fa
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

رفتن به کانال در Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

نمایش بیشتر
2 273
مشترکین
+424 ساعت
+127 روز
+2530 روز
آرشیو پست ها
በነስር ህመም የምትሰቃዩ ይኼንን ተዓምር አይታችሁ እራሳችሁን አድኑ!! በጸሎት ሰዓት በጭራሽ ይኼንን አታድርጉ! ለክፋትና ተንኮል ሰይጣንን የሚያገለግሉ ሰዎች! https://youtu.be/h2V_tcUzej8

#አስታውሱ! ደካማነትህን አስታውስ፣ ያንጊዜ በጣም ጠንቃቃ ትሆናለህ፣ ሊጎዱህ በሚችሉ በትምክህትና በውዳሴ ከንቱም አትሸነፍም፡፡ የተሰጠህን በፍቅር የተሞላ የእግዚአብሔርን ቸርነት አስታውስ፣ ይህም በምስጋና የተሞላ ሕይወት እንድትመራ ያደርግሃል። በእግዚአብሔር ፍቅርና ሥራ ላይ ስትታመን ፍጹም የሆነ እምነት በልብህ እያደገ ይመጣል፡፡ ከእግዚአብሔር ጋር ያሳለፍከው ጊዜ ደግሞ በእምነት እንድትኖር ያበረታታሃል፡፡ የሰዎችን ፍቅርና ካንተ ጋር ያሳለፉትን መልካም ጊዜ አስታውስ፡፡ የሰዎችን ቀናነት ትጠራጠር ዘንድ ወይም ያደረጉብህን ክፉ ነገር ታስብ ዘንድ ይገባሃልን? የቀደመ ፍቅራቸው ስለ እነርሱ ይማልዳል ያንተንም ቁጣ ያበርዳል፡፡ ሞት እንዳለ አስታውስ፣ እንዲሁ በዓለም ያለ ፈተናም እንደሚያልፍ፡፡ "ሁሉ ከንቱ ነው፣ ነፋስንም እንደመከተል ነው፡፡" መክብብ 1፥14 ማለትን ትረዳለህ፡፡ በእግዚአብሔርፊት መቆምህንና እርሱም እንደሚመለከትህ አስታውስ፣ ያኔ ኃጢአት አትሰራም እግዚአብሔርን ታየዋለህና፡፡ ስለ አንተ የፈሰሰውን የክርስቶስን ክቡር ደም አስታውስ፡፡ በዚህም ሕይወትህ ያለውን ዋጋ በእርግጥ ታውቃለህ፤ በዓይኖችህ ፊት የከበረ ይሆናል፣ ስለዚህም በከንቱ በመኖር አታጠፋውም፣ "በዋጋ ተገዝታችኋልና" 1ኛ ቆሮ.6:20 እንዲል ቅዱስ ጳውሎስ፡፡ በወላጆችህ እምነት በተጠመቅህባት ቦታ ለእግዚአብሔር የገባኸውን ቃል አስታውስ፤ ዲያብሎስን፣ ሥራዎቹን ሁሉ፣ ሐሳቦቹንና ጥበቡን፣ ኃይሉንም ትክድ ዘንድ፡፡ በዚህ ዓለም እንግዳመሆንህንና ወደ ሰማያዊው ቤትህ እንደምትመለስ ዘወትር አስታውስ፡፡ ያን ጊዜ በዚህ ዓለምና በደስታው ተስፋ ማድረግን ትተዋለህ፡፡ በጠባቡ በር መጓዝ ወደ መንግስተ ሰማያት እንደሚያደርስህ አስታውስ፡፡ ሰፊው ደጅ ፊት ለፊትህ ተከፍቶ ብታየው፣ አልፈኸው ሂድ ከእሱም ራቅ፣ በእርሱ የሄዱ እንዳሉ አልቀዋልና፡፡ ዘላለማዊውን ሕይወትህን አስታውስ፣ ሁልጊዜም ስለዚህ ትጋ፡፡ የእግዚአብሔር ልጅ መሆንህንና እርሱን መምሰል እንዳለብህ አስታውስ፡፡ እውነተኞች ከሆኑት ከእግዚአብሔር ልጆች ጋር አካሄድህን አስተካክል፡፡ የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ መሆንህን አስታውስ፡፡ በውስጥህ ያለውንም ቅዱሱን የእግዚአብሔር መንፈስ አታሳዝን፡፡ ዘወትርም ቅዱስ የእግዚአብሔር ማደሪያ ሁን፡፡ (ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.facebook.com/hailegebrieltube2021 https://www.tiktok.com/@walkinaddistv

መምህር ተስፋዬ መናገር ያልፈለገውንና የከበደውን ታርክ ነገረን!! አዶናይን በገዛ ሀገሩ አሳፈሩትያሳዝናል!! ሰሞኑን አነጋጋር የነበሩት አባት ምላሽ ሰጡ!! https://youtu.be/K2KddCk4TUQ

«አንተ ሰው የበደለህን ይቅር ሳትል ወደ ጾም አትግባ፡፡ አንተን በበደለህ ሰው ላይ በቁጣ እያለህ የምትጾመው ጾም ከንቱ ነው፤ እግዚአብሔርም አይቀበለውም፡፡ ጾምህን በፍቅርና እርሱን ተስፋ በማድረግ በእምነት ካላደረግኸው አንተን ፈጽሞ ሊረዳህ አይችልም፡፡ በጠብ ሆኖና በውስጡ ጠላትነትን አንግሦ የሚጾም ጸዋሚ እግዚአብሔርን ይጠላዋል፤ ከመዳንም ፈጽሞ የራቀ ነው፡፡» #ቅዱስ_ኤፍሬም

"እውነተኛ ክርስቲያን በቃሉ ብቻ ሳይሆን በኑሮው ይሰብካል'' አባ እንጦንስ

እውነተኛ አምልኮት የሚጀምረው ይኼንን የህይወት መርህ በመረዳት ነው! ደክሜ ለፍቼ ዛሬም ባዶ ነኝ ምን ላድርግ? መንበርከክ ከቻላችሁ ይኼንን ታገኛላችሁና ንቁ! https://youtu.be/tOQp-qaVcLQ

"እጅግ ምርጡ ጸሎት 'ጌታ ሆይ አንተ ሁሉን ታውቃለህ የፈቀድከውን አድርግልኝ።' ማለት ነው።" (ባሕታዊ ቴዎፋን)

ወንድሜ በኔ በኃጢያተኛዋ ላይ ቅዱስ ሚካኤል ያደረገውን አንድ ምስክርነት ልናገር ሐሙስ ማለትም በ 11 ቅዱስ ቁርባን ልቀበል ነበር እና እሮብ ማታ ከየት መጣ ሳልለው ታመምኩ ከዛ ትናንት ማታ ማለትም 11 ማታ በጣም ብሶብኝ ሙሉ ሰውነቴ መንቀጥቀጥ ይጀምራል መንቀጥቀጥ ስልህ ቀላል እንዳይመስልህ ከዛ በቃ ሞትኩ አበቃ ማለት ነው እላለው ለራሴ እና አይኔን ሳልገልጥ ግን አባቴ ድርሳነ ሚካኤል ሲያደርስ ይታወቀኛል እና አንዴ እየፀለየ አንዴ እየደባበሰኝ በ ፀሎቱ መፅሐፍ አይነጋም አበቃለት ያልኩት ሌሊት ነግቶ ለመመስከር በቅቻለው ወንድሜ 🥹🥹🥹

በመምህር ተስፋዬና በመጋቢ ሐዲስ እሼቱ መካከል የተፈጠረው ምንድነው?? ብዙ ባልና ምስቶች በጸበል ተፋቷል የመጋቢ ሐዲስ ንግግር! #አጋንንት #መናፍስት #ጸሎት https://youtu.be/h792LhWyHN8

የአመቱ ሰው ይበለን! ቅዱስ ሚካኤል የሚገርም ቀን ነበር። እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን። 🙏🙏🙏

#ህዳር_12 በዓለ ሢመቱ #ለሊቀ_መላእክት_ቅዱስ_ሚካኤል "#ሚካኤል ሥዩም በዲበ ኃይላት፤ በኃይላት ላይ የተሾምክ ሚካኤል› ሲል ቅዱስ ኤጲፋንዮስ እንዳመሰገነው፤ - #ቅዱስ_ሚካኤል በኃይላት መላእክት ላይ የተሾመ ሊቀ መላእክት እንደመሆኑ በዓለ ሢመቱ ኅዳር ፲፪ ቀን በመላው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በድምቀት ይከበራል፡፡ (መጽሐፈ አክሲማሮስ) ኃይላት የተባሉት መላእክትም ሰዎች በዓለም ፈተና ውስጥ ሆነው ሰይጣን ሊያደክማቸው ሲፈልግ ኃይልን ብርታትን የሚሰጡ፣ ይህን ዓለም ንቀው በበርሃ ወድቀው ከሥጋ ምኞት ጋር የሚጋደሉትን፣ በከተማም እየኖሩ መንፈሳዊ ትሩፋት የሚያደርጉትን ደግሞ የሚያበረቱ ናቸው፡፡ - ቅዱስ ጴጥሮስ በመልእክቱ ‹እርሱም ወደ ሰማይ ያረገ እግዚአብሔርም ተቀምጦ ያለ መላእክትና ሥልጣናት ኃይላትም የተገዙለት ነው…› ሲል  ‹ኃይላት› በማለት ያነሣቸው በኢዮር አራተኛይቷ  ከተማ  የሚኖሩትን  ነው፡፡ በእነዚህ ላይ እግዚአብሔር  ቅዱስ ሚካኤልን አለቃቸው አድርጎ ሾሞታል፡፡ (፩ኛጴጥ.፫፥፳፪) - #የቅዱስ_ሚካኤል  ሢመት  በነገደ  መላእክት  ላይ ብቻም ግን  አይደለም፤  የእግዚአብሔር  ሕዝብ  በሆኑት  ላይም ጭምር ነው፡፡ ኃያሉ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል የስሙ ትርጓሜ በዕብራይስጥ ‹‹እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው!›› ማለት እንደሆነ ቅዱሳት መጻሕፍት ይጠቅሳሉ፤ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመዝገበ ቃላት መጽሐፋቸው ላይ እንዳሰፈሩት ደግሞ የስሙን ፊደላት በመተንተን እንዲህ ተርጉመውታል፤ ሚ-መኑ፣ ካ-ከመ፣ ኤል-አምላክ፤ ‹‹መኑ ከመ አምላክ፤ እንደ አምላክ  ማን ነው!›› (መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ) - የሰማይ ሠራዊት ሁሉ አለቃቸው  ለፍጥረት ሁሉ የሚማልድ  ይህ ኃያል መልአክ  ቅዱስ  ሚካኤል በብሉይ  ኪዳን  የእግዚአብሔር  ሕዝብ  የተባሉትን  እስራኤል  ዘሥጋን  ሲረዳና  ሲጠብቅ  እንደነበረ ተጽፎልን  እናገኛለን፡፡ ለምሳሌ  መልአኩ  ቅዱስ  ሚካኤል  ለኢያሱ  በኢያሪኮ  ምድረ  በዳ  እንደተገለጠለት  ‹‹… ዐይኑን  አንሥቶ  ተመለከተ፤  እነሆም፥  የተመዘዘ  ሰይፍ  በእጁ የያዘ  ሰው  በፊቱ  ቆሞ አየ፤  ኢያሱም  ወደ  እርሱ  ቀርቦ፥  “ከእኛ  ወገን  ወይስ  ከጠላቶቻችን  ወገን  ነህ?” አለው፡፡  እርሱም “እኔ  የእግዚአብሔር  ሠራዊት  አለቃ  ነኝ፤  አሁንም  ወደ  አንተ መጥቼአለሁ፡፡” ሲል ተናግሯል፡፡ (ኢያ.፭፥፲፫) - እግዚአብሔር አምላክ ሕዝበ እስራኤልን ከግብጽ ባርነት ነፃ ሲያወጣቸው ይመራቸው የነበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነበር፡፡ ‹‹ በመንገድህ ይጠብቅህ ዘንድ፥ ወዳዘጋጀሁልህም ስፍራ ያገባህ ዘንድ፥ እነሆ ፥እኔ መልአኬን በፊትህ እልካለሁ››  እንዲል፤  ሹመቱ  በእግዚአብሔር  ሕዝብ  ላይም  በመሆኑ  ስለ  እነርሱ ከእግዚአብሔር ምሕረትን ይለምንላቸው  ነበር፡፡ (ዘፀአት.፳፫፥፳) - ነገር ግን ኃጢአት ሲሠሩ እግዚአብሔር ኃጢአተኞችን ይቀጣልና ሕዝቡን  ‹‹ራስህን ጠብቅ፤ ስማው፤ እንቢም አትበለው፤ ስሜ በእርሱ ስለሆነ ይቅር አይልምና›› ብሎ  አስጠንቅቋቸው  ነበር፤   ይህም   ቅዱስ  ሚካኤል  በእግዚአብሔር  ሕዝብ  ላይ  መሾሙን  ያስረዳናል፡፡  (ዘፀ.፳፫፥፳፩) ቅዱስ ገብርኤል በእግዚአብሔር  ሕዝብ  ላይ  ቅዱስ ሚካኤል  ስለመሾሙ ሲመሰክር ‹‹በእውነት   በመጽሐፍ   የተጻፈውን   እነግርሃለሁ፤   በዚህም  ነገር  ከአለቃችሁ  ከሚካኤል  በቀር   የሚረዳኝ  ማንም  የለም›› ብሎአል፡፡  ስለዚህም  ለኢያሱ   የተገለጠውና  እስራኤላውያንንም  የመራው  መልአክ  ቅዱስ  ሚካኤል  መሆኑን እንረዳለን፡፡ (ዳን.፲፥፳፩) - የቅዱስ ሚካኤል አማላጅነት በሐዲስ ኪዳንም እንደነበር ይህ ነቢይ በትንቢቱ ‹‹በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች  የሚቆመው  ታላቁ  ሚካኤል ይነሣል›› በማለት  ተናግሮለታል፡፡ ስለዚህም   ቅዱስ  ሚካኤል   እኛን  ከሰይጣን  አሽክላና  ወጥመድ  ይጠብቀንና  በጸሎቱ  በእግዚአብሔር  ፊት  ይቆምልን  ዘንድ  በእኛም  ላይ  ሹም  ነው፡፡ ምክንያቱም  እኛ  የእግዚአብሔር  ሕዝቦችና  የርስቱ ወራሾች ነንና፡፡  (ዳን.፲፪፥፩) በመጽሐፈ ስንክሳርም ተመዝግቦ እንደምናኘው ቅዱስ ሚካኤል በየወሩ በዐሥራ ሁለት ቀን ለመታሰቢያው በዓል ተሠርቶለታል፤ እርሱ ስለ እኛ የምድሩን ፍሬ ይባርክልን ዘንድ ዝናሙም በጊዜው እንዲወርድልን የወንዙንም ውኃ እንዲመላልን ነፋሱንም የምሕረት ነፋስ እንዲያደርግልን ሁሉንም የተስተካከለ እንዲያደርግልን ወደ እግዚአብሔር በጸሎት ይማልዳልና፡፡ (ስንክሳር ኅዳር ፲፪) - ስለሆነም በኃጢአት ባርነት ተይዘን በችግር እና በመከራ ውስጥ ተዘፍቀን ለምንኖር ሰዎች ስለ  ሕዝበ  እስራኤል  በእግዚአብሔር  ፊት  የቆመው  ሊቀ  መላእክት  ቅዱስ  ሚካኤል  ለእኛም  ያማልደንና ተራዳኢ ይሆነን ዘንድ በጸሎት እንማጸነው። አምላካችን  እግዚአብሔርም  የምሕረት  ፊቱን  ወደ  እኛ  በመመለስ በጸብና  በጦርነት  ምትክ  ፍቅርን፣  ሰላምንና  መግባባትን፤  በመለያየት  ምትክ አንድነትን እንዲሰጠን በቅዱስ ሚካኤል ስም እንለምን። #የሊቀ_መላእክት_ቅዱስ_ሚካኤል አማላጅነትና ተራዳኢነት  አይለየን፤  አሜን፡፡ / መጽሐፈ ዘኅዳር 12 : መጽሐፈ አክሲማሮስ /

🙏 እንኳን ለሊቀ መላእክት ለቅዱስ ሚካኤል በዓለ ሢመት በሰላም በጤና አደረሳችሁ 🌺
🙏 እንኳን ለሊቀ መላእክት ለቅዱስ ሚካኤል በዓለ ሢመት በሰላም በጤና አደረሳችሁ 🌺

#ኅዳር_11 #ቅድስት_ሐና ኅዳር ዐሥራ አንድ በዚች ዕለት አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እናቷ የሆነች የተመሰገነች የቅድስት ሐና የዕረፍቷ መታሰቢያ ነው። ይችም ቅድስት ከኢየሩሳሌም አገር ከሌዊ ነገድ ከካህኑ አሮን ትውልድ የሌዊ የሜልኪ ልጅ ለሆነ ለማጣት ልጁ ናት። ለማጣትም ሦስት ሴቶች ልጆች አሉት የታላቂቱም ስሟ ማርያም ናት ሁለተኛዋም ስሟ ሶፍያ ሦስተኛዪቱም ስሟ ሐና ናት ታላቂቱ ማርያምም ለባል ተድራ አዋላጅ የሆነች ሰሎሜን ወለደቻት እርሷም መድኃኒታችንን ከወለደችበት ጊዜ ጀምሮ በስደቷም ወራት ከአረጋዊ ዮሴፍ ጋር እመቤታችንን ድንግል ማርያምን ያገለገለቻት ናት። ሶፍያም ለባል ተድራ ለመጥመቁ ዮሐንስ እናቱ የሆነች ቅድስት ኤልሳቤጥን ወለደቻት። ይችንም ቅድስት ሐናን ከይሁዳ ነገድ ለሆነ ጻድቅ ስሙ ኢያቄም ለሚባል አጋቧትና እመቤታችንን ቅድስት ድንግል ማርያምን ወለደቻት እሊህም ሰሎሜና ኤልሳቤጥ ለቅድስት ሐና የእኅትማማች ልጆች ናቸው። የዚችንም የቅድስት ሐናን በሥውር የምትሠራውን ገድሏንና ትሩፋቷን እንዳናስታውሰው አናውቀውም ግን ከሴቶች ሁሉ እንደምትበልጥና እንደምትከብር እናውቃለን እንረዳለን እርሷ አምላክን በሥጋ ለወለደችው ወላጅዋ ትሆን ዘንድ የተገባት ሁናለችና ከሴቶች ሁሉ የሚበልጥና የሚበዛ ትሩፋትና ተጋድሎ ባይኖራት ይህ ታላቅ ጸጋ ባልተገባት ነበር። ይህችም ጻድቅት ሐና መካን በመሆንዋ ልጅን ይሰጣት ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ዘወትር በጸሎት ትማልድ ነበር እግዚአብሔርም በእርሷ ለዓለም ሁሉ ድኅነት የተደረገባትን ይቺን የተባረከችና የከበረች ልጅን ሰጣት እርሷም አምላክን የወለደች እመቤታችን ድንግል ማርያም ናት። ስለዚህም ይህን ታላቅ ጸጋ ስለሰጣት የበዓሏን መታሰቢያ በደስታ ልናከብር ይገባናል። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን በጸሎቷ የሚገኝ በረከቷም ከእኛ ጋር ይሁን ለዘላለሙ አሜን። (#ስንክሳር_ዘወርኀ_ኅዳር)

ለንስሐ አባቴ ሳልናዘዝ ቅዱስ ቁርባን ተቀበልኩ የተፈጠረውን ተመልከቱ!! የሰላቢ መንፈስና የሆቴሎቻችን ጉድ! 3 ሚሊዮን ብር በመተት የተቀማው ወጣትና መከራው! https://youtu.be/r_wogRLw57A

😡 ዝም ብትልም ያፈናቅሉሀል ንብረትህን ያወድሙብሀል በመጨረሻም እንደ አርሲ ምዕመናን ጨፍጭፈው ይገድሉሀል። ዲያቆን ዮሴፍ ፍሥሓን ማሰርም ለኦርቶዶክሳዊያን ከተደገሰው የመከራ ትሩፋት አንዱ ነው። እ
😡 ዝም ብትልም ያፈናቅሉሀል ንብረትህን ያወድሙብሀል በመጨረሻም እንደ አርሲ ምዕመናን ጨፍጭፈው ይገድሉሀል። ዲያቆን ዮሴፍ ፍሥሓን ማሰርም ለኦርቶዶክሳዊያን ከተደገሰው የመከራ ትሩፋት አንዱ ነው። እንደ ዲያቆን ዮሴፍ ነቅተህ ፍትህ ስትጠይቅም ያፍኑሀል ያስሩሀል ድራሽህን ያጠፉሀል። ምክንያቱም ኦርቶዶክስን ማዳከም ማመንመን ማፅዳት ማጥፋት ቋሚ ተረክ ያለው ፕሮጀክት ስለሆነ ነው። ከሆነውና እየሆነ ካለው ይልቅ ሊሆን ያለው በብዙ እጥፍ አደ,ገኛ አስፈ,ሪ እና ጅምላ ጨራ,ሽ ነው። ዛሬ የተሻለ ካልሰራን ዛሬን የሚያስናፍቅ መከ,ራ ከፊታችን ላይ አለ። መፍትሄው አንድ ልብ ሆኖ ለእውነት መቆም አስተማማኝ ፍትህን መፈለግ ብቻ ነው። (የኔታ ገብረ መድህን እንየው) ዲያቆን ዮሴፍ ከስራ ቦታ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ተወስዷል። ያለበት ቦታም አልታወቀም። በምስራቅ አርሲ በኦርቶዶክሳዊያን ላይ በተደረገው ግፍ ጠንከር ያለ ትችት ሲያቀርብ ቆይቶ ነበር።

ወላጆች ሴት ልጆቻችሁን ጠብቁ ዘመኑ እጅግ ከፍቷል ይኼንን ተመልከቱ!! መላቀቅ ያልቻልነው የዝሙት መንፈስ ፈተናዎች! መንፈሳዊነት ከማንነት ጋር ሲጣመር! #ንቁ https://youtu.be/S9jbIrUo9fY

#ቅዱስ_ሚካኤል! ህዳር 12

ኅዳር ፲ /10/ ‎ ‎በዚች ቀን ቅዱሳት ንጹሐት መነኰሳይያት ደናግል እናታቸው ሶፍያም በሰማዕትነት አረፉ። እኚህም ቅዱሳት ከተለያዩ አገሮችና ቦታዎች ሲሆኑ መለኮታዊ ፍቅር በአንድነት ሰበሰባቸው የም
ኅዳር ፲ /10/ ‎በዚች ቀን ቅዱሳት ንጹሐት መነኰሳይያት ደናግል እናታቸው ሶፍያም በሰማዕትነት አረፉ። እኚህም ቅዱሳት ከተለያዩ አገሮችና ቦታዎች ሲሆኑ መለኮታዊ ፍቅር በአንድነት ሰበሰባቸው የምንኲስናንም ልብስ ለበሱ ይኸውም የመላእክት ልብስ ነው። በሮሜ አገር ከአሉ ገዳማትም በአንዱ የሚኖሩ ሆኑ ቅድስት ሶፍያም በእነርሱ ላይ እመ ምኔት ሆነች። ‎እርሷም ጸጋንና ዕውቀትን የተመላች ናት የቅዱሳን መነኰሳትን ገድል በማንበብ እየጾሙ እየጸለዩ በምድር ላይ እንደ መላእክት እስከ ሆኑ ድረስ መንፈሳዊ ዕድገትን አሳደገቻቸው ከእነርሱም በአንድ ገዳም ውስጥ ሰባ ዓመት ያህል የኖሩ አሉ ከውስጣቸውም ልጅ እግሮች የሆኑ አሉ። ‎ ‎ከሀዲ ንጉሥ ዑልያኖስም ከፋርስ ንጉሥ ከሳቦር ጋር ሊዋጋ በሮሀ ሀገር በኩል በሚያልፍ ጊዜ እርሱ ሳቦር ሊወጋው ወደርሱ እንደሚመጣ ሰምቷልና አልፎ ሲሔድም በውስጡ እሊህ ደናግል ያሉበትን ገዳም አይቶ ይህ ምንድን ነው ብሎ ጠየቀ ሰዎችም ይህ የደናግሎች ገዳም ነው አሉት። ‎በዚያንም ጊዜ ወደዚያ ገዳም ገብተው ደናግሎችን እንዲገድሏቸው በገዳሙ ውስጥም ያለ ገንዘባቸውን ሁሉ እንዲዘርፉ ወታደሮቹን አዘዘ ወታደሮችም ገብተው እሊያን ደናግል በሰይፍ ገደሏቸው ገዳሙንም አጠፉ የገዳሙን ገንዘብ ሁሉንም ዘረፉ። ‎ ‎ከሀዲውን ንጉሥ ግን ስለ መንጋዎቹ በቀል እግዚአብሔር ተበቀለው ይህም እንዲህ ነው ያጠፋው ዘንድ ሰማዕት መርቆሬዎስን አዘዘው መርቆሬዎስም በአካለ ነፍስ ሒዶ በጦር ወጋውና በክፉ አሟሟት ሙቶ ወደ ዘላለም ሥቃይ ሔደ። እሊህ ቅዱሳት ደናግል ግን ወደ ዘላለም ተድላ ደስታ ገቡ። ‎ ‎ወስብሐት ለእግዚአብሔር #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 https://www.tiktok.com/@walkinaddistv

"We believe that our Lord, God and Saviour Jesus Christ, the Incarnate - Logos is perfect in His Divinity and perfect in His Humanity. He made His humanity One with His Divinity without Mixture, nor Mingling, nor Confusion. His Divinity was not separated from His Humanity even for a moment or twinkling of an eye. At the same time, we anathematize the Doctrines of both Nestorius and Eutyches".

ስንታረድ ስንገደል እግዚአብሔር ለምን ዝም ይላል?? ገዳማት በማዞር ዕድሜያችንን የሚጨርሱ ክፉ መናፍስትና ሴራቸው! በድመት ሥጋ የተደገመ መተት ያስከተለውጣጣ! https://youtu.be/Cr1fsh1E8Nw