HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
رفتن به کانال در Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
نمایش بیشتر2 276
مشترکین
+324 ساعت
+137 روز
+3830 روز
آرشیو پست ها
አብዛኛው ስንበት ተማሪ አይቆርብም ለምን ይሆን?? የሰንበት ትምህርት ቤቶች የመናፍስት ፈተና! ዛሬ ጸበል እንጠጣለን ነገ ደግሞ እንሰክራለን!! #ethiopia https://youtu.be/ZQeZJJPMjsc
ገድላትና ድርሳናትን የማንበብ ልምዳችንን ልናዳብር ይገባል ውድ ቤተሰቦቼ። የቅዱሳኑን ረድኤት በረከት የምናገኝበት ወሳኝ መንገድ ነውና በማንበብና በመኖር ልንባረክ ይገባል። በርቱ።
የካቲት ፳፭ /25/በዚች ቀን የከበሩ አውሳንዮስና ፊልሞና ስሟ ሉቅያ የሚባል አንዲት ድንግልም በሰማዕትነት ሞቱ። እሊህ ቅዱሳንም በአፍራቅያ ሀገር ሳለ በከበረ ሐዋርያ ጳውሎስ ትምህርት ያመኑ ናቸው ከሀድያንም ዝሑራ በሚባል ኮከብ ስም ለሚጠሩት ለአርታዳሚ ጣዖት በዓልን በአደረጉ ጊዜ አይተው በስሕተታቸው ሊዘብቱ እሊህ ቅዱሳን ተሰብስበው ወደ ጣዖቱ ቤት ገቡ ሰዎችም ለጣዖቱ ሲሠዉና ከፍ ከፍ ሲያደርጉት በአዩአቸው ጊዜ በክብር ባለቤተ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ፍቅር እሳትነት ልባቸው ነደደ ከጣዖቱም ቤት ወጥተው ወደ ክርስቶሳዊት ቤተ ክርስቲያን ሔደው የክብር ባለቤት የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብሩንና ልዕልናውን አብዝተው አመሰገኑ። ከዚያ ካሉት አንድ ሰው በሰማቸው ጊዜ በጣዖታቸው ላይ እንደ ዘበቱ የተናገሩትን ልብ ብሎ በመኰንኑ ዘንድ ወነጀላቸው መኰንኑም በፈረስ ተቀምጦ ሔደ ከወታደሮቹም ጋር ቤተ ክርስቲያኒቱን ከበባት ከምእመናንም ሰዎች የሸሹ አሉ። እሊህንም ሦስቱን ቅዱሳን ያዛቸው የብረት ዘንጎችን በእሳት አግለው በቅዱሳኑ ጐኖች ውስጥ አደረጉት ከዚህም በኋላ የከበረ አውሳንዮስን ወደ ጒድጓድ ወረወሩትና ነፍሱን እስከ ሰጠ ድረስ በደንጊይ ወገሩት። የከበረ ፊልሞናንና የከበረች ሉቅያን ግን ብዙ ጊዜ በጸና ሥቃይ ያሠቃዩአቸው ጀመር ነፍሳቸውንም ይወስድ ዘንድ እግዚአብሔርን ለመኑት እርሱም ልመናቸውን ተቀብሎ ነፍሳቸውን ወሰደ። በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ እነሆ የምስክርነታቸውና የሃይማኖታቸው መታሰቢያ ተጽፎአል ። በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239
እንዲህ_እያላችሁ_ስገዱ!
እግዚአብሔር አንተ አምላኬ ነህ (X7)
እግዚአብሔር አንተ ጌታዬ ነህ (X7)
እግዚአብሔር አንተ ንጉሤ ነህ (X7)
እግዚአብሔር አንተ የዕለት ምግቤ ነህ (X7)
እግዚአብሔር አንተ የሕይወት መጠጤ ነህ (X7)
እግዚአብሔር አንተ የአንደበቴ ብርታት ነህ (X7)
እግዚአብሔር አንተ የዓይኔ ብርሃን ነህ (X7)
እግዚአብሔር አንተ ሰላሜ ነህ (X7)
እግዚአብሔር አንተ በረከተ ነህ (X7)
እግዚአብሔር አንተ የመንገደ መሪ ነህ (X7)
እግዚአብሔር አንተ ብርሃንና እውነተ ነህ (X7)
እግዚአብሔር አንተ ደስታዬ ነህ (X7)
እግዚአብሔር አንተ እውቀተ ነህ (X7)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
እንዲህ_እያላችሁ_ስገዱ!
እግዚአብሔር አንተ አምላኬ ነህ (X7)
እግዚአብሔር አንተ ጌታዬ ነህ (X7)
እግዚአብሔር አንተ ንጉሤ ነህ (X7)
እግዚአብሔር አንተ የዕለት ምግቤ ነህ (X7)
እግዚአብሔር አንተ የሕይወት መጠጤ ነህ (X7)
እግዚአብሔር አንተ የአንደበቴ ብርታት ነህ (X7)
እግዚአብሔር አንተ የዓይኔ ብርሃን ነህ (X7)
እግዚአብሔር አንተ ሰላሜ ነህ (X7)
እግዚአብሔር አንተ በረከተ ነህ (X7)
እግዚአብሔር አንተ የመንገደ መሪ ነህ (X7)
እግዚአብሔር አንተ ብርሃንና እውነተ ነህ (X7)
እግዚአብሔር አንተ ደስታዬ ነህ (X7)
እግዚአብሔር አንተ እውቀተ ነህ (X7)
=> አስተውሉ! የቤት ዕቃዎችን መግዛት ስንፈልግ፥ በጣም እንጠነቀቃለን፡፡ የሻጮቹን ማንነት አይተን፣ የዕቃዉንም ጥንካሬ አገላብጠን ተመልክተን ነው የምንሸምተው፡፡ ሚስት ስናገባም ከዚህ የበለጠ ልንጠነቀቅ ይገባናል፡፡ የገዛነው ዕቃ ችግር ቢኖርበት ለሸጠልን ሰው መመለስ እንችላለን፡፡ ሚስት ስናገባ ግን ወደ ቤተሰቦቿ መመለስ አንችልም፤ እስከ ዕድሜአችን ፍጻሜ ድረስ ከእኛ ጋር ነው የምትኾነው፡፡ ክፉ ናት ብለን ብንመልሳት፥ በሕገ እግዚአብሔር መሠረት አመንዝራ እንኾናለን፡፡ ስለዚህ ሚስት ስትመርጡ የሀገራችሁን ሕገ መንግሥትን ብቻ አታንብቡ፤ ከኹሉም በፊት ሕገ ቤተ ክርስቲያንን አንብቡ እንጂ፡፡
#ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
የበርሜል ጊዮርጊስ ጸበል ያደረገውን ተዓምር ተመልከቱ!! የጨነገፈ ትውልድ ውጤቱ ይኼ ነው!! ስንወልደ ክፉው መንፈስ ተከትሎናል!! ጠንቋይ ቤት የሄደ ሰው!! https://youtu.be/8iCt6Nvejes
የካቲት ፳፬ /24/
በዚች ቀን የከበረ አባት ኤጲስቆጶስ አጋቢጦስ አረፈ።
ይህም አባት በከሀድያን ነገሥታት በዲዮቅልጥያኖስና በመክስምያኖስ ዘመን ነበር። ወላጆቹም ደጎች ምእመናን ነበሩ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት አስተምረውት ዲቁና ተሾመ።
ከዚህም በኋላ እናትና አባቱን ትቶ ወደ አንድ ገዳም ሔዶ በዚያም በጾም በጸሎት እየተጋደለ የሸመገሉ መነኰሳትን አገለገለ። የተጋድሎውና የኃይሉ ጽናት ወሬው በተሰማ ጊዜ ስሙ ሉክያኖስ የሚባል መኰንን ወደርሱ ልኮ አስመጥቶ ያለ ውዴታው በግድ የጭፍራ አለቃ አድርጎ ሾመው።
ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ እጅግ የሚወደው መልከ መልካም የሆነ ወጣት ብላቴና ነበር ክፉ ጋኔንም ያሰቃየው ነበር። ከዚህ ከአስጨናቂ ደዌ ያድነኝ ዘንድ የወታደሩ አለቃ አጋቢጦስን ፈጥናችሁ አምጡልኝ አለ።
ቅዱሱም በእግዚአብሔር ኃይል አዳነው በመጨረሻም ንጉሡን ከወታደርነት ውስጥ አሰናብተኝ አለውና አሰናበተው አስቀድሞ ወደ ነበረባትም ቦታው ተመለሰ ብዙ ዘመናትም እጅግ እየተጋደለ ኖረ። በዚያችም አገር በኤጲስቆጶስነት ተሹሞ በዙ ተአምራትን እያደረገ የክርስቶስን መንጋዎች በበጎ አጠባበቅ ጠበቃቸው።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለም አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
ፍቅር ሲመነምን ውጤቱ የበዙ ጥፋቶችን ማስከተል ይሆናል!!
የፍቅር እጦት ቂም እና ጥላቻን ይፈጥራል። ይህ ደግሞ በኃጢአት ሐሴት ማድረግን ያመጣል። መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል፦ "ጠላትህ ቢወድቅ ደስ አይበልህ በመሰናከሉም ልብህ ሐሴት አያድርግ" ምሳ 24፥17
ሌላው የፍቅር እጦት ውጤት ቁጣ እና ክፋት ነው። እንዲህ ያለው ሁኔታ ስድብን፣ ጠብን፣ ግድያን፣ ነቀፋን፣ ማዋረድንና ስም ማጥፋት ማስፋፋትን ያስከትላል። ከዚህ በተጨማሪ የፍቅር እጦት ወይም ጉድለት ወደ ቅንዓት፣ ወደ አላዋቂነት፣ ወደ ኩራት፣ ወደ ጽናትን ማጣትና ወደ ጭካኔ ይመራል።
ለእግዚአብሔር የሚሆን ፍቅርን ማጣት በብዙ ጉዳዮች ውስጥ ሊገለጥ ይችላል፤ ከእርሱም መካከል ጸሎትን፣ መጽሐፍ ቅዱስንና ቤተ ክርስቲያንን መርሳት ጥቂቶቹ ናቸው። በእግዚአብሔር ፊት መቆምን ማጣት እና በእግዚአብሔር መንግሥት ፈጽሞ ሐሴት አለማድረግ ሌሎቹ ጉድለቶች ናቸው።
#ብጹዕ_አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
ስለ #POPPOLIVE ይኼንን ጉድ ስሙ!! #POPPOLIVE ህይወተን አመሰቃቀለው!! #ፖፖላይቭ አእምሮዬን ተቆጣጥሮታል!! #ethiopia #poppolive https://youtu.be/S2AfRlB8oMA
ቅድስት (የዐቢይ ጾም ሁለተኛ ሳምንት)
«ቅድስት» ማለት የዘይቤ ፍችው «የተቀደሰች የተለየች» ማለት ነው። ምስጢራዊ መልእክቱ ግን የምስጢረ አድኅኖት ታላላቅ ሥራውን ለመጀመር መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶሰ በገዳመ ቆሮንቶስ ገብቶ ከቆመ ሳያርፍ፣ ከዘረጋ ሳያጥፍ የጾማት የአርብዓው ቀንና ሌሊት ልዩ የሆነችና ክብርት ጾም የምትጀመርበትን ሁለተኛ ሳምንት ከልብ ያሳስበናል፡፡ ማቴ. 4-2
ቅድስት የዐቢይ ጾም ሁለተኛ ሰንበት ስያሜ ነው፡፡ ስያሜውም ከኢትዮያዊው የዜማ ሊቅ ከቅዱስ ያሬድ የተገኘ ነው። ከዚህ ሰንበት ዋዜማ ጀምሮ ስለ ዕለተ ሰንበት ቅድስና ይዘመራል፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም ሰንበቱን ስለ ቅድስና ልጆቿን ታስተምርበታለች፡፡
በቅዳሴ ጊዜ የሚሰበከው ምስባክ፤ የሚነበቡ መልዕክታት፤ የሐዋርያት ሥራ ና ወንጌል ስለ ቅድስት የሚያስተምሩ ናቸው፡፡ ‹‹ቅዱስ›› ማለት ልዩ፤ ክቡር ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔር አምላካችን በባሕርዩ ቅዱስ ነው፡፡ ይህም ቅድስና ከማንም ያላገኘው የባሕርይ ገንዘቡ ነው። መጻሕፍትም የባሕርይ ቅድስናውን ተባብረው መስክረዋል፡፡ ባባሕርዩ ቅዱስ ስለሆነ ‹‹ቅዱስ፡ ቅዱስ፡ ቅዱስ›› እየተባለ ይመሰገናል፡፡ ( ኢሳ 6፡1-3፤40፡25 ራዕ 15፡4 ፤ 1ሳሙ2፡2-3፡፡) እኛም ቅዱስ ልጁ በሥጋ ተገልጦ እንዳስተማረን በየዕለት ጸሎታችን ‹‹ስምህ ይቀደስ›› እንለዋለን፡፡
የቅድስና ምንጭ ቅድስናን የሚሰጥ እርሱ ብቻ ነው፡፡ ‹‹ ቅዱስ ›› የሚለው ቃል ለሰዎች ለመላእክት፣ ለቦታ፣ ለዕቃ፣ ለዕለታት … ቢቀጸልም ቅድስናቸው በባሕርይው ቅዱስ ከሆነው ከእግዚአብሔር የተገኘ ነው፡፡ ይህም የጸጋ ቅድስና ይባላል፡፡
እግዚአብሔር ቅዱስ ስለሆነ በመልኩና በምሳሌው አክብሮ የፈጠረንን እኛም ቅዱሳን እንድንሆን ይፈለጋል፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ‹‹ዳሩ ግን እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ሁን›› ተብሎ ስለተጻፈ የጠራቸው ቅዱስ እንደሆነ እናንተ ደግሞ በኑሮአችሁ ሁሉ ቅዱሳን ሁኑ ›› ያለንም ይህንን ሲያስተምረን ነው። ከመፈጠራችን አስቀድሞ መጠን በሌለው ፍቅር የወደደን እግዚአብሔር ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣን፤ ለውርደት ሳይሆን ለክብር፤ ለርኩሰት ሳይሆን ለቅድስና፤ ለሞት ሳይሆን ለሕይወት ነው፡፡ የመፈጠራችንም ዓላማ በፊቱ በፍጹም ምግባርና ሃይማኖት በመመላለስ ከእርሱ ጋር እንድንኖር ነው፡፡ ብርሃን ከጨለማ፡ ጽድቅ ከኃጢአት፡ ጋር ኅብረት የለውምና ከእርሱ ጋር ለዘላለም ነግሰን ለመኖር በቅድስና መኖር ይጠበቅብናል፡፡
ቅድስናችን በኑሮአችን ሁሉ እንዲሆን ታዘናል (1ጴጥ1፡15)፡፡ ስለዚህ በተሰማራንበት የሥራ መስክ፣ በማኅበራዊ ኑራአችን፣ በምንበላው ምግብ፣ በምንለብሰው ልብስ፣ በንግግራችንና በመሳሰለው ሁሉ ለእግዚአብሔር ደስ የሚያሰኘውን በማድረግ እግዚአብሔርን በሚሞት ሥጋችን እናክብረው፡፡ ‹‹እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ የኃጢአትንም ጭንቀት ከእኛ አስወግደን በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግስት እንሩጥ፡፡
የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን እንከተለው፤ እርሱ ነውርን ንቆ፣ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጧል ›› ተብሎ እንደተጻፈ ደምን እስከ ማፍሰስ ድረስ ተጋድሎ አድርገን ከኃጢአት ርቀት በቅድስና እንድንኖር ይገባናል (ዕብ 12፡1)።
ሥጋዊ ምኞታችንንና መሻታችንን ሰቅለን አሮጌው ሰዋችንን አስወግደን ንስሐ ገብተን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀብለን በቅድስና እንድናኖር ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
ዘንድሮ ጉድ እኮ ሆነናል ወገን!! የጎረቤታችን ማደግና መለወጥ ለምን ይቆጨናል?? ከዲያብሎስ ጋር ሆነን እንማራለን እንናገራለን!! የዲያብሎስ ሴራን እወቁ!! https://youtu.be/xzpS9h10yAA
የካቲት ፳፪ /22/በዚች ቀን የኤጲስቆጶስ አባ ማሩና የዕረፍቱ መታሰቢያና በከሀዲ በዲዮቅልጥያኖስ ዘመን በፋርስ አገር ለተገደሉ ሰማዕታት ሥጋቸው የፈለሰበት ነው። ኤጲስቆጶስ ማሩናንም ስለ ድንቆች ተአምራቶቹ ስለ ትሩፋቱና ስለ ጽድቁ የአኖሬዎስና የአርቃዴዎስ አባት ታላቁ ቴዎዶስዮስ ንጉሥ ወደ ፋርስ ንጉሥ ላከው ከእርሱም ጋርእጅ መንሻ በመካከላቸው ስለ አለው ፍቅር ተላከ። ወደ ሳቦር ወደ ፋርስ ንጉሥም በደረሰ ጊዜ ታላቅ ክብርንም አከበረው በቤተ መንግሥቱም እልፍኝ ውስጥ አኖረው። ይህ ቅዱስም የንጉሡ ልጅ ጋኔን አድሮባት እንደታመመች በሰማ ጊዜ የከበረ አባ ማሩና ብላቴናዪቱን ጠርቶ በፊቱ አቁሞ በላይዋ ጸለየ ጋኔኑም ከእርሷ ወጥቶ ዳነች ንጉሡም ልጁ እንደዳነች አይቶ እጅግ ደስ አለው የአባማሩናንም ፍቅርና አክብሮት ጨመረ። ከዚህም በኋላ አባ ማሩና በፋርስ ሀገር በሰማዕትነት ስለሞቱ የከበሩ ሰማዕታት ሥጋቸውን ስለ መሰብሰብ ከንጉሥ ዘንድ ፈለገ ንጉሡም የሰማዕታትን ሥጋቸውን ይሰበስቡ ዘንድ ቤተ ክርስቲያንም ሠርተው በውስጧ ሥጋቸውን ያኖሩ ዘንድ አዘዘ ያች ቤተ ክርስቲያንም በዚች ዕለት ከበረች። ዳግመኛም በታላቋ ከተማ ውስጥ በከበረ አባ ማሩና ስም ያማረች ቤተ ክርስቲያንን ሠሩ እርሷም ማረፊያ የተባለች ናት። ከዚህም በኋላ ይህ አባት ወደ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ ተመልሶ በሮሜ አገር ሁለት ዓመት ተቀመጠ የእነዚያ ሰማዕታት ቤተ ክርስቲያን በከበረችበት በዚች ዕለት አረፈ ከቤተ ክርስቲያኒቱም ክብር ጋር በዓሉንና መታሰቢያውን የሚያከብሩለት ሆኑ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239
በዚች ቀን የኤጲስቆጶስ አባ ማሩና የዕረፍቱ መታሰቢያና በከሀዲ በዲዮቅልጥያኖስ ዘመን በፋርስ አገር ለተገደሉ ሰማዕታት ሥጋቸው የፈለሰበት ነው።
ኤጲስቆጶስ ማሩናንም ስለ ድንቆች ተአምራቶቹ ስለ ትሩፋቱና ስለ ጽድቁ የአኖሬዎስና የአርቃዴዎስ አባት ታላቁ ቴዎዶስዮስ ንጉሥ ወደ ፋርስ ንጉሥ ላከው ከእርሱም ጋርእጅ መንሻ በመካከላቸው ስለ አለው ፍቅር ተላከ። ወደ ሳቦር ወደ ፋርስ ንጉሥም በደረሰ ጊዜ ታላቅ ክብርንም አከበረው በቤተ መንግሥቱም እልፍኝ ውስጥ አኖረው።
ይህ ቅዱስም የንጉሡ ልጅ ጋኔን አድሮባት እንደታመመች በሰማ ጊዜ የከበረ አባ ማሩና ብላቴናዪቱን ጠርቶ በፊቱ አቁሞ በላይዋ ጸለየ ጋኔኑም ከእርሷ ወጥቶ ዳነች ንጉሡም ልጁ እንደዳነች አይቶ እጅግ ደስ አለው የአባማሩናንም ፍቅርና አክብሮት ጨመረ።
ከዚህም በኋላ አባ ማሩና በፋርስ ሀገር በሰማዕትነት ስለሞቱ የከበሩ ሰማዕታት ሥጋቸውን ስለ መሰብሰብ ከንጉሥ ዘንድ ፈለገ ንጉሡም የሰማዕታትን ሥጋቸውን ይሰበስቡ ዘንድ ቤተ ክርስቲያንም ሠርተው በውስጧ ሥጋቸውን ያኖሩ ዘንድ አዘዘ ያች ቤተ ክርስቲያንም በዚች ዕለት ከበረች።
ዳግመኛም በታላቋ ከተማ ውስጥ በከበረ አባ ማሩና ስም ያማረች ቤተ ክርስቲያንን ሠሩ እርሷም ማረፊያ የተባለች ናት። ከዚህም በኋላ ይህ አባት ወደ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ ተመልሶ በሮሜ አገር ሁለት ዓመት ተቀመጠ የእነዚያ ሰማዕታት ቤተ ክርስቲያን በከበረችበት በዚች ዕለት አረፈ ከቤተ ክርስቲያኒቱም ክብር ጋር በዓሉንና መታሰቢያውን የሚያከብሩለት ሆኑ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ፦ መጽሐፈ ስንክሳር
#እንዴት_ደስ_ይላሉ!!
ቆይታ ከመልአከ መንክራት መምህር ግርማ ወንድሙ ጋር! በአገልግሎት መደራረብ የተነሳ ለወራት ሳላገኛቸው ስለቀረው በእጅጉ የናፈቁኝን አባቴን ለማግኘት የዐቢይ ጾም ከገባ 4 ቀኑን በያዘበት በዕለተ ሐሙስ ከሰዓት በኋላ እጅግ ወደተከበሩትና ወደተወደዱት በሞገስ በጸጋ ወደከበሩት አባቴ ቤት ደረስኩ። የቤታቸው ኮሪደር ጋር መጽሐፍ እያነበቡና እየጻፉ አገኘዋቸው።
በናፍቆት የተገናኙ አባትና ልጅ ሲገናኙ በደስታ ሰላምታ እንደሚለዋወጡ ሁሉ ሰላምታ ተለዋወጥን ጉልበታቸውን እና እጃቸውን ሳምኩኝ። የተወደዱ ቤተሰቦቻቸው በፈገግታና በፍቅር ተቀበሉኝ አጠገባቸው ቁጭ አልኩ። ልጄ እንዴት ነህ እየበረታህና በአገልግሎት እየጠነከርክ ነው አሉኝ። በጸሎታቸው እየበረታው እንደሆነ ነገርኳቸው። በአንድ መንፈሳዊ አገልግሎት ውስጥ ስለሆንን ሳላወራቸው ይረዱኛል።
በፍቅርና በስስት ዓይናቸው እያዩኝ እንዲህ አሉኝ አይዞህ ልጄ ጠንክር በርታ እያሉ የሕይወታቸውን እና የአገልግሎታቸውን ልምድ ነገሩኝ በተገናኘን ቁጥር ምክራቸውን ይሰጡኛል። እኔም ምክራቸውን ስንቅ አድርጌ እየተጓዝኩ ቢሆንም ሁሌም ምክራቸው ያበረታኛል። እያሳቁ አጫወቱኝ የደረሱበት መንፈሳዊ ልዕልና ያስደንቀኛል። ለአገልግሎት የሚሆን ምክርና ጸሎት በረከት ተቀብዬ ተመለስኩ።
ጽናት፣ ፍቅር፣ ብርታት፣ ጥንካሬ፣ አይበገሬነት፣ በክርስቶስ ከፍ ማለት፣ በጸሎት ማደግ፣ በደስታ መኖር፣ በበረከት መትረፍረፍ፣ ለሌሎች መኖር፣ ሌሎችን ማገልገል፣ ትህትና፣ መምህርነት፣ አሸናፊነት፣ መስገድ፣ መጸለይ፣ በጸጋ መሞላት፣ ማገልገል፣ መስጠት፣ ዝምታ፣ በፈተና መፅናት ይሄንን ሁሉ የታደሉት ሐዋርያ፣ ሰባኬ ወንጌል፣ ሰዳዴ አጋንንት፣ ፈዋሴ ዱያን፣ መልአከ መንክራት መምህር ግርማ ወንድሙ የምወድዎት የምሳሳልዎት አባቴ ስለሰጡኝ አባታዊ ፍቅር ምክርና በረከት ሁሉ ከልቤ አመሰግናለው ቅዱስ ጌታ እግዚአብሔር እድሜ ጤና ፍቅር ይስጥዎት።
ዕድሜና ጤናን ጨምሮ ጨማምሮ ያድላችሁ በእውነት!!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@Estifanos2239
