RN.05 - Channel
رفتن به کانال در Telegram
ከኢትዮጵያና አዉሮፓ የሚተላለፍ የራድዮ ፕሮግራም አዲሱን ዩቱብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ: https://www.youtube.com/c/RN05Channel ፌስቡክ ገፃችንን like ያድርጉ: https://www.facebook.com/RNZeroFive/ https://twitter.com/RNZeroFive Support Us: http://bit.ly/3c09jfJ https://RNZeroFive.com
نمایش بیشتر2 342
مشترکین
+524 ساعت
+67 روز
-730 روز
آرشیو پست ها
2 342
+1
~ 3ቱን ጥያቄዎች በመመለስ ይሳተፉ! ~
~~~~~~~
1- በደርግ, በኢህአዴግ እና በብልፅግና ዘመን ምርጫ ለሀገራችን ያመጣው ለዉጥና ፋይዳ ምንድን ነው?
2- ምርጫ ባይኖርስ ሀገራችንና ህዝባችን ምን የተለየ ነገር ይቀርባቸዋል ብለው ያስባሉ?
3.ሀገራችን ዉስጥ አሁን በደረስንበት ፖለቲካዊ እድገት የሀገራችንን መንግስታት የምናፀናበት ወይንም የምንቀያይርበት ደረጃ ላይ እንገኛለን ብለው ያስባሉን? እንዴት ?
#የአቅል_አይምሮ_ትዝብት_ለrn05
2 342
+1
#በአፓርታይዷ #አክሱም #ከተማ ኢድ አልተሰገደም! ይህ ለመጅሊሱ ምኑ ነው??
~~~~~~~~~~
.
"የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳይ ምክር ቤት ዋና ጸሐፊ ሀጅ መሀመድ ካሕሳይ አግላዩና ጨቋኙ አዲሱ የአክሱም ከተማ ስያሜ ተቀባይነት እንደሌለው እና ሙስሊሙ እንደሚታገልበት ገልጸዋል። ይህን ያሉት በመቐለ ህዝበ ሙስሊሙ የዒድ ሰላቱን ለመስገድ በተሰበሰበት ወቅት ነው። በአክሱም ለመጀመሪያ ጊዜ በዛሬው ዕለት የዒድ ሰላት አልተሰገደም። ሙስሊሙ የቁም እስረኛ ሁኖ በቤቱ አሳልፏል።" ትግራይ ሙስሊም ሚድያ እንደዘገበው
.
የፌደራል መጅሉሱ ገፅ ግን Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council በበኩሉ እንደተለመደው "የእድ አል አድሃ በዓል በመላው ሀገሪቱ በድምቀት እየየከበረ ይገኛል " ሲል ዘግቧል:: ይህ ማለት መጅልሱ #በአፓርታይዷ #አክሱም #ከተማ ሊሆን ስለሚችለው ነገር ቅድመ ጥረትም ሆነ ቅድመ ግንዛቤ የለዉም የሚለዉን ያሲዛል :: አልያም" መላ ሀገሪቱ" ማለት በመጅልሱ ካርታ መሰረት ከየት እስከየት ነው የሚለዉን ጥያቄ እንድናነሳ ያስገድደናል!
ለነገሩ የኢትዮጵያ የመንግስት ሚድያዎችም አክሱም አጀንዳ እንዳይሆን ቶሎ ብለው #መቀሌ ላይ ስለመሰገዱ በመዘገብ ለኢትዮጵያ ህዝብ ነግረዋል !! የመንግስት " መላ ሀገሪቱ " የተሰኘው ካርታ በዚህ ኬዝ ቢያንስ እስከ መቀሌ ይደርሳል:, የመጅሊሱስ?
.
በስትራቴጅና በልምድ አልያም በደመነፍስ የሚሰሩ ስራዎች ልዩነታቸው ግልፅ ነው! ለማለት ነው :: ይሄው ነው!"
#የአቅል_አይምሮ_ትዝብት_ለRN05
2 342
የመጣ ሁሉ እንደ ትራፊክ ፖሊስ ዳር እያስያዘ ይቀጣዋል! ብቻ (አልሃምዱሊላህ) አዛኙ ጌታችን አላህ አለን! የእሱ ውሳኔ ከሁሉም ውሳኔ በላይ ነው። የቀልባችንን ንፅህና በመልካም ንግግራችንና ተግባራችን መጠበቁ ላይ ይርዳን እንጂ፥ እሱ የተበዳዮች ወኪል ነው፤ ከምንፈራው ነገር ሁሉ ይጠብቀናል፣ የምንመኘውንም መልካም ነገር ሁሉ ይሰጠናል። ኢንሻአላህ!
.
እናንተስ ሃሳብ ምን ይመስላል?? ?
የእናንተን እይታ በኮመንት መስጫው ላይ አጋሩን!
=============
.
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive
2 342
ከመደጋገፍ ወደ መጠላለፍ፡ የጀመዓዎች አላማና- የመበስበስ ሚስጥር
#abu_fulan_ለrn05
.
በአንድ ሀገር ውስጥ የሙስሊሙን መንፈሳዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ለውጦችን ለማምጣት የሚቋቋሙ ጀመዓዎች መነሻ ራዕይ የተቀደሰ መሆኑ እሙን ነው። አብዛኞቹ የሚቋቋሙት የአማኙን እውቀት ለማሳደግ偏 ስነ ምግባሩን ለማነፅ፣ ህይወቱን ለማሻሻል እንዲሁም በሚኖሩበት ሀገር ፍትህን ለማስፈን እና ወደ እድገት ማማ ለማውጣት በማለም ነው።
.
ሆኖም ግን፣ በታሪክም ሆነ በወቅታዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች በተደጋጋሚ የሚታይ አንድ አሳዛኝ እውነት አለ፦ ሙስሊሙን ኡማ በሁለንተናዊ መልኩ ለማሳደግ የተነሱ ጀመዓዎች፣ በሂደት ፊታቸውን ወደ እርስ በእርስ ፍጅትና ጠላትነት ያዞራሉ። በውስጣቸው ያሉ ታላላቅ ምሁራን፣ ኡስታዞችና ሸኾች ከኢስላማዊ ማንነት ይልቅ ለቡድናዊ ማንነታቸውና ጥቅማቸው ጥብቅና ሲቆሙ ይታያሉ።
.
እነዚህ የለውጥ መሳርያ መሆን የነበረባቸው ጀመዓዎች ራሳቸው የችግሩ አካል የሚሆኑበት “ቡድናዊ ስብራት” ለምን ይከሰታል? ምክንያቶቹን እና መውጫ መንገዶቹን (በአላህ ፍቃድ) በዚህ አጭር ፅሁፍ በዚህ ዘርፍ ተመራማሪ ለሆኑ ሙስሊም ምሁራን መነሻ ሃሳብ ይሆን ዘንድ ካሳለፍኩት ትንሽዬ የዳዕዋ ስራ ተሞክሮዬ በመነሳት ለመዳሰስ እሞክራለሁ።
.
የቀልብ መቆሸሽ እና የጀመዓ ህልውና አባዜ
በየትኛውም ጀመዓ ውስጥ የኒያ (የግብ) መቀየር የጀመዓው "እጅ እጅ ማለት" ዋናው መንስኤ ነው። የትኛውም ጀመዓ ሲቋቋም “ኢስላምንና ሙስሊሙን ኡማ መኻደም" ዋና ግቡ መሆኑ ግልፅ ነው። ነገር ግን ጀመዓው አድጎ የራሱ መዋቅር፣ በጀት፣ ቢሮክራሲ እና የስልጣን ተዋረድ ሲኖረው፣ የውስጥ አባላቱ ትኩረት (ኒያ) ሳይታወቃቸው ይለወጣል።
.
ዋናው ትኩረት ኢስላምን መኻደም መሆኑ ቀርቶ “ጀመዓውን ማቆየት፣ ሰፊ ገቢ (በጀት) ማግኘት፣ ተደራሽነትን ማስፋት እና ከሁሉም ጀመዓዎች የበላይ መሆን እንዲሁም መጅሊስን የመሰሉ ህዝባዊ ተቋማትን መቆጣጠር” ይሆናል። በዚህ ጊዜ ጀመዓው ራሱን እንደ አንድ ኢስላማዊ ጀመዓ ሳይሆን ራሱ ኢስላምና የኢስላም ብቸኛ ተወካይ አድርጎ ማየት ይጀምራል። ከእሱ ውጭ ያሉ ተመሳሳይ አላማ ይዘው የተነሱ ጀመዓዎች ደግሞ እንደ አጋር ሳይሆን፣ የህልውና እና የጥቅም ተቀናቃኝ (ወይም ጠላት) ተደርገው መወሰድ ይጀምራሉ። ለጥቆ የሚከሰተውን ሙሲባ መመልከት የሚችል ሁሉ በገሀዱ አለም እየተመለከተው ስለሆነ፣ እዚህ ጋር መዘርዘሩ የተከበረውን አንባቢዬን ጊዜ በማቃጠል አላህ ፊት እንዳልጠይቅ እሰጋለሁ።
.
“እኛ እና እነሱ”፦ የቡድን ጭፍንነት ስነ-ልቦና
የሰው ልጅ ስነ-ልቦና በቡድን የመደራጀት እና ለገዛ ቡድኑ የማድላት ተፈጥሯዊ ዝንባሌ አለው። በጀመዓዎች ወይም በቡድኖች ውስጥ ያሉ አክቲቪስቶች፣ ምሁራንና ኡስታዞች አብዛኛውን ጊዜያቸውን፣ ጉልበታቸውን እና ማህበራዊ ህይወታቸውን የሚያሳልፉት በጀመዓው መዋቅር ውስጥ ነው። ይህም “እኛ” (የእኛ ጀመዓ አባላት) እና “እነሱ” (ከእኛ ውጭ ያሉ ጀመዓዎች) የሚል አደገኛ ስነ-ልቦናዊ ክፍፍል ይፈጥራል።
.
በዚህ ሂደት ውስጥ የጋራ ኢስላማዊ ማንነት ይደበዝዝና ቡድናዊ ማንነት ይገዝፋል። ምሁራንና ኡስታዞች ከኢስላም ይልቅ ለጀመዓው ባላቸው ታማኝነት መለካት ይጀምራሉ። የዚህ ስነ-ልቦና አደገኛው ጎን፣ ሌላው ጀመዓ የሚያደርገው እንቅስቃሴ ለኢስላምና ለሙስሊሙ ኡማ የሚጠቅም ቢሆን እንኳን “ከእነሱ” የመጣ ስላልሆነ ብቻ ውድቅ የማድረግ ወይም የማጠልሸት ዝንባሌ መፈጠሩ ነው። የዚህንም ተጨባጭ ውጤት ለተከበረው አንባቢዬ እተዋለሁ።
.
የፊክራ አክራሪነት
ጀመዓዎች ወይም ቡድኖች የራሳቸው የሆነ መርሃ-ግብር እና ርዕዮተ-ዓለም አላቸው። በውስጣቸው ያሉ ምሁራንና ኡስታዞች ይህንን መርሃ-ግብር ብቸኛው “ሙስሉሙን ኡማ ማዳኛ መንገድ” አድርገው የመውሰድ አዝማሚያ ያሳያሉ። ይህ ሲሆን የሚከተሉት ችግሮች ይከሰታሉ፦
.
~ የሃሳብ መድረቅ፦ ከራሳቸው መስመር ውጭ ያሉ አማራጭ መንገዶችንና የተሻሉ ሃሳቦችን ማስተናገድ ያቅታቸዋል።
~ የባለቤትነት ሽሚያ፦ “ሙስሊሙ ኡማ ሊድን የሚችለው በእኛ መንገድ ብቻ ነው” የሚለው እምነት፣ ሌላውን አካል እንደ አጋዥ ሳይሆን ኡማውን ወደ ተሳሳተ አቅጣጫ እንደሚመራ የኢስላም ጠላት አድርጎ የመፈረጅ አባዜን ይወልዳል። ይህ ጭፍንነት በመልካም "ኒያ" የተነሱ ጀመዓዎችን እርስ በእርስ እንዲፋለሙ እና የሞት ሽረት ጠላትነት ውስጥ ይከታቸዋል።
.
የአመራሩ ጥቅምና ስጋት
የጀመዓው አመራር ነገሮችን በቁርኣንና ሐዲስ መነፅር ከመመልከት ይልቅ ከጀመዓ ጥቅም አንፃር የመመልከቱ ምክንያት የግል ጥቅምን እና ዝናን አስጠብቆ የመጓዝ አባዜ ነው። በብዙ ጀመዓዎችና ስብስቦች ውስጥ ከፊት የመሆን፣ የእውቅና፣ የዝና፣ የጥቅማጥቅም ዋስትና መስፈርቱ “ለስብስቡ ወይም ለጀመዓው መስመር ታማኝ መሆን” እንጂ “ለእውነትና ለፍትሕ መቆም” አይደለም።
.
አንድ ሙስሊም ምሁር ለሙስሊሙ ኡማ ይበጃል ብሎ የጀመዓውን ስህተት በግልጽ ከተናገረ፣ ከጥቅማጥቅም መገለል ብቻ ሳይሆን እንደ ከሃዲ ሊቆጠር ይችላል። ይህ ፍርሃት ሙስሊም ምሁራን የህሊና ነጻነታቸውን አጥተው የጀመዓው አስፈጻሚ እና የጭፍን ትረካዎች ጠበቃ እንዲሆኑ ያስገድዳቸዋል።
.
መደምደሚያ እና መውጫ መንገድ
~~~~~~~
ሙስሊሙን ኡማ ለመኻደም ጀመዓ ወይም ቡድን ወይም ድርጅት ማቋቋም እጅግ አስፈላጊ መሣሪያ መሆኑ እሙን ነው። ነገር ግን መሣሪያው ራሱ ግብ መሆን የጀመረ ዕለት አደጋው የከፋ ይሆናል። ታዲያ እነዚህ በንፁህ ኒያ የተመሰረቱ ጀመዓዎች (ተብሊግ፣ ኢኽዋን፣ ሰለፊ፣ ሱፊ…) ሙስሊሙን ከማገልገል ወጥተው ወደ መጠላለፍ እንዳይገቡ የሚከተሉት የመከላከያ መንገዶች ያስፈልጋሉ፦
ኢስላማዊ የጋራ እሴቶች የበላይነት፦ ከማንኛውም ጀመዓ ወይም ስብስብ በላይ የሆኑ፣ ሁሉም የሚስማማባቸው ደማቅ ቀይ መስመሮች እና ኢስላማዊ የጋራ እሴቶች መጠበቅ የነፍስ ወከፍም የጋራ ግዴታችን በመሆኑ አላህ የሰጠንን አቅም ሁሉ በመጠቀም ልንጠብቃቸው ይገባል።
ቀጣይነት ያለው ራስን መፈተሽ፦ ኢስላማዊ ጀመዓዎችና ድርጅቶች “መጀመሪያ የተነሱበትን አላማ እያገለገሉ ነው ወይስ ሌላ አላማ?” የሚለውን በገለልተኛ አካል በየወቅቱ መገምገም አለባቸው።
የምሁራን የህሊና ነጻነት መከበር፦ በጀመዓዎች ወይም በስብስቦች ውስጥ ያሉ ሙስሊም ምሁራንና ኡስታዞች በነጻነት የተለየ ሃሳብ የሚያራምዱበት እና ጀመዓቸውን የሚተቹበት (Self-criticism) ባህል መገንባት አለበት።
ጀመዓ የለውጥ “መሳሪያ” እንጂ የለውጡ “መጨረሻ” አለመሆኑን ማመን ተገቢ ነው። በጥቃቅንና አነስተኛ ማንነት ተጠምቆ ትልቁን ኢስላማዊ ማንነት መሸርሸር እጅግ ግዙፍ ኃጢአት መሆኑ ፈፅሞ ሊዘነጋ አይገባም። በዚህ አይነቱ በሽታ የተጠቃ ጀመዓ፣ ከዚህ በሽታ እስካልተፈወሰ ድረስ፣ ጀመዓው የቱንም ያህል ኢስላምንና ሙስሊሙን ኡማ ያገለገለ ቢመስልም፣ አንድ ቤት እየገነባ፥ ሙሉ ከተማ እያፈረሰ መሆኑ ሊታወቅ ይገባል።
የመጨረሻ መልዕክቴ
የምንወዳችሁና የምናከብራችሁ ተሰሚነት ያላችሁ ኡስታዞችና መሻኢኾች! በቡድንተኛነት ልክፍት የተመቱ ጀመዓዎችን የማከም ስራችሁን አትዘንጉ። ከበሽታቸው የማይፈወሱ የመሆናቸው ምልክቶች ከታያችሁ ወይም የማከሙ አቅም የለንም ካላችሁ ደግሞ መነካካቱን አቁሙ። እባካችሁ እናንተ ተመታችሁ፣ ሚስኪኑን ኡማ አታስመቱት። ኡማው በስንቱ ይመታ?!
በዐቂዳው ተመታ!
በአኽላቁ ተመታ!
በገንዘቡ ተመታ!
በቤተሰቡ ተመታ!
በልጆቹ ተመታ!
2 342
~የአቡ ፍርድስ ማስታወሻ እና ራድዮ ነጋሺ ትዝታዎች !❤️🙏
~ የእህቶቻችን እና ወንድሞች የዋትሳብ ትግል ድምፅ ሲታወስ!❤️🙏
~~~
.#አቡፍርደዉስ እንደፃፈው
.
ራድዮ ነጋሺ፦ ከማይክሮፎን ባሻገር የተገነባው የ20 ዓመታት ሕያው ማኅበረሰብ እና ታሪካዊ ገድል
በሳውዲ ዓረቢያ የስደት ቆይታዬ ወቅት በጋዜጠኝነት ያሳለፍኳቸው ዓመታት እና ከራድዮ ነጋሺ (Radio Negashi) ጋር የነበረኝ ትስስር በሕይወቴ ውስጥ እጅግ ጥልቅና የማይረሳ ትዝታን ጥሎ ያለፈ ትልቅ የታሪኬ ምዕራፍ ነው።
ራድዮ ነጋሺ የሙስሊሙ ማኅበረሰብ ድምፅ ሆኖ ሲነሳ "ከድምጻችን ይሰማ" ታሪካዊ ንቅናቄ አስር ዓመታት ቀድሞ ነበር። ከስዊድን (ስቶክሆልም) እየተቀነባበረ በየሳምንቱ ማክሰኞ ማክሰኞ ወደ አድማጮቹ የሚደርሰው ይህ ጣቢያ፣ ለሁለት አስርተ ዓመታት (ለ20 ዓመታት) ሙሉ ለሕዝቡ ተደራሽ በመሆን ታላቅ መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት አበርክቷል።
እኔ ይህንን ተቋም በአድማጭነት አውቀውና እወደው የነበረ ቢሆንም፣ በባልደረባነት የተቀላቀልኩት ግን ጣቢያው ከተመሠረተ ከ10 ዓመታት በኋላ—ያንን ታላቅና ታሪካዊ የ"ድምጻችን ይሰማ" የመብት ትግል ተከትሎ ነበር። ራድዮ ነጋሺ በወቅቱ የሕዝቡን ብሶትና የትግሉን እንቅስቃሴ በአግባቡ በማስተጋባት ረገድ ግንባር ቀደም የነበረ እውነተኛ የሕዝብ ልሳን ነበር። እኔ ጣቢያውን ከተቀላቀልኩ በኋላ፣ ተቋሙ ከወትሮው የሚዲያ አሠራር ወጣ ባለ መልኩ ቴክኖሎጂን በመጠቀም በዓለም ዙሪያ ያሉ ሙስሊሞችን ልብ ያገናኘባቸውና አዳዲስ አብዮቶችን የፈጠረባቸው ድንቅ ማኅበረሰባዊ ተግባራት ተጀመሩ
.
1. የዕለት ተዕለት የመጽሐፍ ትረካዎች በዋትስአፕ (WhatsApp)
ሚዲያው ከሳምንታዊ ከአየር ሰዓት በተጨማሪ በዋትሳብ ወደ እያንዳንዱ ሰው ስልክ ዘልቆ መግባት የቻለበት አንዱ ትልቅ ስኬት በዋትስአፕ የተጀመረው መድረክ ነበር። በየዕለቱ በርካታ እህቶችና ወንድሞች ድምፃቸውንና ጊዜያቸውን መሥዋዕት በማድረግ፣ ጠቃሚ ኢስላማዊና ማኅበራዊ መጻሕፍትን በድምፅ እየተረኩ ለሺዎች ያደርሱ ነበር።
ይህ ጥረት ስደት ላይ ሆኖ መጻሕፍትን ለማግኘትና ለማንበብ ጊዜና ዕድሉ ለሌላቸው ወገኖች ትልቅ የእውቀት አምባ መሆን ችሎ ነበር።
2. የዙም (Zoom) ስቱዲዮ የጋዜጠኝነት ሥልጠናዎች
ተቋሙ ትግሉን በእውቀትና በጋዜጠኝነት ስነ ምግባር የታነፀ ትግል እንዲሆን ለማድረግ ስልጠና መስጠት ግድ ነበር ።
.
አዳዲስ አቅሞችን የሚፈጥር ማዕከልም ነበር በዘርፉ በሳልና ስመ-ጥር በሆኑ የሚዲያ ጋዜጠኝነት ባለሙያዎች አማካኝነት፣ በዙም ስቱዲዮ (Zoom Studio) አማካኝነት ጥራት ያላቸው የጋዜጠኝነት ሥልጠናዎች በየጊዜው ይሰጡ ነበር። ይህ ሥልጠና ከማንበብና ማዳመጥ ወደ ተግባር የተሻገሩ፣ እንደ እኔ ያሉ በርካታ አድማጮችን ወደ ንቁ የሚዲያ ባልደረባነትና የሕዝብ ድምፅነት ያሻገረ የዕውቀት ብርሃን ነበር።
.
3.አቡ ሾዎ በሚል ዓለም አቀፍ የግጥም ውድድሮች እና የኪነ-ጥበብ መነቃቃት
ራድዮ ነጋሺ የኪነ-ጥበብና የስነ-ጽሑፍ ማዕከልም ነበር። በዓለም ዙሪያ በሚገኙ ሙስሊም ገጣሚዎች መካከል በየጊዜው ታላላቅ የግጥም ውድድሮችን ያዘጋጅ ነበር። ይህ መድረክ በርካታ ድንቅና ስውር ተሰጥኦ ያላቸውን ገጣሚዎች ለዓለም ያስተዋወቀ ከመሆኑም በላይ፣ ለደረጃው የሚመጥኑ ማበረታቻዎችንና ሽልማቶችን በማበርከት በዓይነቱ ብቸኛና አርአያ የሚሆን የሚዲያ ተግባር ነበረው።
.
4. የልበ ብርሃን ድምፅ፦ ማየት ለተሳናቸው ወገኖች የተደረገ ተደራሽነት
ከሁሉ በላይ የራድዮ ነጋሺን የሰብአዊነት ልክ የሚያሳየው ማየት ለተሳናቸው ሙስሊም እህቶችና ወንድሞች ያደረገው ልዩ ድጋፍ ነው። የዕውቀት ብርሃን ለሁሉም እኩል መድረስ አለበት በሚል እምነት፣ የተለያዩ ኢስላማዊ መጽሔቶችንና ጽሑፎችን በድምፅ በመተረክና በማዘጋጀት እውቀቱ በቀላሉ እንዲደርሳቸው ይደረግ ነበር። ይህ ተግባር በጨለማ ውስጥ ላሉ ወገኖች የእውቀትና የእምነት ብርሃን የፈነጠቀ፣ ታላቅ የበጎ አድራጎት ገድል ነበር።
.
ከስቶክሆልም ማክሰኞ ማክሰኞ ይተላለፍ ከነበረው የ20 ዓመታት ታሪክ ጀምሮ፣ በ"ድምጻችን ይሰማ" ወቅት የነበረው ግንባር ቀደም ተጋድሎ፣ ከዚያም በዋትስአፕ፣ በዙምና በሰብአዊ ተግባራት የዘለቀው የራድዮ ነጋሺ ጉዞ ቀላል የሚባል ታሪክ አይደለም። እኔም መጀመሪያ በአድማጭነት፣ በኋላም በትግሉ ማግስት በታሪካዊ አጋጣሚ የሥራው ባልደረባ በመሆን ያሳለፍኳቸው የሳውዲ የኑሮ ዓመታት ዛሬም ድረስ በኩራትና በትዝታ የምመለከተው ታላቅ የሕይወቴ አሻራ ነው። . https://www.facebook.com/share/p/1BBE6FapbB/
2 342
ማንም ይሁን ማን በስህተቱ ልክ ብቻ ይተቻል፣ ተጠያቂም ይሆናል!
~~~~~~~~
#abu_fulan_ለRN05
.
አንድ ማህበረሰብ ጤናማ በሆነ መልኩ ሊገነባ የሚችለው፣ የማህበረሰቡ አባላት በሙሉ የሚመሩበት እኩል የሥነ-ምግባርና የህግ ሚዛን ሲኖር ብቻ ነው። ከእነዚህ መሰረታዊ መርሆች መካከል ዋነኛው፦ ማንም ይሁን ማን ከተሳሳተ በስህተቱ ልክ ብቻ ሊገሰፅና ተጠያቂ ሊሆን ይገባል የሚለው ነው።
.
ኃላፊነት፣ ግልፅነትና ተጠያቂነት የአንድ የበሰለ ማህበረሰብ መገለጫዎች ናቸው።
ስህተት በዘር፣ በሃይማኖት ወይም በስልጣን ደረጃ ታይቶ አይመዘንም።
ግለሰቡ የቱንም ያህል ተሰሚነትና ዝና ይኑረው—ኡስታዝም ይሁን ፈላስፋ፣ ወይንም ተራ አማኝ—በሰራው ጥፋት ልክ ብቻ ተጠያቂ መሆኑን ፈፅሞ ልንዘነጋው አይገባም።
.
በሰሞኑ አጀንዳዎች ዙሪያ...
ሰሙኑን አንድ ኡስታዝ "አላህ በህልሜ አናገረኝ" ሲሉ፣ ሌላኛው ፈላስፋ ደግሞ "ሙስሊምም ክርስቲያንም አይደለሁም" ማለቱ በማህበራዊ ሚዲያ ሲዘዋወር ሰንብቷል።
.
እነዚህን እጅግ አወዛጋቢ መልዕክቶች አብዛኛው ሙስሊም ማህበረሰብ አጨብጭቦ ከመቀበል ይልቅ፣ ከግለሰቦቹ ዝናና ማእረግ በላይ ለእምነቱ እውነት በመቆም ይህንን ስህተት ለማረም በገባው መጠን ሲረባረብ ታይቷል-ይህም አስደሳች ግብረ-መልስ ነበር ባይ ነኝ!
.
"የግለሰቦች ክብር ሁሌም መጠበቅ አለበት!" የሚለው መርህ የማይናወጥ አቋማችን ቢሆንም፣ የእምነታችንን አጥር ለመናድ መሞከር ግን በፍጹም የማይደፈር ደማቅ ቀይ መስመር ነው!
.
ከተሰጡት ማብራሪያዎች ምን እንረዳለን?
የኡስታዙ ማብራሪያ፦ በማህረሰባችን ትችትና ወቀሳ ምክንያት ከላይ የጠቀስነው ኡስታዝ "አላህ አናገረኝ" ያለዉን -ለማስተላለፍ የፈለጉት "ኢልሃም" (ጌታዬ አሳወቀኝ) ማለታቸው እንደሆነ በመግለጽ፣ በተደበሰበሰ መልኩም ቢሆን ስህተታቸውን አምነዋል። አልሃምዱሊላህ! ነገር ግን "አላህ በህልሜ አናገረኝ" የሚለው ቃል ራሱ አደብ ማጣት መሆኑ ሊሰመርበት ይገባል።
.
የፈላስፋው ማብራሪያ፦ "ሙስሊምም፣ ክርስቲያንም አይደለሁም" ያለው ፈላስፋ ደግሞ "በቃል እንጂ በተግባር ሙስሊም አይደለሁም" ለማለት የፈለገ አስመስሎ ረዥም ንግግር አድርጓል። አልሃምዱሊላህ! ይሁን እንጂ፣ ጉዳዩ እሱ እንደሚለው ስለ ተግባር ከሆነ "በተግባር ሙስሊምም ክርስቲያንም አይደለሁም" ማለት ጨርሶ ስሜት አይሰጥም። ቢያንስ "ክርስቲያን" የሚለውን ቃል ሳይጨምር "ሙስሊም አይደለሁም" ቢል ኖሮ ምን ማለቱ እንደሆነ መገመት ይቻል ነበር።
.
የማህበረሰባችን ንቃትና የተገኘው ትምህርት
ታዳጊው ትውልድ ፈጣሪውን (አላህን) እንዳይዳፈር እንዲሁም የክህደትን ቃላት ከአንደበት ማውጣት በዋዛ እንዳይመለከት የተደረገው ርብርብ እጅግ የሚያስመሰግን ነው። ይህ እንቅስቃሴ የማህበረሰባችንን ጤናማ እድገትና "ሁሉም ሰው በእኩል ደረጃ ተጠያቂ ነው" የሚለውን የእስልምና እሴት በተግባር ያሳየ ነው።
.
ይህንን ንቁ ትውልድ ላሳየኸኝ፣ ኡስታዙንና ፈላስፋውንም በጓሮ በር ወደ ሀቁ ለመለስካቸው አምላኬ የዘላለም ክብርና ምስጋና ይገባህ! አልሃምዱሊላህ!
.
አንድ ማሳሰቢያ፦
ምክንያታችን ምንም ይሁን ምን፣ ለጉዳዩ ሊሰጠው ከሚገባው ክብደት ለማሳነስም ይሁን ለማጋነን የምንሞክር ሰዎች አላህን እንፍራ! ለማለት እወዳለሁ፡፡
.
ሁላችንም ተሳሳች ነንና- የተሳሳተ ሰው በተሳሳተው ልክ የመጠየቅ ልምድ ሲዳብር፤ ፍርሃት ሳይሆን መከባበር፣ መበቀል ሳይሆን መተራረም የሰፈነበት ጠንካራ ማህበረሰብ መገንባት ይቻላልና።
.
እናንተስ ሃሳብ ምን ይመስላል?? ?
የእናንተን እይታ በኮመንት መስጫው ላይ አጋሩን!
=============
.
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive See less See less .
#ተጠያቂነት #እኩልነት #የማህበረሰብ_ንቃት #ኢስላማዊ_እሴቶች
2 342
~በእርግጥ ሁላችንም መለዮ ለባሾች ነን?!
~~~~~~
#የአቅል_አይምሮ_ትዝብት
.
በዋናነት በሚመለከተው ሃይማኖታዊ ጉዳይ በ #አፓርታይዷ_አክሱም በሙስሊሞች ላይ የሚደርሰዉን ግፍና በደል በተመለከተ አንድ መስመር መጻፍ ወይንም ቃል መተንፈስ ያልቻለውና ስራው በዉን ምን እንደሆነ ግራ የሚያጋባው የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ እነሆ "ሀገር አቀፍ የሰላምና የጸሎት መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ላካሂድ ነው፣ ሀገር አቀፍ የሰላምና የጸሎት መርሃ ግብር ግንቦት 16 ቀን 2018 በአዲስ አበባ አራዳ ፓርክ አካሂዳለሁ" ሲል አዉጇል፡፡ ፓርክን በጋራ ጸሎት ለመክፈት ነዉን? ይህ የተቋሙ ታላቅ ግብ ነዉን? ስንት ጥሪ የሚያሻቸው ጉዳዮች አልተከሰቱምን?
.
ብዙ የሃገራችን ተቋማት የተመሰረቱበት አላማና የሚሰሩት ስራ ሁሌም ግራ እንዳጋባ ቀጥሏል፡፡
.
ምናልባት መጅሊሱ ራሱ የዚሁ አካልና ሞተር ሆኖ እንጂ ፣ እንዲሁም ምን ያህል መወሰን ይችላል የሚለው ጥያቄ ምላሽ የሚሻው ሆኖ እንጂ በእርግጥም ተቋሙን ለቆ መዉጫው ጊዜ እጅግ ቢዘገይም ቢያንስ አሁን መሆን ነበረበት!
.
እናንተስ ሃሳብ ምን ይመስላል?? ?
የእናንተን እይታ በኮመንት መስጫው ላይ አጋሩን!
=============
.
ለተጨማሪ መረጃ ቴሌግራማችንን ተቀላቀሉ
https://t.me/RNZeroFive
2 342
~ የትግራይ ሲኖዶስ አዋጁ የአክሱምን የዓለም ቅርስነት ደረጃ እንዴት አደጋ ላይ ይጥለዋል?
~~~~~~~~~~~~
Mohammedawel Hagos እንደፃፈው
.
ዛሬ በ«አዲስ ስታንዳርድ» ላይ “Legacy of All, Possession of One: How religious declaration endangers Axum's World Heritage status” በሚል ርእስ በወጣው አዲስ መጣጥፌ (commentary) ላይ ከሁለት ሳምንት በፊት የትግራይ ሲኖዶስ ያሰለፈው ውሳኔ በዩኔስኮ (UNESCO) የተመዘገበውን የዓለም ቅርስነት ክብር እንዴት አደጋ ላይ ሊጥለው እንደሚችል ለማሳየት ሞክሬአለሁ። በዚህ ጽሁፌ ላይ ያነሳኋቸው ዋና ዋና ነጥቦችን የሚከተለኡት ናቸው፦
የ«ቅድስት ከተማ» አዋጅ እና የህግ ረቂቅ፦ የትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሲኖዶስ አክሱምን "ቅድስት ከተማ" በማለት ማወጁን ተከትሎ፣ በከተማዋ አልኮልና ጫትን ለመከልከል፣ ሆቴሎችን ለመቆጣጠርና የመላ ከተማዋን መልክ ለመቀየር የሚያስችሉ "ህጎችን" እያዘጋጀ መሆኑን አስታውቋል። ይህ ህገ-መንግስታዊውን የሃይማኖትና የመንግስት መለያየት (አንቀፅ 11) የሚጥስ መሆኑን አንስቼአለሁ።
የታሪክ መፋለስ፦ አክሱም በአብዛኛው የታሪክ ዘመኗ ክርስቲያን አልነበረችም። ታዋቂዎቹ የአክሱም ሐውልቶች የተተከሉት ክርስትና ከመምጣቱ በፊት፣ በአረማውያን (Pagan) ነገሥታት ዘመን ለቀብር መታሰቢያነት ነበር። የዩኔስኮ ምዝገባም ይህንን የሰው ልጅ የጥበብ እና የባህል ብዝሃነት ውጤት ነው የሚቀበለው።
የመጀመሪያው ስደት (ሂጅራ) አሻራ፦ አክሱም የክርስትና ብቻ ሳይሆን የኢስላምም ወደ አፍሪካ መግቢያ በር ነች። የነገሥ (አሥሐማ) ለነቢዩ መሐመድ ተከታዮች የሰጠው ጥበቃ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ የፍትህ መገለጫ ነበር። አክሱምን ለአንድ ሃይማኖት ብቻ ማጥበብ ይህንን ታላቅ ታሪክ መካድ ነው።
የአፄ ዮሐንስ አራተኛ የታሪክ ቅራኔ፦ ሲኖዶሱ ለአፄ ዮሐንስ አራተኛ "ሰማዕትነት" እውቅና መስጠቱ የታሪክ ጠባሳዎችን ይቀሰቅሳል። ጄ. ስፔንሰር ትሪሚንግሃም (1952) እንዳስፈረው፣ በንጉሱ ዘመን በወሎ፣ በጎንደርና በትግራይ (በተለይም በአክሱም) ሙስሊሞች ላይ አስገዳጅ ጥምቀት፣ ስደትና የመጻሕፍት መቃጠል ደርሷል። ይህንን ታሪክ ወደ ቅዱስነት ማምጣት ዕርቅን አያወርድም።
የአሁኑ ቀውስ፦ ሚያዝያ 12 ቀን 2018 ዓ.ም በተላለፈው ውሳኔ መሠረት ሂጃብ ተከልክሏል፣ የጁምዓ ሶላት እንዳይሰገድ ታግዷል፣ አዛን ተከልክሏል፣ የሙስሊሞች የቀብር ሥነ-ሥርዓት በዋናው አስፋልት ላይ እንዳያልፍ ተደርጓል። ይህም የአክሱም ሙስሊሞችን የመኖር መብት የሚነፍግ ነው። ፕሮቴስታንቶችም በተመሳሳይ የቤተክርስቲያን መሥሪያ ቦታ ተከልክለዋል።
መንግሥት በጥር 2018 ዓ.ም የነጋሽ መንደርን "የሰላምና አብሮ መኖር ተምሳሌት" በማለት በዩኔስኮ የጊዜያዊ ቅርስነት መዝገብ ላይ አቅርቧል። በአንድ በኩል ሂጅራን እያወደሱ፣ በሌላ በኩል በአክሱም ሙስሊሞችን ማግለል ፍጹም የግብዝነት ቅራኔ ነው።
መፍትሔው ምንድን ነው? (የሁለት ቀጠናዎች መፍትሔ - Two-Zone Solution)
የመጀመሪያው ቀጠና (የገዳማቱ ክልል)፦ በጽዮን ማርያም ቤተክርስቲያንና በገዳማቱ ዙሪያ ያለው የተከለለ ቦታ የኦርቶዶክስ እምነትን ቅድስና በጠበቀ መልኩ ይከለላል፤
ሁለተኛው ቀጠና (የዓለማዊቷ ከተማ ክልል)፦ ቀሪው የአክሱም ከተማ ክፍል በኢፌድሪ ሕገ-መንግሥት መሠረት የሚመራ፣ የሃይማኖት እኩልነት የተረጋገጠበት፣ ሙስሊሞች መስጂድ የሚሠሩበት፣ ሂጃብ የሚለብሱበት፣ ፕሮቴስታንቶችም እምነታቸውን በነፃነት የሚያስፋፉበት ሰፊ የከተማው አካል መሆን አለበት።
በዚህ ጽሁፌ የፌደራል መንግሥት፣ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር እና ዩኔስኮ (UNESCO) በአክሱም ላይ እየተካሄደ ያለውን የሰብአዊና የሃይማኖት መብት ጥሰት እንዲያስቆሙ፣ ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱ እንዲከበር እና የአክሱም የዓለም ቅርስነት ለሁሉም የሰው ልጅ የጋራ ቅርስነቱ እንዲጠበቅ የበኩላቸውን እንዲያደርጉ ጥሪ አቀርባለሁ።
አክሱም የማግለልና የጭቆና ሳይሆን የፍትህና የአብሮነት ተምሳሌት ሆና መቀጠል አለባት!
የመጣጥፉን ሙሉ ይዘት በአዲስ ስታንዳርድ ድረ-ገፅ ላይ (https://addisstandard.com/legacy-of-all-possession-of.../) ማንበብ ትችላላችሁ። ሃሳባችሁን በኮሜንት አጋሩኝ።
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
