fa
Feedback
Zehohitebirhan_official ዘኆኅተ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ገጽ

Zehohitebirhan_official ዘኆኅተ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ገጽ

رفتن به کانال در Telegram

የቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ሰንበት ት/ቤት ይፋዊ የቴሌግራም ገጽ ነው :: በዚህም ገጽ ላይ መንፈሳዊ ጹሁፎች ፣ የቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ መረጃዎች ፣ መልእክቶች እና ሌሎችም ይቀርቡበታል።

نمایش بیشتر
2 287
مشترکین
+324 ساعت
+167 روز
+4930 روز
آرشیو پست ها
ይህ መጠይቅ የተዘጋጀው የሰንበት ትምህርት ቤት በማኅበረሰቡ መካከል ያለውን በጎ ተጽዕኖ፣ ማኅበራዊ አገልግሎት እና የወጣቶች ሥነ-ምግባር ቀረጻ ሚና ለመገምገም ነው። ጥናቱ ይበልጥ ተጽዕኖ ፈጣሪ ሊያደርጉ የሚችሉ አዳዲስ የልማትና የበጎ አድራጎት ፕሮጀክቶችን ለመቀየስ ያለመ ነው። እርስዎ የሚሰጡን እውነተኛና ቀጥተኛ ምላሽ ለጥናታችን ጥራትና ስኬት እጅግ ወሳኝ ነው። በዚህ ፎርም የሚሰበሰበው ማንኛውም መረጃ ለዚሁ የጥናት ምርምር ሥራ ብቻ የሚውል ሲሆን፣ የእርስዎ ግላዊ መረጃ ሙሉ በሙሉ ምስጢራዊነቱ የተጠበቀ ይሆናል። የተለያዩ የጥያቄ ዓይነቶች የቀረቡ ሲሆን  እባክዎን ሁሉንም ጥያቄዎች በጥንቃቄ በማንበብ ምላሽዎን እንዲሰጡን በአክብሮት እንጠይቃለን። ለሰጡን ጊዜና ትብብር ከልብ እናመሰግናለን! https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSf8qlWxlejlXIMxq4ONiJj_FAIX4rOUYiOI1wtbl1qG7wpu6Q/viewform?usp=dialog

የኆኅተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ቤተሰቦች እንደሚታወቀው የክረምት ትምህርት በቅርቡ ይጀምራል እናንተም ቢማር ብላችኹ የምታስቡትን እኅት ፤ ወንድም ፤ ጓደኛ ፤ የስራ ባልደረባ ከታች ባሉት የመመዝገቢያ አማ
የኆኅተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ቤተሰቦች እንደሚታወቀው የክረምት ትምህርት በቅርቡ ይጀምራል እናንተም ቢማር ብላችኹ የምታስቡትን እኅት ፤ ወንድም ፤ ጓደኛ ፤ የስራ ባልደረባ ከታች ባሉት የመመዝገቢያ አማራጮች እናስመዝግብ፤ መንፈሳዊ ግዴታችንንም እንወጣ። ጎግል ፎርም፡ https://forms.gle/5iUBg9UWjWHs3CEy8 ቴሌግራም: @HbRegistrarBot

የኆኅተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ቤተሰቦች እንደሚታወቀው የክረምት ትምህርት በቅርቡ ይጀምራል እናንተም ቢማር ብላችኹ የምታስቡትን እኅት ፤ ወንድም ፤ ጓደኛ ፤ የስራ ባልደረባ ከታች ባሉት የመመዝገቢያ አማ
የኆኅተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ቤተሰቦች እንደሚታወቀው የክረምት ትምህርት በቅርቡ ይጀምራል እናንተም ቢማር ብላችኹ የምታስቡትን እኅት ፤ ወንድም ፤ ጓደኛ ፤ የስራ ባልደረባ ከታች ባሉት የመመዝገቢያ አማራጮች እናስመዝግብ፤ መንፈሳዊ ግዴታችንንም እንወጣ። ጎግል ፎርም፡ https://forms.gle/5iUBg9UWjWHs3CEy8 ቴሌግራም: @HbRegistrarBot

የኆኅተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ቤተሰቦች እንደሚታወቀው የክረምት ትምህርት በቅርቡ ይጀምራል እናንተም ቢማር ብላችኹ የምታስቡትን እኅት ፤ ወንድም ፤ ጓደኛ ፤ የስራ ባልደረባ ከታች ባሉት የመመዝገቢያ አማ
የኆኅተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ቤተሰቦች እንደሚታወቀው የክረምት ትምህርት በቅርቡ ይጀምራል እናንተም ቢማር ብላችኹ የምታስቡትን እኅት ፤ ወንድም ፤ ጓደኛ ፤ የስራ ባልደረባ ከታች ባሉት የመመዝገቢያ አማራጮች እናስመዝግብ፤ መንፈሳዊ ግዴታችንንም እንወጣ። ጎግል ፎርም፡ https://forms.gle/5iUBg9UWjWHs3CEy8 ቴሌግራም: @HbRegistrarBot

🔔 ለቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል ሰ/ት/ቤት አገልጋዮች በሙሉ! የኪነ ጥበብ ክፍላችን ያዘጋጀው የ፫ ወራት የተውኔት (ትወና) እና የሥነ-ጽሑፍ ሥልጠና ምዝገባ ተጀምሯል! 🎯 የሥልጠ
🔔 ለቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል ሰ/ት/ቤት አገልጋዮች በሙሉ! የኪነ ጥበብ ክፍላችን ያዘጋጀው የ፫ ወራት የተውኔት (ትወና) እና የሥነ-ጽሑፍ ሥልጠና ምዝገባ ተጀምሯል!
🎯 የሥልጠናው ዘርፎች፦ ሥነ-ጽሑፍ (ግጥም፣ ድርሰት) እና ትወና (የመድረክ ክህሎት)
📅 ቀናት፦ ረቡዕ (ምሽት 12:00) እና እሑድ (ከሰዓት 9:00) ⏳ የምዝገባ ማጠናቀቂያ፦ እስከ ሰኔ 02 ቀን ብቻ! ⚠️ ቦታው ለ፳ (20) አገልጋዮች ብቻ የተገደበ ነው።
የተሰጣችሁን የጸጋ ስጦታ በዕውቀት አሳድገው ማገልገል የሚፈልጉ ሁሉ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን አሁኑኑ ይመዝገቡ፦ 👇👇👇 📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌 https://forms.gle/HbzAqMoEH8C7psxGA 📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌 “ቤተ ክርስቲያናዊ ጥበብን ለቀጣዩ ትውልድ በብቃት እናስረክብ!”

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያናችን እና በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ። ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም. አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት አባታዊ የኀዘን መልእክት እንደሚከተለው ነው፦ መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ ‹‹ወረሰዩ አብድንቲሆሙ ለአግብርቲከ መብልዐ ለአዕዋፈ ሰማይ፣ ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም፦ የአገልጋዮችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፥ የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት።›› (መዝሙረ ዳዊት ፸፰፥፪) በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው። የእምነት ነፃነት ተደፍሮ መቶ ዓመታት ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በተቃጠለበት፣ እንዲሁም የካራ ኩፍቴና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በተዘረፈበት በዚህ ክፉ ቀን፤ በርካታ ምእመናን በግፍ መሰዋታቸውና በመቶዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ከቀዬአቸው መፈናቀላቸው ቤተ ክርስቲያናችንን በእጅጉ ያሳዘነ ክስተት ነው። የሰላም፣ የፍቅርና የታሪክ ማህደር የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በምድራዊ መከራ ውስጥ ያሉትን ምእመናን በምታጽናናበት በዚህ ወቅት ራሷ በፈተና ውስጥ ሆና ከመቸገሯም በላይ በአርሲ ምድር በተደጋጋሚ የሚስተዋለው በደልና ግፍ በሁላችንም ልቡና ውስጥ "እስከ መቼ?" የሚል የቁጭት እና የኀዘን ጥያቄን ፈጥሯል። በመሆኑም ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን። በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን። በመጨረሻም ቤተ ክርስቲያናችን ለሰላም፣ ለይቅርታና ለሰው ልጆች ክብር ሁል ጊዜ የምትቆም መሆኑን በመግለጽ ይህንን የኀዘን ሰዓት አምላካችን በምሕረቱ ያሳልፍልን፣ የሞቱትን ነፍሶቻቸውን በመንግሥቱ ይቀበልልን፣ የተጎዱትንም በቸርነቱ ያጽናናልን በማለት አባታዊ የኀዘን መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን። እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!! ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!! አሜን። አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም. አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ © የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት

ማሳሰቢያ ዛሬ ሳምንታዊው የሰንበት ትምህርት ቤታችን ጉባኤ ይኖራል ሁላችንም 11:00 ላይ እንገኝ:: ሰላም ቆዩ

ማንም መቅረት የማይችልበት የአባልነት ጥሪ!! ውድ የኆኅተ ብርሃን ቤተሰቦች ረቡዕ ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም በሰንበት ትምህርት ቤታችን የቀጣይ ሥራ አመራር ምርጫ አካሔድ በተመለከት ጠቅላላ ጉባኤ ይኖረናል በዕለቱም ከሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሥልጠና ስለሚኖር ከ8:30 ጀምሮ በመገኘት ኆኅተ ብርሃናዊ ግዴታችንን እንድንወጣ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡