Civil Engineering
رفتن به کانال در Telegram
*ለሲቪል ; ለአርክቴክቶች÷ለኮንስትራክሽን ÷ ለሀይድሮሊክ መሀንዲሶች እና ተማሪዎች የተዘጋጀ ትምህርታዊ ቻናል ፡፡ @engineer03 http://www.Indiabix.com በዚህ ደግሞ ማንኛውንም ጥያቄና መልስ ታገኛላችሁ! ╯▅╰╱▔▔▔▔▔▔▔╲╯╯☼ ▕▕╱╱╱╱╱╱╱╱┛▂╲╲╭ ╱▂▂▂▂▂▂╱╱┏▕╋▏╲╲ ▔▏▂┗┓▂▕▔┛▂┏▔▂▕▔ ▕▕╋▏▕╋▏▏▕┏▏▕
نمایش بیشتر1 366
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-27 روز
-330 روز
آرشیو پست ها
1 366
ክፍል አንድ፡ ስለ አዲሱ የሕንፃ አዋጅ ቁጥር 1356/2017 ማወቅ ያለብዎት ወሳኝ ነጥቦች!
*
ማንኛውንም ግንባታ ከመጀመርዎ ወይም የጥገና ሥራ ከማከናወንዎ በፊት የአዋጁን ይዘት መረዳት ከሕግ ተጠያቂነት ከመታደጉም በላይ፣ ንብረትዎን ካልተገባ ብክነት ይጠብቃል። ለዛሬ የአዋጁን ተፈጻሚነት፣ የ"ህንፃ" ትርጉም እና የግንባታ ባለቤቶች ግዴታን እንደሚከተለው በዝርዝር አቅርበንላችኋል።
🏢 "ህንፃ" የሚለው ቃል ሰፊ ትርጉም የተሰጠው ሲሆን የሚከተሉትን ግንባታዎች ያጠቃልላል፦
• ማንኛውም ለመኖሪያ፣ ለንግድ፣ ለኢንዱስትሪ ወይም ለሌላ አገልግሎት ታስቦ ከምድር በላይ ወይም በከርሰ-ምድር (Basement) የተገነባ ቋሚ ወይም ጊዜያዊ ግንባታ፤
• እንደ አጥር፣ የፍሳሽ ማስወገጃ መስመሮች፣ የውሃና መብራት ዝርጋታዎች ያሉ ተያያዥ ሥራዎች፤
• በህንፃው ግቢ ውስጥ የሚሰሩ መንገዶች እና ለህንፃው አገልግሎት እንዲውሉ ተለይተው የተሰሩ ማናቸውም መሰረተ-ልማቶች።
📍 የአዋጁ ተፈጻሚነት ወሰን (አንቀጽ 3)
አዋጁ በማንና የት ላይ ተፈጻሚ እንደሚሆን በአንቀጽ 3 ላይ በዝርዝር ተደንግጓል፦
• በከተሞች ውስጥ፦ 10,000 (አሥር ሺህ) እና ከዚያ በላይ ነዋሪዎች ባሏቸው ከተሞች በሚከናወኑ ግንባታዎች ሁሉ።
• ከከተማ ወሰን ውጭ፦ ለሕዝብ አገልግሎት የሚውሉ ሕንፃዎች (ትምህርት ቤት፣ ሆስፒታል ወዘተ)፣ የኢንዱስትሪ ወይም የዘመናዊ እርሻ ተቋማት እና የሪል ስቴት ግንባታዎች።
• ለነባር ሕንፃዎች፦ አዋጁ ከመውጣቱ በፊት የተገነቡ ሕንፃዎች ቢሆኑም፤ ለአካል ጉዳተኞች ተደራሽ ለማድረግ በሚደረግ ማሻሻያ እንዲሁም ለሕዝብ ደህንነትና ጤንነት አስጊ የሆኑ ሕንፃዎችን ለማስተካከል ወይም ለማፍረስ አዋጁ ተፈጻሚ ይሆናል።
@ConstructionProxy
1 366
📍 Location: Addis Ababa, T/Haymanot, Merkato and Jemmo
Transportation is not included.
1 366
🌊 የውሃ ጉልበት ወደ ብርሃን፦ የግድብ ስራ
የውሃ ኤሌክትሪክ ግድብ ማለት በተፈጥሮ የሚፈስን ወንዝ "ቆይ እስኪ!" ብሎ በመገደብ፣ የውሃውን የከፍታና የፍጥነት ጉልበት ወደ ጥቅም የመቀየር ጥበብ ነው። ሂደቱ ልክ እንደ ሰንሰለት የተያያዘ ነው።
1. ማከማቻና መነሻ (The Reservoir & Intake)ግዙፉ ግድብ ውሃውን ይይዘዋል። እዚህ ጋር ውሃው የእንቅስቃሴ ዝግጁነት (Potential Energy) ይኖረዋል ማለት ነው። ልክ በሩ ሲከፈት ውሃው በከፍተኛ ግፊት በጠባብ ቱቦዎች (Penstocks) ውስጥ ይወርዳል።
2. የመሽከርከር ጥበብ (The Turbine)ይህ በከፍተኛ ግፊት የሚመጣ ውሃ ተርባይን የተባለውን ግዙፍ መዘውር ይመታዋል። እዚህ ጋር የውሃው ግፊት ወደ እንቅስቃሴ ጉልበት (Mechanical Energy) ይቀየራል።
3. የብርሃን መፈጠር (The Generator)ተርባይኑ ሲሽከረከር ከእሱ ጋር የተያያዘውን ጄነሬተር ያሽከረክረዋል። በጄነሬተሩ ውስጥ ያሉት מגነቶች (Magnets) ሲሽከረከሩ የኤሌክትሪክ ፍሰት ይፈጥራሉ።
4. ማከፋፈል (Transformers & Grid)የተፈጠረው ኤሌክትሪክ በትራንስፎርመር አማካኝነት ቮልቴጁ ከፍ እንዲል ከተደረገ በኋላ፣ በረጅም የኤሌክትሪክ ገመዶች አማካኝነት እስከ ቤታችን ድረስ ይደርሳል።
✨ ለምን ይለያል? (The Magic of Hydropower)ታዳሽነት፦ ውሃው ተርባይኑን አሽከርክሮ አልፎ ይሄዳል እንጂ አይጠፋም፤ ለሌላ አገልግሎት (ለእርሻ፣ ለንጽህና) መዋል ይችላል። አስተማማኝነት፦ እንደ ፀሐይ ወይም ንፋስ ሳይሆን፣ ውሃን በግድብ አቁሮ በማስቀመጥ በፈለጉት ሰዓት ኃይል ማመንጨት ይቻላል።
ኢትዮጵያዊ ኩራት፦ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ (GERD) ያሉ ፕሮጀክቶች የዚህ ቴክኖሎጂ ትልቁ ማሳያና የሀገር ተስፋ ናቸው።በአጭሩ፦ ግድብ ማለት ተፈጥሮ የሰጠችንን የውሃ በረከት፣ በሰው ልጅ ጥበብ አቅልመን ጨለማን የምናበራበት ድልድይ ነው።
1 366
TEDDY_AFRO_ስምምነን_ጉሬጌ_Sememene_GuReggae_Track_5_Official_Lyrics_Video.mp34.96 MB
1 366
🏗️ ከበዓል መልስ የኮንስትራክሽን ሳይት ማኔጅመንት፦ የሰኞ ማለዳ ስንቅ
በዓላትን አክብሮ ወደ ሥራ የሚመለስ ሠራተኛ ላይ ድካም፣ ትኩረት ማጣትና መዘናጋት ሊታይ ይችላል። ይህ ደግሞ በኮንስትራክሽን ዘርፍ ለአደጋና ለሥራ መጓተት ዋነኛ መንስኤ ነው። ሰኞ ማለዳ ሥራ ከመጀመሩ በፊት የሚከተሉትን ነጥቦች መተግበር ውጤታማ ያደርጋል፦
1. የደህንነት ንቃተ-ተሃድሶ (Safety Toolbox Talk)በመጀመሪያው ቀን ጠዋት ሁሉንም ሠራተኞች በማሳተፍ አጭርና ግልጽ የሆነ የደህንነት ገለፃ ማድረግ። የትኩረት ነጥብ፦ ስለ ግል ደህንነት መጠበቂያ (PPE) አጠቃቀም፣ ስለ ሳይቱ አደገኛ ቦታዎች እና ስለ ተገቢ የሥራ ሂደቶች ማስታወስ። አላማ፦ የሠራተኛውን አእምሮ ከበዓል ድባብ አውጥቶ ወደ ሥራው ደህንነት እንዲመለስ ማድረግ።
2. የማሽነሪዎችና የሳይቱ ፍተሻ (Site Inspection)ሥራ ከመጀመሩ በፊት ለተወሰነ ጊዜ ተዘግቶ የነበረው ሳይትና ማሽነሪዎች በጥንቃቄ መፈተሽ አለባቸው። ማሽነሪዎች፦ ኤክስካቫተሮች፣ ዶዘሮችና ሌሎች ከባድ ማሽኖች ለብልሽት ወይም ለስርቆት አለመጋለጣቸውን ማረጋገጥ። መሠረተ ልማት፦ የኤሌክትሪክ መስመሮች፣ ስካፎልዲንግ (Scaffolding) እና ጉድጓዶች ደህንነታቸው የተጠበቀ መሆኑን መፈተሽ።
3. ድካምንና ሞራልን ማመጣጠንሠራተኞች በበዓል ምክንያት ሊደክሙ ስለሚችሉ ሥራውን ቀስ በቀስ ማስጀመር። ቀላል ጅምር፦ በመጀመሪያው ቀን ከባድና እጅግ ውስብስብ የሆኑ ሥራዎችን ከመጀመር ይልቅ ቀለል ያሉና የዝግጅት ሥራዎችን መስራት። ንቃት፦ የሠራተኞችን ንቃት መከታተል፤ በድካም ምክንያት የሚመጡ ስህተቶችን ለመቀነስ የአጭር ጊዜ እረፍቶችን መስጠት።
4. የሰው ኃይል ብቃትና ዝግጁነትእያንዳንዱ ሠራተኛ ለሥራው ብቁና በአካልም ሆነ በአእምሮ ዝግጁ መሆኑን ማረጋገጥ። ከበዓል መልስ የሚታዩ የጤና መጓደሎችን ወይም ከፍተኛ የትኩረት ማጣትን መለየት።
5. የሥራ ዕቅድ ክለሳ (Resource Planning)በበዓል ምክንያት የተቋረጡ ሥራዎችንና የቀሩ የጊዜ ገደቦችን (Deadlines) መገምገም። ሠራተኛውን ሳያስጨንቁ ፕሮጀክቱ በታቀደለት መሠረት እንዲቀጥል የጊዜ ሰሌዳውን ማስተካከል። ለማስታወስ፦ "ደህንነቱ የተጠበቀ ጅምር፣ የተሳካ ፕሮጀክት መሠረት ነው።"
1 366
⭐️የ mat foundation አይነቶች
1. Flat plate -
እንደ ፓድ ፋውንዴሽን ሆኖ ሙሉ ህንፃው ሚያርፍበትን ቦታ ይሸፍናል።
⏺ብረት ደግሞ ኮለን እና ሺር ዎል ያለበት ጋር spacing ማጥበብ (ብረት ጨመር ማረግ)
2. Plate thickened under the column
⏺የ ኮለኖቹ ሚመጣው ክብደት በ ሶሌታው ውፍረት ብቻ ልንቋቋመው ካልቻልን የኮለኖቹን ረድፍ ከ ሶሌታው ስር ጥልቀቱን እንጨምራለን
3. Piled raft foundation
⏺ማታችን በ pile ቢደገፍ ልክ እንደ pile cap ሆኖ ግን ጥልቀት የሌለው shallow
4. Beam and slab two way raft foundation
⏺ሶሌታችን ላይ ግሬድ ቢም ሲረበረብ አይነት ነገር
5. Ridged /cellular raft foundation
⏺ፋውንዴሽኑን እንደ ቤዝመንት ስንጠቀመው
6. Plate with pedestal
- ኮለኖቹ ላይ ከ ሶሌታው በላይ ኮርቻ ሲኖረው
1 366
እንዴት በደላሎች ይዘወራል?
👉የመንግስትና የግል ሽርክና ውጤቱ "ለሚ ናሽናል ሲሚንቶ" በደላሎች ሴራ እየታመሰ ነው ተባለ‼
የመንግስትና የግል ባለሀብቶች በጋራ ሽርክና (Joint Venture) የመሰረቱትና የሀገሪቱ ትልቁ የኢንዱስትሪ ተስፋ የሆነው ለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ምርት፣ በደሴ ከተማም ሆነ ኮምቦልቻ በደላሎችና ስግብግብ ነጋዴዎች "የዋጋ ቁማር" ሰለባ መሆኑን የምርቱ ተጠቃሚዎች ገልፀዋል።
ይህ በሰሜን ሸዋ ለሚ ከተማ አቅራቢያ የሚገኘው ግዙፍ ፋብሪካ፣ አንድ ኩንታል ሲሚንቶን በ1,140 ብር እያከፋፈለ ቢሆንም፤ በደሴና ኮምቦልቻ ከተማ ግን ምንም ዓይነት ይፋዊ የዋጋ ጭማሪ ሳይደረግ በ2,400 ብር እንዲሸጥ እየተደረገ ይገኛል በማለት ነው ጥቆማ አቅራቢዎቹ ያስረዱት።
የመንግስትና የግል ሽርክና የሆነው ኩባንያ ለምን በደላላ ቁጥጥር ስር ወደቀ?
ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት የመንግስት ድርሻ ያለበትና የህዝብን የግንባታ ፍላጎት ለማርካት የተቋቋመ መሆኑ ይታወቃል። ሆኖም ግን፣ ቀደም ሲል ምርቱ ደሴና ኮምቦልቻ ሲደርስ የትራንስፖርት ወጪ ተጨምሮበት በ1,500 ብር ሲሸጥ የቆየው ሲሚንቶ፣ አሁን ላይ በኩንታል የ900 ብር ልዩነት ታይቶበታል። ይህ ድንገተኛ "ዝርፊያ" የመንግስትና የግል አጋርነቱን ዓላማ የሚጻረርና የዜጎችን የመኖሪያ ቤት የመስራት ህልም የሚያጨልም ሆኖ ታይቷል።
በከተማዋ የሚገኙ ግንባታ አቅራቢዎችና ተጠቃሚዎች እንደገለጹት፤ በደላሎችና በወኪል አከፋፋዮች መካከል በተፈጠረ "ያልተገባ የጥቅም ትስስር" ሳቢያ ዋጋው ከአቅም በላይ ሆኗል።በዚህም "የግንባታ ዘርፉ ክፉኛ ፈተና ላይ ወድቋል"ብለዋል። በከተማዋ የተጀመሩ የግልና የመንግስት ግንባታዎች "ቀጥ" ብለው መቆማቸውን ጠቁመዋል።
"የመንግስት እጅ ያለበት ፋብሪካ ምርት እንዴት በደላሎች ይዘወራል?" የሚሉት ቅሬታ አቅራቢዎች፣ መንግስት አስቸኳይ ጣልቃ በመግባት ይህን የገበያ ምስቅልቅል እንዲያስተካክልና ወንጀለኞችን ተጠያቂ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።
1 366
+4
🛣️ የባቱ - አርሲ ነገሌ የፍጥነት መንገድ ግንባታ ዋና ዋና ሥራዎች ተጠናቀቁ!
የአዲስ አበባ - ሞያሌ - ናይሮቢ - ሞምባሳ ዓለም አቀፍ የመንገድ ኮሪደር አካል የሆነው የሞጆ - ሐዋሳ ክፍል 3 (ባቱ - አርሲ ነገሌ) የ57 ኪሎ ሜትር የፍጥነት መንገድ ግንባታ በስኬት መጠናቀቁ ተበሰረ።
📍 የፕሮጀክቱ ዋና ዋና መረጃዎች፦ርዝመት፦ 57 ኪሎ ሜትር የመንገዱ ስፋት፦ 31.6 ሜትር (ከመካከለኛ አካፋይ ጋር) ወጪ፦ 5.3 ቢሊዮን ብር (በዓለም ባንክ ድጋፍ የተሸፈነ) ተቋራጭ፦ ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ (CCCC) 🌟
ይህ የፍጥነት መንገድ ምን ፋይዳ አለው?የጉዞ ጊዜን ይቀንሳል፦ ከሞጆ - ሐዋሳ የነበረውን የ4 ሰዓት ጉዞ ወደ 2 ሰዓት ዝቅ ያደርገዋል። የንግድና ግብርና ትስስር፦ እንደ ስንዴ፣ ቲማቲም፣ ሽንኩርት እና ድንች ያሉ የግብርና ውጤቶች በፍጥነትና ሳይበላሹ ለገበያ እንዲቀርቡ ይረዳል። ቱሪዝምን ያነቃቃል፦ ወደ ሐይቅ ዳርቻዎች (ደምበል፣ ላንጋኖ፣ አብያታ፣ ሻላ) እና ወደ ሐዋሳ ለሚሄዱ ጎብኚዎች ምቹና ፈጣን ጉዞን ያረጋግጣል። ዓለም አቀፍ ትስስር፦ ይህ መንገድ 10,000 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የታላቁ የምስራቅ አፍሪካ ኮሪደር (ኬፕታውን ትራንስ አፍሪካን ሐይዌይ) ወሳኝ አካል ነው።
መንገዱ ዘመናዊ የትራንስፖርት ሥርዓት (ITS - Intelligent Transport System) የተገጠመለት በመሆኑ፣ ደህንነቱ የተጠበቀና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ ሆኗል።የአካባቢው ማህበረሰብም ሆነ የሀገሪቱ የንግድ እንቅስቃሴ ከዚህ ታላቅ ፕሮጀክት ከፍተኛ ተጠቃሚ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል። እንኳን ደስ አለን! 🇪🇹
1 366
+4
በጅግጅጋ የተገነባው ተለዋጭ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ሲገነባ የቆየው የ6.93 ኪሎሜትር ተለዋጭ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ፕሮጀክት መጠናቀቁን ተከትሎ፣ ደረጃውን የጠበቀ የትራፊክ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ተበሰረ።
መነሻውን የጅግጅጋ ከተማ መግቢያ አድርጎ ቶጎ-ጫሌ አደባባይ ላይ የሚያበቃው ይህ ግዙፍ የመንገድ ፕሮጀክት፣ 30 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ የተገነባ ነው። ግንባታው የእግረኛ እና የብስክሌተኞች መተላለፊያን ጨምሮ ዘመናዊ የከተማ መንገድ ሊያሟላቸው የሚገቡ መመዘኛዎችን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል።የመንገዱን ግንባታ ሀገር-በቀሉ ይርጋለም ኮንስትራክሽን ያከናወነው ሲሆን፣ የማማከርና የቁጥጥር ሥራው ደግሞ በኤልዳ አማካሪ ድርጅት እና በዳምራ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ጥምረት ተከውኗል።
ለዚህ ታላቅ የመሠረተ ልማት ግንባታ ማስፈጸሚያ የዋለው 672 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ሙሉ በሙሉ በፌደራል መንግሥት በጀት የተሸፈነ መሆኑ ተረጋግጧል።የመንገዱ መጠናቀቅ በተለይ በጅግጅጋ ከተማ መግቢያና መውጫ ላይ ይታይ የነበረውን ከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅ በከፍተኛ ሁኔታ ያቃልላል ተብሎ ይታመናል። ለጭነት ተሽከርካሪዎች፦ ከቶጎ-ጫሌ እና ከደገሀቡር የሚመጡ ከባድና ቀላል የጭነት ተሽከርካሪዎች የከተማዋን መሃል ሳያቋርጡ እንዲያልፉ አማራጭ ሆኖ ያገለግላል። ለከተማዋ ገጽታ፦ ፕሮጀክቱ የጅግጅጋን ሁለንተናዊ ዕድገትና ውበት ከማሳለጥ ባለፈ፣ የንግድ እንቅስቃሴውን ቀልጣፋ እንደሚያደርገው ተመልክቷል። በአሁኑ ወቅት የመንገዱ ዋና ዋና ስራዎች ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት የጀመረ ሲሆን፣ የትራፊክ ምልክቶች ተከላና ሌሎች ጥቃቅን የማጠናቀቂያ ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ ከወጣው መረጃ ለመረዳት ተችሏል።
1 366
73. የግንባታ ዘርፉ ስራ ግዥ ክፌያ አፆጻጸም - - - - - -
የመንግስት መ/ቤት የግንባታ ዘርፌ ስራ ግዥ ክፌያ የሚፆፀመው የግንባታውን የክንውን ዯረጃ መሰረት አዴርጎ እና የሚከተለውን አፆፃፀም ተከትል መሆን ይኖርበታሌ፡-
እንዯ ስራው ውስብስብነት ሇዚህ ዓላማ ከተቀጠረ አማካሪ ወይም ከመ/ቤቱ መሃንዲስ በሚሰጥ የክፌያ የምስክር ወረቀት መነሻነት ብቻ ይሆናሌ፡፡ የክፌያ የምስክር ወረቀት እንዱሰጠው ከሥራ ተቋራጩ ጥያቄ በቀረበበት በ7 (ሰባት) የሥራ ቀናት ውስጥ የቁጥጥር ስራውን የሚያከናውነው አማካሪ ወይም የመ/ቤቱ መሃንዲስ የምርመራውን ሥራ ማጠናቀቅ ይኖርበታል፡፡
የክፌያ የምስክር ወረቀት በአማካሪው ወይም በመ/ቤቱ መሃንዲስ ተረጋግጦ ሲቀርብ መ/ቤቱ በ30 (ሰሊሳ) ቀናት ተገቢውን ክፉያውን ለሥራ ተቋራጩ መፈፀም አለበት፡፡
በክፌያ የምስክር ወረቀት መሰረት ከሚፈጸመው ከእያንዲንደ ክፌያ ላይ ለግንባታ ሥራው ጥራት ዋስትና እንዱሆን 7% (ሰባት በመቶ) በማያዣ መልክ ተቀንሶ ይያዘሌ፡፡ የግንባታ ስራው ሲጠናቀቅ እና ጊዜያዊ ርክክብ ሲደረግ በዚህ ንዐስ አንቀጽ ፉዯሌ ተራ /ሠ/ መሰረት ከሚያዘው ገንዘብ ሊይ 50% (ሃምሳ በመቶ) ለሥራ ተቋራጩ ይለቀቃል፡፡ ቀሪው 50% (ሃምሳ በመቶ) ጊዜያዊ ርክክብ ከተደረገበት ጊዜ አንስቶ በአንድ ዓመት የጥገና ጊዜ ተይዞ የሚቆይ ሲሆን፣ የስራ ተቋራጩ በ12 ወራት የሚቆይ በሁኔታ ሊይ ያልተመሰረተ ዋስትና ካቀረበ የተያዘው ገንዘብ ይለቀቅለታል፡፡
(the text is due to font problem , read page 133 for more.)
1 366
የ2018 ዓ/ም 2ኛ ሩብ ዓመት የኮንስትራክሽን ስራዎች ቀጥተኛ ዋጋ ጥናት
2018E.C 2nd Quarter Construction Works (Only Direct Cost)t
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ
1 366
ስራ ላይ ያለው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን የህንጻ መመሪያና ስታንዳርድ ቁጥር 127/2014.
Addis Ababa City Administration Building Permit and Control Authority Building Guidelines and Standards (Directive No. 127/2014).
1 366
የ2018 ዓ/ም 2ኛ ሩብ ዓመት የኮንስትራክሽን ስራዎች ቀጥተኛ ዋጋ ጥናት
2018E.C 2nd Quarter Construction Works (Only Direct Cost)t
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ
