HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
رفتن به کانال در Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
نمایش بیشتر2 275
مشترکین
+124 ساعت
+117 روز
+3230 روز
آرشیو پست ها
የመምህር ግርማ ወንድሙ የነገው አገልግሎት ሙሉ መርጃ ይኼው!! የመምህር ግርማ ወንድሙን አድራሻ ስጠይቁኝ ለነበራችሁ በሙሉ!! #ethiopia #habesha https://youtu.be/Ix_loQV1jDQ
አስገራሚ ምስክርነቶች! የአቡነ እጨገ ዮሐንስ ዘጠገሮ Haile Gebriel Reacts19 - በማለዳ ንቁ is live! https://youtu.be/Nnraw4yzUBw
"የአባትን ምክር እንስማ!"
መልካም ወጣት የአባቶቹን ቃል ሰምቶ የሚተገብር፡ እነርሱን አርአያ የሚያደርግ እንጂ፡ ራሱን በግሉ ሐሳብ ብቻ የሚመራ አይደለም፡፡ ራእየ ኒፎን በተሰኘው መጽሐፍ ውስጥ እንዲህ የሚል አለ፡- “በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሳለን ዘወትር ከምሥጢራት ሊካፈል ወደ ቤተ ክርስቲያን በመገሥገሥ የሚተጋ ለጽድቁ ሥራ የሚጋደል አንድ ወጣት ወደ አባታቸን ቀርቦ “አባቴ ሆይ የዘለዓለም ሕይወት እንዳገኝ ምን ላድርግ?” ሲል ጠየቀው፡፡ “ልጄ ንጹሕ ነፍስ ያለችህ ኾነህ ሳለህ በኃጢአት ከተበላሸ አንድ ሽማግሌ ምን የሚጠቅም ነገር አለና ትጠይቀኛለህ?” አለው፡፡ “ምክንያቱም አባቴ የእግዚአብሔር ቃል “አባትህን ጠይቅ ይነግርሃል” ይላልና፤ ከአንተ የሚጠቅመኝን ቃል ለመስማት ጠየቅሁህ፡፡ እባክህ የማልጠቅም ከኾንሁ ከእኔ ፊትህን አትመልስብኝ፡፡”
“ለመመንኮስ አስበሃል ወይስ ለሰው ሁሉ የተፈቀደውን ሕይወት በመኖር ፈጣሪህን ደስ ለማሰኘት ነው ምኞትህ? በማለት ወጣቱን ጠየቀው፡፡ “አባቴ ለጊዜው በዚህ እየኖርሁ ለየትኛው ሕይወት የተገባሁ እንደ ኾንሁ ራሴን መፈተን እፈልጋለሁ፡፡ ከዚያ የእግዚአብሔር ፈቃድ ወደምትመራኝ እሄዳለሁ፡፡” አለው፡፡ እንግዲያውስ ልጄ በሰዎች መካከል የምትኖር ከኾነ በእነዚህ ነገሮች ዙሪያ ጥንቃቄ ልታደርግ ይገባሃል፡፡ በማንም ላይ ትችትን አትሰንዝር፤ በማንም አትሳለቅ፤ ለመቆጣት አትቸኩል፤ ማንንም አትናቅ፡፡ እገሌና እገሌ በቅድስና ይኖራሉ፤ እገሌና እገሌ ደግሞ በኃጢአት ተውጠዋል ብለህ ከመናገር ተጠንቀቅ፡፡ ምክንያቱም “በማንም አትፍረድ” ማለት ይህ ነውና፡፡ ሁሉንም ሰው በተመሳሳይ ሐሳብ በእኩል ወዳጅነት በንጹሕ ልቡና ተመልከት፡፡ እንደ ክርስቶስ አድርገህ ተቀበላቸው፡፡
በሰዎች ላይ የሚፈርድን ሰው ጆሮህን ከፍተህ አትስማው፡፡ የበለጠ ግን በሚሰጠው ሐሳብ ተስማምተህ ደስተኛ እንዳትኾን ተጠንቀቅ፤ አፍህንም ጠብቅ፡፡ በሌላ አነጋገር ለመናገር የዘገየህ ለጸሎት ግን የምትፋጠን ኹን፡፡ ምንም እንኳ እያደረገ ያለው ስሕተት ቢኾንም በሌሎች ሲፈርድ የሰማኸውን ሰውም በሕሊናህ እንዳትፈርድበት ተጠንቀቅ፡፡ ከዚያ ይልቅ የራስህን ድክመት እያሰብክ በራስህ ላይ የምትፈርድ ኹን፡፡” አለው፡፡
“አባቴ አኹን የነገርከኝ ዘወትር ሳያቋርጡ በተጋድሎ ለሚኖሩ ነው፡፡ የማልጠቅም እኔ እግዚአብሔርን እንዴት ደስ ማሰኘት እችላለሁ? በማለት የመከረውን ሁሉ በደንብ ከሰማ በኋላ ጠየቀው፡፡ “ልጄ በብዙ ምኞትና የሥጋ ፈቃድ ለሚቃጠል ወጣት ንጽሕናንና ትሕትናን ከያዘ ተስፋ ያለው ነው፡፡ በጸጋ እያደገ እስኪሄድም ጌታ እግዚአብሔር ከዚያ በላይ አይጠብቅበትም፡፡ ስለዚህ ወጣትነትህን በንጽሕናና በትሕትና አስጊጠው፡፡ ራስህን በትሕትና ከሁሉ በታች አዋርድ፡፡ ይህን ካደረግህ በእውነት ከክርስቶስ ጋር ኅብረት ይኖርሃል፡፡
በሕሊናህም በቅድስና ታላላቅ ቅዱሳን የደረሱበት ከፍታ ላይ እንደ ወጣህ አታስብ፡፡ ይልቅስ ነፍሴ ሆይ በእግዚአብሔር ፊት የሚያቀርብሽ ምንም መልካም ሥራ የለሽም፡፡ ዕለት ዕለት በክፋት ከአጋንንት እንኳ እየባስሽ ሄደሻል፡፡ በፍርድ ቀን የሚጠብቅሽ ቅጣት ምን ያህል ይኾን? ወዮልሽ! በማለት ራስህን ውቀስ፡፡ ጸሎት ስትጸልይም በዓለም ካሉት ኃጢአተኞች ሁሉ የከፋው ሰው ጸሎት እንደ ኾነ ቊጠር፡፡ … አንድ ሰው ሲበድልህ ካየህ ስለ እርሱ ራስህን ውቀስ፡፡ አንተን ሰው ቢሰድብህ፣ ቢተችህ፣ ቢሳለቅብህ፣ ፈጽሞ ቢያዋርድህ እንኳ በሕሊናህ ራስህን አዋርደህ በሕይወት እንኳ ለመቆየት የማይገባህ መኾንህን እመን፡፡ ይቅርታና ድኅነት የሚመጡት እነዚህን ተከትሎ ነው፡፡” አለው፡፡ (ታምራት ውቤ (ቀሲስ፣ ተርጓሚ)፣ ራእየ ኒፎን፣ 2013 ዓ.ም፣ ገጽ 222-228። እንግዲህ የአበው ምክር እንዴት አድርጎ እንደሚቀርጽ ልብ እንበል፡፡ ይህን የመሰለ ወደ መልካምነት የሚመራ ምክር ልናገኝ የምንችለው በመልካምነት ሕይወት ውስጥ ካሉት አበው መኾኑን ልብ ማለት አለብን፡፡
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
የመምህር ግርማ ወንድሙ ጥብቅ መልዕክት ለመተተኞችና ሟርተኞች!! የሚያጋቡና የሚያፋቱ የዛር ቡዳ መናፍስቶች!! የጸሎት ሰዓት ፈተናዎችን እንዴት እንቋቋም?? https://youtu.be/2rbBHBWDUsE
#አስደንጋጩ!_የመናፍስት_ተዋርሶ_በየገዳማቱና_መጠንቀቅ_ያለብን_ነገሮች!! የራሔሎ መንፈስ ያለባቸው ሰዎች ምልክቶች! ሴቶችን በመንፈስ አደንዝዞ የሚያስነውሩ!! https://youtu.be/3oo3jVOt468
ጸበል ልርጭሽ፣ ቅባዕ ቅዱስ ልቀባሽ እያሉ ኀፍረተ ሥጋ ስር መግባት ምን ይሉታል!! የእጅ መዳፍ ማንበብና አጋንንታዊ ሴራው ሲገለጥ!! የመዝሙረ ዳዊት ጥቅሞች! https://youtu.be/dyGUvoRvCnY
በስንቱ ድራማ ይዞብን የመጣውን ጉድና ተንኮል ተመልከቱ!! ኢየሱስ ጌታ ነው የሚለውን አጋንንቱም ያውቁታል!! 3ቱ እግዚአብሔር አጥብቆ የሚጠላቸው ነገሮች!! https://youtu.be/ZI4QSPYWwcI
መናፍስት በእርግዝና ወቅት አብረው እንዳይወለዱና መጠንቀቅ ያሉብን ወሳኝ ጉዳዮች!! በእርግዝና ወቅት ልናደርግ የሚገቡ ጥንቃቄዎች! የዲያብሎስ ውጊያና ፈተና!! https://youtu.be/qkMPIbJgnDY
መምህር ግርማ ወንድሙ ሲያደርጉ ዘወትር ለምን እንቃወማለን?? ቀጣይ አገልግሎት በ27 በቅዱስ ፋኑኤል ቤተክርስቲያን ይካሄዳል!! https://youtu.be/Z7dY-LAMJ7g
+1
<< ለችግረኛና ለምስኪን የሚያስብ ምስጉን ነው፤ እግዚአብሔር በክፉ ቀን ያድነዋል። >> መዝሙር 41:1፤
************
(መጋቢት 21 ቀን 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ፥ኢትዮጵያ)
ሰዉን ለመርዳት ሰዉ መሆን በቂ ነዉ እንደተባለዉ ሁሉ በዛሬዉ እለት ማለትም በቀን 21/7/2017 ዓ.ም መልአከ መንክራት መምህር ግርማ ወንድሙ እና መልአከ ኃይል ቀሲስ ኃይለመለኮት ግርማ ወንድሙ እኛም ሰዉ ነን እና ሰዉን ልንረዳ ይገባል በማለት ወደ መቄዶንያ የአረጋዊያን መርጃ ማእከል በማቅናት ለተወሰነ ሰዓት ማለትም ለ 5 ሰዓታት ብቻ በቆየ መንፈሳዊ አገልግሎት 4ሚሊዮን ሰባት መቶ ሺህ ብር በማሰባሰብ ዛሬም ከተቸገሩት ጎን መቆማችንን አሳይተናል። በተጨማሪም የተቸገሩትን እና የአልጋ ቁራኛ የሆኑትን የመቄዶንያ ህሙማንን በመጎብኘት ልክ እንደዛሬዉ ሁሉ ከጎናችሁ ነን በማለት ፍፁም አብሮነታችንን ገልፀንላቸዋል።
✥┈┈••●◉✞◉●••┈••✥
ከ መልአከ ኃይል ቀሲስ ኃይለመለኮት ግርማ ወንድሙ
21/07/2017 ዓ.ም
ከሕይወት ተራራ ላይ መንፈሳዊነት ይብለጥ!
✥┈┈••●◉✞◉●••┈┈✥
╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯
የልጆቻችን ጸባይና አመል ስቀያየር ይሄንን አስተውሉ!! https://youtu.be/Ab9MCwZ0Xgk?si=Ktzrwbn5guaHsEag
ሕይወቷንና ትዳሯን በሴት ጓደኛዋ የተቀማች አሳዛኝ ነፍስ!! መስገድና መጸለይ ስትጀምር ዲያብሎስ ይጨነቃል ይሸበራል!! ጸሎት ከመጸለያችን ይሔን እናድርግ!! https://youtu.be/roeCcou8htk
. .......ብርቱካን.......
ብዙ ብርቱካኖች ልጠናል ገምጠናል፤
እኒያን ሁሉ በልተን መርካት ተስኖናል ፤
በብርቱካን በላይ ብርቱካን ሽተናል ፤
ነገር ግን !!" በበርካታዎቹ መርካት ከተሳነን ፤
እኛ ላንረካ እርሷም ላታረካን ፤
በአንዲት ብርቱካን ምን አከራከረን ?
መቶ ሚልዮን ሕዝብ አንበላት ተካፍለን?
እንብላት ብንልስ ለስንቱ ትሁነን ❔"
እኛም ሆድ አናብዛ ይልመድብን በቃን፤
ወንዝ አያሻግርም ይህ አበላላችን ፤
ትርንጎ ጨርሰን ብርቱካን ከደረብን ፤
ከብርቱካን በላይ ብርቱካን ከደገምን ፤
ሊኖረው ይገባል ለሆዳችን መጠን ፤
አንድ ቀን እንዳንሞት ብርቱካኗ ነፍታን ።
አንድ ቀን ተተክላ አንድ ቀን ያበበች
በሁለተቸኛው ቀን ፍሬዋን የሰጠች
ላንዱ የጣፋጠች ላንዱ የመረረች
የትናንቱ ጣዕሟን ዛሬ የለወጠች
በረሐ ላይ በቅላ ደጋ የተሸጠች
ምን አይነት ብርቱካን ምን አይነት ፍሬ ነች?
ይሄ ተአምር ነው ፡ ተአምር እንበለው፤
እንደ አባ ገሪማ በአንድ ቀን ተዘርቶ ወዲያው ያመረተው፤
ወይ በርተሎሜዎስ በአንድ ቀን ተተክሎ ወይኑን ያደረሰው ፤
ከቶ ይህ ተአምር ፈጻሚው ከየት ነው ?
ይሄ ተአማር ነው።
የብርቱካን መልኳን ፀሐይ ያገረጣው፤
የፀሐዩ ግለት ለድርቅ ያቀረበው
ነፋስ ቢነፍስበት ዋእይ ቢያገኘው ነው።
የትናንት መልኩን ዛሬ የቀየረው ፤
የአየሩ ንብረት ባይመቻቸው ነው ።
ማን ውሃ አጠጥቶ ለዚህ እንዳበቃት፤
ፍሬዋን በማያት ማወቁ ባያቅት፥
ግራ ቢያጋባንም የጣዕሙ ልዩነት ፤
ብርቱካንነቷን መቼም አንሳሳት ።
ስለዚህ ወገኖች በከንቱ አንፈትፍት ፤
አስወድደን ገዝተን በርካሽ አንሽጣት፤
ተለዋጭ ነው እና የገበያ ሕይወት ።
ሳምንት የረከሰው ይወደዳል ሳምንት፤
ትንሽ ቢዘገይም ይለዎጣል ባመት ፤
ሁሌ ይህ ነው እና የገበያ ሥርዓት።
ነገር ግንይገባል ለነጋዴዎች ስልት፤
ትርፍን በመፈለግ እንዳይጠፋ አይነት ፤
ኪሳራችን በዝቶም አእምሯችን ሲስት ፤
እንዳናደባልቅ ኀዘን እና ተውኔት ፤
መኖር ይገባናል በጾም እና ጸሎት ።
© መ/ር ጽጌ አስተርአየ
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
«ማንም ቢሆን የወንድሙን የውድቀት ወሬ አይስማ፤ ምክንያቱም በውስጡ በእርሱ ላይ ከመፍረድ ይድናልና። ከሐሜተኛ ጋር አትሒድ፤ ስለማንም በክፉ የተነገረን ሐሜት አትመን።» ቅዱስ ሙሴ ፀሊም
ሰዎች በቁርባን ተጋብተው ለምን ይፋታሉ? የመተት መንፈስ ውስጣችን እንዳደፈጠ ማወቂያው መንገድና መፍትሔው!! የመጽናትና የመታገስ ሕይወትን እንዴት እንለማመድ! https://youtu.be/_O02bbaI8fc
ደብተራው ልጅቷን ደፍሮ ምስጥሩ እንዳይወጣ ያደረገውን ጉድ ተመልከቱ!! በጥበብና በዕውቀት ስም የሚሰራው የአጋንንት ማዋረስና ሴራው!! #ethiopia #ጸሎት https://youtu.be/TsB9BcOUP8c
«ግብዝነት»
ግብዝ ሰው (አስመሳይ ሰው) በድብቅ እግዚአብሔር የለም ብሎ የሚያምን ነው፤ እግዚአብሔር አለ ብሎ የሚያምን ቢኾን ኖሮ፣ እርሱን ፊት ለፊት ለማታለል ባልደፈረ ነበር። በሕይወታችን አስመሳይነትን ለብሰን የምንኖር ከኾነ አኗኗራችን ድራማ ይኾንብናል። የሚኾነውና እንዲኾን የምንፈልገው እርስ በእርሱ ይምታታብናል። መልካም መባል እጅግ የምንፈልግና በሰዎች ዘንድም እንደዛ እንድንባል የሚያደርጉ ነገሮችን በማስመሰል የምንተውን፡ ከእውነተኛ የመልካምነት ሕይወት ግን ፈጽሞ ራቅ ያልን ጥቂት ሰዎች አይደለንም።
ግብዝነት ተግባራዊ የኾነ የመጠራጠር ሕይወት ነው። እግዚአብሔርን በአንደበታችን ላንክደው እንችላለን፣ በሕይወታችን ውስጥ ሰዎች እርሱን የምናመልክ አድርገው እንዲያስቡ አድርገን ልንተውን እንችላለን፡ በድብቅ ወይም በስውር በውስጣችን ያለው ግን ድፍረትና ትዕቢት፡ ራስን ማክበር ስለ ኾነ እግዚአብሔር ከሚፈቅደው ውጪ ኾነን እንገኛለን። የዚህ ኹሉ መነሻው ከእውነት መንገድ መውጣትና እውነትን በተግባራዊ የሕይወት ክፍላችን ውስጥ መግፋታችን ነው። ለዚህም ነው ሕይወታችን ከጥፍጥና ይልቅ ምሬት እንዲስማማው ያደረግነው።
መልካም የኾነው እርሱ በአርአያውና በአምሳሉ ፈጠረን እኛ ግን በፈቃዳችን ጥመት ምክንያት ሌላ አርአያን ተላበስን። ውስጣችንን በዚህ ዓለም ፍቅር አሰከርናት፥ የእግዚአብሔር የኾነውን በጎ ነገር ከተግባራዊ ሕይወታችን አራቅነው፥ ራሳችን ላይ በክፉ ዝንባሌያችን ምክንያት የዝሙትን እሳት አነደድን። ራሳችንም ባነደድነው የዝሙት እሳት ተቃጠልን፣ ረከስን፣ ቆሸሽንም፤ ኾኖም በሰዎች ዘንድ ንጹሕ አድርገን ራሳችንን በማሳየት ጻድቅ ተሰኘን፥ ይህ በእጅጉ አስገራሚ ነው።
ግብዝነታችን ከማደጉ የተነሣም፥ ግብዝ መኾናችንም ተረሳን፥ ውስጣችን በከንቱ ውዳሴ፥ በዚህ ዓለም ክብር ገነነች። ሰዎችን ከሰዎች አበላለጥን፥ ፍትሐዊነትን ከአእምሮችን በግብዝነታችን ብሩሽ አጠብናት፥ ፍትሕ ርትዕ የምትመስል ሌላ አዲስ ነገር አበጃጀን። ስለዚህም የማንሰማ፥ የማናስተውል፥ አፍቅሮተ ሰብእ የሌለን፥ በራስ ወዳድነት ጽናት የታጠርን፥ ከእግዚአብሔር ይልቅ ለዓለም የተመቸን፥ በውስጣችን ፈጽሞ የረከስን፥ ወደ እውነተኛ ሕይወት የመመለስ ፍላጎትና ወኔያችን የሞተብን ስንት ነን? እጅግ ብዙ! እግዚአብሔር በቸርነቱ ዓይነ ልቡናችንን ያብራል።
ዮሐንስ ዘሰዋስው እንዲህ ይላል፦ "አንዳንድ ወጣት ሴቶች (ልጃገረዶች) መጥፎ የኾነውን ያለ ሓፍረት ይፈጽማሉ፤ ሌሎች ደግሞ በታላቅ ጭምትነት እየታዩ ኾኖም በድብቅ ከመጀመሪያዎቹ ይልቅ የባሰውን ይፈጽማሉ፤ ይህም አሳፋሪ ከኾኑ ፈቃዳት ጋር የሚመሳሰል ነው። እንደ መመጻደቅ፣ ክፋት፣ ጥልቅ ኀዘን፣ ሮሜ 1፥ 26 ጉዳቶችን ማሰብ፣ በልብ በሌሎች ላይ መዘበትን የመሰሉ ያልታመኑ (አስመሳይ የኾኑ) ብዙ ደንገጡሮች (ገረዶች) አሉ። አንድ ነገር በማሳየት ብቅ ይላሉ፣ ኾኖም ግን ከሚታየው ሌላ ተቃራኒ ኹኔታ አላቸው።" እንዲል። (ሳሙኤል ፍቃዱ (ተርጓሚ)፣ ምዕራግና ድርሳን፣ የመጀመርያ ዕትም 2011 ዓም ገጽ 168)።
ይህ ሴቶችን ብቻ የሚመለከት ሳይኾን ወንዶችንም የሚመለከት ጉዳይ ነው። ውጫዊ ድርጊታችን ከጥልቅ ውስጣችን ጋር እጅግ ተቃራኒ የኾነብን ጥቂት አይደለንምና! ጥሩ መባልን የምንሻ፣ ነገር ግን በድርጊት ተቃራኒ የኾን፣ የምንቆረቆር የምንመስል ነገር ግን ከቤተ ክርስቲያን ሕግ ፈጽሞ የራቅን ስንት ግብዞች አለን! ሰዎች በውጭ የምናሳየውን ነገር አይተው እርሱማ ጎበዝ ነው፣ እርሷማ ጎበዝ ናት ብለው ያደናነቁን ፍሬ ቢስ አስመሳዮች ብዙ ነን።
ይሄ የኃጢአትን ጣዕም ከመውደዳችን የተነሣ የመጣብን ፅኑ ሕማም መኾኑን ልብ እንበል። ከግብዝነት ሕይወት እንውጣ፤ ክርስቲያናዊውን ሕይወት በተግባር እንግለጥ። ክርስትና እንደ እግር ኳስ ጫዎታ 11 ሰዎችን አስገብቶ ከውጪ መጮኸ አይደለም። የደጋፊነት ሕይወት ሳይኾን በተግባር የሚገለጥ ሕይወት ነው። የብዙዎቻችን ችግር ከተግባር ውጪ ኾነን በተግባር ውስጥ በጥሩ ኹኔታ ያለን አስመስለን መተወናችን ነው።
መፍትሔውም ወደ እውነት ለመመለስ ኹል ጊዜ ሳያቋርጡ መትጋት ነው። እውነት የምትሽሞደሞድ አይደለችም፥ በግል ስሜት የምትሠራም አይደለችም፥ ይልቅስ ከእግዚአብሔር ጋር ባለን አንድነት የምትረዳ ልዩ ሀብት ናት። ጌታ ራሱ "እኔ መንገድ እውነትና ሕይወት ነኝ" እንዳለ፥ እርሱ ባሳየን የአርአያነት ተግባራዊ የኾነ የእርስ በእርስ ፍቅር መንገድነት፥ እውነት የኾነውን የእርሱን ቃል አክብረን፥ ወደ ሕይወት መግባት አለብን። መንገዱን ካላገኘን እውነትን ሕይወትንም ማግኘት አንችልም። ስለዚህ ከግብዝነት ለመውጣት ስለ እውነት በእውነት መኖር መጀመር አለብን። በእውነተኛ የሕይወት ጎዳና ውስጥ እውነተኛ ፍቅር እና እውነተኛ ጣዕም ያለው ሕይወት አለና። ቆም ብለን አኗኗራችንን እንመርምር፥ የገፋናትን እውነት እንመልሳት፥ የጠላናትን አንድነት እንፈልጋት፥ ይህን ጊዜ የምናመልከው አምላክ ከግብዝነት እሳት ያድነናል። ይህ እሳካልኾነ ግብዝነታችንና ተመጻድቋችን ለማናስበው ትልቅ ችግር ይዳርገናል። ማስመሰላችንም ሕይወታችንን መራራና ርባና ቢስ ያደርግብናል፥ የሕይወት ብርሃንም ይነሣብናል። ይህን ኹሌም በማስተዋል ወደየ ልቡናችን እንመለስ!
"አቤቱ ጌታችን ሆይ የኃጢአታችን ክምር የሰናዖርን ግንብ አኽሏል፤ የዐመፃችን ጽናትም ከፈርኦን ብሷል፤ ለምሕረት የላክከውን ሙሴን በትዕቢታችን አልቀበል ብለናል፤ በራሳችን ፈቃድ ለክፉ ሐሳብ ባርያ ኾነናል፤ ካንተ ይልቅ ተድላ ዓለምን መርጠናል፤ በማስመሰልና በግብዝነት ሕይወት ውስጥ ሰጥመን ገብተናል። ስለዚህ አምላካችን ሆይ ወደ እውነት እንመለስ ዘንድ ንጹሕ ልብን ፍጠርልን! ሕሊናችንን ያቆሳሰሉብንን የዚህ ዓለም ጫጫታዎችን አርቅልን። አቤቱ ሆይ በምሕረት ዓይኖችህ ተመልክተኸን ስለ ቸርነትህ ማረን!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
#በልጅነቱ_እናቱ_ለጠንቋይና_ቃሊቻ_የገበረችው_ወጣት_አሳዛኝ_ታርክ!! ተገፍቼ ሃይማኖተን ቀየርኩ የምትሉ አዳምጡ!! ለንስሐ አባታችን መናገር የሌሉብን ነገሮች! https://youtu.be/Ne96tvnSMs0
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
