HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
رفتن به کانال در Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
نمایش بیشتر2 280
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+117 روز
+3830 روز
آرشیو پست ها
"ክርስትና ሰዎችን በተወሰኑ ሀሳቦች ማሳመን አይደለም። ይልቁንም ከክርስቶስ ፍቅርና ታላቅነት ይካፈሉ ዘንድ መጋበዝ ነው፡፡
ሰዎችን በጥዑም ንግግር ለመማረክ ብላችሁ ወጥመድ ውስጥ እንዳትወድቁ ጸልዩ፡፡ በትህትናም መናገርን ልመዱ ሰዎችንም በራሱ በክርስቶስ መማረክ ይገባችኋል፡፡"
ቅዱስ አግናጥዮስ ዘአንጾኪያ
ሲጨንቃችሁ ይሄንን አድርጉ!! ፈተና ስበዛብን ማድረግ ያሉብን ነገሮች የአምልኮት ስግደት ይገራናል መቁጠሪያና የአጋንንት ውጊያ #ethiopia 😱😭🚩
https://youtu.be/ebDWYry8UXM
አንድ ወር ተመላልሰን አልዳንኩም፣ አልተፈወስኩም ለምትሉ የንስሐ አባቴ አሳስተውኝ የገበያ መተት አስቀበርኩኝ ቀኖና ቅጣት አይደለም #ethiopia 😱
https://youtu.be/j8uQGliXA-w
የቤተክርስቲያን የጀርባ ቅማል - የደብተራ መተት የቀሲስ ሄኖክ ጥብቅ መልዕክት ክርስትናችን የሚፈተነው በመከራ ነው #ethiopia #ebstv 😱😍😭🔥
https://youtu.be/SmcJZ2EKvEI
የዲያብሎስ ተወዳጅ ጨዋታዎች - የማንነት ስርቆት ሰይጣንን አስርቡት ክፍል 3 በማለዳ ንቁ 2024 #ethiopia ብጹዕ አቡነ ሺኖዳ #ebstv 😱😭🔥
https://youtu.be/L78hAZtLwAI
ለአጋንንት መኖር ከክፋትና ከተንኮል ጋር 3ቱ መሠረታዊ የአምለኮት መንገዶች በመስተፋቅር ለተጋባችሁ ይድረስ #በማለዳ_ንቁ_2024 #ethiopia 😱😱
https://youtu.be/qv2mWHfdBEI?si=kG1JxIEuP93bzz4c
🍂 + #አቡነ_ጎርጎርዮስ_ዘላዕላይ_ግብፅ፡ በትሩፋት በገድል በጾም በጸሎት በሰጊድ በትኃርምት ሕይወት የከበሩ ፤ የላዕላይ ግብፁ ታላቁ ተአምረኛው አባት መስከረም 24 በዓለ ዕረፍታቸው
🍂 #አቡነ_ጎርጎርዮስ_ዘላዕላይ_ግብፅ፡- ደገኛ የሆኑ ወላጆቻቸው እጅግ ባለጸጎች ነበሩ፡፡ ልጃቸውንም የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት አስተምረው በሃይማኖትና በምግባር ኮትጉተው አሳደጓቸው፡፡ አቡነ ጎርጎርዮስም ሲያድጉ ወደ ኤጲስ ቆጶሳቱ ዘንድ ወስደዋቸው አናጉስጢስነት ተሾሙ፡፡
🍂 ከዚህም በኋላ ወላጆቻቸው በሥርዓት ሚስት ሊያጋቧቸው ሲሉ #ጻድቁ ግን ይህንን አልወደዱምና ፈጽሞ እምቢ አሉ፡፡ሁለተኛም ወደ ጳጳሱ ዘንድ ወስደዋቸው ዲቁና ተሾሙ፡፡
#አቡነ_ጎርጎርዮስ ወደ ታላቁ አባት #አባ_ጳኩሚስ አዘውትረው እየሄዱ ይማሩ ነበር፡፡ እጅግ ባለጸጎች ከሆኑት ቤተሰቦቻቸው ገንዘብ ከፍለው በመውሰድ ለአባ ጳኩሚስ በመስጠት ለመነኮሳቱ መጠለያ ቤትና ሌላም በጎ ሥራዎችን ሠሩ፡፡ከዚህ በኋላ አቡነ ጎርጎርዮስ ዓለምን ፍጹም ንቀው ተጠቃለው ወደ ገዳሙ በመግባት በአባ ጳኩሚስ እጅ መንኩሰው በታላቅ ተጋድሎ ለ፲፫ ዓመታት ኖሩ፡፡
🍂 የቅድስና ሕይወታቸውን አርአያነታቸውንና ምሳሌነታቸውን ያዩ ብዙ አምንዝራዎች የክፋት ሥራቸውን እየተው #ንስሃ እየገቡ ንጹሐን እስኪሆኑ ድረስ የሚጋደሉ ሆኑ፡፡አቡነ ጎርጎርዮስ በአባ ጳኩሚስ ዘንድ ለ፲፫ ዓመታት በታላቅ ተጋድሎ ከኖሩ በኋላ ታላቁ አባ #መቃርስ ወደ አባ #ጳኩሚስ መጥተው አብረው አገለገሉ፡፡
አባ መቃርስም ወደ ገዳማቸው አስቄጥስ ለመመለስ በፈለጉ ጊዜ አባ ጳኩሚስ አቡነ ጎርጎርዮስን አብረው እንዲሄዱ አዘዟቸውና ጻድቁ ወደ አስቄጥስ ገዳም ሄዱ፡፡ከአባ መቃርስ ዘንድም ብዙ ዘመን በታላቅ ተጋድሎ ኖሩ፡፡
🍂 ከዚህም በኋላ አቡነ ጎርጎርዮስ ብቻቸውን በዋሻ ውስጥ እየተጋደሉ ይኖሩ ዘንድ አባታቸውን እንዲያሰናብቷቸው ጠየቋቸው፡፡ አባ መቃርስ ፈቅደውላቸው መርቀው ሸኟቸውና አቡነ ጎርጎርዮስ ተጋድሎአቸውን በዋሻ ውስጥ ለመፈጸም ወጡ፡፡በተራራ ላይ ቆፍረው ባዘጋጇት አንዲት ዋሻ ውስጥም ለ፯ ዓመት ሲጋደሉ ኖሩ፡፡
🍂 #አባ_መቃርስም በየዓመቱ ሁለት ጊዜ ብቻ በልደትና በትንሣኤ ቀን እየመጡ ይጎበኟቸው ነበር፡፡ ሥጋ ወደሙንን አብረው ተቀብለው አባ መቃርስ ወደ ገዳማቸው ይመለሳሉ፡፡
አባታችን ከ፳፪ ዓመት ተጋድሎአቸው በኋላ
🍂 #ጌታችን መልአኩን ልኮ ከ፫ ቀን በኋላ ጊዜ ዕረፍታቸው እንደሆነ ነገራቸው፡፡ መልአኩም መጥቶ ‹‹ከዚህ ከኃላፊው ዓለም ወጥተህ ወደ ዘላለም ሕይወት ትገባ ዘንድ አለህ›› አላቸው፡፡
አባታችንም በአስቄጥስ ገዳም የሚኖሩ መነኮሳትን ጠርተዋቸው ከተሰናበቷቸውና ከተመራረቁ በኋላ መስከረም ፳፬ ቀን በሰላም ዐርፈዋል፡፡
የጻድቁ አባታችን የአቡነ ጎርጎርዮስ 🙏🏽
ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣. 🙏🏽
በጸሎታቸው ይማረን፡፡. 🙏🏽
👉🏻 ሠዐሊ ቀሲስ አማረ ክብረት እንደሣሉት
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
የጻድቁ አባታችን የአቡነ ጎርጎርዮስ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን፡፡ 🙏🏽
👉🏻 ሠዐሊ ቀሲስ አማረ ክብረት እንደሣሉት
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
መተት ላደረጉብን ሰዎች መጸለይና መቁረብ || የኢሬቻ ትሩፋት የዲያብሎስ መቀለጃ መሆን ነው! || ጸሎታችንም ኪሳችንም ባዶ ሆነብን bermel Georgis 😭😱 https://youtu.be/QoC_C_Wp9qE
ሰገደችብን፣ ቆረበችብን!! አልቻልናትም!! እናቱ በሚያመልኩት የዛር መንፈስ ያጋቡት ወጣት በትዳራችን ሰላምና ደስታ ለምን ጠፋ? #ethiopia 😭😱😭
https://youtu.be/vWvDmkec1_M
Repost from ✥ቤተ ኪዳነ ምሕረት መንፈሳዊ የትምህርት ቻናል✥
#ማር_ይስሐቅ_ክፍል ፭
#አንቀጽ 7
ደካማነትን መረዳት የትሩፋት መጀመሪያ ነው፡፡ ረድኤተ እግዚአብሔር ታድናለች፡፡ ሰው አብዝቶ ሲጸልይ ልቡናው ትሑት ይሆናል፡፡ ፈጣሪ ትሑት ልቡና የጸለየውን ጸሎት አልቀበልም አይልም፡፡ ልቡና በመከራ ትሑት ካልሆነ ትዕቢትን መተው አይቻለውም፡፡ ትሕትና መከራን ያርቃል፡፡ ክብርን ያመጣል፡፡ ትዕቢትን ያርቃል፡፡ ሰው ትሑት በሆነ ጊዜ ይቅርታን ያገኛል፡፡ ጸሎት መዝገበ ረድኤት ናት፡፡ የረድኤት መገኛ ጸሎት ናት፡፡ ወነቅዐ መድኃኒት የድኅነት መገኛ ናት፡፡ ከመከራ ማዕበል ሞገድ የምታድን ወደብ ናት፡፡ የድኩማን መጠጊያ ናት፡፡ የሕይወት ተክል ናት፡፡ በጠላት ፊት የተቃጣች ፍላፃ ናት፡፡ ሰው በጸሎት ሀብታት ምሥጢራትን አእምሮ መንፈሳዊን ገንዘብ ያደርጋል፡፡ እያመሰገኑ መጸለይ ደስ ያሰኛል፡፡ ሰው በልቡ ወደፈጣሪው ሲቀርብ ፈጣሪም ጸጋውን ክብሩን ይሰጠዋል፡፡ ደግ ሰው የባሕርዩን ድካም ያውቃል፡፡ ድካሙን የማያውቅ ሰው ትሕትናን አያገኝም፡፡ የጌታን አጋዥነት የሚሻ ሰው እነሆ የባሕርዩን ድካም አወቀ፡፡ ሰው እግዚአብሔርን በሥራው ሁሉ ሊያመሰግን ይገባዋል፡፡ ሰው ሁሉ በራሱ መፍረድ ይገባዋል፡፡
#አንቀጽ 8
እጠገናለሁ ብሎ መሰበር እንደማይመች ንስሓ እገባለሁ ብሎ ኃጢአት መሥራት አይገባም፡፡ ኃጢአት በልዑል እግዚአብሔር ዘንድ የተጠላች የተናቀች ናት፡፡ የኖኅ ዘመን ሰዎች እንዲሁም ሰዶምና ገሞራ ኃጢአትን በማብዛታቸው ጠፉ፡፡ ካህኑ ኤሊ ልጆቹ አፍኒና ፊንሐስ የእግዚአብሔርን ሥርዓት ሲያፈርሱ ባለመቆጣቱ ከሕጉ ይልቅ ልጆቹን በመውደዱ እርሱም ሞተ፡፡ ክፉ ሥራ ሠርተን እግዚአብሔርን አናሳዝነው፡፡
#አንቀጽ 9
የደገኛይቱን ሀገር የመንግሥተ ሰማይን ምሥጢር ማሰብ መልካም ነው፡፡ አብዝቶ መብላት አይገባም፡፡ ትሩፋትን ስንሠራ ጸጋ ይሰጠናል፡፡
💙🌸
ቄስ ቶሎሳ ጉዲና እና ሌሎች አባቶች ስለ እሬቻና መዘዙ የተናገሩት || የሰላም በዓል ተብሎ መከበሩ ከእውነት የራቀ ነው! #ethiopia #irreecha 😭😱😭 https://youtu.be/-yNIrM8gs_w
ጉድ ተመልከቱ! የመኪናን ሞተር በመተት ያሰሩ ክፉዎች || በአጋንንት የተዘጋው ስከፈት እንዲህ ይሆናል || መፈወስና መዳን ቲያትር ለሆነባችሁ! #ebstv 😭😱 https://youtu.be/JgMuS1NWSqE
«ንጽህት የአምላክ እናት ሆይ ፈውሽኝ፤ ነፍሴን የሚያጠቃትን ህመምና ደዌ ፈውሽልኝ አርቅልኝ፤ እንዲሁም በሥጋዬ በአጥንተ በደሜ ውስጥ የተሰገሰገውን አጋንንት እሰርልኝ፤ ለደግነትና ለመልካምነት የተገባሁ ሰው አድርግኝ። ጥልቅ በሆነው ምልጃሽ ጤናን፣ በረከትን፣ ሰላምን፣ ደስታን፣ እረፍትን ታሰጭኝ ዘንድ እጸልያለሁና ስምኝ። ከልጅሽ ከወዳጅሽ ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ አማልጅኝ። አሜን!»
#ግማደ_መስቀል
#ግሸን_ደብረ_ከርቤ
=> መስከረም 21 ቀን የጌታችን አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በደቡብ ወሎ በአምባሰል ተራራ በግሸን ደብረ ከርቤ የገባበትና በዓሉ የከበረበት ዕለት ነው፡፡ ታሪኩም በአጭሩ ዐፄ ዳዊት መንፈሳዊና ደግ ንጉሥ ነበሩ በዘመናቸው በኢትዮጵያ ቸነፈር ተከሥቶ ሕዝቡ ስለ ተሰቃየባቸው እጅግ አዘኑ በጸሎት ወደ እግዚአብሔር ቢያመለክቱም ከእግዚአብሔር ዘንድ የተላኩ ባሕታዊ መጥተው ‹‹የጌታችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መስቀል አስመጥተህ በሀገርህ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አሠርተህ ብታስቀምጥ ረሃቡ ቸነፈሩ ሁሉ ይታገሥልሃል›› አሏቸው፡፡
=> ዐፄ ዳዊትም ከብዙ ገጸ በረከት (ስጦታ) ጋር ‹‹የጌታችንን መስቀል ላኩልኝ›› የሚል መልእክት አስይዘው መልእክተኞችን ወደ ኢየሩሳሌም ሰደዱ፡፡ መልእክተኞቹም በታዘዙት መሠረት መስቀሉን ይዘው መምጣታቸውን ዐፄ ዳዊት ሲሰሙ ‹‹ክተት ሠራዊት ምታ ነጋሪት›› ብለው አሳውጀው መስቀሉን ለመቀበል ጉዞ ጀመሩ፡፡ ዐፄ ዳዊት ስናር (ሱዳን) ደርሰው ከመልእክተኞቹ ጋር ተገናኝተው መስቀሉን በክብር አጅበው ወደ መካከል ኢትዮጵያ ለማስገባት ሲነሡም ከበቅሏቸው ወድቀው ጥቅምት 9 ቀን ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
=> በዚህም ሠራዊታቸው ተደናግጠው የጌታችንን መስቀል እዚያው ትተው የዐፄ ዳዊትን አስከሬን ይዘው ተመለሱ መስቀሉ በስናር (በሱዳን) ከቆየ በኋላ የዐፄ ዳዊት ልጅ ዘርዐ ያዕቆብ ሲነግሡ ወደ መሐል ኢትዮጵያ አምጥተው ቤተ ክርስቲያን አሠርተው ለማስቀመጥ ቢያስቡም ምቹ ቦታ ግን ሊያገኙ አልቻሉም ነበር፡፡ ንጉሡና ሠራዊታቸው ምቹ ቦታ ሲፈልጉ መስቀሉን በኤረር ተራራ፣ በደብረ ብርሃን፣ በመናገሻ ማርያም ዓምባ፣ በእንጦጦ ጋራ ብዙ ጊዜ አስቀምጠውት ቆይተዋል፡፡
=> መስቀሉ በእንጦጦ ጋራ ሳለ እግዚአብሔር አምላክ ‹‹አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል፤ መስቀሌን በመስቀለኛ ተራራ ላይ አስቀምጥ›› የሚል ቃል ለንጉሡ በራእይ ነገራቸው፡፡ መስቀሉን ወደ ወሎ ሀገረ ስብከት እንዲወስዱትም አዘዛቸው ንጉሡና ሠራዊታቸው በእግዚአብሔር መሪነት መስቀሉን ይዘው ወሎ ሲደርሱም ጌታችን ወደ አምባሰል እያመለከተ ‹‹አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል፤ መስቀሌን በመስቀለኛ ተራራ ላይ አስቀምጥ›› ይላቸው ነበር፡፡
=> ንጉሡ መስቀሉን ይዘው ወደ ቦታው ሲያመሩ መስቀለኛው የግሸን ተራራን አገኙ ፤ በዚያም ቤተ ክርስቲያን አሠርተው በ1446 ዓ.ም የጌታችንን መስቀል በክብር አስቀምጠውታል፡፡ ከዚህ በኋላ ንጉሡ ‹‹መሐሏ ገነት፤ ዳሯ እሳት ይኹን! የበረረ ወፍ፣ የሠገረ ቆቅ አይታደንባት! በድንገት ሰው የገደለ፣ ቋንጃ የቈረጠ ወንጀለኛ አይያዝባት!›› ብለው ዐዋጅ አስነግረዋል የእመቤታችን ጽላትም አብሮ በግሸን ደብረ ከርቤ እንዲቀመጥ አድርገዋል፡፡
=> ስለዚህም መስከረም 21 ቀን በየዓመቱ በቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ይከበራል ኀጢአታቸውን ለካህን ተናዘው፣ ንስሐ ገብተው በዚህ ዕለት ወደ ግሸን ደብረ ከርቤ በመሔድ የሚጸልዩና የሚማጸኑ ምእመናን ኹሉ እስከ ሰባት ትውልድ ድረስ የምሕረት ቃል ኪዳን እንደሚያገኙም መጽሐፈ ጤፉት በተባለችው ተጠቅሷል፡፡
#እመቤታችን_በረድኤት_አትለየን!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
በትዳር ውስጥ የምንፈጽማቸው ትልልቅ ስህተቶች! ሩካቤ ሥጋ የተለየው ትዳር የሞተ ነው! ሩካቤ ሥጋና የጸሎት ሕይወት || 7ቱ የጸሎት ሰዓታት 💥🚩🔥😱😭
https://youtu.be/Wwos3LQR-OA
"ሰይጣን እና ሌባ አንድ ናቸው!"
=> ተወደጆች ሆይ ሰይጣን እና ሌባ አንድ ናቸው፡፡ ሰይጣን ጸጋ የሌለው፣ በእምነት ያልጸናው፣ በጸሎት ያልበረታው፣ በምግባር ያላጌጤው ጋር ሄዶ አይታገልም፡፡ ምክንያቱም እንዲህ አይነት ሰው ሰይጣን ሳይጥለው ቀድሞ የወደቀ ነውና፡፡ የሞተ የገደለ ጀግና እንደማይባል ሁሉ ሰይጣንም እሱ ከመጣሉ በፊት ቀድሞ የወደቀለትን ሰው በመፈተን ጊዜውን አያጠፋም፡፡ ሰይጣን ሁሌም ሰይጣናዊ ዓይኖቹ የሚሰደሩት በጸጋ የከበሩት ላይ ነው፡፡ ሰይጣን በመንፈሳዊ ሕይወቱ የበረታው፣ ወደ እግዚአብሔር እጅጉን የተጠጋውን ነው የሚታገለው፡፡ ሌባም ደሃ ቤት ሳይሆን ባለጠጋ ቤት ነው ሊሰርቅ የሚሄደው፡፡ ሌባ ቀን ከሌሊት ለመስረቅ የሚያስበው የባለጠጋን ቤት ነው፡፡ ሰይጣንም በእግዚአብሔር ጸጋ ሐብታም የሆኑትን ጸጋቸውን ለመስረቅ ነው የሚተጋው፡፡
=> ወዳጆቼ ሌባ ባለጠጋን ከመስረቁ በፊት በደንብ ያጣራል፡፡ ሰውዬውን የሚዘርፍበት አሳቻ ጊዜ በደንብ ያጠናል፡፡ ሊሰርቀው ያሰበውን ነገር የት እንደሚያስቀምጥ ለማወቅ ይጥራል፡፡ ይህን ከደረገ ሌባው ባለጠጋውን በቀላሉ ይሰርቀዋል፡፡ ሰይጣንም በመንፈሳዊ ሕይወትህ ብርቱ እና ጸጋው ያደረብክ ከሆንክ አንተ ጋ ተጠግቶ ጸጋህን ለማስገፈፍ ከመሞከሩ በፊት አንተ የእኔ እና የቅርቤ በምትላቸው ሰዎች ስላንተ በደንብ ያጣራል፡፡ ጠንካራ እና ደካሞ ጎንህንም ይለያል፡፡ በየትኛው መንፈሳዊ ሕይወትህ ቸልተኛ እና ንዝህላል እንደሆንክ ያጣራሃል፡፡ ያኔ ደካማ ጎንህን ተጠቅሞ፣ ፈተናውህ አሸክሞ ይዋጋሃል ከቀናው ይጥልሃል፡፡
=> ሌባ ገንዘብ ወርቅ ወዘተ ያለበትን ቤት ነው እያነፈነፈ በቀንም በሌሊትም የሚዘርፈው፡፡ ሰይጣንም ጸጋ እግዚአብሔር ያላቸውን የበረቱትን የጸኑትን፣ በቅዱስ ቁርባን የተወሰኑትን፣ በጸሎት የተጉትን፣ በምግባር የተትረፈረፉትን፣ በመንፈሳዊ ሕይወታቸው በሁለት እግር የቆሙትን ነው መንፈሳዊ ወርቃቸውን ለመስረቅ የሚጥረው፡፡ ወዳጆቼ እንኳን ሰይጣን ወፎች እንኳን ፍሬ ያፈራን ዛፍ ነው የሚጠለሉት፡፡ ለምሳሌ ወፎች ፍሬ ያፈራን ሾላን በሁለት መልኩ ይጠለሉታል፡፡ አንደኛው የሾላውን ፍሬ ለመብላት ነው፡፡ ሁለተኛው ሾላ ፍሬ የሚያፈራው ቅጠሉ ከተንሰራፋ ቦኃላ ነው ስለዚህ በቅጠሉ ይጠለላሉ፡፡ ወዳጄ አንተም መንፈሳዊ ጸጋ ስታገኝ፣ ፍሬ ስታፈራ ሰይጣንም ፍሬህን እየቀነጠበ ለመልቀም ብሎም ለመንጠቅ ይሞክራል፡፡ ምክንያቱም ባንተ ሰዎች እንዳይጠለሉ ፍሬህን ይነጥቅሃል፡፡
=> አንድ ሰው በሥራው ባለ ጠጋ እየሆነ ሲመጣ የወዳጆቹም የሌቦቹም ዓይን ውስጥ ይገባል፡፡ አንተም በመንፈሰዊ ሕይወትህ ባለ ጸጋ እየሆንክ ስትመጣ የሰይጣን ዓይን ውስጥም እየገባህ ትመጣለህ፡፡ ያኔ ነው እንደ ልጅነትህ ጨዋታ ከሌባ ጋር አባሮሽ የምትጫወተው፡፡ እህቴ ላንቺ ድንግልናሽ ወርቅሽ እና ጸጋሽ ነው፡፡ ሰይጣን ይህንን ጸጋሽን ለማሳጣት በወንድ እንደ ሌባ ሆኖ በዝሙት ድንግልናሽን ያሳጣሻል፡፡ ይህ ከሆነ ሰይጣን ጸጋሽን ክብርሽን ሰርቆሻል፣ አሰርቆሻል ማለት ነው፡፡ ወንድሜ በመንፈሳዊ ሕይወትህ በርትተህ፣ በጸሎት ተግተህ ያገኘኸውን ጸጋ በዝሙት ካጣኸው ሰይጣን እንደ ሌባ በሴት ተመስሎ ጸጋህን ሰርቆሃል አሰርቆሃል ማለት ነው፡፡
=> ትላንት በቅዱስ ቁርባን ታትመህ በዓላትንና የምትወዳቸውን ታቦቶች እያስታከክ የምትቆርብ ሆነህ ዛሬ ግን ይህንን መለኮታዊ ሰማያዊ ጸጋ በዝሙት ካጣኸው ሰይጣን በደንብ ጸጋህን ሰርቆሃል ዘርፎሃል፡፡ ወደድክም ጠላህም የሰይጣን ብርቱ ውጊያ ከበረታብህ አንድ የሚሰርቅህ፣ የሚዘርፍ ነገር አለ ማለት ነው፡፡ አንዳንዴ አንተ የማታውቀው ሰይጣን የሚያውቀው ጸጋ እና ስጦታ ስላለህ ነው የሰይጣን ፈተና ብርቱ የሚሆንብህ፡፡ ልብ በል ሰይጣን ካንተ ከደካማው ጋር ትለቅ ግብግብ ውስጥ ከገባ እንደ ሌባ ገንዘብህን ወቅርህን ሊነጥቅህ ነውና ተጠንቀቅ፡፡
=> ባለጠጋ ቀድሞ ያልተጠነቀቀውን ሌባ ከሰረቀው፣ ለዘረፈው በኃላ ቢጮኽ፣ ኡኡ ቢል ትርፉ ጸጸት፣ ቁጭት እና ከንቱ ለቅሶ ነው፡፡ ወዳጄ አንተም ጸጋህን ካጣህ፣ በሌባው በሰይጣን ከተዘረፍክ በኃላ ብትጮኽ፣ ኡኡ ብትል ዋጋ የለውም፡፡ ተረቱስ ‹‹ቀድሞ ነበር እንጂ መጥኖ መደቆስ፣ አሁን ምን ያደርጋል ድስት ጥዶ ማልቀስ›› አይደል፡፡ ስንቶች አለን ጸጋችንን ካጣን፣ በሰይጣን ከተሰረቅን በኃላ ጸጸታችንን በእንባ እሳት ላይ ጥቀደን የምናለቅስ፡፡ ሰይጣንም ሌባም የሚያንኳኳው የባለጠጋን ቤት ነው፡፡ ልዩነቱ ሌባ በሥጋ ባለጠጋ የሆኑትን ሲሆን ሰይጣን ደግሞ በመንፈሳዊ ሕይወት ጸጋ ያላቸውን በመሆኑ ነው፡፡
=> ወዳጄ ሌባ የዘረፈውን ባለጠጋ መልካም ባለጠጋ ጓደኞቹ ካሉት አዋጥተው ሌባው የሰረቀውን ብቻ ሳይሆን እጥፍ ይሰጡታል፡፡ አንተም በሰይጣን ብርቱ ትግል ጸጋህን ብታጣም የነፍስ ወዳጆች የሆኑትን ቅዱሳን መላእክትንና ቅዱሳንን ብትማጸን ከፈጣሪያቸው አማልደው፣በጸሎት ጠይቀው ያጣኸውን የተነጠቅኸውን ጸጋ ያሰጡኻል ያስመልሱልሃል፡፡ ግን ይህ የሚሆነው በንስሐ በሆነ ጸሎት ነው፡፡ አንዳንዶቻችን ባለ ማወቅ ጸጋችንን በሰይጣን በመነጠቅ ተስፋ ቆርጠን፣ ጸጋችንን የምናስመልስበት መንገድ ጠፍቶን ግራ በመጋባት ቆመናል፡፡ እስኪ ባለጸጋ እመቤት የሆነችው ወለላይቱን ወላዲተ አምላክን በንስሐ በሆነ ጸሎት እና ከልብ በሆነ ጸጸት እንማጸናት በእውነት ትላንት ካጣነው ጸጋ የበለጠ ትሰጠናለች ታሰጠናለች፡፡ ስለዚህ ሌባው ሰይጣን ጸጋችንን የሰረቀን የዘረፈን ሁሉ ወደ ወለላይቱ እንማልል፡፡
=> ደንግልና ያጣን በንስሐ ቅድስናን እናገኛለን በነፍስ ድንግል እንሆናለን፡፡ በዝሙት የወደቅን በንስሐ ታጥበን ከበረዶ ይልቅ እንነጻለን በዚህም የቀድሞ ቅድስናችንን እናገኛለን፡፡ ጸጋው ያላችሁ ጸጋችሁን ተጠንቅቃችሁ ያዙ፡፡ ጸጋችሁን ያጣችሁ ጸጋችሁን ለማስመለስ ወደ እመቤታች ፊታችሁን መለስ አድርጉ፡፡ ወዳጆቼ እግዚብሔር የሚያዝንብን ኃጢአት በመሥራታችን ሳይሆን በንስሐ ወደ እሱ ባለመመለሳችን ነው፡፡ ስለዚህ ከሌባው ከሰይጣን ጠንቀቅ ለማለት ጸሎትን፣ ትጋትን፣ ትዕግስትን ወለላይቱን እመቤታችንን ጠበቅ አድርገን እንያዝ፡፡ በያላችሁበት እጅጉን የከበረ ሰላምታዬ ከግሸን በግሸኗ እመቤት ስም ይድረሳችሁ፡፡
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
መምህር ግርማ ዘመኑን የዋጁ አባት ናቸው የጸሎትና የቡራኬ ጊዜ ሳይኖረን በዲያብሎስ ተቀደምን bermel giorgis || ቤርሜል ጊዮርጊስ ጸበል 😭😱
https://youtu.be/e46HgV5-IFg
ተጠንቀቁ! በሞዴስ የሚደግሙ መተተኞችን ኢሬቻ አቴቴና ፈረቀሳ የባዕድ አምልኮ የስንፈተ ወሲብ መድኃኒት መጠቀም መዘዙ || የማዕድ ጸሎትና በረከቱ 😱😭
https://youtu.be/XwqYgO89Ji0
