BOLE GENERAL SECONDARY SCHOOL(OFFICIAL PAGE)
رفتن به کانال در Telegram
1 981
مشترکین
+224 ساعت
+47 روز
-1230 روز
آرشیو پست ها
13/09/2018
ለ11ኛ ክፍል ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች ነገ ጠዋት 1፡00 ሰዓት ላይ ቱቶርያል በተጠናከረ መልኩ እንደሚሰጥ እና ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚደረግ እንገልጻለን፡፡
ለ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የመልቀቂያ ፈተና የኦንላይን ልምምድ ያድርጉ!
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ተፈታኞች ፈተና የሚለማመዱበት አድራሻ ይፋ አድርጓል።
ተፈታኞች በተደለደሉበት ክልል ወይም ከተማ አስተዳደር ትይዩ ያለውን ሊንክ በመጠቀም፣ User Name በሚለው ላይ የፈተና አዳራሽ መግቢያ ካርድ ላይ ያለውን አድሚሽን ቁጥር በማስገባት እና Password በሚለው ላይ 1234 በማስገባት በዴስክቶፕ ኮምፒውተር፣ በላፕቶፕ፣ በታብሌት፣ በስልክ እና በመሰል የኤልክትሮኒክስ መሳሪያዎች ማንኛውንም አይነት የኢንተርኔት አማራጭ በመጠቀም እስከፈተናው ድረስ መለማመመድ እንደሚችሉ ተገልጿል።
Repost from BOLE GENERAL SECONDARY SCHOOL(OFFICIAL PAGE)
ውድ ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች የ12ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና መስጫ ቀን የተሻሻለ መሆኑን ስንገልፅ የተያያዘውን መረጃ እንድትመለከቱ በማሳሰብ ነው።
Repost from Digital Exellence (Bole edu )
Photo from Eph
ውድ ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች የ12ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና መስጫ ቀን የተሻሻለ መሆኑን ስንገልፅ የተያያዘውን መረጃ እንድትመለከቱ በማሳሰብ ነው።
Repost from Digital Exellence (Bole edu )
Photo from Eph
04/09/2018
ውድ ተማሪዎች ከነገ ጠዋት ጀምሮ
1. ሁሉም ተማሪዎች 2:20 ሰዓት ላይ ተጠናቀው ግቢ ውስጥ በመገኘት ሰንደቅ ዓላማ ስነ-ስርዓት ላይ ይገኛሉ። አርፋጅ ተማሪዎች በተለመደው አስተዳደራዊ ውሳኔ የሚዳኙ ይሆናል።
2. ሁሉም ተማሪዎች ከነገ ጀምሮ በላይኛው በር በኩል የሚገቡ ይሆናል። ይህ የሆነበት ምክንያት የዩኒፎርም ÷ የመታወቂያ እና የጸጉር አቆራረጥ ሁኔታን ለመከታተል ነው።
ቀን 27/08/18
ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች
ሰኞ በቀን26/2018 ያልተገኛችሁ ተማሪዎችና በተከታታይ ቀሪ ኖርዋችሁ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸሁ የቀራችሁበትን ምክኒያት የሚገልጽ መረጃ ነገ ስትመጡ ቀሪ ለሚከታተላችሁ ር/መምህር እንድታቀርቡ።ማስረጃ የሌላችሁ ወላጆቻችሁ ን በማስመጣት የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ የምናስፈርማችሁ ሲሆን የት/ቤቱን ህግና ስርአትን የማታከብሩትን ሞዴል ፈተና ላይ የማናስቀምጣቸሁ መሆኑንን እያሳወቅን ወላጆችም እንድትከታተሏቸዉ ስንል እናስገነዝባለን ።
23/08/2018
ለ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች ነገ የቅዳሜ ቱቶርያል በተጠናከረ መልኩ እንደሚሰጥ እና ቁጥጥር እንደሚደረግ እየገለፅን ትላንት ርዕሰ መምህራን በየክፍላችሁ ያስተላለፍነውን መልዕክት በልዩ ትኩረት በመመልከት እንድትገኙ እናሳውቃለን። ማጠናከሪያው ላይ ያልተገኘ ተማሪ ከእስከአሁሉ የተለየ እርምጃ ት/ቤቱ እንደሚወሰድበት በጥብቅ እናስገነዝባለን።
የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ።
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ከሰኔ 24 እስከ ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቆናል።
በሌላ በኩል ፦
- የሬሜዲያል ፕሮግራም ሀገር አቀፍ ፈተና ከግንቦት 17 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ/ም ➡️ ግንቦት 19 ኢድ አልአድሃ
- የቅድመ ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ/ም
- የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (NGAT) ከሃምሌ 29 እስከ ሃምሌ 30 ቀን 2018 ዓ/ም
- የመሰረታዊ የንባብና የስሌት ክህሎት ምዘና ጥናትና ምርምር መረጃ መሰብሰብ ከሚያዚያ 26 እስከ ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ/ም ... ይሰጣል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሚያዚያ 16 ቀን 2018 ዓ.ም
@tikvahethiopia
16/08/2018
ማስታወሻ
ለ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች ነገ የቅዳሜ ቱቶርያል በተጠናከረ መልኩ እንደሚሰጥ እና የሚሞላ ፎርም በተነገራችሁ መሠረት ነገ ብቻ የሚጠናቀቅ ይሆናል።
ለ9ኛ ክፍል ተማሪዎች የነገ ፈተና በተነገራችሁ መሠረት ከ10ኛ ክፍል ተማሪዎች ጋር በጠዋት ፈረቃ የምትፈተኑ መሆኑን ለማስታወስ እንወዳለን።
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
