ነው እንዴ ምትመለከተው.." አላህ ይዘንልኝ 💔

አንዲት ኒቃቢስት ከፊቴ ቆማ፣ እቃ ለማውጣት ቦርሳዋን ትከፍታለች። በዚህ ጊዜ ሦስት የመንገድ ድመቶች መጥተው ይተሻሿታል፣ ይንጠለጠሉባታል፤ ላያቸውማ ልክ አሳዳጊያቸው ነው የሚመስሉት። ከዚያም ከቦርሳዋ ምግብ አውጥታ አስቀመጠችላቸው። እስቲ አስቡት፤ ኒቃቢስት ናት፣ መልኳን አያውቁትም፤ ግን የምትራራላቸውን ሴት ጠረን እና ልብ ያውቃሉ። በጣም ገርሞኝ 'እንደ እንስሳት ሰዎችን በልብ ብናይ' ምናለ አልኩ! መልካምነት መጋረጃ የለውም" ድመቶቹ የኒቃቡን ጨርቅ ሳይሆን የልቧን ብርሃን ነው ያዩት። እኛ ሰዎችም እንዲህ አይነት ንጹህ እይታ ቢኖረን ኖሮ፣ ብዙ አለመግባባቶች በቀሩ ነበር። የሰው ልጅ ከሌሎች ፍጥረታት የሚለየው በደመ-ነፍስ Instinct ብቻ ስለማይመራ ነው። እንስሳት የተራቡ ጊዜ ይበላሉ፣ የተቆጡ ጊዜ ይነክሳሉ። የሰው ልጅ ግን ራሱን "ከገራ" መራብ እየቻለ መጾም፣ መቆጣት እየቻለ ይቅር ማለት፣ መጥላት እየቻለ መውደድ ይችላል። ይህ "ራስን መግራት" ነው ሰውን "ድንቅ ፍጡር" የሚያደርገው። የሰው ልጅ ካለፈው ተምሮ፣ የወደፊቱን አልሞ፣ በአሁኑ ሰዓት የመወሰን ብቃት አለው። ይህ አእምሮአዊ ልዕልና ደግሞ ከምግባር Ethics ጋር ሲዋሃድ ሰውን ወደ "የላቀ ልዕልና " ደረጃ ከፍ ያደርገዋል። ራስን አለመግራት ግን ሰውን ከእንስሳት በታች "አውሬ" ሊያደርገው ይችላል። ሰዎች ብዙውን ጊዜ እውነቱን ሳይሆን፣ የእነሱን ቀድሞ የነበረ አመለካከት የሚደግፍላቸውን ነገር ብቻ መርጠው ያያሉ። ይህ ደግሞ አእምሯችንን በጠባብ ሳጥን ውስጥ ይቆልፈዋል። ከዚህ ሳጥን ወጥቶ እውነቱን እንደ እውነቱ ለማየት "የማሰብ ልዕልና" እና ትልቅ ትዕግስት ይጠይቃል። የሰው ልጅ ችግሩ "አቅም ማጣቱ" ሳይሆን አቅሙን "ለመግራት" ፈቃደኛ አለመሆኑ ነው። ብዙ ጊዜ በስሜት Emotion እና በጥቅም እንመራለን እንጂ የሰው ልጅ ልዩ ታላቅ ፍጡር ነው!

ደግነት ደንቆሮ የሚሰማው ዕውሮችም የሚያዩት ቋንቋ ነው።

...አንድ ቀን አላህ በምትጠብቀው መልካም ነገር ያበስርሃል... እርሱ ዕጣ ፈንታን በቅጽበት ቀያያሪ የሆነ ጌታ ነው .... ምቾትንም መከራ ካደከመው ልብ ውስጥ ሊከስት ዘንድ ቻይ ነውና....በአላህ
...አንድ ቀን አላህ በምትጠብቀው መልካም ነገር ያበስርሃል... እርሱ ዕጣ ፈንታን በቅጽበት ቀያያሪ የሆነ ጌታ ነው .... ምቾትንም መከራ ካደከመው ልብ ውስጥ ሊከስት ዘንድ ቻይ ነውና....በአላህ ላይ መልካምን እንጅ አትጠርጥር... [..وَاللَّهُ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ..] «.. አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው፡፡...»

«....ባሪያው ጌታውን እስከሚረሳው ድረስ ከርሱ ይዘናጋል....ጌታውም ይናፍቀውና ከፍቅሩ የተነሳ እርሱን እንዲያወሳ ሚያደርገው መከራን ይልክበታል.....ባሪያውም ይመለስና አላህን ማፍቀር ይጀምራል.
«....ባሪያው ጌታውን እስከሚረሳው ድረስ ከርሱ ይዘናጋል....ጌታውም ይናፍቀውና ከፍቅሩ የተነሳ እርሱን እንዲያወሳ ሚያደርገው መከራን ይልክበታል.....ባሪያውም ይመለስና አላህን ማፍቀር ይጀምራል.... አላህም ፍቅሩን ይሰጠዋል.....መከራውንም ያነሳለትና ጥሩ የሆነ ሲሳይን ይለግሰዋል..» ሰይዲ ሙተወሊ ሸዕራዊ 💙

Repost from Halal Fkr
አቡ ነውፈል “ፍቅር የማይዘው ሊኖር ይችላል?” ወይ ተብሎ ተጠየቁ፡ ‹‹አዎ! ደረቅና ደደብ ሰው ፍቅር ላይዘው ይችላል›› አሉ፤ ዓሊይ ቢን ዓብዳም ‹‹ፍቅር የማያጠቃው ሰው የለም፤ ተፈጥሮው ደረቅ፤
አቡ ነውፈል “ፍቅር የማይዘው ሊኖር ይችላል?” ወይ ተብሎ ተጠየቁ፡ ‹‹አዎ! ደረቅና ደደብ ሰው ፍቅር ላይዘው ይችላል›› አሉ፤ ዓሊይ ቢን ዓብዳም ‹‹ፍቅር የማያጠቃው ሰው የለም፤ ተፈጥሮው ደረቅ፤ ወኔው ጎደሎ ወይም የተዛባ ተፈጥሮ ያለው ሰው ሲቀር›› ብለዋል፡፡ ©️baledaw         𝓗𝓪𝓵𝓪𝓵 𝓕𝓴𝓻 ™

ሁሉም ነገር መስተካከል ያለበት አይደለም....ምናልባት አንዳንድ ህመሞች የሚሽሩት እንደነበረው ሲተው ነው...የሚያገግሙት ባለመነካታቸው ውስጥ ነው ...ምናልባት ባለመስተካከል ውስጥ ነው ሰላሙ ያለው
ሁሉም ነገር መስተካከል ያለበት አይደለም....ምናልባት አንዳንድ ህመሞች የሚሽሩት እንደነበረው ሲተው ነው...የሚያገግሙት ባለመነካታቸው ውስጥ ነው ...ምናልባት ባለመስተካከል ውስጥ ነው ሰላሙ ያለው ....ምናልባትም ትላንታችን ባለመታወሱ ውስጥ ነው መረጋጋት ያለው ...ይህ ሽሽት አይደለም..አላህ ልቦችን ከሚያክምባቸው መንገዶች አንዱ እንጂ...ስለዚህ .. ሰው ሲያዝን ..ሲከፋው ..ድባቴ ውስጥ ሲገባ ከዛ ሰው ጎን መሆን ...ማባሸር ችግሩን መጋራት.. ህመሙን መታመም ..መፍትሄውን ማፈላለግ የወዳጅነት ማዕረጉ እና ደንቡ ቢሆንም ...አንዳንዴ ግን እነዚህ ነገሮች በዝምታ የሚከናወኑ እና ፋታ በመስጠት ውስጥ የሚፈፀሙ ናቸው...በዛ መልኩ ወዳጅነታችን ሚገለፅባቸው ቀናቶች አሉ...!

Story

አፍሪካ ቲቪ ለወንዶች ብቻ የወጣ ማስታወቂያ

ከባድ ነው በዚህ ዝናብ፣ታክሲ ግፊያ፣እና ላጤነት🥲

"..ሁሌም ቢሆን ችግርህን ለማንም ሳትናገር ለመፍታት ጣር.." "..ላንቺም ቢሆን..?" "..መች ነው እኔ 'ማንም' የሆንኩት?!.." "አይ እኔኮ ከአንተ ውጪ ከማንም ጋር እንዳታወራው ስትዪኝ..." "..እኮ መች ነው እኔ ካንተ ውጪ የሆንኩት?.." "..አፍ አፌን አትበዪኛ ላስረዳሽ.." "..ተወው አታስረዳኝ እንደውም እኔ ነኝ ጥፋተኛ.." "..ካልሽ..እሺ .." "..አየህ ብትወደኝ ኖሮ ልታስረዳኝ ትሞክር ነበር.." "..ላስረዳሽ የምችለው ነገር እንዳለ ካወቅሽ እኮ.." "..ተወኝ.. ምንም አታብራራልኝ.." "..እሺ ይቅርታ.." "..የልብህን ከተናገርክ በኋላ ይቅርታ?!..ቀልደኛ.." "..አንድ ነገር ልንገርሽ.." (ዝምም) "..ለማንም የማልናገረው ችግሬ አንቺ ነሽ.." (ሳቀች) "..ሂዛ..ሞዛዛ.." (ፈገግኩላት) የምሬን እንደሆነ ማን በነገራት .. (..የሰው ዕጢ..)

ሴቶች ግን ተለክታችሁ የገዛችሁት የሚበቃቹህ ሂጃብ ስራ ስትጀምሩ ወይም ወጣ ወጣ ስንሉ ወደ  ታች የሚለው ለምንድነው ?ከሂጃቡ ነው ወይስ ከመንገዱ እና ስራ ቦታው ?💔

የመዲናውን ባየነው አይኑን፣ በኑር አረንጓዴ የተኳለውን፣ ፊቱ ከጨረቃ የሚያበራውን፤ ሰሉ አለ ረሱል ﷺ💚

الصلاة والسلام عليك يا سيدي يا رسول الله ♥

~ከኢብሊስጋ የተደረገ ምናባዊ ኢንተርቪው ~~ ¤ጋዜጠኛው ÷ከስምህ እንጀምር። ዓለም የሚያውቅህ በብዙ አስፈሪ መጠሪያዎች ነው። ሸይጧን፣ ኢብሊስ፣ ሰይጣን... እነዚህ ግን ትክክለኛ ስሞችህ ናቸው? ኢብሊስ: "ሸይጧን ወይም ኢብሊስ ትክክለኛ ስሜ ሳይሆን ተግባሬን የሚገልፁ ቅጽሎች ናቸው ።ሸይጧን' ማለት እኮ 'ከእዝነት የራቀ' ወይም 'ባላንጣ' ማለት ነው። 'ኢብሊስ' ደግሞ 'ተስፋ የቆረጠ' ማለት ነው። እነዚህ በአላህ እዝነት ተስፋ ቆረጬ ከነበረኝ ክብር ስባረር የተሰጡኝ የውድቀት ማዕረጎች ናቸው። ዛሬ የምታውቀኝ በእነዚህ ስሞች ነው። ነገር ግን... ከመውደቄ በፊት... እኔ ግን በአንድ ወቅት የራሴ ስም ነበረኝ... አዛዚል! ያ ስም የክብር ነበር። ያ ስም የአምልኮ ነበር። ዛሬ ግን ያ ስም በሰማያት መዝገብ ላይ ተፍቋል።" ¤∞∞ ጋዜጠኛው፡ "አዛዚል... ደስ የሚል ስም ነው ! ግን ይህ የክብር ስም ወደ 'ኢብሊስ' የተቀየረው በአንድ ጀንበር አልነበረም። እስኪ እናንተ ጂኖች ከምን ተፈጠራችሁ? አደም ከመፈጠሩ በፊት ምን ትሰሩ ነበር? ኢብሊስ÷እኛ የተፈጠርነው እናንተ ከመፈጠራችሁ በብዙ ሺህ ዓመታት በፊት ነው።እናንተ ከጭቃ አፈር ስትፈጠሩ እኔና ወገኖቼ ጂኖች ግን የተፈጠርነው ከሚንቀለቀል፣ ከማይጨስ ንጹህ የእሳት ነበልባል (ማሪጅ) ነው። እንደ ነፋስ ፈጣን፣ እንደ ብርሃን ረቂቅ፣ እንደ እሳት የሚንቀለቀል ተፈጥሮ ተሰጠን። እኔ የዚህ ተፈጥሮ ውጤት ነኝ። የጥንታዊው ነበልባል ልጅ ነን። እየውልህ እኛ ጂኖች ከተፈጠርን በኋላ ከሰው ልጅ በብዙ ሺህ ዓመታት ቀድመን ምድርን እንኖርባት ነበር። እኛ በባህሪያችን የረቀቅን፣ ከቦታ ቦታ በፍጥነት የምንወነጨፍ ኃያላን ነበርን።ወገኖቼ ጂኖች በምድር ላይ እንደ ልባቸው ይኖሩ ነበር። ∞ ግን ወገኖቼ... ጂኖች... ስሜታቸውን መቆጣጠር አቃታቸው። ተፈጥሯችን እንደ ነበልባሉ ስለነበር፣ ቶሎ እንቀጣጠል ነበር። እሳትነታቸው ፈተናቸው። ስልጣን ሲበዛባቸው አመፁ። ምድርን በደም አጨቀዩዋት። እርስ በርስ ተላለቁ።ምድሪቱን በጥፋትና በክፋት አደፏት። ምድር በጂኖች ጩኸትና ግጭት ታወከች። ያኔ ነበር አላህ መላእክትን ልኮ ምድርን እንዲያጸዱ ያዘዘው። ብዙዎቹ ጂኖች ጠፉ፣ የተረፉትም ወደ ተራራዎችና ደሴቶች ተሰደዱ።" ​ጋዜጠኛው፡ "አንተስ በዚያን ጊዜ ከእነርሱ ጋር ነበርክ? እንዴት ነው ከጥፋቱ ተርፈህ ወደ ሰማያት ከፍ ያልከው? አመፅ ውስጥ አልነበርክም?" ​ኢብሊስ፡ እኔ ከወገኖቼ የተለየሁ ነበርኩ። እነርሱ በምኞት ሲታወሩ፣ እኔ በዚያን ጊዜ የአምልኮ ጥማት ነበረኝ። ወገኖቼ ሲያምፁ እኔ እሰግድ ነበር። እነሱ ሲያጠፉ እኔ አላህን አመሰግን ነበር።በአምልኮቴና በንጽህናዬ ምክንያት መላእክት ወደ ሰማይ ይዘውኝ ወጡ። የአምልኮቴ ጽናት ከመላእክት ጋር እንድቀላቀል አደረገኝ። የጂን ዘር ሆኜ ሳለ፣ በመላእክት መሃል እንደ አንዱ ሆኜ ተቆጠርኩ።በሰማያት ውስጥ እኔ አላህን ያላወደስኩበት ሱጁድ ያላረግኩበት አንድም ኢንች ስፍራ የለም።መላእክት ያከብሩኝ ነበር። በጋራ ለአላህ ምስጋና እናቀርብ ነበር። ዓለሙ ንጹህ ነበር። እኔም ንጹህ ነበርኩ... ወይም ቢያንስ፣ ንጹህ እንደሆንኩ አስብ ነበር። ጋዜጠኛው፡ "ታዲያ ያ ሁሉ ክብር፣ ያ ሁሉ እውቀትና አምልኮ... እንዴት በአንድ አፍታ ሊፈርስ ቻለ? የውድቀትህ ዘር የተዘራው መቼ ነበር? አዳም ሲፈጠር ነው ወይስ ከዚያ በፊትም በውስጥህ የሆነ ነገር ነበር?" ​ኢብሊስ፡ ውድቀት በአንድ ሌሊት አይመጣም።በመላእክት መካከል ስኖር አንድ ነገር አስተዋልኩ። እነርሱ የታዘዙትን ብቻ የሚያደርጉ፣ የራሳቸው ፍላጎት የሌላቸው ፍጡራን ናቸው። እኔ ግን ጂን ስለሆንኩ ምርጫ ነበረኝ። ምርጫ ኖሮኝ መታዘዜ ከእነርሱ የተሻልኩ እንደሆንኩ እንዲሰማኝ አደረገኝ።ይህ ልዩነት በውስጤ ስውር ኩራት ፈጠረ። እኔ ከጂን ተፈጥሬ በመላእክት ጉባኤ ከተቀመጥኩ፣ ታዲያ ከእኔ በላይ ማን አለ?' ብዬ ማሰብ ጀምሬ ነበረ። ትህትና የመሰለ ትዕቢት ነበር የያዝኩት። አምልኮዬ ለራሴ ክብር ምንጭ ሆነብኝ። ራሴን እንደ ልዩ ፍጡር ማየት ጀመርኩ። ይህ ሁሉ የሆነው ገና ያ የሸክላ ሰው ከመምጣቱ በፊት ነው። እናም አላህ ... 'በምድር ላይ ምትክን (ከሊፋ) አደርጋለሁ' ብሎ ያንን አስደንጋጭ ዜና ሲናገር... በውስጤ የነበረው እሳት በቅናት ነደደ።መላእክት ስለ ደም መፋሰስ ፈሩ። እኔ ግን ለምን?' አልኩ። 'እኔ እያለሁ ለምን ሌላ ያስፈልጋል?'የሚለው ስሜት አንገበገበኝ። ጋዜጠኛ: ከዚያ አዳም ተፈጠረ። ገና ነፍስ ያልተዘራበት፣ የተጋደመ የሸክላ ምስል ሆኖ ስታየው... ለመጀመሪያ ጊዜ ምን ተሰማህ?" " ኢብሊስ:ንቀት። ንጹህ ንቀት። አዳም ከጭቃ ተቦክቶ፣ ገና ነፍስ ሳይዘራበት አርባ ቀን (ወይም ዓመታት) ተቀምጦ ነበር። በዛን ጊዜ ነበር የእኔ ክፋት የጀመረው። ገና ነፍስ ሳይዘራበት፣ እንደ ደረቅ ሸክላ ተጋድሞ ሳለ ወደ እሱ ሄድኩ።ሆዱን መታሁት፤ እንደ ባዶ ጋን ድምጽ አሰማ።ባዶ ነው' አልኩ። ውስጡ ክፍት መሆኑን አየሁ። 'ውስጡ ክፍት ከሆነ ራሱን መቆጣጠር አይችልም፣ በምኞት ይሞላል' ብዬ ተረዳሁ። ውስጡን ሳይ ባዶነት፣ ሆድ፣ እና ፍላጎት ብቻ አየሁበት።ለአላህ ክብር የሚመጥን አልነበረም። ያኔ በራሴ እንዲህ አልኩ፦ "ይህ ፍጡር በእኔ ላይ ከተሾመ አልታዘዘውም፤ እኔ በእርሱ ላይ ከተሾምኩ ግን አጠፋዋለሁ።" በልቤ ውስጥ ያለው ኩራት ገና ነፍስ ሳይነፋበት ዘላለማዊ ጠላቴ አደረገው። ጌታዬ ለአለም ሚስጥር አድርጎ ያቀረበውን እኔ እንደ ተራ ቆሻሻ አየሁት። ጋዜጠኛው፡ "በኋላ ላይ ነፍስ ተዘራበት። ተነሳ። እና አላህ ስሞችን አስተማረው። አንተ የማታውቃቸውን ስሞች። በዚህ ጊዜ ምን ተሰማህ? ኢብሊስ: እውቀት በነጻ ሲሰጥ ማየት ያማል።እኔ ለሺህ ዘመናት የለፋሁ ተማሪ ነኝ። አዳም ግን ገና ትናንት ተፈጠሮ፣ ምንም ሳይለፋ፣በአንድ ጀምበር ሁሉንም ስሞች አወቀ።እውቀቱ የተሰጠው ነው እንጂ ያገኘው አልነበረም።ዕውቀቱ እንደኔ ጥረት ውጤት ሳይሆን የፈጣሪ ስጦታ ነበር። ይሄ አድሎ ነው ብዬ አሰብኩ ።ይህ ፍጡር የተከበረው በራሱ ጥንካሬ ሳይሆን፣ በተሰጠው ሚስጥር ነው። ያ ደግሞ የበለጠ አናደደኝ። ጋዜጠኛው፡ "አሁን ወደ ወሳኙ ቀን እንምጣ። ፡ 'ለአዳም ስገዱ የሚለው ትዕዛዙ ተላለፈ፣ ሁሉም ወደቁ። ሁሉም ግንባራቸውን መሬት አስነኩ። አንተ ግን ቀጥ ብለህ ቆምክ። በዛች ቅጽበት... በዛች ሰከንድ ምን እያሰብክ ነበር? የምር፣ እምቢ ማለት የሚያስከትለውን መዘዝ አላወቅክም ነበር? ኢብሊስ: ያቺ ቅጽበት...ትዕዛዙ እንደ ነጎድጓድ ሲያስተጋባ መላእክቱ ሁሉ ጅብሪል፣ ሚካኤል፣ እስራፊል እንደ ተራራ ናዱ። ታላቅ የሱጁድ ማዕበል ሆነ።‎እኔ ግን ቀጥ ብዬ ቆምኩ።ፊት ለፊቴ ያ ከጭቃ የተሰራ ሰው አለ። ትዕዛዙ ከጌታዬ እንደሆነ፣ አውቃለሁ... ይቀጥላል~~~