fa
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

رفتن به کانال در Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

نمایش بیشتر
2 279
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+57 روز
+3230 روز
آرشیو پست ها
«የአህያዋ ተማሪ...» "አህያይቱም የእግዚአብሔርን መልአክ አየች፣ ከበለዓምም በታች ተኛች፣ በለዓምም እጅግ ተቆጣ፣ አህያይቱንም በበትሩ ደበደባት።" ◈ እግዚአብሔርም የአህያይቱን አፍ ከፈተ፣ በለዓምንም፥ ሶስት ጊዜ የመታኸኝ ምን አድርጌብህ ነው? አለችው። በለዓምም አህያይቱን እንዲህ አላት ስላላገጥሽብኝ ነው፣ በእጀስ ሰይፍ ቢኖር አሁን #በገደልሁሽ ነበር አላት። አህያይቱም በለዓምን ከብዙ ጊዜ ዘመን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ የምትቀመጥብኝ አህያህ አይደለሁምን? አለችው። በውኑ እንዲህ አደርግ ዘንድ ልማዴ ነበርን? አለችው። እርሱም እንዲህ አላደረግሽም አላት። እግዚአብሔርም የበለዓምን ዓይኖች ከፈተ፣ የእግዚአብሔርን መልአክ በመንገድ ላይ ቆሞ የተመዘዘም ሰይፍ በእጁ ይዞ አየ፣ ሰገደም በግንባሩም ወደቀ። (ዘኁ.22:27-31) ◈ በማንኛውም ጊዜ የተለያየ ችግር፣ ወጥመድ፣ የመንፈስ እስራትና መከራ ውስጥም ብትሆን፣ ወይም ስልጣን፣ ማዕረግ፣ ሃብትና እውቀት ቢኖሩህም፣ ስግደት ስትጀምር፣ ከዚህ በፍት ያላየኸውን ያላወቅኸውን መንፈሳዊ መረጃ እግዚአብሔር ይገልጥልሃል። ለሰበዓ ሰገልም የሄሮድስን ተንኮል የገለጸው በአምልኮት በመንበርከካቸው ነው። ሌላ መንገድ አግኝተው ወደ ሃገራቸው ስመለሱ የሚያስታውሱት በመንበርከካቸው እና በስግደታቸው ያገኙትን እርካታ በደስታ ተቀብለው ነው። መንበርከክ የመንፈሳዊውንና የዓለምን ድብቅ የምስጥር አጀንዳ፣ የማወቅያና የመገንዘቢያ ቁልፍ ነው። መስገድ ስትጀምር ዓይኖችህም ጆሮዎችህም ይከፈታሉ። ◈ በለዓምን፣ «የእግዚአብሔር መልዓክ አህያህን ሶስት ጊዜ ለምን መታህ? እነሆ፣ መንገድህ በፊቴ ጠማማ ነውና እቋቋምህ ዘንድ ወጥቼአለሁ።» አለው። (ዘኁ 22፥32) ከስግደት በኋላ ጉልበት፣ ትምክህትና፣ እብርት የሉም። ምክንያቱም በራዕ ውስጥ ያለ ሰው፣ ወደ ውስጥና ውጭ በማየት፣ ነፍሱ በበረከት ጥማት ስለምትጠመድ ነው። ሥጋዊ ክንድና ወኔ፣ በተገለጠ ራዕይ ፍት ባዶ ነው። አሁን አማራጩ ከእርግማን ዓለም ወጥቶ፣ የእግዚአብሔርን መንገድ መያዝ ብቻ ነው። ◈ «በለዓምም የእግዚአብሔርን መልአክ፣ በድያለሁ አንተ በመንገድ ላይ በፍቴ እንደቆምህብኝ አላወቁሁም» አለ (ዘኁል 22:34) የአህያዋ ተማር በድያለሁ አለ። ስግደት የውስጥ የበደል ምስጥርህን እንዲታወጣው ለንስሐ ያግዝሃል። የበለዓምም ስግደት ለዘሮቹ ወርዶ ሰበዓ ሰገል በቤተልሔም ለተወለደው አምላክ «ባዩት ጊዜ ተንበርክከው ሰገዱ» የአህያዋ ተማርዎች የአባቶቻቸውን አደራ አይረሱም። ከራሱና ከዘሩ ላይ እርግማንን ለማቆምና የእርግማንን ኃይል ለመሻር፣ በለዓም በራዕይ ውስጥ ማለፍ መሰረታዊው ግዴታ ነበር። ከዚህም የተነሳ እግዚአብሔር ለእስራኤል ሕዝብ ያሳየው የጥበቃው ፍቅር ስገለጥ፣ የእርግማንን ኃይልና የአህዛብን የአፍዝ አደንግዝ አዚም መሪውን በለዓምን ጨምሮ በቁጥጥር ሥር በማዋል የአምላክነቱን ክብር አሳይቶአቸዋል። ክብር ምስጋና ለአምላካችን ይሁን! እንበርታ! #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

«የእግዚአብሔርን አባትነት በረሃብ እና በጥጋብ፣ በድህነት እና በባለጠግነት አትመዝነው። እርሱ ሲፈልግ በምግብ፣ ሲያሻው ደግሞ ያለ ምግብም ሊያኖርህ ይችላል። አባት ስለሆነ ግን ለአንተ ያዘጋጀው እና የፍቀ‍ሩ መታወቂያ ያደረገው መንግሥቱን ነው። ስለዚህ ከወራሽነት እንዳትወጣ ልጅነትህን ጠብቅ።» መልካም የዐቢይ ጾም ይሁንልን!

አልዛይመር፣ አስም፣ ዲዳና ደንቆሮ የሚያደርጉ የወሰንጋላ፣ የመተትና የዛር መናፍስቶች ፈተና || አባትና እናት ጸሎት ሲያቆሙ ፈተናው ይበዛል #ethiopia https://youtu.be/1fdRgxUw5s8

"ሰውነታችሁን ለሰይጣን ምቹ አታደርጉ" ❖ ተወዳጆች ሆይ የብዙዎቻችን ሰውነት ለሰይጣን ምቹ ነው፤ ለሰይጣን ምቹ ሰውነት ማለት ንስሐ ያልገባ በኃጢአት ግራ የሚጋባ ሰውነት ነው፤ ለሰይጣን ምቹ የሆነ ሰውነት ማለት በሐሜት፣ በቧልት፣ በምቀኝነት፣ በክፋት፣ በዝሙት፣ በስኳር፣ በአድመኝነት፣ በዘረኝነት ወዘተ የረከሰ ሰውነት ማለት ነው፡፡ ❖ ለሰይጣን ምቹ ሰውነት ማለት ለፈጣሪ የማይንበረከክ፣ ሰማያዊ አምልኮት የማያቀርብ፣ የማይሰግድ፣ የማይጸልይ፣ የማይጾም፣ ቅዱስ ቁርባን የማይቀበል ነው፤ የአንዳንዶቻችን ሰውነት ለምጽዋት የተዘረጋ ነው፤ ነገር ግን በዝሙት የረከሰ ነው፤ ይህ ለሰይጣን ምቹ ነው አንዳንዶቻችን ጸሎተኛ ነን በጸሎተኝነታችን ልክ እጅግ ሐሜተኛ እና ቅናተኛ ነን፤ በዚህም ለሰይጣን ምቹ ነን፡፡ ❖ አንዳንዶቻችን እጅግ አማኝ እና ሰርክ ለኪዳን፣ ለቅዳሴ እና ለጉባኤ ከቤተ ክርስትያን የማንርቅ ነን ነገር ግን ሲበዛ ቂመኛ እና ይቅርታ የለሾች ጨካኝ ነን፤ በዚህም ለሰይጣን ምቹ ነን አንዳንዶቻችን ቅዱስ ቁርባን ተቀብለን አንደበታችንን በመዓዛ መለኮት ማጣፈጥ እየቻልን ‹‹እግዚአብሔር ይቅር ይበለኝና›› እያልን አንደበታችን በሐሜት የመረረ ነው፤ በዚህም ለሰይጣን ምቹ ነን፡፡ ❖ አንዳንዶቻችን በመንፈሳዊ እውቀታችን ሰዎችን መክረን፣ አስተምረን ከኃጢአት መልሰን ለንስሐ እናበቃለን እኛ ግን ተመክረን የማንሰማ፣ ከኃጢአታችን መመለስ ያቀተን፣ ንስሐ የማንገባ ለቅዱስ ቁርባን የማንበቃ ነን፤ በዚህ ለሰይጣን ምቹ ነን፡፡ ❖ አንዳንዶቻችን የወሲብ ፊልም ማየት፣ ግለ ወሲብ መፈጸም ኃጢአት እንደሆነ ለሰው እንናገራለን እናስተምራለን በዚህም እነዛ ሰዎች ከዚህ ሰይጣናዊ ሱስ ተላቀው ንስሐ ይገባሉ ልማደ ሰይጣንንም ይተዋሉ፤ እኛ ግን ሰው ባላየ እግዚአብሔር ባየ የወሲብ ፊልም እናያለን ግለ ወሲብ እንፈጽማለን፤ በዚህም ለሰይጣን እንመቻለን፡፡ ❖ አንዳንዶቻችን መጽውቱ ብለን ሰዎች እንዲመጸውቱ፣ ድሆችን እንዲረዱ እናደርጋለን፤ የእኛ እጅ ግን በታንክ ፍሬን ተይዟል፣ መመጽወትም እንቢ ብሎናል፤ በዚህም ለሰይጣን ምቹ ነን፡፡ ❖ አንዳንዶቻችን ሰዎች ሲያማቸው እንዲጸልዩ፣ ጸበል እንዲጠመቁና በዚህም እንደሚድኑ መክረን እነዛ ሰዎች በምክራችን ተጠቅመው ጸልየው ተጠምቀው ይድናሉ፤ እኛ ስንታመም ግን እምነት አጥተን በየሆስፒታሉ እንንከራተታለን፤ በዚህ ለሰይጣን ምቹ ነን፡፡ ❖ ወዳጆቼ በየትኛውም ጉድለታችን ሰይጣን ወደ ሕይወታችን ይገባል፤ ሰይጣን ትንሿን ስህተታችንን፣ የኃጢአት ፍላጎታችንን አይቶ ወደ እኛ ጎራ ይልና ትንሿን ስህተት ትልቅ፣ ኃጢአትን ደግሞ ጽድቅ አድርጎ የእሱ መጫወቻ ያደርገናል፡፡ ❖ ሰይጣን አንዴ በዝሙት ከጣለን ስሜታችን ደግሞ ደጋግሞ ይጥለናል፤ ሰይጣን በመርፌ ቀዳዳ ስህተት ይገባና እኛ ግን ከስህተታችን በሰፊው በር መውጣት ያቅተናል፤ ዛሬ ሥጋዊ ፍላጎታችን፣ ዓላማችን፣ እውቀታችን፣ ትምህርታችን፣ ርእዮተ ዓለማችን፣ አመለካከታችን በራሱ ለሰይጣን ምቹ ስለሚሆን ልናስተውል እና ልንነቃ ይገባናል፤ ዛሬ ከላይ እስከታች፣ ከቤተ ክህነት እስከ ቤተ መንግስት፣ ከዓለማዊው እስከ መንፈሳዊው፣ ከምሁሩ እስከ ፊደል ነውሩ፣ ከወጣቱ እስከ አዛውንቱ ያለነው ሰውነታችን ለሰይጣን ምቹ ስለሆነ ሕይወታችን በፈተና፣ በስቃይ፣ በመንፈሳዊ ባዶነት የተመላ ነው፡፡ እግዚአብሔር ✍️ ‹‹እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ነኝና፣ ሰውነታችሁን ቀድሱ፣ ቅዱሳንም ሁኑ›› ብሎ አዞናል፡፡ ❖ ነገር ግን ሰውነታችንን በኃጢአት አረከስን፣ ሕገ እግዚአብሔርንም አፈረስን፤ በዚህም ለሰይጣን ምቹ ሆንን፤ ሰይጣን ለራሱ ምቹ በሆነ ሰው እና ሰውነት ላይ እንደፈለገ ይሆናል፣ የፈለገውን ዓላማ ይፈጽማል፣ ለሚፈልገው ዓላማ መጠቀሚያ ያደርገዋል፡፡ (ዘሌ 11÷44) ✍️ ቅዱስ ጳውሎስም ‹‹ሰውነታችሁን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ሕያው ቅዱስም መሥዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ በእግዚአብሔር ርኅራኄ እለምናችኃለሁ›› በማለት የልመና ጥሪ ያቀርብልናል፡፡ (ሮሜ 12÷1) ❖ በእውነት ሰውነታችን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ነው? ሰውነታችን ቅዱስ እና መሥዋዕት ነው? ሰውነት በኃጢአት ሲረክስ ነፍስም ትረክሳለች፡፡ ❖ ልብ በሉ ቆሻሻ ነገር ላይ እና ቆሻሻ ስፍራ ላይ ዝንቦች ይሰፍራሉ፤ በኃጢአት የቆሸሸ እና የተበላሸ ሰውነት ላይ አጋንንት ይሰፍራሉ፤ በቆሻሻ ነገር እና በቆሻሻ ስፍራ ላይ ዝንቦች ለሰው ጎጂ የሆኑ በሽታዎችን ያከማቻሉ፤ በኃጢአት በቆሸሸ ሰውነት ላይም አጋንንት መንፈሳዊ ሕይወታችንን የሚያጠለሽ፣ ነፍሳችንን የሚያቆሽሽ ክፉ መርዙን ይረጫል፣ ጎጂ የሆነ ኃጢአትንም ያጠራቅማል፣ የሥጋ እና የነፍስ በሽታ ይሆናል፡፡  ✍️ ‹‹በእነርሱ እንዳትረክሱ ሰውነታችሁን አታርክሱ›› ብሎናል ‹‹በእነርሱ እንዳትረክሱ›› ያለው አንድም በሰይጣን ክፉ ምሪት እና ተግባራት ሰውነታችንን፣ ነፍሳችንን እንዳናረክስ ነው፡፡ (ዘሌ 11÷43) ❖ ስለዚህ ሰውነታችሁን ለንስሐ፣ ለጽድቅ፣ ለጾም፣ ለጸሎት፣ ለስግደት እና ለቅዱስ ቁርባን ምቹ አድርጉ እንጂ በፍጹም ለሰይጣን ምቹ አታድርጉ፡፡ ✍️"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል" (ምሳ 1፥33)

የአይነጥላ መንፈስ ሌላ ማንነት በሕይወትህ ይሰጥሃል፣ ያቆረቁዝሃልም በቅዳሴ ወቅት መቼ እንቀመጥ በማለዳ ንቁ 2024 | መምህር ግርማ ወንድሙ | 😭😭 https://youtu.be/-NYFY-ChVKE

ከአይነጥላ መንፈስ ጋር ለመዘሞት ቤርጎ ቤት የሚከራየው ወጣት የጠቋር መንፈስ የአያያዝ ስልቱና ባሕሪይው መምህር ግርማ ወንድሙ | ተስፋዬ አበራ 😰😰🙄 #ethiopia #orthodox #sibket #eotc #tewahido #habeshatiktok #ethiopianmusic #ethiopian https://youtu.be/DLkKqrf4jqg

እኔ በጭራሽ ሲዖል መግባትን፣ መሞትን አልፈራም ከክርስቶስ መለየትን እንጂ የእማሆይ ዜና ማሪያም ድንቅ ትምህርት የአባ ቢሾይ መንፈሳዊ ሕይወት 😰😰🙏 https://youtu.be/PI88ppsy8IM

አገልጋዮች ብዙ ዘመን ተኝታችኋል ንቁ! ካህኑም፣ ዲያቆኑም ተኙ ይሉናል || በጸሎት የተወለዱ ልጆች የሚያገኙት በረከቶች በማለዳ ንቁ 2024 ግርማ ወንድሙ 😭😭 https://youtu.be/AYKuQcTqjfc

‹‹ተጣልሁ፣ እርሱም ከተጣልሁበት ከጥልቁ ሰማኝ፣ ሞት በሲኦል መካከል አሳለፈኝ፣ አንተ ግን ጠበቅኸኝ፡፡ ባሕር ከበበኝ አንተም ያለ መቅዘፊያ ጠበቅኸኝ (ከለልኸኝ)፡፡ አንተ በጥልቁ ቆለፍኽብኝ፣ ወደ ባሕሩም ጣልኸኝ፡፡ወደ ባሕሩ ጥልቅ ወረድሁ፣ እሞት ዘንድ ግን አልተውኸኝም፡፡ ሞት ሰለቀጠኝ፣ አንተ ግን በአፉ ውስጥ ሕያው አድርገህ አኖርኸኝ፡፡ ምንም እንኳን ውኃው ቢሸፍነኝም፣ እታፈን ዘንድ ግን አልተውኸኝም፡፡ ዳሩ ግን መደነቅ ያዘኝ! ህይንተ ሞት ሕይወት ከፍ ከፍ አደረገኝ! ተስፋዬ ሙሉ ለሙሉ ሲሟጠጥ አንተ መለስኸኝ፡፡ ስለዚህ ከጥልቁ ባሕር አንደበቴ በብዙ አመሰገነህ፣ ከባሕሩ ጠልልም በደስታ ለገናናው ስምህ ዘመርኩልህ፡፡ ጌታ ሆይ፥ በኢየሩሳሌም ባለው ታላቅ ቤተ መቅደስ በታቦቱ ተውኩህ (ከአንተ ተለይቼ ወጣሁ)፣ ነገር ግን በመሬት ሥር በጥልቁ ለእኔ መንገድን ስታዘጋጅልኝ አገኘሁህ፡፡ አንተ ከውኆች በላይና በታች፣ በእርሱ ውስጥና ከርሱ ወዲያም በምልዓት አለህ፡፡ አድባራት፣ ቀላያት፣ አቅጣጫዎች ኹሉም ያለማቋረጥ ያለመታከት ያመሰግኑሃል፡፡›› (የምሕረት በር፣ ገጽ 261፣ ዮና.3፡3- ነገሬን ሰማኝ) -- እኛንም ይስማን! #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

ቋንቋችን የተደበላለቀ ነው፣ አንስማማም የትዳር ትልቁ መናፍስታዊ ፈተና || የጸሎትና የስግደት ጊዜ የለንም መምህር ግርማ ወንድሙ ተስፋዬ አበራ 😭😰🙄 https://youtu.be/PnUGM6MCN5I

«ምርጫችንን እናስተካክል! የቱ ይበልጣል?» አንድ እውነተኛ ክርስቲያን ለሦስት ሠራተኞች በቤቱ ውስጥ የቀን ሥራ ሰጣቸው። ሠራተኞቹ ሥራቸውን በጨረሱ ጊዜ ይሸልማቸው ዘንድ ጠራቸው። ታዲያስ ከፊታቸው ሦስት የወርቅ ሳንቲምና ሦስት መንፈሳዊ መጻሕፍትን አስቀምጦ፥ የወርቅ ሳንቲሙን ወይም መጽሐፉን እንዲመርጡ ነገራቸው። ሁለቱ ሠራተኞች ወዲያውኑ "በበጋ እንጨት እንገዛበታለን" እያሉ የወርቅ ሳንቲሞችን ወሰዱ። ሦስተኛው ሠራተኛ ከፊቱ ያለውን መጽሐፍ አንሥቶ "ዐይነ ሥውር እናት አለችኝ ምሽት ምሽት ላይ ከዚህ መጽሐፍ የኾነ ነገር አነብላታለሁ" እያለ ወሰደ። ሃይማኖተኛው ክርስቲያንም ፈገግ አለበትና እባክህ የመጽሐፉን የመጀመሪያውን ገጽ ከፍተህ ምን እንደ ተጻፈበት አንበብ አለው። ወዲያውኑ ሠራተኛው መጽሐፉን ሲከፍት፥ ባየው ነገር ተደነቀ ሦስት የወርቅ ሳንቲም በመጀመሪያው ገጽ ላይ ተጣብቆ ነበርና። ከዚያን እውነተኛው ክርስቲያን ሦስቱን ሠራተኞች እንዲህ አላቸው "ስሙ፤ ምድራዊ ቁሶች መልካሞች ናቸው። ነገር ግን ዘለዓለማዊ ቁሶች የበለጠ መልካሞች ናቸው። ዘለዓለማዊ ነገር የሚፈልግ ሁሉ ምድራዊውን ነገርንም እንደማያጣ ዕወቁ። ክርስቶስ እንዲህ ብሏልና " እናንተስ አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፤ ሌላው ሁሉ ይጨመርላችኋል።" ማቴ ፮፡፴፫። (Orthodox parables and short history) ይህ ታሪክ አሁን ያለነውን አብዛኛዎቻችንን የሚመለከት ይመስለኛል። ብዙዎቻችን የምንሠራው ምድራዊ ነገር ለማግኘት ብቻ ብለን ነው። ሌላው ቀርቶ ድርጊታችን ዓለማዊ ኾኖ እንኳን የሚያጸድቅ ሽልማት ሲቀርብልን አንፈልግም እንላለን። ምርጫችን በተራ ኃላፊ ነገር ላይ ብቻ የተመሠረተ ነውና። እሳትና ውኃ ቀርቦልን ምረጡ ስንባል ልቡናችን የሚከጅለው እሳት የተባለውን ዓለማዊ ሥራ ለመሥራት ብቻ ነው። ጾምና ምግብ በምርጫ ቀርቦልን ጾምን ትተን ምግብን ብቻ በመምረጥ ሆዳም የኾን ጥቂት አይደለንም። መጽሐፍ ቅዱስና ተራ የዚህ ዓለም ልብ ወለድ ቀርቦልን ወዲያው የምንመርጠው ልብወለዱን ነው። ይህ እንግዲህ በምን ያህል ርቀት የክርስትናን ጉዳይ ሳንረዳ እንደቀረንና ሕይወታችንም እውነተኛ የሕይወትን ትርጒም ትታ ፍሬ አልባ እንደ ኾነችብን አመልካች ነው። ከክርስትና መከራ እና ከዓለማዊ ደስና የቱ ይሻላችኋል ተብሎ ምርጫ ቢቀርብልን የሁላችንም ምርጫ ደስታን ማግኘት ነው። ምክንያቱም በመከራ ውስጥ የሚገኘውን የማይመረመር ደስታ አናውቀውምና። ሕይወትና ሞት ቀርቦልን የምንመርጠው ሞትን ነው። ይህም ማለት የሞትን ሥራ በጣም እንወደዋለን የሕይወትን ሥራ ግን ፈጽሞ እንጠላለን። ፖለቲከኛው በፖለቲካው፣ ነጋዴው በንግዱ፣ ሠራተኛው በሥራው የሚመርጠው የቱን ነው? ፍትሐዊነት የጎደለውን የሞትን ሥራ አይደለምን? ከፍቅረ እግዚአብሔርና ከፍቅረ ዓለም በእኛ ዘንድ የቱ ይበልጣል? በዕለት ተዕለት የሕይወት መርሐችን ውስጥ ፍቅረ ዓለም እጅጉን ሠልጥኖብናል። ዓለማዊ ፊልሙ ውስጥ ያለው ፍትወት፣ በመጠጥ ውስጥ ያለው ስካር፣ በዘፈን ውስጥ ያለው ጭፈራ፣ መቀባባቱ፣ አለባበስን አጋንኖ የተለየ ለመምሰል መሞከሩ፣ ታምራላችሁ መባሉ በጣም የሚጣፍጥ ይመስለናል፤ ኾኖም ፍቅረ እግዚአብሔርን ምን ያህል ጣፋጭ እንደ ኾነ ለመረዳት ትንሽ እንኳን ጥረት አናደርግም። በእርግጥ ለመቅመስ ብንጥር ያ ሁሉ ነገር የማይጠቅም መኾኑን እንረዳ ነበር! ስለዚህ የቀረቡልንን ምርጫዎች በእርጋታ እንመርምር፡ የበለጠውን ትተን ወደሚያንሰው አንጓዝ። በጽድቅ ውስጥ እኛ ይበቃናል የምንለው ሳይኾን እግዚአብሔር ያስፈልጋችኋል የሚለውን ሦስት የወርቅ ሳንቲም ሳያስቀምጥልን መቼም አይቀርም። ሌላው ቀርቶ እኛ በምንመርጠው ዓለማዊነት ውስጥ ከምናገኘው አንድ ሳንቲም የሚበልጥ ወደ እግዚአብሔር ስንሄድ ለምድራዊ ኑሯችን ስንኳን ሦስት እጥፍ ይሰጠን ነበር። ክርስቶስ በመስቀል ላይ የከፈለልንን የፍቅር መሥዋዕትነት ከማስታወስ ይልቅ የዚህ ዓለም ኃላፊ ታሪኮችን ብቻ በማስታወስ አእምሯችንን ያደካከምን ስንቶች ነን? ከወንጌል ይልቅ የፊልም አክተር በሕልማችን የሚመጣብን፣ ከመዝሙር ይልቅ ዘፈን ከአፋችን የሚፈስ፣ ከመንፈሳዊ ጥበብ ይልቅ ዓለማዊ ድንቍርና የሚስማማን፣ ከትሕትና ይልቅ ትዕቢት የሚያንቀን ስንቶች ነን? እንግዲህ የወርቁን ወርቅ መጽሐፍ ቅዱስን ትተን በምድራዊ ወርቅ የተመሰሉትን ዓለማውያት መጻሕፍትን ብቻ በማንበብ የተጠመድን ክርስቲያኖች የቆምንበትን እንመርምር። ለዴማስ በምርጫ ቅዱስ ጳውሎስ እና ተሰሎንቄ ቀርበውለት ነበር፥ ዴማስ ግን የተወደደውን ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስን ትቶ ተሰሎንቄን መረጠ። ተሰሎንቄ ውጫዊ መልኳ የዴማስን ልብ ማረከው። እንግዲህ እኛም እንዲሁ ነው እያደረግን ያለነው። በሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የተመሰለች ወንጌልን ትተን ኀላፊ የኾነች የዚህ ዓለም ጣዕምን ወደናልና። ለጊዜው ምርጫችን ልክ ይመስለናል፥ ኾኖም የእግዚአብሔር ቃል የተጻፈበትን ቅዱስ መጽሐፍ ትተናል። የችግሮቻችን ኹሉ ምንጭ አመራረጣችን ላይ ነው ያለው። ምርጫችን ካልተስተካከለ ሕይወታችን ጨለማ ውስጥ ይኾናል። ወደ ትዳር ሕይወት የሚጓዙ አካላትም፡ ሊያገቡት ያሰቡትን አካል ከእምነታቸው አስበልጠው ይመርጣሉ። እምነቱ ርቱዕ ወይም ቀና ኦርቶዶክሳዊ አለመኾኑን እያወቁ፡ እምነቱን ትተው እርሱን ይመርጣሉ። ለዚህም የተሳሳተ ምርጫቸው የየራሳቸውን የመከላከያ ምክንያት ያዘጋጃሉ። ምርጫቸው ልክ እንዳልኾነ እንዲነገራቸው ፈጽሞ አይፈልጉም። ስለዚህ እነዚህ አካላት ስለ ሃይማኖታቸው በፍጹም ልልነት ውስጥ ኾነው ሳለ ጠንካሮች እንደ ኾኑ አድርገው ለማሳየት ይፈልጋሉ። ነገሮችን ኹሉ በራሳቸው ስሜትና ግለ ምልከታ እንዲታይ ይፈልጋሉ እንጂ እንደ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን እንዲታይ አይፈልጉም። ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ወደ እነርሱ እንዲወርድ ይፈልጋሉ እንጂ እነርሱ ወደ ሥርዓቱ መሄድ አይፈልጉም። ይህ በእጅጉ ያስገርማል። ኦርቶዶክሳዊት ሃይማኖታችን ወርቅ ያለበትን መጽሐፍ ቅዱስን ትምስላለች። ከላዩ ሲታይ ወርቆቹ አይታዩም፥ ስለዚህም ዓለማውያን ብዙም አይመርጡትም። ኾኖም ግን ውስጡ ለሥጋ ሕይወታችን የሚያስፈልጉ ወርቆችም አሉት። ስለዚህ ዕይታችንን እናጥራ፡ እውነተኛውን የክርስትና ሕይወት ምርጫ እንረዳ። ከእኛ ስሜትና መረዳት ይልቅ እግዚአብሔርን ከልብ ለመስማት እንዘጋጅ፤ የየዕለት የሕይወት ምርጫችንን በፈቃደ እግዚአብሔር መሠረት ላይ እናቁመው። እግዚአብሔር የሚወደውን ፈቃድ ትተን ለምድራዊ ሕይወት ምቾት ብቻ ስንል የተቅበዘበዝንበት ጊዜ ይበቃል። የእውነት የእግዚአብሔርን ፈቃድ ማድረግ እንጀምር። እግዚአብሔር በቸርነቱ ዐይነ ልቡናችንን ወደ እውነተኛ ምርጫ ይምራልን። እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ምልጃ ይርዳን አሜን! #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

«ንስጥሮስ ሆይ፤ እወድሃለሁ፤ እጠላሃለሁ!» ክርስቶሳዊ ፍቅር ማለት ሰውን ከሰውነቱ እስከ ኃጢአቱ መውደድ ነው። እንደ ጌታ ካሰብክ ሰውን ኃጥእ ጻድቅ ሳትል በሰውነቱ ብቻ ትወደዋለህ። ይህ ዓይነት መውደድ ቢከብድም ክርስቶሳዊ፣ ቅዱሳዊ መውደድ ነው። ጌታችን ኃጢአተኞችን ሳይሆን ኃጢአትን ነው የሚጠላው። ዘማዊ ቢሆን/ብትሆን/ ዝሙትን/ዋን/ ጥላ እንጂ ዘማዊ ነው/ናት/ ብለህ ሰውዮውን/እሷን/ አትጥላ። ሌባ ቢሆን ሌብነትን ጥላ እንጂ ሌባ ነው ብለህ ሰውዮውን አትጥላ። ሰካራም ቢሆን መጠጥን ጥላ እንጂ ጠጪውን አትጥላ። ውሸታም ቢሆን ውሸትን ጥላ እንጂ ዋሸ ብለህ ሰውዬውን አትጥላ። ንፉግ፣ ተሳዳቢ፣ ነገረኛ፣ ምቀኛ፣ ጠንቋይ፣ አስጠንቋ፣ ዘረኛ፣ መተተኛ፣ እምነተ ቢስ፣ አጭበርባሪ፣ ከዳተኛ፣ ወዘተ ቢሆን መጥፎ ተግባሩን ጥላ እንጂ ሰውዬውን አትጥላ። ቅዱስ ቄርሎስ የክርስቶስን መለኮትነት፣ የእመቤታችንን የአምላክ እናትነት የካደውን ንስጥሮስን "ንስጥሮስ ሆይ አንተን እወድሃለሁ ኑፋቄህን ግን እጠላለሁ" በማለት ሰውን ተግባሩን እንጂ ሰውነቱን መጥላት እንደሌለብን ተናግሯል። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

«የመጀመሪያ ልጃቼውን ለመንፈሱ የገበሩ ቤተሰቦች ይናገራሉ!» አንድ እውነታ ልንገራቹ ይሄ የራሴ ታሪክ ሰለሆነ በአካባቢያችን የነበሩ አንድ ሰው ለእኔ ቤተሰብ አበልጅ የሆኑ ቤተሰብ ነበሩ። ሰውየው ሞራ ገላጭ ናቸው ኮከብ ቆጣሪ እናም በጣም ብዙ ሰው እቤታቸው እየመጣ መፀሀፍ ያሰገልጣሎ፤ ለገበያ ለትምህርት፥ ለሀብት ያሰራሎ ሰውየው ሁሎም ልጆቻቸው ሀብታሞች ናቸው። ለግዜው ቦታውን መጥቀሰ ባያሰፈልግም የታወቀ ሁቴል ጠጅ ቤት ድራፈት ቤት ወፈጮ ቤት የእህል በረንዳ አረቄ ማከፋፈያ ሱቆች አሏቸው፤ ይሄ ሁሎ ሀብት በሰውየው ነው ይሄ ሀብት ሲመጣ ግን ያው በግብር ነው ሰውየው የተዋረሱት እሱም የመጀመርያ ሴት ልጃቸውን ለመንፈሱ ነው፤ አንድ ልጅ ከወለደች በኋላ ግብር ሰጧት እጅ እና እግሯ ታሰሮ ለመንፈሱ ግብር ሆነች ያም ሀብት ቀጠለ በልጆቹ ሁቴል የተመገበ ሰው የቤቱን ምግብ ይጠላዋል። የወር ደሞዙን እዛ ነው የሚያራግፈው መጠጥ ቤቱ ተጠቃሚዎች በመቀመጫ ተስተናጋጅ ይደባደብበታል ብቻ ታሪኩ ሰፌ ነው ታዋቂ ሰዎች ገብተው በሁቴሎ በመጠጥ ቤት ከደንበኝነት አልፈው ቤተኛ ሆነው ስንቶች ትዳራቸው ቤታቸው ፈርሶ ከንቱ ሆነው ቀርተዋል። ይሄ ትክክለኛ ታሪክ ነው የምነግራችሁ ቦታው እዚሁ መሀል አዲሰ አበባ ነው። በዚህ መልኩ ሰውየው ልጆቻቸውን ሀብታም አድርገው ሲኖሩ በመሀል ሰውየው ታመው ሞቱ፤ ከዛን አንዱ ዘመድ ተረክቦ በአዲሰ አበባ መሰራት ጀመረ በመሀል ግን ልጆቹ አግብተው የወለዷቸው ልጆች የሁሉም የመጀመርያ የመጀመርያ ልጆች በሸተኛ ናቸው። ሰውየውን ከገደለ በኋላ ልጆቹን ጀመረ አንዷን ሴት በራሷ የጭነት መኪና ከባሏ ጋር ገልብጦ እሱ ዳነ እሷ ሞተች ግብር የተሰጠችው የመጀመርያ ልጅ አብዳ ከቤት ብር ብላ ወታ ወንዝ ገብታ ሞተች የሷ ልጅ በአክሰቷ ቡና ቤት ከተለያዮ ወንዶች ጋር ነው የምታድረው ይሄ ከሆነ በኋላ ጠንቋዮ ከሁለት ሴት ነው ልጆቻቸውን የወለዷቸው የመጀመርያዋ ሰባት ልጅ ከሁለተኛዋ፤ ሶስት ወልደው የመጀመርያዋ ስትሞት ነው ሁለተኛዋን ያገቡት እና ሶስት የወለዱት። የመጀመርያዋ ሴት ልጆች ናቸው ባለሀብቶቹ የሁለተኛዋ ግን ያው ተማሪዎች ነበሩ ሰውየውን ገደለ አንዷን ሴት በራሷ መኪና ገደለ አንዷን አሳብዶ ገደል ከቶ ገደለ ልጇን በዘመኑ በሸታ አሰያዘ ፈጣሪ በቃ ሲል በአንዷ ልጅ ቤተሰቡን ጠራ የመጨረሻዋ ልጅ ከሰፈር ልጆች ጋር ወደ እሰጢፋኖሰ ሰትመላለሰ የመምህር ግርማን ቪሲዲ እየገዛች እቤት ሰትወሰድ በቤተሰቡ ውሰጥ ታሪክ ተለወጠ። እናትየዋ ቀን አልቆጠሩም ንሰሀ ሲገቡ እነዛ ባለሀብት እርግፍ አረገው የተቀበረውን የሰሯትን አውጥተው ለመምህር አሰረክበው ንሰሀ ገብተው ተጠምቀው መንፈሱ ተሸኝቶ ቤተሰቡ ተባርኮ ዛሬ የመምህር ተማሪዎች ናቸው። ቤተሰቡን የለወጠችው ልጅ በቤተክርሰትያን አግብታ ሶስት ወልዳ በውጭ ትኖራለች እናት ቆርበው አሁን ሊሞለክሱ ነው ልጆቹ በሙሎ በቤተክርሰትያን ውሰጥ ለሚሰሩ የበረከት ሰራ አሰባሳቢ ተቆጣጣሪ ተባባሪዎች ናቸው ታሪኩ ሰፊ ነው ቤተሰቦቼ ባጭሩ ነው ያሰቀመጥኩላቹ ይሄ የእራሴ የአበልጆቻችን ታሪክ ነው እኝህ ሞራ ገላጭ አባት እኛም ቤት ገብተዋል በዚህ ክፉ ሰራቸው ብቻ ተመሰገን ሁላችንንም ላደነ አምላክ ይሄ ሁሎ የዘመኑ ሐዋርያ በሆኑት በመምህር ትምህርት ነው እሳቸውን የሚቃወም የደብተራ የጠንቋይ የዛር ልጆች ናቸው በእዚህም ቤተሰብ በእኔም ቤተሰብ ውሰጥ የነበረ የመምህር ግርማ ጥላቻ ከባድ ነበር ግን ቢፃፍ አያልቅም ሰለዚህ አትፈረዱባቸው ይማራቸው ፈጣሪ። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

"በጠላት ዘመን ማንቀላፋት ለመታረድ ነው" ብፁዕ አቡነ ሰላማ ዘባሌ (1931ዓ.ም -1996ዓ.ም)
"በጠላት ዘመን ማንቀላፋት ለመታረድ ነው" ብፁዕ አቡነ ሰላማ ዘባሌ (1931ዓ.ም -1996ዓ.ም)

«በግፍ የሚገደሉት ሰማዕታት አይደሉም?» በግፍ ለሚገደሉት አባቶች፣ ካህናት፣ ምዕመናን እና ወጣቶች ለምን እውቅና ከለከልናቸው? በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም ሼር በማድረግ ለወዳጆ አዳርሱ! ተወዳጆች ሆይ ጾመ ነነዌ ሦስት ቀን ናት። ነገር ግን የእግዚአብሔርን ቁጣና መአት የምታርቅ፣ ሀገርን ሕዝብን ከእግዚአብሔር የምታስታርቅ ናት። ዮናስ የእግዚአብሔርን ድምጽ አልሰማም፣ የተባልኩትን አልፈጽምም በማለቱ በባህር ተጣለ አሳ ነባሪ ወጣው። እኛም የእግዚአብሔርን ድምጽ አንሰማም፣ ትእዛዙን አንፈጽምም ስንል፣ በኃጢአት እንወድቃለን ዓለም ትውጠናለች። ጾመ ነነዌ የነነዌ ሕዝብ በሀገራቸውና በራሳቸው ላይ የመጣውን የእግዚአብሔርን ቁጣ፣ መዓት እና መቅሰፍት ያራቁበት ነው። እኛም በሀገራችን፣ በሃይማኖታችን፣ በቤተ ክርስቲያናችን በገዳሞቻችን ላይ የመጣውን ፈተና እግዚአብሔር እንዲያርቅልን ሦስቱን ቀን በተለይ የሰባቱን የጸሎት ጊዜያት በአግባቡ በመጠቀም ልንጸልይ፣ ልምጾም እና ልንሰግድ ይገባናል። ከዚህ በፊት በደብረ ኤልያስ የሆነውን ሳንረሳ ሰሞኑን በዝቋላ ገዳም አባቶች ላይ የሆነው ነገር በእውነት የሥጋን ሳይሆን የነፍስን ልብ ይሰብራል። ምክንያቱም ዓለምን ንቀው ለዓለም የማጸልዩትን፣ ከዓለም ተለይተው ዓለሙን ሰላም አድርግልን የሚሉትን አባቶች መግደል ሀገርን መግደል ነው። ይብላኝ ለእኛ ንስሐ ሳንገባ፣ ቅዱስ ቁርባን ሳንቀበል በቁማችን ለሞትነው። አባቶቻችንስ ሁለት ክብር ያገኛሉ። አንደኛው ቀድመው በምንኩስና ሕይወት ስለሞቱ የምንኩስና ክብራቸውን ያገኛሉ። ሁለተኛ እንደ ቀድሞ አባቶቻችን በግፍ በመገደላቸው ሰማዕታት ናቸው፣ የሰማዕትነትን ክብር ያገኛሉ። ስለዚህ ሰሞኑን የተገደሉት የዝቋላ ገዳም አባቶቻችን ቅዱሳንም ሰማዕታትም ናቸው። በእውነት በረከታቸው ይደርብን! #_ትዝብት :- በጣም የሚገርመኝ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በቤተ ክርስቲያን ጉዳይ፣ በሃይማኖት ጉዳይ እንዲሁም ኦርቶዶክስ ብቻ በመሆናቸው ብዙ አባቶች፣ ካህናት፣ ምዕመናን እና ወጣቶች እየተገደሉ ነው። ተገደሉ ተብሎ ለአንድ ሰሞን የማህበራዊ ሚዲያ መነጋገሪያ ከማድረግ በዘለለ የተደረገ ነገር የለም። በሃይማኖታቸው እና ስለ ሃይማኖታቸው የሞቱት በሙሉ ሰማዕታት ናቸው። ለምንድነው ቤተ ክርስቲያናችን ይልቁንም ቅዱስ ሲኖዶስ የሞቱትን አባቶች፣ ካህናትን፣ ምዕመናንን እና ወጣቶችን ሰማዕታት ብለው እንዲታወቁ የማያደርጉት? በግፍ ለሚገደሉት ለምን እውቅና ነፈግናቸው? በዚህጉዳይ ግብጾች ከእኛ በጣም የተሻሉ ናቸው። ግብጾች በግፍ የተገደሉትን የቤተ ክርስቲያን ልጆች በሲኖዶሳቸው ሰማዕታት ብለው የሞቱበትም ቀን በየዓመቱ እንዲታሰብ ያደርጋሉ። ለሞቱት ሰማዕታት እውቅና ይሰጣሉ። ታሪካቸውን ጽፈው አሳትመው ለምዕመናኑ ያሳውቃሉ። ለሃይማኖት እስከ ሞት ዋጋ እንደሚከፈል የሞቱትን አብነት አድርገው ያስተምራሉ። በእኛ ዘንድ እንዲ አልተለመደም። ወዳጆቼ በዘመነ ሰማዕታት የሚደረገውና የሚሆነው ነው አሁን በእኛ ጊዜ እየተደረገ እና እየሆነ ያለው። ስለዚህ አባቶቻችን ሆይ በግፍ የሚገደሉት እና የሚሞቱት የቤተ ክርስቲያኗ ልጆች ለእኛም ለሌሎቹም ጽናት ብርታት እንዲሆኑ ስማቸውን መዝግባችሁ፣ የሞቱበትን ቀን ወስናችሁ "ይኸው የዘመናችን ሰማዕታቶቻችሁ" በሉን። ነገ የሚመጣው ቀለል ያለ ሳይሆን ቆለል ያለ ነው። ከትላንቱ ያነሰ ሳይሆን የባሰ ነው። ስለዚህ ሰማዕታቶቻችን እንድናከብራቸው እናንተ በቅዱስ ሲኖዶስ አክብራችሁ ስጡን። እኛ እንዳንረሳቸው እናንተ አስታውሷቸው። እኛ እንድናነባቸው እንድንማርባቸው ታሪካቸውን ጻፉልን። የአባቶቻቼንናየምዕመናኑን ሞት የአንድ ሳምንት ሐዘን አናድርገው። እንደውም ቢቻል የሚገደሉትን አባቶች እና ምዕመናንን የራሳችንን ስንክሳር አዘጋጅተን ታሪካቸውን ሰንደን ለትውልድ ማስቀመጥ አለብን። ትላንት በዘመነ ሰማዕታት የሞቱት አባቶች እና ምዕመናን አሁን በግፍ ከሚገደሉት በምን ይለያሉ? የቀድሞ አባቶች የሰማዕታቱን አሟሟት እና ሞት ጽፈው ስላስቀመጡልን እኮ ነው በስንክሳሩ በገድላቱ የምናነባቸው። የዘመናችን ሰማዕታቱም የሚነበቡ ስለሆኑ የሰማዕታት አምላክ እንዳይወቅሰን ተገደሉ ሞቱ ከማለት እውቅና እንስጣቸው፣ እናክብራቸው፣ ጽፈን ለታሪክ እናስቀምጣቸው። "ስላንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን፣ እንደሚታረዱ በጎች ተቆጠርን" ሮሜ 8፥36 #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

"ጌታ [እግዚአብሔር] በምድራዊ ኑሯችን ውስጥ ብዙ የሚያበሳጩ ነገሮች፣ ብዙ ኀዘናት እና መልካም ያልሆኑ ገጠመኞች በእኛ ላይ እንዲደርሱ ይፈቅዳል። ይኸውም እኛን የምትጎዳ ዓለም ላይ እምነታችንን እን
"ጌታ [እግዚአብሔር] በምድራዊ ኑሯችን ውስጥ ብዙ የሚያበሳጩ ነገሮች፣ ብዙ ኀዘናት እና መልካም ያልሆኑ ገጠመኞች በእኛ ላይ እንዲደርሱ ይፈቅዳል። ይኸውም እኛን የምትጎዳ ዓለም ላይ እምነታችንን እንዳናደርግ ነው። የተድላ፣ የሰላም እና የጽናት ሁሉ መገኛ እርሱ ብቻ መሆኑን [በተግባር እንድንማር] እንድንረዳ ነው።" (አረጋዊ ታዴዎስ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

"ምስክርነት" ዲያቢሎስ ከዚህ በላይ ገና ይሞክራል አይሳካለትም እንጂ እርሱ በእነ ዘመድ ኩን አና በመሰሎቻቸው ላይ አድሮ የዘረፋቸውን በተለያየ መልኩ በጥንቆላዉ እና በመተቱ ላይ የክርስቲያንን ካባ ለብሰዉ የተሰማሩትን ቤተ ክርስቲያኗን አይቶ የድንግል ማርያም ልጅ ደናግሎቹ ጳጳሳቱ መነኮሳቱ እያሉ ከአለም መምህር መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙን በአዚም ከወደቅንበት ንቁ ብለዉ እንዲቀሰቅሱን እና በነፍሳችን እረፍትን ለስጋችን ፈዉስን እንድናገኝ ከንስሐ እና ከስጋ ወደሙ በመቀበል ወደእርሱ እንድንቀርብ እና ቢልክልንም ዲያብሎስ ግብሩ ስለቀረ ቢጯጯህም ሁሉም በቅናት ጥላቻ እንደተወጠረ ቆዳ ሊያደርጓቸዉ ሲሞክሩ እኛም ስለ አባታችን ስንጨነቅ እና ስናለቅስ አይቶ አበሯቸዉ እንዲያገለግለን የራሳቸዉን ልጅ አባታችንን ቀሲስ ኃይለ መለኮት ግርማን ቀባልን ዲያብሎስ መንጫጫቱን ቢቀጥልም የራሳቸውን ልጅ ከመቀባቱ በፊት እጅግ በሚልየን የሚቆጠሩ ካህናት መምሕራን  እና በተሐያየ የፀጋ ስጦታ ያላቸዉ ተማሪዎችን ጭምር አበርክተዉልናል ለምሳሌ ቀሲስ ሔኖክ : መምህር  :ተስፋዬ: ሊቀ ትጉኃን በአንተ ይሁን : በአለም ዙሪያ ያለን ተማሪዎቻቸዉ በሙሉ ከእግዚአብሔር የተላኩልን የዘመናችን ቅዲስ አባት እንደሆኑ እናዉቀለን ለዚህም የድንግል ማረያም ልጅ ክብሩ ይስፋ ፀጋው አይጓደልብን :: እኔ መምሕርን ሳላዉቃቸዉ ለ 16, አመታት በማህፀን ካንሰር ስሰቃይ አምላኬ ዩ ቲዪብ ላይ በድንገት አምጥቶልኝ ትምሕርታቸውን በመከታተል እና አርሳቸዉ በ አስተማሩት መሠረት የዛሬ 11, አመት የምሕር መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ አምላክ እውነት ከሆንክ እኔንም ባለሁበት ፈዉሰኝ ብዬ ለ 16, ፍልሰታ አርሳቸዉ በሬዲዮ አቢሲኒያ ላይ ተፈዉሻለሁ :: ይህንን ለመመስከር ግን ሁሉንም ዘጋግቶብኝ ከተፈወስኩ ከአምስት አመት በኻላ ኮለራዶ አሜርካ የዛሬ አምስት አመት ለመመስከር እና በመስቀላቸውም ለመባረክ በቅቻለሁ ::አብ የተከለዉ አይነቀልም ከዛም በኻላ ለመቁጠር የሚያዳግቱ ብዙ ተአምራቶች ተደርገዉልኛል እየተደረጉልኝም ስለሆነ ከእርሳቸው የተማርኩት ቢኖር ለእነዚህ ሰዎች ከመፀለይ በተረፈ ልቦናችሁን መልሶ እናንተንም ለንስሐ እና ለሥጋ ወደሙ እንዲያበቋችሁ እና ጠላቶቻቸውን እንዲያስገዛላቸዉ ነዉ ተጨማሪ መረጃ (ምስክርነት) ለሚፈልግ በዚህ ስልክ ቁጥር መደወል (ቴክስት) ማድረግ ይቻላል 1 (904)418-2703 ወንድማችን ኃይለ ገብርኤል እጅግ በጣም እናመሠግንሐለን እናከብርሃለን : አይዞህ አትደናድ በስድብ አያስቱህ:: አቧራው ዲያብሎስ አሸንፎ እንደማያውቅ ሁላችንም እናዉቃለን:: እረጅም እድሜ አና ጤና ለቅዱሳን አባቶቻችን ያድልልን ::አሜን አሜን አሜን🙏🙏🙏

ይድረስ ለማህበረ ሟርተኞች፣ ለዘመዱኩንና ወዳጆቹ በሙሉ የክርስትና ጋግርቶች መምህር ግርማ ወንድሙ 2024 #ethiopia #orthodox 🙏🙏🙄 https://youtu.be/zcJJ8NZibG8

ለወንድማችን MELOS አና ለዘማሪት ሶፊያ ሽባባው ይድረስ እኛ ኦርቶዶክሳዊያን ለቅዱሳን ለምን እንሰግዳለን? Sofia Shibabaw Melos 😭🙏🙄 https://youtu.be/RggWsxV5nAg