BUREAU OF FINANCE - ADDIS ABABA CITY ADMINISTRATION - Page
رفتن به کانال در Telegram
2 960
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+117 روز
+5430 روز
آرشیو پست ها
ዛሬ ከሰዎች ለሰዎች ድርጅት ጋር በመተባበር በሀገራችን በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን የስማርት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግንባታ አስጀምረናል።
ይህ ስማርት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግንባታው ሲጠናቀቅ ወጣቶችን በማኑፋክቸሪንግ፣ በአውቶሞቲቭ፣ በኤሌክትሪክና ኤሌክትሮኒክስ፣ በኮሚዩኒኬሽንስ፣ በቴክስታይል እና የሲኤንሲ (CNC) ቴክኖሎጂዎች ላይ ተግባር ላይ ያተኮረ እና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን የሚጠቀም ስልጠና ይሰጣል።
ሀገርን ማልማት እና ከድህነት መላቀቅ በንድፈ ሃሳብ ብቻ በተገደቡ ትምህርቶች ማሳካት ስለማይቻል፣ ሃሳብን የሚያፈልቁ አዕምሮዎችን እና የሚሰሩ እጆችን ያጣመረ ክህሎት መር የሰው ሀይል እጅግ አስፈላጊ ናቸው።
ዛሬ ያስጀመርነው ፕሮጀክት በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ወጣቶቻችንን ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት፣ ከንድፈ ሃሳብ ወደ ተግባር የሚያሸጋግር፣ አዲስ የሥራ እድል የሚፈጥር የክህሎት ድልድይ የሚሆን ነው።
የዚህ ኮሌጅ ግንባታ በጥራትና በተቀመጠለት ጊዜ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ በልዩ ትኩረት የምንከታተለው ሲሆን፣ ፕሮጀክቱን በትብብር የሚገነባው የረጅም ጊዜ የልማት አጋር የሆነው ሰዎች ለሰዎች ድርጅት እና የሚሰራው ለትውልድ የሚሻገር አሻራ ነው ብላችሁ መሬታችሁን ለፕሮጀክቱ የለቀቃችሁ አርሶ አደሮችን በራሴና በተጠቃሚ ወጣቶች ስም ምስጋናዬን አቀርባለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የሚገነባው "የአዲስ አበባ ስማርት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ" የሶስትዮሽ ስምምነት ተፈረመ።
########################
ቀን ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም ፋይናንስ ቢሮ
የከተማ አስተዳደሩ ከ«ሰዎች ለሰዎች ድርጅት» (Menschen für Menschen) ጋር በመተባበር በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 ከግማሽ ቢሊየን ብር በላይ በሚደርስ በጀት የሚገነባውን "የአዲስ አበባ ስማርት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ" ወደ ተግባር ለማስገባት የሚያስችል የሶስትዮሽ የመግባቢያ ስምምነት ፊርማ ሥነ-ሥርዓት ተካሄደ።
በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብድልቃድር ሬድዋን፣ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ፣ እንዲሁም የሰዎች ለሰዎች ድርጅት የቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ሰባስቲያን ብራንዲስ ተገኝተው ተፈራርመዋል።
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ እንደተገለጸው ኮሌጁ በ2 ዓመታት ጊዜ ውስጥ ግንባታውና የማሽነሪዎች ዝርጋታው ተጠናቆ ወደ ሥራ ሲገባ በየዓመቱ ከ800 በላይ ወጣቶችን በዘመናዊ የቴክኖሎጂ ዘርፎች ዎርክሾፖች እና ማሽነሪዎች፣ መማሪያ ክፍሎች፣ የአስተዳደር ሕንጻዎች፣ ኮንቬንሽናል እና ኤሌክትሮኒክ ቤተ-መጻሕፍት፣ የካምፓስ አገልግሎት መስጫ ማዕከላት፣ ስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና አረንጓዴ ቦታዎችን ያካትታል።
በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱልቀድር ሬድዋን "ዛሬ የምንፈራረመው የሶስትዮሽ ስምምነት ተራ የአስተዳደራዊ ሰነድ ፊርማ ሳይሆን፣ የከተማችንን ወጣቶች የወደፊት ተስፋ የሚያለምልም ታሪካዊ መነሻችን ነው" ብለዋል።
አክለውም የሰዎች ለሰዎች ድርጅት እስካሁን በሀገራችን ከ11 ቢሊዮን ብር በላይ በማውጣት ለበርካታ ዜጎች ያደረገውን ዘላቂ የልማት ውለታ በማንሳት ለዚህ አዲስ ፕሮጀክት ላደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
የዚህ ተቋም የግንባታ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በነገው ዕለት የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ በተገኙበት እንደሚካሄድ ተገልጿል።
ይህ የሶስትዮሽ ስምምነት የወጣቶችን የሥራ ዕድል ፈጠራ የሚያፋጥን፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን
በማድረግ በከተማዋ የተሳካ የሞዴል አጋርነት ማሳያ እንደሚሆን ተመላክቷል፡፡
ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ እናመሰግናለን !!
ዌብሳይት:- aabof.com.et
ፌስቡክ:-https://www.facebook.com/aabof.gov.et?mibextid=ZbWKwL
ቴሌግራም:- https://t.me/AACABOFP
ዩቲዩብ:- youtube.com/channel/UCTPN7Re7T7tp_ekAhVuw2uA
ዋትሳፕ:-https://chat.whatsapp.com/FLSn12vRmsR9JsKUVDWxgtuuuu
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህግ ማስከበርና መልካም አስተዳደር ክላስተር የ2018 በጀት አመት እቅድ አፈጻጸም የግምገማ መድረክ አካሂዷል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህግ ማስከበርና መልካም አስተዳደር ክላስተር የ2018 በጀት አመት እቅድ አፈጻጸም የግምገማ መድረክ የተቋማቱ ሀላፊዎችና አስተባባሪዎች በተገኙበት የአፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ሰፊ ዉይይት ተካሄዷል።
በመርሃግብሩ ላይ ተገኝተዉ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ሀላፊና የክላስተሩ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ እንደገለፁት ክላስተሩ እቅድ ይዞ ወደ ተግባር የገባዉን ያለምንም መሸራረፍ በመተግበሩ በቅንጅት በርካታ ስራዎች መስራት መቻሉን ጠቁመዉ፣ሰላሟ የተረጋገጠባት ከተማ እንዲፈጠር ሀይማኖታዊና ባህላዊ የአደባባይ ኩነቶች ፍጹም ሰላማዊ እንዲሆኑ በመስራት የሕብረ ብሔራዊ አንድነት መገለጫ በሆነችዉ ከተማ የጸጥታ መዋቅሩ ከላይ እስከ ታች ህዝቡን የሰላም ባለቤት በማድረግ የአዲስ አበባን ሁለንተናዊ ደህንነት ላይ በስፋት ስለመሰራቱ ተናግረዋል።
ሀላፊዋ አያይዘውም በአጠቃላይ በክላስተሩ 15 ተቋማት የተሰሠሩ አበይት ተግባራትን በዝርዝር ያብራሩ ሲሆን በተደራጀና በተናበበ መልኩ በመሠራቱ ዉጤታማ ስራ መሠራቱንም ጨምረዉ ገልጸዋል።
የዉይይት መድረኩን የመሩት የክላስተሩ ሰብሳቢ የሆኑት ክብርት ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ በግምገማ መድረኩ የተገኙ ግኝቶች በክላስተሩ ላይ በ2019 እቅድ ላይ በማካተት የህዝቡን ን ሁለንተናዊ ጥያቄ ሊመልሱ የሚችሉ እንዲሆኑ በማስቻል በቅንጅት ዉስጥ የተሠጡ ተልእኮዎችን ተቋማት እንደየ ስራ ሀላፊነታቸዉ ላቅ ባለና ተጨባጭ ዉጤት ሊያመጣ በሚችል መልኩ በትኩረት እንደሚሰራ አመላክተዉ የፍትህ የበላይነትን በማረጋገጥ በግብ ያስቀመጥናቸዉን ህዝቡ ስጋት ዉስጥ እንዲገባ የሚያደርጉትን ስራዎች ከዚህ ቀደም ክላስተሩ እንደሰራዉ ሁሉ ከፊታችን የሚካሄዱ ትላልቅ ሁነቶች የ2019 የኢሬቻ በዓላትና የመስቀል ፣ሌሎች የአደባባይ በዓላት እንዲሁም አለም አቀፍ ሀገር አቀፍ ሁነቶች ለከተማዋ ተደማሪ የህብረብሔራዊነት መገለጫ እንዲሆኑ ክላስተሩ በበትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል።
የክላስተሩን አጠቃላይ የአመሠራረትና የስራ አፈጻጸም ሪፖርት በሰነድ መልክ የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ የአገልግሎት አሰጣጥና ስታንዳርዳይዜሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ አለምጸሃይ ማሞ አማካኝነት ቀርቦ ሰፋ ያለ ዉይይት ተደርጎበታል።
በመድረኩ የ15 ተቋማት ሀላፊዎች፣የክፍለ ከተማና የወረዳ ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ሀላፊዎች፣የፖሊስ አባላት፣የክፍለ ከተማ አስተባባሪዎችና የማእከል ዳይሬክተሮች ሲሆኑ በመጨረሻም በክላስተሩ በ2018 በጀት አመት የእቅድ አፈጻም ተቋማቱ ለነበራቸዉ የላቀ ተሳትፎ የምስጋና የምስክር ወረቀት በማበርከት መርሃግብሩ ተጠናቋል።
በአዲስ አበባ እየተከናወኑ ያሉ ዘመን ተሻጋሪ የልማት ስራዎች መዲናዋን የዓለም አቀፍ ትኩረት ማዕከል አድርገዋታል!
አዲስ አበባ ልክ እንደ ስሟ አዲስ እና ማራኪ ሆና በድጋሚ እየተወለደች ባለችበት በዚህ ወቅት፣ በመዲናዋ እየተከናወኑ ያሉ ዘመን ተሻጋሪ የኮሪደር፣ መልሶ ማልማት እና የወንዞች ዳርቻ ልማቶች የከተማዋን ገጽታ ሙሉ በሙሉ እየቀየሩት ነው።
ከጫፍ እስከ ጫፍ የተዘረጉ ዘመናዊ መንገዶች፣ ለእግረኞች እና ለብስክሌተኞች የተሰናዱ ምቹና ደህንነታቸው የተጠበቁ መንገዶች፣ እንዲሁም ለዓይን ማራኪ አረንጓዴ ስፍራዎችና መናፈሻዎች ከተማዋን ለነዋሪዎቿ እጅግ ምቹ እና ስሉጥ የኑሮ ከባቢ እንዲኖራት አድርገውታል።
የዚህ ታላቅ ለውጥ ሌላው አስደናቂ ገጽታ ፍትሃዊ የልማት ተደራሽነት መረጋገጡ መሆኑ ሲሆን፣ በአንድ አካባቢ ብቻ ሳይወሰን በሁሉም ክፍለ ከተሞችና ሰፈሮች ውስጥ በእኩል ደረጃ እየተዳረሰ ይገኛል።
ዛሬ አዲስ አበባ የአፍሪካ የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን በድምቀት አስጠብቃ፣ ዓለም አቀፋዊ ደረጃዎችን የሚያሟሉ መሠረተ ልማቶችን በማሟላት የኮንፈረንስ ቱሪዝም ዋና መዲና መሆን ችላለች።
ከዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚመጡ ታላላቅ እንግዶች የሚጎርፉባት፣ በንግድ፣ በባህልና በዕውቀት ልውውጥ ደምቃ የምትታይ፣ ቀንና ሌሊት እግር የሚበዛባት ሕያው ከተማ ሆና የምትቀጥለው መዲናችንን በሁሉ አቅጣጫ አብባና አምራ ማየት የጋራ ኩራት ነው።
ይህቺን ታላቅ መዲና በጋራ ጠብቆና ከፍ አድርጎ ማስቀጠል ደግሞ የሁላችንም ታሪካዊ ኃላፊነት ነው።
"የተሻሻሉት አዋጆችና ደንቦች የከተማ አስተዳደሩን ያደገውን በጀት መጠን (502 ቢሊዮን ብር) የሚመጥኑ፣ አገልግሎቶችን በቴክኖሎጂ ዲጂታላይዝ በማድረግ ቀልጣፋና ዘላቂ ልማትን የሚያረጋግጡ ናቸው።"
አቶ አብዱልቃድር ሬድዋን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ
ሐምሌ 14/2018 ዓ.ም ፋይናንስ ቢሮ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ቢሮ በተሻሻለው የግዢና ንብረት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 92/2018፣ በተሻሻለው የግዢ አፈጻጸም መመሪያ ቁጥር /2018 እና በተሻሻለው የፋይናንስ አስተዳደር ደንብ ቁጥር 202/2018 ዓ.ም ላይ ከሴክተር መስሪያ ቤት ኃላፊዎች፣ ከክፍለ ከተማ ፋይናንስ ጽህፈት ቤት ኃላፊዎች እና ከተቋማት ግዥና ፋይናንስ ዳሬክቶሬቶች ቡድን መሪዎች ጋር ውይይት አካሄደ።
የግዢና ንብረት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 92/2018፦ የአዋጁ መሻሻል ዋና አስፈላጊነት የኤሌክትሮኒክ የግዥ ስርዓትን ተግባራዊ ለማድረግ፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት፣ ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ፣ ወጪ ቆጣቢነትን ለማስፈን እና ግዥዎች በጊዜ ሰሌዳቸው መሰረት እንዲፈጸሙ ለማስቻል እና የልማት ድርጅቶች በመንግስት ግዥ ስርዓት ውስጥ የሚኖራቸውን ሚና እና ድርሻ በግልፅ በመደንገግ፣ መመሪያዎችን እንደሁኔታው የሚጠቀሙበትን አሰራር ለመዘርጋት ያለመ እንደሆነ በፋይናንስ ቢሮ የመንግስት ግዥ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል ብዙአየሁ በሰነዱ አብራርተዋል።
በኦዲትና ኢንስፔክሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ መዓዛ አበበ የግዥ አፈፃፀም መመሪያ ቁጥር /2018 የቀረበ ሲሆን፤ መመሪያው በአስፈጻሚ አካላት አዋጅ ቁጥር 84/2016 እና በግዥና ንብረት አስተዳደር አዋጁ ለፋይናንስ ቢሮ በተሰጠው ስልጣን መሰረት የተዘጋጀ ነው። የቀደመው መመሪያ ረጅም ጊዜ ያገለገለ ቢሆንም፣ አሁን ካለው የኢኮኖሚ እድገት፣ የገበያ ተወዳዳሪነት አንፃር ማሻሻል ማስፈለጉን ተናግረዋል።
የፋይናንስ አስተዳደር ደንብ ቁጥር 202/2018 ከተሻሻለው የፋይናንስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 51/2009 ጋር ተናባቢ ማድረግ፣ የአሰራር ጉድለቶችን ማረም፣ የበጀትና የጥሬ ገንዘብ አስተዳደር ጣሪያዎችን ወቅቱ ከደረሰበት ቴክኖሎጂ ጋር ማጣጣም፣ እንዲሁም እንደ እዳ መሰረዝ ያሉ አዳዲስ ድንጋጌዎችን በማካተት ለአፈጻጸም ምቹ እንደሆነ በቻናል አንድ ፕሮግራሞች ማስተባበሪያ ዩኒት አስተባባሪ አቶ አብይ ቢተው ገልፀዋል።
የመድረኩ ተሳታፊዎች በመመሪያው መሻሻል ላይ አስተያየትና ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን ላነሷቸው ጥያቄዎች በኃላፊዎች ምላሽ ተሰጥቷል።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱልቃድር ሬድዋን በማጠቃለያቸው እንደገለጹት፤ መድረኩ ተቋማት ወደ ፋይናንስ ቢሮ የሚያደርጉትን አላስፈላጊ ምልልስ አስቀርቶ ራሳቸውን ችለው እንዲወስኑ አቅም የሚፈጥር እና ቴክኖሎጂን በመጠቀም 24 ሰዓት አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ቢሮ ኃላፊው በቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችን ጠቅሰው በሂደት የሚያጋጥሙ ችግሮችን በስልጠና መፍታት፤ የኦዲት ግኝቶችን በአፋጣኝ የማጥራት ስራ መስራት፤ የ2018 በጀት ዓመት ሂሳብ በመዝጋት አርዓያነት ላሳዩ ክፍለ ከተሞችና ሴክተሮች ምስጋና በማቅረብ፣ ያላጠናቀቁ ተቋማት እስከ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም አጠናቀው ሪፖርት እንዲያደርጉ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ እናመሰግናለን !!
ዌብሳይት:- aabof.com.et
ፌስቡክ:-https://www.facebook.com/aabof.gov.et?mibextid=ZbWKwL
ቴሌግራም:- https://t.me/AACABOFP
ዩቲዩብ:- youtube.com/channel/UCTPN7Re7T7tp_ekAhVuw2uA
ዋትሳፕ:-https://chat.whatsapp.com/FLSn12vRmsR9JsKUVDWxgtuuuu
እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለን!
#######################
በከተማ ደረጃ በተካሄደው የ2018 በጀት ዓመት በተካሄደው የከተማ ሴክተር ቢሮዎች የአፈፃፀም ምዘና፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ቢሮ በከተማ ደረጃ ከሚገኙ ሴክተር ቢሮዎች ከፍተኛ አፈፃፀም ማሰመዝገብ ከቻሉ ተቋማት አንዱ በመሆን የእውቅና ሰርተፊኬት ተበርክቶለታል።
ይህ ከፍተኛ የስራ አፈጻጸም መምጣት የቻለው ከላይ እስከታች የሚገኝ ሁሉም አመራርና ባለሙያ ተናቦና ተግባብቶ በጋራ መስራት በመቻሉ ነው። በመሆኑም ሁላችሁንም እንኳን ደስ አላችሁ ልል እወዳለሁ።
በቀጣይ በጀት ዓመት ይህ ተግባብቶና ተናቦ የመስራት ባህል ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከአደራ ጭምር አሳስባለሁ!
ክቡር አቶ አብዱልቃድር ሬድዋን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ!
ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ እናመሰግናለን !!
ዌብሳይት:- aabof.com.et
ፌስቡክ:-https://www.facebook.com/aabof.gov.et?mibextid=ZbWKwL
ቴሌግራም:- https://t.me/AACABOFP
ዩቲዩብ:- youtube.com/channel/UCTPN7Re7T7tp_ekAhVuw2uA
ዋትሳፕ:-https://chat.whatsapp.com/FLSn12vRmsR9JsKUVDWxgtuuuu
ትጋት ያሸልማል!
በ2018 በጀት ዓመት የህዝባችንን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ስራዎችን በመስራት የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ቢሮዎች፣ ተቋማት፣ ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች እውቅናና ሽልማት አበርክተናል።
በዚሁም መሰረት፦
የካቢኔ አባል ከሆኑ ቢሮዎች፦(መኪና ተሸላሚዎች)
1ኛ. ሰላምና ፀጥታ ቢሮ
2ኛ. ጤና ቢሮ
3ኛ. ገቢዎች ቢሮ እና ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ
4ኛ. ትምህርት ቢሮ
5ኛ. ልዩ ተሸላሚ የሆነው :-ለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል
ከክፍለ ከተሞች፦ (መኪና ተሸላሚዎች)
1ኛ. ቦሌ ክፍለ ከተማ
2ኛ. ለሚኩራ ክፍለ ከተማ
3ኛ. አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ
የካቢኔ አባል ካልሆኑ ተቋማት፦ (መኪና ተሸላሚዎች)
1ኛ. ደንብ ማስከበር ባለስልጣን
2ኛ. መንገዶች ባለስልጣን
3ኛ. ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን
4ኛ. አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ባለስልጣን
5ኛ. ፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ሲሆን
በተጨማሪም 33 ወረዳዎች፣ ከሁሉም ክፍለ ከተማ ከእያንዳንዱ ወረዳ ከአንድ እስከ ሶስት የተሻለ አፈፃፀም ያላቸው ተሸላሚ ሆነዋል።
የካቢኔ አባል ከሆኑ ቢሮዎች፦የሰርተፍኬት ተሸላሚዎች
1. ፋይናንስ ቢሮ
2. ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ
3. ኮሙኒኬሽን ቢሮ
4. ንግድ ቢሮና
5. ፍትሕ ቢሮ
የካቢኔ አባል ካልሆኑ ተቋማት፦(የሰርተፍኬት ተሸላሚዎች)
1. ሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት
2. የመስሪያ ቦታዎች ልማት አስተዳደር
3. አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ
ከክፍለ ከተሞች:-
(የሰርተፍኬት ተሸላሚዎች)
1. ኮልፌ ክፍለ ከተማ
2. ልደታ ክፍለ ከተማና የካ ክፍለ ከተማ ናቸው።
ዛሬ የተሰጠነው እውቅናና ሽልማት የሁሉም አመራር፣ በየደረጃው ያሉ ባለሞያዎች፣ የባለድርሻ አካላት እና አብሮን ለሰራው ህዝባችን ለጋራ የቅንጅት ስራ የተሰጠ ሲሆን ይህም ይበልጥ ሰርተን የህዝባችንን የመልማት ፍላጎት የምናሳካበት፣ የውድድር መንፈስን የምንፈጥርበት፣ ወደኋላ የቀሩት ራሳቸውን ፈትሸው ወደፊት የሚመጡበት እንጂ የሚያዘናጋን አይደለም።
በመሆኑም፤ እውቅናው በቀጣይ በጀት ዓመት አልቀን በመስራት የህዝባችንን ተጠቃሚነት እንድናረጋግጥ፣ የአገልግሎት ተደራሽነትን አልቀን እንድንሰራ ከትልቅ አደራም ጭምር ነው።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን አብዝቶ ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
https://www.facebook.com/share/p/1DM5zd9rZc/
