HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
رفتن به کانال در Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
نمایش بیشتر2 271
مشترکین
-424 ساعت
+127 روز
+2630 روز
آرشیو پست ها
«በፍትወታት መካከል የልቡና ቁጣ የሚባል አለ፤ ይህ ቁጣም ከተፈጥሮ ጋር የሚስማማ ነው። ያለ ቁጣ ሰው ንጽሕናን ሊቀዳጅ አይችልም፤ በጠላት የሚዘራበትን ነገር ሁሉ መቆጣት ይገባዋል። ኢዮብ ይህ ቁጣ በተሰማው ጊዜ ጠላቶቹን እንዲህ ሲል ተራግሟል፦ ‘ክብር የሌላችሁ፣ ስም የሌላችሁ፣ መልካም ነገር ሁሉ የጎደላችሁ፤ የመንጋዬን ጠባቂ ከሆኑ ውሾች ጋር እንኳ አብረዋቸው እንዲኖሩ ብቁ አድርጌ የማልቆጥራቸው ሰዎች ናችሁ’ (ኢዮብ 30፡1, 4 ንጽጽር፤ ሰብዓ ሊቃናት)። ይህንን ከተፈጥሮ ጋር የሚስማማውን ቁጣ ሊቀዳጅ የሚሻ ሰው፣ በውስጡ ለልቡናው ተፈጥሯዊ የሆነውን ሁኔታ እስኪያጸና ድረስ የራስን ፈቃድ ሁሉ ሰቅሎ መጣል አለበት።»
*ማብራሪያ፡ "ፍትወታት" (በግሪክ፡ πάθος) የሚለው ቃል እዚህ ላይ እንደ ኃጢአተኛ ምኞቶች ብቻ ሳይሆን፣ የነፍስ ተፈጥሯዊ ችሎታዎችንና ስሜቶችን ሁሉ ያጠቃልላል።
«የዕለቱን ወንጌል አናንብብ!»
(የማርቆስ ወንጌል 13፡14-21)
«ነገር ግን በነቢዩ በዳንኤል የተባለውን የጥፋት ርኵሰት በማይገባው ስፍራ ቆሞ ብታዩ፥ አንባቢው ያስተውል፥ በዚያን ጊዜ በይሁዳ ያሉ ወደ ተራሮች ይሽሹ፥ በሰገነትም ያለ ወደ ቤት አይውረድ ከቤቱም አንዳች ይወስድ ዘንድ አይግባ፥ በእርሻም ያለ ልብሱን ይወስድ ዘንድ ወደ ኋላው አይመለስ። በዚያን ወራትም ለርጉዞችና ለሚያጠቡ ወዮላቸው። ነገር ግን ሽሽታችሁ በክረምት እንዳይሆን ጸልዩ፤ በዚያን ወራት እግዚአብሔር ከፈጠረው ከፍጥረት መጀመሪያ ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ያልሆነ ደግሞም የማይሆን የመከራ ዓይነት ይሆናልና። ጌታስ ወራቶቹን ባያሳጥር፥ ሥጋ የለበሰ ሁሉ ባልዳነም፤ ነገር ግን ስለ መረጣቸው ምርጦች ወራቶቹን አሳጠረ። በዚያን ጊዜም ማንም። እነሆ፥ ክርስቶስ ከዚህ አለ፥ ወይም። እነሆ፥ ከዚያ አለ ቢላችሁ አትመኑ።»
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
«ዑራኤል የተባለ መላእክ ሊረዳኝ መጣ» (ዕዝ.ሱቱ ፪፥፩)
«በነገደ መላእክት ከተሾሙት ሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ቅዱስ ዑራኤል የቅዳሴ ቤቱ የሚከበርበትና ለነቢዩ ዕዝራ ሱቱኤል የዕውቀትን ጽዋ ያጠጣበት ዕለት ሐምሌ ፳፪ በቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ይከበራል፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ዑራኤል የጸሎቱና የረዳትነቱ ኃይል አይለየን፤ አሜን!»
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
«ስለ ጨለማ ጊዜያት»
«አየሩ ከደመናማ ወደ ጥርት ከዚያም ወደ ዝናብ ይቀየራል፤ ከሰው ተፈጥሮ ጋርም እንዲሁ ነው። አንድ ሰው ሁልጊዜ ደመናት ፀሐይን አንዳንድ ጊዜ እንደሚሰውሩ መጠበቅ አለበት። ቅዱሳን እንኳ የጨለማ ሰዓታት፣ ቀናትና ሳምንታት ነበሯቸው። ያኔ "እግዚአብሔር ትቷቸዋል" ይላሉ፤ ያለ እርሱ ድጋፍ ምን ያህል እጅግ በጣም ወራዳ እንደሆኑ በእውነት እንዲያውቁ። እነዚህ የጨለማ ጊዜያት፣ ሁሉም ነገር ትርጉም የለሽ፣ አስቂኝና ከንቱ ሲመስል፣ አንድ ሰው በጥርጣሬና በፈተናዎች ሲከበብ፣ የማይቀሩ ናቸው። ነገር ግን እነዚህ ጊዜያት እንኳ ለበጎ ሊሰበሰቡ ይችላሉ።
የጨለማ ቀናትን በቅድስት ማርያም ዘግብጽ ምሳሌ በመከተል በተሻለ ማሸነፍ ይቻላል። ለአርባ ስምንት ዓመታት ከዮርዳኖስ ማዶ በበረሃ ኖረች፤ እናም ፈተናዎች ሲደርሱባትና የቀድሞ ኃጢአተኛ ሕይወቷ በአሌክሳንድሪያ ወደ በረሃ በፈቃደኝነት የገባችውን ቆይታ እንድትተው ሲጠሯት፣ መሬት ላይ ትተኛለች፣ ለእርዳታ ወደ እግዚአብሔር ትጮኻለች፤ ልቧ እስኪዋረድ ድረስም አትነሣም ነበር። የመጀመሪያዎቹ ዓመታት ከባድ ነበሩ፤ አንዳንድ ጊዜ በዚህ መንገድ ለብዙ ቀናት መተኛት ነበረባት፤ ነገር ግን ከአሥራ ሰባት ዓመታት በኋላ የእረፍት ጊዜ መጣ።
በእንዲህ ባሉ ቀናት ጸጥ በል። ወደ ማኅበራዊ ሕይወት ወይም መዝናኛ እንድትወጣ አትሸነፍ። ራስህን አትራራ፤ ከጌታ ጩኸትህ ውጭ በምንም ነገር መጽናኛ አትፈልግ፦ አቤቱ፥ እኔን ለማዳን ፍጠን! አቤቱ፥ እኔን ለመርዳት ፍጠን (መዝሙር 70፡1)! በእስር ቤት በጣም ፈጥኛለሁ መውጣት አልችልም (መዝሙር 88፡8)፤ እና ሌሎች እንዲህ ያሉ ልመናዎች። ከሌላ ምንጭ እውነተኛ እርዳታ ልትጠብቅ አትችልም። ለአጋጣሚ እፎይታ ስትል ያሸነፍከውን ሁሉ አትጣል። ሽፋኖቹን በራስህ ላይ ጎትት፤ አሁን ትዕግሥትህና ጽናትህ እየተፈተኑ ነው። ፈተናውን ከጸናህ፣ ጥንካሬውን የሰጠህን እግዚአብሔርን አመስግን። ካልጸናህ፣ በፍጥነት ተነሥ፣ ምሕረትን ጸልይና አስብ፦ የሚገባኝን አገኘሁ! ምክንያቱም ውድቀቱ ራሱ ቅጣትህ ነበር። በራስህ ላይ በጣም ተማምነህ ነበር፤ እናም አሁን ወደ ምን እንደመራህ ታያለህ። ልምድ አግኝተሃል፤ ምስጋና መስጠትን አትርሳ።»
3ቱ የክፉ መናፍስት በእኛ ውስጥ የመደበቅና የማድፈጥ ጥበብ!! ከሚጸልየው ጋር ትጣላለህ ከማይጸልየው ጋር ትስማማለህ! የብጹዕ አቡነ ኤርሚያስ ጥብቅ መልዕክት! https://youtu.be/f-7koGiUj7k
«የዕለቱ የምክር ቃል»
ቅዱስ፣ ጥንቁቅ፣ ግልጽና ብልህ ሁን፡፡ እርጋታን የተላበሰ ሰብእና ይኑርህ፡፡ ደስተኛ ሁን፤ ሰላምታህ በፈገግታ የታጀበ ንጹህ ይሁን፡፡ ንግግርህ የታረመ አጭርና በጨው እንደተቀመመ ጣፋጭ ይሁን፡፡ ቃላቶችህ የተመጠኑ እና ጤናሞች ሁሉም የሚረዳቸው ይሁኑ፡፡
የጓደኛህን ምስጢር አትግለጥ፤ ለሚወዱህ ሁሉ የታመንክ ሁን፡፡ ወደ ጭቅጭቅ እና ንትርክ ከመግባት ራህን ጠብቅ፡፡ የሚሰሙህ ሁሉ እንዳይጠሉህ ወደ ጠብ አትግባ፡፡ ከሰይጣን በቀር ምንም ጠላት አይኑርህ፡፡
የሰዎችን ስህተት አትመራመር፤ የባልንጀራህ ኃጢአት አትግለጥ፡፡ የባልጀራህ ውድቀት ደጋግመህ አታውራ፡፡ በራስህ ኃጢአት ላይ ፍረድ እንጂ በሌሎች ላይ አትፍረድ ገዢያቸው አይደለህምና፡፡
ኃጢአትን በፈጸመ ሰው ላይ ወቀሳ አታብዛ አንተም ትበድላለህና፡፡ ነገር ግን ከኃጢአቱ ይመለስ ዘንድ ረዳትና መካሪ ሁነው፡፡ ከወደቀበትም የስህተት ሥራ እንዲወጣ አበርታው፡፡ ተስፋውን በእግዚአብሔር ላይ ቢያደርግ ኃጢአቱን ልክ በእሳት ፊት እንደወደቀ ገለባ ፈጥኖ እንደሚወገድለት ንገረው፡፡
ተፈጥሮ እንደ መጽሐፍ ፍጥረታት እንደ ጽላት ይሁኑህ፡፡ ከእነሱ ሕግጋትን ተማር፤ በተመስጦ ሆነህ በመጽሐፍ ያልሰፈሩትን ምስጢራት ተረዳ፡፡
እግዚአብሔርን ከሚፈራ በቀር ባለጸጋ የሆነ ሰው ማነው? የእውነት እውቀት ከጎደለው ሰው በላይ ፍጹም ደሃ የሆነ ማን ነው? ሁል ጊዜም እውነተኛ ፍቅራችን ጸንቶ ይቀጥል ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸልይ፡፡ እርሱን ለምነው፡፡ ስለ ቸርነቱ ምስጋና አቅርብ፤ ምክሬን ፈጽሞ ቸል አትበል፡፡
#ቅዱስ_ኤፍሬም_ሶርያዊ
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
ጸሎታችን ምን ዓይነት ይዘት ይኑረው? 4ቱ ኦርቶዶክሳዊ ጸሎት ልያካትተው የሚገቡ ነገሮች!! መዝሙረ ዳዊትና ውዳሴ ማሪያምን መጸለይ ያለው በረከት!! https://youtu.be/VkrMjB6Dalc?si=0gUlFmYgxQxQOJGs
የእምነት ኃይል ስኖራችሁ እግዚአብሔር ይኼንን ያደርግላችኋል!! መተት በትዳር ሕይወታችን የሚያስከትለው መዘዝና መፍትሔው!! የምቀኛ ሰው ባሕሪይና መገለጫው!! https://youtu.be/dmdlltm3dDI
የልብሷን ጨርቅ እንደ መቁጠሪያ የተጠቀመች ብርቱዋና ጠንካራዋ ሴት!! #ethiopia https://youtu.be/7K9IyGn5hOM
🛑 ጸበል ለመጠመቅ ከመኼዳችን በፍት ይሄንን ማድረጋችንን እንወቅ!! Haile Gebriel Reacts19 Estifanos Tube #ethiopia https://youtu.be/o_miE5xIe2g
«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!»
«የማቴዎስ ወንጌል 11፡25-30»
«በዚያን ጊዜ ኢየሱስ መልሶ እንዲህ አለ። አባት ሆይ፥ የሰማይና የምድር ጌታ፥ ይህን ከጥበበኞችና ከአስተዋዮች ሰውረህ ለሕፃናት ስለ ገለጥህላቸው አመሰግንሃለሁ፤ አዎን፥ አባት ሆይ፥ ፈቃድህ በፊትህ እንዲህ ሆኖአልና። ሁሉ ከአባቴ ዘንድ ተሰጥቶኛል፤ ከአብ በቀር ወልድን የሚያውቅ የለም፥ ከወልድም በቀር ወልድም ሊገለጥለት ከሚፈቅድ በቀር አብን የሚያውቅ የለም። እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ። ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ ከእኔም ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤ ቀንበሬ ልዝብ ሸክሜም ቀሊል ነውና።»
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
✨ #ሐምሌ_19_ቀን ቅዱስ ቂርቆስና ቅድስት ኢየሉጣ ንጉስ ላስቀረጸው ለጣኦት አንሰግድም ብለው ወደ እሳት ብረት ጋኑ የሚጣሉበት ጊዜ በቀረበ ወቅት እናቱ ኢየሉጣ ግን ልቧ ፈራ የልጇን ዐይን እያየች ሆዷ ባባ በፍርሃትም ታወከች ።
🍂 ልጇም « #እናቴ_ሆይ_አትፍሪ ልብሽም አይጠራጠር ዳዊትን ከጎልያድ ሰይፍ ፣ ዳንኤል ከአናብስት አፍ ፣ አናንያን አዛርያንና ሚሳኤልን ከእቶን እሳት ፣ሶስናን ከክፉ ረበናት ያዳነ አምላክ እኛንም ያድነናል ።
ከዚህ ከብረት ግርማ የተነሣ አትፍሪ ከሚያልፈው ጭንቀትና መከራ ለመዳን ብለሽ በዘለዓለም እሳት ለመቀጣት ትመርጫለሽን ? እናቴ ሆይ ! ዛሬ ገድላችንን ፈጽመን ገጸ እግዚአብሔርን እንመልከት ፣ አምላካችንንም ደስ እናሰኘው ፤ ‹‹ ከክርስቶስ ፍቅር የሚለየን ማነው ? ›› የሚለው የቅዱስ ጳውሎስ ቃል ትዝ ይበለሽ ፡፡ ( ሮሜ 8 ፥ 35 )
🍂 #እናቴ ! አይዞሽ አትፍሪ ኋላ በአብርሃም እቅፍ ለመግባት ፤ የሕይወትን አክሊል ለመቀዳጀት ፣ የብርሃን መጎናጸፊያ ለመጎናጸፍ ፤ አሁን በዚህ እሳት ውስጥ ማለፍ ይኖርብናል ፡፡
አንድ ሰዓት ለማትሞላ መከራ ብለሽ ለዘለዓለም መከራ አንዳረግ ፤ ይልቅስ የአንድ ሰዓት መከራ ተቀብለን ለዘለዓለም በመንግሥተ ሰማያት ከብረን ገነን እንኖር ዘንድ ጨክኚ መከራውን አትሰቀቂ መቀነትሽን አጥብቂ ፤ በትውልደ ጻድቃን ስትወደሺ እንድትኖሪ ዛሬ መከራውን ድፈሪ አላት ። ደግሞም በሥጋ ብንሞት በነፍስ ሞት የለብንም ። »
✨ እያለ መረጃ እየጠቀስ አጽናናት ይህም አልበቃ ቢለው ቀሚሷን እየጎተተ « #እናቴ_ነይ_በርቺ ገድላችንን እንፈጽም አላት ። » ሆኖም እናቱ ኢየሉጣ ፍርሃቷ በቀላሉ ሊለቃት አልቻለም ፤ በዚህ ጊዜ ሕፃኑ ቂርቆስ ወደ እግዚአብሔር እንዲህ ሲል ጸለየ
‹‹ አቤቱ አምላኬ ሆይ ይህቺን ባርያህን ከርስትህ የምትለያት ከሆነ ከባለሟልነትህ አውጣኝ ከሕይወትህ መዝገብ ፋቀኝ ፤ አቤቱ አዝመራውን አቃጥለህ ፍሬውን ልትባርክ ትወዳለህን ይህን እንዳታደርግ ቸርነትህ ትከለክልኻለች ።
🍂 እንጨቱን ቆርጣችሁ አንድዱት ቅጠሉን ግን ጠብቁት ብለህ ልታዝ መለኮታዊ ባሕርይህ አይደለም ፣ እንደዚሁ ልጅን አጽንተን እናትን መተው ባሕርይህ አይደለም ፤ እንጨቱን ከእነቅጠሉ ትጠብቃለህ እንጂ ።
ከጌታ ይልቅ እኔ በረታሁ ፤ ቅዱሳኖቹን ድል ነሣሁ ፤ ከመንጋውም አንድ በግ ቀማሁ በማለት ጠላት እንዳይደነፋ ለእናቴ ኀይለ መንፈስ ቅዱስን አሳድርባት ›› ብሎ ጸለየ ።
ያን ጊዜ ኢየሉጣ የብረት ጋኑ ለምለም ሣር መስሎ ታያት በምንጭ ላይም እንደሚወርድ ጠል መሰላት የልጇን ምዕዳን ሰምታ ቃሉንም አክብራ በፍጹም ልቧ ጨክና እናትና ልጅ ተያይዘው ወደ እሳት ውኃ ገቡ ፡፡
✨ እስከ ሞት የታመኑለት በዐላውያን ነገሥታት የመሰከሩለት እውነተኛው አምላክ ሊቀ መላእክት #ቅዱስ_ገብርኤልን ላከላቸው እግዚአብሔር ዘግይቶም ቢነሣ የሚቀድመው የለምና መልአኩ ገብርኤል እየበረረ መጥቶ የጋለውን የብረት ጋን በበትረ መስቀሉ ቢባርከው ውኃው ቀዘቀዘላቸው ።
🍂 ልብሳቸው ሳይሰበሰብ ሰውነታቸው ሳይሸበሸብ ልክ እንደሚስማማ ሙቅ ውኃ ሆኖላቸው ደስ እያላቸው ታጥበው ወጥተዋል እግዚአብሔርን አመስግነዋል በዚያ የተሰበሰቡም እጅግ አደነቁ ።
#ኢየሉጣም በልጇ ገድልና ምክር ተደስታ እንዲህ አለችው « ልጄ በሥጋ ብወልድህም በግብርና በገድል አባቴና መምህሬ ነህ » ብላ መሰከረችለት ። ባሕረ ጥበባት ቅዱስ ያሬድ « እናትና ልጅ በሃይማኖት ተባበሩ » ሲል ይገልጣቸዋል ።
✨ ዳግመኛም ‹‹ ልጅ እናቱን መንግሥተ ሰማያትን እንወርስ ዘንድ ከእሳቱ ነበልባል የተነሣ አትፍሪ አላት ምስጋና ለእግዚአብሔር ይግባውና እናትና ልጅ በሃይማኖት ተባበሩ ሰማዕትም ሆኑ ። » ሲል ዘምሯል ።
የቅዱስ : ገብርኤል : የቅድስት : ኢየሉጣና : የቅዱስ : ቂርቆስ ምልጃና : ጸሎታቸው : ይጠብቀን : አሜን ።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
እኛ ሳናውቀው መንፈስ ቅዱስን ከእኛ የሚያርቁ 5 ባህርያት!! መንፈስ ቅዱስ ከእኛ ለምን ይርቃል? መንፈስ ቅዱስ ከእኛ እንዳይርቅ ምን እናድርግ? #ጸሎት #ንቁ https://youtu.be/XM5_s3w1T4Q
🙏🙏 አባቶቻችን እግዚአብሔር አምላክ ረጅም ዕድሜና ጤና ያድላችሁ። መቼም ይኼ አንድነት እንዳይመጣና አባቶች በአንድነት እንዳያገለግሉ አድፍጠው ስታገሉ የነበሩና አገልግሎቱ እንድቋረጥ የባጥ የቆጡን ሲያወሩ የነበሩ ሁሉም ይፈሩ። ዲያብሎስ አፍሮ እግዚአብሔር የከበረበትና የነገሰበት አገልግሎት ነበር። ገና ከዚህ በላይ ያገለግላሉ ጠላት ይፈር ይዋረድ። 🙏🙏
ፈረንጆቹ መምህር ግርማን የጠየቁት ጥያቄና የአባታችን አስገራሚ መልሶች!! የእኛ ሀገር መምህራን ይቃወማሉ ፈረንጆቹ ይጠይቃሉ ይማራሉ!! #hailegebriel https://youtu.be/MzrrL0wxKls
የመምህር ግርማ ተከታይ እያሉ እኛን ለማሸማቀቅ ለሚሞክሩ ፈሪሳዊያን ይድረስ!! ብዙዎቻችን ያልተረዳነው የአጋንንቱና የመናፍስቱ ፈተና!! #ዲያቆን #ጸሎት #ንቁ https://youtu.be/lDOp1sY8CCc
መምህር ግርማ ጠንቋይ ናቸው እያልኩ ብዙ ሰዎችን አሳስቻለሁ! አባቶችን የሚያሳዲዱ 5ቱ ውሾችና ሴራቸው ስገለጥ! እንግዳ ስለመቀበል እስካሁን ያልተረዳናቸው ነገሮች! https://youtu.be/yKJBHDHmsXQ?si=fPGwtGUFbtlajwTK
+++ ሊቀ መልአኩ ቅዱስ አለሁ ይበላችሁ። ከፈተና ከመከራ ይጠብቃችሁ። የተዘጋውን ይክፈትላችሁ በተቸገራችሁበት ነገር ሁሉ ቅዱስ ሩፋኤል አለሁ ይበላችሁ። ፈታኼ ማህጸን ነውና በልጅ እጦት ለምትቸገሩ የተዘጋውን ከፍቶ በዲያብሎስ የተያዘውን ቦታ አስለቅቆ በልጅ ይባርካችሁ። በዚህ ሰዓት ለመውለድ በሚጥ ላይ ያላችሁ ቅዱስ ሩፋኤል ፈጥኖ ይድረስላችሁ። ለመውለድ በመንገድ ላይ ያላችሁ ቅዱስ ሩፋኤል የተባረከ ልጅ ያስታቅፋችሁ። በኑሮ በገንዘብ የተቸገራችሁ ቅዱስ ሩፋኤል የሰላቢውን መንፈስ ይሰርላችሁ።
ሁላችሁም አሜን ቅዱስ ሩፋኤል ያድርግለን በሉ።
ለሁሉም ሸር አድርጉ።
+++ አስተውሉ ድርሳኑን፣ መልክአውን ማንበባችሁን በጭራሽ እንዳትረሱ። የኼ ካልሆነላችሁ ደግሞ በድምጽም ቢሆን መልክዐውንና ድርሳኑን ማዳመጥ እንዳትረሱ። ለላው ደግሞ የቅዱስ ሩፋኤል ቤተክርስቲያን በአቅራቢያችሁ ደጁን ርገጡ በስሙ ዘክሩ።
ሰላም እደሩ 🙏🙏🙏
+5
++ አገልጋይ ማለት ምቾት የሌለውን ስራ የሚሰራ ማለት ነው። አገልጋይ ማለት በሙላት በኩል ሳይሆን በጉድለት በኩል የሚቆም ነው። አገልጋይ ቅጥር የሚያድስ ነው። አገልጋይ ማለት ችግር ጎልጓይ ሳይሆን ችግር ፈቺ ነው። አገልጋይነት የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ ነው።
++ በሕይወታችን ውስጥ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ የሚጎዱን ሰዎች ይኖራሉ መቼም ቢሆን ሥራችን፤ ሀሳባችንና ንግግራችን በሌሎች መጥፎነት ሊገታ አይገባም ለእኛ ቀና ድርጊት መልካም ምላሽ ባናገኝ እንኳን እኛ እንደ ሰው ቀናነታችንና ደግነታችንን ልንቀጥል ይገባል። በልባቸው ውስጥ ክፋት የነገሰ ሰዎች መርዝን በማር እየለወሱ የእኛን ሰላማዊና ቀና ማንነት እንዲያበላሹ ልንፈቅድላቸው አይገባም የሚሰድቧችሁን መርቁ እንደተባለ በመፅሐፍ ቅዱስ መልካምነት ለራስ ነው!
++ በቀጣይም ገዳሙ ተሰርቶ እስኪያልቅ እኔና የመንፈስ ቅዱስ ልጆቼ ከጎናችሁ መሆናችንን ላሳዉቃችሁ እወዳለሁ! የቀሲስ ኃይለመለኮት መልዕክት ነው።
ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
