fa
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

رفتن به کانال در Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

نمایش بیشتر
2 280
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+77 روز
+3930 روز
آرشیو پست ها
◈ በመከራ ውስጥ ካለችሁ የዩናስን ዓሣ ነባሪ አስታውሱ፤ ከፍራቻ ትገላገላገላላችሁ መከራው እግዚአብሔር ጸጋውን ሊያበዛላችሁ ስለፈለገ ያዘጋጀው ዓሣ ነባሪ እንደሆነ የምታውቁበት ጊዜ ይመጣል የዚህ ዓለ
◈ በመከራ ውስጥ ካለችሁ የዩናስን ዓሣ ነባሪ አስታውሱ፤ ከፍራቻ ትገላገላገላላችሁ መከራው እግዚአብሔር ጸጋውን ሊያበዛላችሁ ስለፈለገ ያዘጋጀው ዓሣ ነባሪ እንደሆነ የምታውቁበት ጊዜ ይመጣል የዚህ ዓለም የባሕር ዓሣዎች ብዙ ስለሆኑ ስትዋጥ እንዳይከፋህ መጠንቀቅ ይኖርብሃል፤ የመጀመሪያው ባህታዊ ጻድቁ አባ ጳውሊ የተናገረውን መዘንጋት የለብህም "ከመከራ መራቅ የሚወድ ከእግዚአብሔር ይርቃል" ብሏል። በእውነት መከራ የጸሎት ትምህርት ቤት ነው፤ በመከራዬ ሳለሁ ወደ አምላኬ ጮኽሁ እርሱም ሰማኝ፤ በሲኦልም ሆድ ውስጥ ሆኜ ጮኽሁ ቃሌንም አደመጠ። (ዮናስ 2፥3) (አቡነ ሽኖዳ 3ኛ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239

በአጋንንት ዙሪያ የምታዩ ህልሞችና ፍችዎቻቸው ሰውና ህልም ሰው መንፈሳዊ ሕልምን እንዴት ያያል? ሳይንስና ሕልም | መምህር ግርማ ወንድሙ 🙏💥🚩😭 https://youtu.be/h7PC7rSp6o8?si=qySz4INCwV7gYyEg

እንዳትድን፣ እንዳትፈወስ ጥፍር ቀጥዬ አስመጣኋት || ከተወዛዋዦች ጀርባ ያለው የአጋንንት ሴራ || የወንድምን ኃጢአት መሸፈን || የዛር መንፈስና መተት 🚩💥😱 https://youtu.be/BCLml9gVbCs

«ፈተናን በጥበብ (ከቅዱሳን ሕይወት)» ◈ ቅድስት አፎምያ ትዳር የጽድቅ መንገድ እንደሆነ በኑሮ ያሳየች፣ በቅዱስ መጽሐፍ እንደተጻፈ ጥበበኛ ሴት ከመሆኗ የተነሳ በምጽዋት ለእግዚአብሔር ታበድር የነበረች፣ በጸናች እምነቷ፣ እግዚአብሔርን በመፍራቷ ምክንያት የእግዚአብሔር መልአክ በዙሪያዋ ሰፍሮ ያዳናት፣ መንፈስን ሁሉ በእምነት መነጽር የመመርመርን ነገር ሁላችን የተማርንባት ከህይወት መዛግብት የሚያበሩ ገጾች መሃል አንዷ ናት። ◈ ለበልዓም ያይደለ ለአህያው የተገለጠ የእግዚአብሔር መልአክ ታዲያ እንደምን ላሉ ሰዎች ፈጣን ረድኤቱ ይገለጥ ይሆን? ለሚለው በልባችን ለሚመላለስ ጥያቄ መልስ የሆነች ቅድስት አፎሚያ ምንም እንኳ የአምላኩ ወዳጅ የሆነ በዘመኑ ሁሉ በፍጹም ልቡ በመፍራት እግዚአብሔርን ሲያገለግል የኖረ፥ ከኃላፊ ሀብትና ንብረት ይልቅ በዝክረ ቅዱሳን ብል የማይበላውን የነፍስን ረድኤት ያወረሳት ባለቤቷ አስተራኒቆስ ያረፈ ቢሆንም የሚያጽናና የሚያረጋጋትን መልአክ እርዳታ በኑሮአቸው አትርፎላት ነበርና፣ ለሃይማኖት የቀናች በምግባርም እጅጉን የጸናች ነበረች። ◈ አስቀድሞ በቅድስት ሥላሴ አምሳል የተፈጠረ የሰውን ልጅ በገነት፥ በሥጋ ብእሲ የተገለጠ ጌታችንን ደግሞ ገዳመ ቆሮንቶስ ቀርቦ የፈተነ የመልካም ነገሮች ጠላት ሰይጣን ቅድስት አፎሚያንም በቅንነቷና ለጥሩ ምግባሯ መሰናክል ሊሆን በምትወደውና ዘወትር የምትዘክረው ብርሃናዊ መልአክ አምሳል ሳይቀር ሊያስታት ቢሞክርም እርሷ ግን እምነቷ ከእውቀት የተባበረ ነበርና በፍጹም ማመን ድል ነስታዋለች፣ በዚያም የተበሳጨ ዲያቢሎስ ዳግመኛ በጨለማ ገጹ ተገልጦ ሊያጠፋት ሲሞክር እለት እለት በስእሉ ፊት ትማጸነው የነበረ ቅዱስ ሚካኤል በፈጣን ረድኤቱ ደርሶ ታድጓታል። ◈ አፎሚያን ልጅ ባለመውለዷ ተጠቅሞ የፈተናት ሰይጣን ዛሬም የጎደለንን ነገር እያጎላ እርሱ ወደሚፈልገው አላማ ሊመራን ይወዳል በህይወታችን የጎደለ እና በኑሮአችንን የጠፋብንን ተጠቅሞ ለዘለዓለም ከህይወት መንገድ የሚያጠፋ የጥፋት መልእክተኛ ነውና! በምትወደውና በምታከብረው የዘወትር ወዳጇ በሆነ ብርሃናዊ መልአክ ተመስሎ እንደቀረባት እኛንም በምንወዳቸው፣ በምናከብራቸው ሁሉ ሊፈትነን ይቀርባል፤ ብዙዎቻችን ቤተክርስቲያን ውስጥ በመኖርና በምንወደው መልካምነት፥ ብሎም በአገልግሎት መፈተናችን ቢያስገርመንም ጠላታችን ግን ለክፉ አይደክምምና በጠነከርንበት መጠን ፈተናውም እንዲበረታብን እንድንረዳ ይህ ለአብነት ተጽፎልናል። ◈ ፈተና መሆኑን አውቀን ስንተጋም እንደ ኢዮብ በመከራ ሥጋ ደግሞ ሊያለፋን በብዙ ይጥራል፤ ነገር ግን ይህ ሁሉ ከንቱ እንደሆነ የተረዳ ማንነትን ከያዝን ስለደረሰብን መከራ ከማዘን ይልቅ ጥሪያችን እግዚአብሔር ቸርነቱን በእኛ ይገልጥ ዘንድ ተራዳኢ መልአክ እንዲሰድልን፥ እንደነ አናንያም ባያድነን እንኳን ፈቃዱ ለበጎ ነው ልንል ይገባናል፤ ከእኛ በላይ ለራሳችን የሚያስብልን ፈጣሪ ቸል ሊለን እንደማይወድ አንድያ ልጁን እስኪሰጠን የወደደን እርሱ በረቀቀ ፍቅሩ አስተምሮናልና። ◈ እምነትን ማወቅ መንፈስንም መመርመር ተገቢ ስለ መሆኑም፣ መስቀሉን ያልተሸከሙ ነገር ግን ፍጹማን የሚመስሉ ሁሉ ከእግዚአብሔር እንዳልሆኑና ይልቁንም ለተአምራት ለምንገዛ ክፉና አመንዝራ ልቦች ሰይጣንም ስንኳ የቱ ድረስ በዚህ እንዲጠቀም፣ የንዋያተ ቅዱሳትን ክብር በርሳቸውም ስለሚገኝ ሁሉ በረከት ቅድስት አፎሚያ በህይወቷ አብርታ ለደካሞች ሁላችን አሳይታናለች። የኃያሉ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ረድኤት ጠብቆት ከትውልዱ ሁሉ ጋር ይሁን። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

በቀን 1800 እየሰገደ አጋንንትን የቀጠቀጠ፣ ያስጨነቀ ወጣት || እተቸኩሉ እትፍጠኑ ተረጋጉ #ethiopia አባ ገብረ ኪዳን | መምህር ግርማ ወንድሙ 😱💥😭🚩 https://youtu.be/u4Rm4Mv-I8s

ቀሲስ ሄኖክን ለምን ይጠሉታል? || ከውቃቢ አምላኪ ቤተሰቦች የተወለዱ || ብቸኝነትና የአጋንንት ፈተና || ሰይጣን በገንዘብ ላይ ያለው ሴራ #eotc 😱🚩💥 https://youtu.be/FcA6v6IxNUg

◈ ትዝ ይላችኋል ለመጀመሪያ ጊዜ ውዳሴ ማርያም ገዝተን ነጠላችንን አጣፍተን ለጸሎት የቆምንባት ቀን፤ ቃሉን በቀስታ ዝግ ብለን፣ የምናነበውን እየሰማነው፣ የእለቱ ውዳሴ ማርያም አልቆብን ወደ አንቀጸ ብርሃን ገብተን እሱንም ሳንሰለች ጨርሰን፤ አቤት ቃሉ እንዴት እንደጣፈጠን! አዎ ያች ቀን ናት ጸሎታችን ፍሬ ያፈራችበት። ◈ ደግሞ ታስታውሳላችሁ ለመጀመሪያ ጊዜ ያስቀደስንባት ቀን፤ ገላችንን በዋዜማው ታጥበን፣ ያለን ሽቱ በመጠኑ ተቀብተን የሌለንም በወይራ በጡንጅት..በእጽዋቱ ታጥነን በነጋታው ጠዋት ወደቤቱ ገስግሰን፣ ገና ከአጥሩ በር ስንደርስ ተሳልመን በሩን(ካቡን) ስመን ከውጨኛው የቤተክርስቲያኑ በር ላይ ተደፍተን መቃኑን ስመን ስንገባ፣ በሥዕሉ ፊት መቆም ከብዶን ልባችን እየፈራ ጉልበታችን እየተብረከረከ፣ ያላንዳች ምርኩዝ (መቋሚያ) ቀጥ ብለን ቁመን ወዲያ ወዲህ ብናይ የምንቀሰፍ ስለመሰለን ጸጥ ብለን ሁለቱን ሰዓት ያስቀደስንባት ያች ቀን! አቤት ተመስጧችንኮ! ምን ጊዜ ገብተው ምን ጊዜ እትው በሰላም እንዳለ የማናስታውስባት ቅዳሴው አጭር የመሰለን ያች ቀን ናት ፍሬ ያፈራንባት። ◈ ትዝ ይላችሁ እንደሆነ ለመጀመሪያ ጊዜ ጉባኤ አለ ተብሎ የሄድንባት ቀን ወይም ሰንበት ት/ቤት የገባንባት ቀን ታስታውሳላችሁ፤ አዲስ ማስታወሻ ገዝተን ሰላሳ ደቂቃ ቀድመን ተገኝተን፣ ዘማሪዎች ዓውደ ምህረት ወጥተው ሲዘምሩ መላእክት መስለውን በሆዳችንም «ውይ መታደል» ብለን መንፈሳዊ ቅናት ወርፎን፣ ሰባኪው ሲሰብክ ልባችንን ዘልቆ ነፍሳችንን ሲያረሰርሳት ዳግም ኃጢአት የማንሰራ እስኪመስለን ድረስ የተማረክንበት ቀን! ያች ቀን ናት ፍሬ ያፈራንባት። ◈ ታስታውሳላችሁ ለመጀመሪያ ጊዜ መንፈሳዊ ጉዞ የተሳተፍንባት ቀን ያየነው የሰማነው ገነት እስኪመስለን ድረስ እጹብ እጹብ ብለን አድንቀን፤ ለመጀመሪያ ጊዜ የጽዋ መርሐግብር ወይም ማኅበር የተሳተፍንባትን ቀንስ አስታወሳችሁ መቼነው ወሩ የሚደርስ ብለን ማኅበሩ ሳያልቅ የቀጣይ ወሩ የናፈቀን ዕለት፣ ያች ቀን ናት ፍሬን ያፈራንባት። ◈ ምስጢር የተካፈላችሁስ የመጀመሪያዋን ቀን ታስታውሳላችሁ፤ ከአርባና ከሰማንያ ቀናችን በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሥጋወደሙን የወሰድንባት ቀን፤ በበዓል ቀን ሳር በጥሻለሁ የሚል ኃጢአት ሳይቀረን ተናዘን የተሰጠንን ቀኖና ጨርሰን፣ ገና የዋዜማ ዋዜማ ጀምረን ልብሶቻችንን አጣጥበን ሽቱ ረብርበን የብቻ አስቀምጠን፣  በዕለቱ ነጭ ልብሳችንን አውጥተን ለባብሰን ከሌለን ደግሞ እስከመዋስ ደርሰን እንደ መላእክት አሸብርቀን ወደ ደጁ ስንሄድ ያለው የልብ ሃሴትና ፍርሃት፣ የሚገባኝ አይደለም ብለን የፈራነው ፍርሃት፣ ከቁርባን በፊትም ሆነ በኋላ ህግ እንዳንጥስ የፈራነው ፍርሃት፣ ግብረ ሌሊት ከቆሙት ጋር በሌሊት ሂደን አብረን ቆመን፣ ቅዳሴው ሲጀመርም በፍርሃት ሆነን ጨርሰነው እየተንቀጠቀጥን ሥጋወደሙ የተቀበልንበት ቀን፣ ከዚያ ወጠን ምራቃችንን ላለመትፋት ላለመሳል፣ ሰንግሮን እንዳንወድቅ፣ ላቭ እንዳይወጣን የምናደርገው ጥረት፣ ትን እንዳይለን ሳናወራ የበላንባት ቀን፣ ክፉ ነገር እንዳናይ ብለን ማኅበራዊ ሚዲያ ከመግባት የተቆጠብንባት ቀን፣ ክፉ ነገር እንዳይወጣን ሃሰት እንዳንናገር ብዙ ሳናወራ እያሰብን ተጠንቅቀን ያወራንባት ቀን፣ ያስቀደስንበትን ልብስ ለብሰን እስከማደር የደረስንባት ቀን፣ ምግብ ስንበላ ላለመታጠብ ጥፍራችንን ሳናስነካ የበላንባት ቀን፤ አዎ ያች ቀን ናት ፍሬ ያፈራንባት፤ መድኃኔዓለም የቀደመ ፍቅራችንን ይመልስልን በእውነት። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

«በመንፈሳዊ ሕይወትህ ለውጥ እንዲኖርህ» ◈ የፀሎትን ህይወት ተለማመድ ተጠቀምበትም፣ ከመንፈሳዊ አባቶችና ሊቃውንት መምህራን ምክርና ትምህርት አትራቅ፣ ከቅዱሳት መፃህፍት ጋር ያለህን ግንኙነት አዘው
«በመንፈሳዊ ሕይወትህ ለውጥ እንዲኖርህ» ◈ የፀሎትን ህይወት ተለማመድ ተጠቀምበትም፣ ከመንፈሳዊ አባቶችና ሊቃውንት መምህራን ምክርና ትምህርት አትራቅ፣ ከቅዱሳት መፃህፍት ጋር ያለህን ግንኙነት አዘውትር፣ የምትውልባቸውን ቦታዎች የምታነባቸውን መጽሐፍት የምትመርጣቸውን ባልጀሮችህን ምረጥ፤ ለመንፈሳዊ ህይወትህና ለሌሎች ወንድሞችህና እህቶችህ የሚያሰናክሉ እንዳይሆኑ ተጠንቀቅ፣ የእግዚአብሄር ቤተመቅደስ መሆንህን ዘወትር አትዘንጋ፣ አላዋቂነትህን ተቀበል "እኔ ብቻ" አትበል ውዳሴ ከንቱንም አትፈልግ፣ ለሰራሃው ሃጢአት ሳትዘገይ ንስሃ ግባ፣ ልበ ደንዳናነትንና አመፀኛነትን ከአንተ አርቃቸው፣ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ለመኖርና የቃሉ ሙላት በውስጥህ ኖሮ ከክርስቶስ ጋር መኖርን ተለማመድ በቃሉም ፀንተህ ተገኝ፣ የቅዱሳንን ተጋድሎና ፍቅር በመመልከት እነርሱን ለመምሰል ትጋ፣ ከዚህ በፊት የነበርክበትን የኃጢአት ህይወት ኮንነው፣ ሰዎችን ባልንጀራህን አፍቅር ከጥላቻም ራቅ፣ ነገርን ሁሉ ለበጎነው ብለህ ተቀበል። ጌታ ሆይ ይህን እንድናደርግ ሁላችንንም እርዳን። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

◈ አቤቱ አንተን እናመሰግንሃለን 'የብርሃን አምላክ ሆይ የሕይወት መገኛ የዕውቀት መጀመሪያ ከደገኛው ክብር አስቀድሞ የዐረቦን ክብር የሰጠኸን ነፍስን የፈጠርክ መንፈስ ቅዱስን በመስጠት የሚጠቅም የጥ
◈ አቤቱ አንተን እናመሰግንሃለን 'የብርሃን አምላክ ሆይ የሕይወት መገኛ የዕውቀት መጀመሪያ ከደገኛው ክብር አስቀድሞ የዐረቦን ክብር የሰጠኸን ነፍስን የፈጠርክ መንፈስ ቅዱስን በመስጠት የሚጠቅም የጥበብ መገኛ የቅዱሳን መምህር ረዳት የምትሆን የዓለም መሠረት የንጹሓንን ጸሎት የሚቀበል ተቀዳሚ ተከታይ የሌለህ አንተን እናመሰግንሃለን። ◈ ቀዳሜ በኩር የምትሆን የአብ ቃል ለምንለምንህ ለኛ ለሁሉም የሚበቃ የአንተን ጸጋ የሰጠኸን ነውር ነቀፋ የሌለብህ ልዩ አባት ብል የማይበላው ነቀዝ የማያበላሸው ገንዘብ ያለህ በፍጹም ልባቸው ለሚለምኑህ የምትሰጥ ዓለም ሳይፈጠር የነበረ ብርሃን ባሕርይህን ያዩት ዘንድ መላእክትን ደስ የሚያሰኛቸው የማይለወጥ ጠባቂያችን ነህ። ◈ በእኛ የነበረውን ጨለማ በአባትህ ፈቃድ ያራቅክልን ከጨለማ ወደ ብርሃን ያመጣኸን ከሞት አድነህ ሕይወትን የሰጠኸን ለኃጢአት ከመገዛት ነጻ ያወጣኸን በመስቀልህ በሰማይ ወዳለው ወደ አባትህ ያቀረብከን፤ አቤቱ በወንጌል የሕይወትን መንገድ መራኸን በነቢያት አረጋጋኸን፥ አጸናኸን ያቀረብከን አምላክ አንተ ነህ። ◈ ዳግመኛ አቤቱ ዕውቀትህን ግለጽልን ላንተ ለፈጣሪያችን ምስጋናን እናቀርባለን፤ አርምሞ ጽርዓት በሌለበት ምስጋና እኛ ቤተሰቦችህ አገልጋዮችህ እናመሰግንሃለን፥ ሕዝቡም አንተን ያመሰግናሉ። (ጸሎተ ኪዳን ዘነግህ_ #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

«ማንም ኋለኛ ነኝ ብሎ ተስፋ አይቁረጥ!» ◈ ከመጀመሪያ ጀምሮ መልካም ነገርን መምረጥ መልካም ነው፤ በመልካምነት አለመቀጠል ግን ብዙ ወቀሳን ያመጣል፤ የብዙ ሰዎች ክፉ መኾን በዚሁ የሚመደብ ነው፤ ብዙዎች ሕይወታቸውን በመልካም ጀምረው በኋላ ግን በክፋት መርዝ ተጠምቀው ሲሰክሩ ተመልክቻለሁ፡፡ እናንተ ግን እንዲህ አትሁኑ ምንም እንኳን አሁን ወደ ክፋት ጥልቅ ወርዳችሁ ቢኾንም "ከዚሁ ተመልሰን መውጣት አይቻለንም፤ መለወጥም አይኾንልንም" በማለት ተስፋ የምትቆርጡ አትኹኑ፤ እናንተ ስትፈቅዱ እግዚአብሔርም ሲረዳችሁ ከክፋት ዐዘቅት መውጣት በእጅጉ ቀላል ነውና፡፡ ◈ ከኹሉም በላይ አመንዝራ ተብላ በከተማው ትታወቅ የነበረችውን ሴት በመልካምነቷ እንዴት እንደምትወደስ አልሰማችሁምን? እየነገርኳችሁ ያለሁት በወንጌለ ዮሐንስ ስለተጠቀሰችው ሴት አይደለም፤ በእኛ ዘመን ስላለችውና ፍኒሳ ከተባለችው ክፉ ከተማ ስለተገኘችው ሴት እንጂ ይህቺ ሴት አስቀድማ በመካከላችን በአመንዝራነቷ ትታወቅ ነበር፤ በክብር ቦታ ሁሉ የመጀመሪያውን ስፍራ የምትይዝ ሴት ነበረች፤ ስሟ በሀገሩ ሁሉ የገነነ ነበር በእኛ ዘንድ ብቻ ሳይሆን በሲልስያና በቀጰዶቅያም የታወቀ ነበር፡፡ ይህቺ ሴት ብዙ ከተሞችን አፍርሳለች፤ የብዙ ወላጅ አልባ ሕፃናትን ንብረት በልታለች፤ ብዙዎች "መተተኛ ናት" ይሏታል ውበቷን ብቻ ሳይኾን መድኃኒትም ጭምር ትጠቀም ነበርና፡፡ ◈ ከዚሁ የተነሣ በአንዱ ቀን የንግሥቲቱን ልጅ እስከ ማማለል ደርሳለች፤ ጭካኔዋ ክፉ የክፉ ክፉ ነበር፤ ከዕለታት በአንዲቱ ቀን ግን ማመን እስኪያቅተኝ ድረስ ተለውጣ አየኋት፤ ራሷን በእግዚአብሔር የጸጋው ዙፋን ፊት ድፍት ብላ ስታለቅስ አየኋት አሁን የቀድሞ ክፉ ሥራዎቿ ኹሉ ርግፍ አድርጋ ትታለች በእርሷ ላይ ከነበሩት አጋንንት ጭፍራ ተፋትታ የክርስቶስ ሙሽሪት ኾናለች፡፡ በእውነት ከእርሷ የሚከፋ ሰው በዓይኔ አላየሁም አሁን ግን ራሷን ከእንደዚህ ዓይነቱ ክፉ ሥራ ከልክላለች፤ ከዚህ በፊት ስትለብሳቸው የነበሩት የምንዝር ጌጦች ስፍር ቁጥር የላቸውም አሁን ግን እነዚህን ኹሉ አወላልቃ ጥላ ለእግዚአብሔር በሚገባ የማቅ ልብስ ራሷን የክርስቶስ ደቀ መዝሙር አድርጋለች፡፡ ◈ ይህቺን ሴት ወደ ቀድሞ ሕይወቷ ለመመለስ የሀገሪቱ መኳንንት ከዙፋናቸው ወርደው ለምነዋት ነበር ወታደሮች ከነትጥቃቸው መጥተው አስፈራርተው ሊወስዷት ሞክረው ነበር፤ ነገር ግን ወደ ቀድሞ ሕይወቷ ይመልሷት ዘንድ አልተቻላቸውም፡፡ ይህቺ ሴት ከዚያ አስነዋሪ ሕይወቷ ተመልሳ ለቅዱስ ቁርባን በቅታለች፤ ለእግዚአብሔር ጸጋ የተገባች ኾና ተገኝታለች ኃጢአቷን ኹሉ በጸጋው አጥባለች ከተጠመቀች በኋላ ራሷን መግዛት ችላለች፤ ይህቺ ሴት የቀድሞ ሕይወቷን፣ ገላዋን ለብዙ ወዳጆቿ ያሳየችበትን ሕይወት "የእስር ቤት ሕይወት" ብላ ትጠራዋለች፤ በእውነት "ኋለኞች ፊተኞች ይኾናሉ፤ ፊተኞችም ኋለኞች ይኾናሉ" የሚለው የከበረ ቃለ ወንጌል በእርሷ ሲፈጸም አየነው፤ መለወጥ ከፈለግን እኛን ማሰናከል የሚቻለው ኃይል እንደሌለ ዐወቅን፤ ተረዳን፡፡ ◈ እንኪያስ እኛም ተስፋ በመቁረጥ፥ በኃጢአት ዐዘቅት ሰምጠን የምንቀር አንኹን፤ ከእኛ መካከል በጽድቅ በረኻነት የሚኖር ማንም አይገኝ ፊተኛ ነኝ የሚል ማንም አይገኝ፤ ብዙ አመንዝሮች እርሱን አልፈውት ሊሔዱ ይችላሉና፤ ማንም ኋለኛ ነኝ ብሎ ተስፋ አይቁረጥ፤ ከልቡ ከተጸጸተና ከተመለሰ ፊተኛ መኾን ይቻለዋልና፡፡ (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ከብሩካንና ጻድቃን የተወለዱ ክፉዎች || ማጅክ መሰል አጋንንታዊ ሴራ || ይድረስ ለቤት አከራዮች || ዘመኑን መዋጄት እንዴት ነው? #eotc #ebs 💥🔥🚩😱 https://youtu.be/wE12y3gulrE

3ቱ የዝሙት አሳብን ማቆሚያ መንገዶች ጠዋትና ማታ የመጸለይ ጥበብ ዘመናዊ የስልብና መንፈሶች || የቡዳ ዛር አጋንንት በትዳር #ethiopia 🚩💥🔥😭 https://youtu.be/T1vwDypmPRk

ከሰይጣንም ጋር ቢሆን መደራደርና መስማማት || ከማያውቁት መልአክ የሚያውቁት ሰይጣን ይሻላል #ethiopia 🔥 መምህር ግርማ ወንድሙ | ተስፋዬ አበራ 2024 https://youtu.be/miPk8V9iZ4U

የሌሊት ጸሎት ለምን ከባድ ይሆናል? በቅናት ውስጥ አጋንንት ሲያደፍጥ ስትራቡ ክርስቶስን አትርሱ! || የተባረከ ትዳር ማለት ምንድነው? #eotc 💥🔥 https://youtu.be/REfMbo0Q-qI?si=RM1uJI9qQDXPx-1w

◈ ጌታ ሆይ ለዉጠኝ፡ አምላኬ ሆይ ለዉጠኝ፡ አባቱን የማይመስል ልጅ ሆኛለሁና ለዉጠኝ፡ አድር ባይ ሆኜ ለሁሉም አለሁ እላለሁና ለዉጠኝ፡ ማንነቴ የሬሳ ሸክም ሆኖብኛል እና ለዉጠኝ ብቸኛ ምርጫዬ እስከማደርግህ ድረስ ለዉጠኝ፡ መምሸት መንጋቱ የተፈጥሮ ሂደት መስሎኛልና ለዉጠኝ፡ ጌታዬ ለዉጠኝ እያልን እንጸልይ። ዲንጋዩን ልብ አዉጥቼ የስጋ ልብ እሰጣችኋለሁ አይደል የሚለዉ...የስጋ ልብ ማለት በቀላሉ ለፍቅር የሚነካ፤ ለበጎነት የሚነካ፤ ለቸርነት የሚነካ፤ የስጋ ልብ እሰጣችኋለሁ ማለት ነዉ፤ መለወጥ ይችላል እግዚአብሔር ጸሎት ደካማዉ ብርቱ የሚሆንበት ዉስኑ በሁሉ የሚገኝበት መንፈሳዊ ጥበብ ነዉ። ◈ ብዙ ሰዉ በአድመኛነቱ፤ በዘረኛነቱ፤ በክፉቱ የሚገፍበት በዚች ምድር ላይ እረጂም ዕድሜ የሚኖር እየመሰለዉ ነዉ፤ እድሜአችሁ ታይቶ እንደሚጠፋ እንፋሎት ነዉ። መጽሐፍ ነገ ምን እንደምንሆን አናዉቅም ነገ እንጠራ የዛሬ ሳምንት እንጠራ አናዉቅም ነገ የእግዚአብሔር ምሥጢር ነዉ፤ ከእኛ የሚጠበቀዉ ዛሬ ተቀድሶ መኖር ነዉ ሁላችንም ሞታችንን ተሸክመን ነዉ የምንዞረዉ ከሞት የሚዘገይ እንጂ የሚቀር የለም፤ ሁላችንም በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት ነዉ የምንቆመዉ ያኔ ምንድነዉ የምንመልሰዉ? የቀረን ዘመን አይደለም ለጠብ ለፍቅርም የሚበቃ አይደለም፤ አይደለም ለኃጢአት ለጽድቅም የማይበቃ አጭር ጊዜ ነዉ፤ ይሄንን አዉቀን እንድንመለስ እንድንቀየር እግዚአብሔር ይርዳን። ◈ ዘመኑን ዋጁ የሚለዉ ቃል ብዙ ጊዜ ዘመኑን ምሰሉ ብለን ነዉ የምንተረጉመዉ ዘመኑን ዋጁ ማለት በዘመኑ ላይ ተጽዕኖ ፍጠሩ፤ በዘመኑ ላይ እናንተ ወደ ዘመኑ ፍለሱ ማለት አይደለም፤ ዘመኑ ወደ እናተ ይፍለስ ነዉ ለዚያ እኮ ነዉ የአምልኮ ቄንጣችን እስታይላችን የበዛዉ የምናመልከው አምላክ ዘመናዊ አምላክ አይደለም ዘለአለማዊ አምላክ ነዉ፤ ስለዚህ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ልንሆን ይገባል የፍቅር ጀማሪዎች፤ የይቅርታ ጀማሪዎች ልንሆን ይገባል፤ ተጽዕኖ ፈጣሪ ትዉልዱን መለወጥ አለብን እንኳን እኛ ዲንጋይ ተጽዕኖ ይፈጥራል፤ ለተቀመጠበት ስፍራ ይይዛል እኛ ቃሉን ይዘን ሕያው የሆነዉን ስሙን ይዘን ይሄ አልጫ ያለዉን በዘረኝነት የቆሸሸዉን ባድመኝነት የቆሸሸዉን እንዴት መለወጥ ያቅተናል። ዘመኑን እንድንዋጅ ቀኖቹ ክፉዎች ናቸውና ዘመኑን ዋጁ። (ኤፌ 5÷16) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

የቤት ሰራተኞቻችሁን በጥንቃቄ ያዙ! ስግደት የሚያመጣቸው በረከቶች ንቅሳትን ማን አስተማረን? | ንቅሳት አጋንንታዊ ነው ንቁ! #ethiopia 🚩💥🔥😭 https://youtu.be/9-RoDL6fgrs?si=qsmPjJiDsrYezEmg

በዝሙት አሳብና አጋንንት ለምትፈተኑ ይሄን አድርጉ! || እንድንሰክርበት፣ እንድንጨፍርበት የተሰጠን አካል የለም || የትዳር አማካሪ || መምህር ግርማ https://youtu.be/Aeo2Y0ixzYo

«ጾመ ሐዋርያት (የሰኔ ጾም) መቼ ይገባል? ለምንስ ይጾማል?» ◈ ጾመ ሐዋርያት ወይም ሰኔ ጾም ሰኔ 17 ይገባል (ይጀምራል) ሐምሌ 5 ቀን ይፈታል። ይህ ጾም ከቤተ ክርስቲያናችን የአዋጅ አጽዋማት ውስጥ አንዱ ሲሆን ቅዱሳን ሐዋርያት ጌታችንን ምሣሌ አድርገው የጾሙት ጾም ነው። የሰኔ ጾም ይህ ጾም የሐዋርያት ጾም በመባል ይታወቃል ስለ ምን የሐዋርያት ጾም ተባለ ቢሉ በበዓለ ጰራቅሊጦስ ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ የጾሙት ጾም ስለሆነ ነው። ◈ የሰኔ ጾም የሚጾምበት ጊዜያት (የሰኔ ጾም ቢያንስ 15 ቢበዛ 45 ቀናት ያህል ይጾማል፤ የሰኔ ጾምን እስከ 9 ሰአት እንድንጾም ቤተክርስቲያን አውጃለች። ጾሙ የሚገባበት ቀን በየዓመቱ የተለያየ ቢሆንም የጾሙ ማብቂያ ዕለት ግን ሐምሌ 5 ድረስ ነው።) ◈ ቅዱሳን ሐዋርያት የአምላካቸውን የመምህራቸውን አርአያ ተከትለው እርሱ ወደ ማዳን ሥራው ማለትም ህሙማነ ሥጋን በተዓምራት ሕሙማነ ነፍስን በትምህርት ከማዳን አስቀድሞ የስራውን መጀመሪያ በገዳመ ቆሮንቶስ ገብቶ 40 ቀን 40 ሌሊት እንደ ጾመና እንደጸለየ ሁሉ ቅዱሳን ሐዋርያትም አብነቱን ተከትለው ጾመዋል፡፡ ◈ ጸጋ መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ ዓለምን ዕጣ ተጣጥለው (ተከፈፍለው) ዞረው ከማስተማራቸው አስቀድመው የሥራቸው መጀመሪያ ጾምን አድርገዋል፡፡ ሐዋርያትም ይህንን ጾም እንደሚጾሙ ጌታችን አስቀድሞ የዮሐንስ ደቀመዛሙርት ወደ እርሱ ቀርበው በጠየቁት ጊዜ ተናግሮ ነበር፡፡ ◈ ‹‹እኛና ፈሪሳውያን ብዙ ጊዜ የምንጦመው ደቀመዛሙርትህ ግን የማይጦሙት ስለምንድን ነው? ብለው ጠይቁት፤ ኢየሱስም እንዲህ አላቸው ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉ? ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወስድበት ወራት ይመጣል በዚያን ጊዜም ይጦማሉ›› ብሎ ነገራቸው። (ማቴ 9፥15-16) ◈ እኛም ይህን ጾም የምንጾመው የሐዋርያትን በረከት ለመላበስ፣ እነርሱ ድል ያደረጉትን ዓለም እንድናሸንፈው አምላካችንን ለመማጸን በመሆኑ ይህንን ‹‹መሣሪያ›› አንጣለው ጾሙም ለመላው ክርስቲያን የተሰጠ ነው፤ አንድ አንዶች እንደሚሉት የቀሳውስት ብቻ አይደለም ለቄስና ለምዕመናን ተብሎ በክህነት ደረጃ የተለየ ጾምም የለም፡፡ ፆሙን የበረከት ፆም ያድርግልን በሰላም ያድርሰን #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239