fa
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

رفتن به کانال در Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

نمایش بیشتر
2 279
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+47 روز
+2930 روز
آرشیو پست ها
◈ የመንፈሳዊው ሰው ሕይወት ውጪያዊ ገጽታ አይደለም። ወይም ሕይወቱ በተራ ተግባርና ግዴታ አይመራም። ከሁሉም በላይ ደግሞ በቃል ብቻ በሚነገሩ ትዕዛዛት ሥር አይተዳደርም። እርሱ መንፈሳዊ ሕይወቱን ከምንም ነገር በፊት ያስቀድማል። በዚህም መሠረት እግዚአብሔር "ልጄ ሆይ ልብህን ስጠኝ፤ ዐይኖችህም መንገዴን ይውደዱ።" (ምሳ. 23፡26) ብሎ እንደተናገረ ልቡ ምን ጊዜም ከእግዚአብሔር ጋር ነው። ዋናው ቁምነገር ልብህን ለእኔ መስጠቱ ላይ ነው፤ ይህን ካደረግህ ዓይኖችህ መንገዴን ይወዳሉ ይልሃል። (አቡነ ሽኖዳ) 🙏🙏 #ውድ_ቤተሰቦቼ_የዩቱብ_ቻናላችንን_ተቀላቁ! #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

🛑በእውነት #አለባበሳችን ማሰናከያ ለምን ሆነብን? ክርስቲያናዊ አለባበስ ማሰናከል ምንድነው || የዘመኑ ትልቁ ፈተና #ethiopia #sibket 😭😰 https://youtu.be/JPqjCItmSYk

😭 ውድ ቤተሰቦቼ ይሄን ከታች ያለውን መልእክት አንብቡትና በዚህ አከባቢ ወይም ከተማ ያላችሁ እህት ወንድሞች እባካችሁ ተባበሯት። 😭😭 😭 ወንድሜ ሀይለ ገብርኤል አንድ እናታችን ትሆናለች እና እድሏን ወስደው እየተጠቀሙበት እሷ ቤት ውስጥ ዘግታ የቤት አይጥ እንድትሆን ነው ያደረጓት እና ቤት ክራይ የምትከፍለውም የላት የምትበላው የምጠጣው የላትም ቢት ውስጥ ናት ስራ ስጠይቅ አታገኝም 😭 እና የቁረበች ናት የምትኖረው ዱባይ ነው እና መልክት ብታስተላልፍላት አንተም የምታውቃቸው ካሉ ወደሀገሯ የምትገባበት ነገር ቢፈጠር ወደ ሀገሬ ገብቸ በቤቱ ተጠልዬ ስለመብርሃን ብዬ እኖራለሁ ነው የምትለው😭 ወንድምዬ የቻልከውን ብታደርግ ብጠይቃት እሷንም ስልኳን ሽር ባደርግልህ ፍቃደኛ ከሆንክ ወንድምዬ እኔ ምኖረው ሳውዲ ነው የንጉሱ ልጅ ነን የመድኃኔዓለም ማህበር ላይ ስላለው በዛ መጣ ስታልቅስ 😭ስትናገር በጣም ታሳዝናለች እና ወደ አንተ መጣው ከምታስተላልፋቸው ነገሮች ነው እንድነግርህ የሆንኩት አመሰግናለሁ ወንድምዬ 😭 ወስብሐት ለእግዚአብሔር 😭 ቢያንስ መርዳት እንኳን ባንችል ለብዙ ግሩፖች እና ቻናሎች ሸር ሸር እናድርግ በእውነት እናግዛት። #ውድ_ቤተሰቦቼ_የዩቱብ_ቻናላችንን_ተቀላቁ! #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

🛑ዘመናዊ ሰዎችን ለይታ ክፉኛ የምታጠቃ መንፈስ || እላፍ ሳቅ፣ ፍንደቃ ጭፈራ፣ ዘፈንና ኮስሞትክስ የሚትወደው ዘመዊዋ መንፈስ ሔርሜት | የሔርሜት መንፈስ 😭😭 https://youtu.be/btnLjLf993A

🛑ሰው የቱን ያህል መንፈሳዊ ዕውቀት ይኑረው፣ ጥንተ ጠላቱ ስለሆነው ዲያብሎስ ካላወቀ ሕይወቱ ከባድና ፈተና ይሆንበታል || በማለዳ ንቁ ተሞክሮ ክፍል 26 😰😭 https://youtu.be/8KtUXjl0pxA

ሰላም ውድ ቤተሰቦቼ ብዙ ሰዎች በበረከት ሥራ ላይ ለመሳተፍ እንዲሁም ለማገዝ እየጠየቃችሁኝ እንደሆነ አወቃለሁ። ለዚህም እግዚአብሔር አብዝቶ ይባርካችሁ በእውነት። ባለፈው ሳምንት ላይ በበረከት ሥራዎች የተሳተፋችሁ ቤተሰቦቼ ሁላችሁም ተባረኩ። አሁንም ቀጥሉበት በእውነት። ከዚህ በታች የገለጽኳችሁ በወጣ ይተካ ብያለሁ። ባላችሁበት ሰላማችሁ ይብዛ። 🙏 የመድኃኔዓለም ማህበራት በአጠቃላይ (29700 ብር) ይሄም ለተቸገሩ እናቶች፣ ወልደው ለተቸገሩ አራስ እናቶች እንዲሁም አቅሜ ደካማ አባት እናቶች አድርሰናል። ክበሩልን በእውነት። 🙏 ሌላዋ እህታችን ደግሞ ሰብለ እንዲሁ (8000 ብር) በመላክ የአንድ ቤተሰብ ሙሉ የወር የቤት ውሽጥ ወጪ በመቻል በበጥታ ደውላ በማናገር ችግሯን የተካፈለች እና በበረከቱ የተሳተፈች እህት ናትና ክበርልኝ በእውነት። 🙏 ሌሎችም እህቶች፣ ወንድሞች በእውነት የውስጥ ሰላም፣ ደስታ፣ በረከት የሚናገኘው በሰዎች ደስታ ነውና። ሁላችንም የአቅማችንን እንተጋገዝ። በአገራችን እንደሚባለው 50 ሎሚ ለአንድ ሰው ሸክሙ እና ፈተና ሲሆን እኛ ስንተባበር ግን ቀላል ይሆናል። እና እንተባበር። አሁን እንድናግዛቸው የተዘጋጁ ቤተሰቦች አሉና ሁላችንም እንተባበር። ለተጨማሪ መረጃ በተለግራም አንግሩኝ በውስጥ መስመር ቤተሰቦቼ። 🙏 @haile_gebriel_tube_bot 🙏 መልካም ቀን ለሁላችሁ።

🛑ርኩሳን መናፍስት ውስጣችን ስገቡ በብዛ ከሰራዊታቸው ጭምር ነው የመናፍስት ፈተና በሕይወታችን በማለዳ ንቁ 2023 #ethiopia #sibket 😂😰😭 https://youtu.be/2Cee09NaugI?si=Lz1LWnRxAwXfkIuM

🛑ርኩሳን መናፍስት ውስጣችን ስገቡ በብዛ ከሰራዊታቸው ጭምር ነው የመናፍስት ፈተና በሕይወታችን በማለዳ ንቁ 2023 #ethiopia #sibket 😂😰😭 https://youtu.be/2Cee09NaugI?si=Lz1LWnRxAwXfkIuM

🛑ከሩካቤ ሥጋ የምንታቀብበት ጊዜያት፣ ቀናት እና ምክንያቶቻቸው ሩካቤ ሥጋ እና የጸሎት ሕይወት በማለዳ ንቁ 2023 #ethiopia #orthodox 😰 https://youtu.be/sD_MX4J1N1Y

ጥያቄ5፡ አስራ ሁለት ጊዜ እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ ለምን እንላለን? ለምን ከአስራ ሁለት አልበለጠም? ከአስራ ሁለትስ ለምን አላነሰም? በጣትስ ለምን እንቆጥራለን? መልስ፡ አስራ ሁለት ጊዜ እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ የምንለው የአብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ስም ፊደላት ሲቆጠሩ 12 መሆናቸውን ለመግለጽ ነው፡፡ ሌላው በ12 ሐዋሪያት ምልጃ አድነን ይቅርም በለን ማለት ነው፡፡ ከ12 ያልበለጠበትና ያላነሰበት ምክንያት የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ስም ፊደላት ከ12 አይበልጥም አያንስምም፡፡ ሌላው የሐዋርያት ቁጥር ብዛታቸው 12 መሆኑን ሲያጠይቅ ነው፡፡ ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ የሆነው በራሱ ጥፋት በወጣበት በአስቆሮቱ ይሁዳ ምትክ ሐዋሪያው ማትያስ በዕጣ መመረጡን (የሐዋ 1÷23-26) ያስረዳል፡፡ ለዚህም ነው ከ12 ያልበለጠው ወይም ያላነሰው፡፡ ወደ ላይ ዕረገቱን ወደታች መውረዱን ለመግለጽ ነው፡፡ #ውድ_ቤተሰቦቼ_የዩቱብ_ቻናላችንን_ተቀላቁ! #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

ጥያቄ 4፡ ጸሎተ ፍትሐት ሰው በሞተ በሦስተኛው ቀን የሚደረገው ለምንድነው?
Anonymous voting

ጥያቄ 3፡ ዕጣን በቤተክርስቲያን ያለው ምሳሌነትና ምስጥሩ ምንድነው?
Anonymous voting

ጥያቄ 2፡ በቤተክርስቲያን አስተምህሮ ሻማ ምሳሌነቱ ምንድነው?
Anonymous voting

ጥያቄ 1፡ በአዲስ አበባ ለመጀመሪያ ጊዜ የተመሠረተው (የተቆረቆረው) ቤተ-ክርስቲያን የትኛው ነው?
Anonymous voting

🙏 የአባቶቻችን ድንቅ ተግባር፦ ◈ "ከመመስገን ይልቅ መነቀፍ የበለጠ ብፅዕና ነው፤ ሰዎች ሲያመሰግኑኝ ለእኔ መንፈሳዊነት አደገኛ እንደሆነና ሰዎች ሲነቅፉኝና በሐሰት ክፉ ሲናገሩብኝ ማመስገንን በአእምሮዬ ውስጥ ተክዬዋለሁ? የማይቻል ነገር ነው ልትሉ ትችላላችሁ ግን መሆን ያለበት ነው፡፡ አቡነ ዮሐንስ የተባሉ አባት በየሳምንቱ ሐሙስ ሐሙስ በአቅራቢያቸው ወዳለ አንድ መንደር ለማስተማር ይሔዱ ነበር፤ በግብፅ እንደተለመደው ወደዚያች መንደር ለመሔድ ሲሳፈሩ ከእንድ ሌላ ሰው ጋር መዳበል ነበረባቸው፤ በዚህ ጊዜ አንድ አክራሪ ሙስሊም ሁል ጊዜ በተመሳሳይ ሰዓት አብሯቸው ይሳፈር ነበር፤ ሊሳፈሩ ሲገቡ ታዲያ ፊቱን ዞር ያደርግና [ጢቅ አድርጎ] ይተፋ ነበር! ይህን አስነዋሪ ድርጊት ለዓመታት ይፈጽም ነበር፤ አንድ ቀን ጳጳሱ ሊሳፈሩ ሲመጡ ያ ሰው አልነበረም፡፡ ◈ አቡነ ዮሐንስ ከልባቸው አዝነው እግዚአብሔርን መጠየቅ ጀመሩ "ጌታዬ ይህንን በረከት ለምን አስቀረህብኝ? ይህንን በረከት ከዚህ በላይ እቀበል ዘንድ እንደማልገባ የወሰንከው በኃጢአቶቼ መብዛት ይሆን?" ◈ ሌላው የተቀደሰ ትውስታ ባለቤት ደግሞ የማይታክቱት የእግዚአብሔር ሠራተኛ ጳጳሱ አቡነ ሳሙኤል ነበሩ፤ እኚህ አባት እንደተለመደው ብዙ ጠላቶች ነበሯቸው፤ እጅግ አስጸያፊ መልእክቶችን እየጻፉ በደብዳቤ መልክ ይልኩላቸው ነበር፤ እሳቸውም እነዚህን አስጸያፊ ስድቦች በመሳቢያቸው ውስጥ ያስቀምጡአቸው ነበር፡፡ ◈ በሚከፋቸውና በሚተክዙ ጊዜ ማኅደራቸውን ከፍተው እነዚህን ደብዳቤዎች የነብቡ ነበር፤ ከዚህ በኋላ የመታደስ ስሜት ይሰማቸዋል ምክንያቱም ነቀፋዎቹን ሲያነብቡ በእያንዳንዱ ስድብ ውስጥ በረከት እንዳለ ስለሚያዩ ነበር፤ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የምናነብበውን በልባችን ውስጥ መትከል የምንለው እንግዲህ ይህንን ነው" ◈ ቤተሰቦቼ እኛስ እንዴት ነን እንዲህ አይነት ጉዳዮች ላይ? ሰዎች ስነቅፉን፣ ሲሳደቡን እንዴት ነው አያያዛችን? (አቡነ አትናስዮስ እስክንድር) #ውድ_ቤተሰቦቼ_የዩቱብ_ቻናላችንን_ተቀላቁ! #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

ጥያቄ 5፡ ህዳር 12 የቅዱስ ሚካኤል በዓል ምንን በማስመልከት ይከበራል?
Anonymous voting

ጥያቄ 4፡ ነገደ ሚካኤል በየትኛው ሰማይ ላይ ሰፈሩ?
Anonymous voting

ጥያቄ 3፡ ቅዱስ ሚካኤል በየትኛው ነገደ መላእክት ላይ ተሾመ።
Anonymous voting

ጥያቄ 2፡ ሚካኤል ማለት ምን ማለት ነው?
Anonymous voting