fa
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

رفتن به کانال در Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

نمایش بیشتر
2 280
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+77 روز
+3930 روز
آرشیو پست ها
መከራና ፈተና የሚታለፈው በጸሎት ብቻ ነው! | በአብሾ መንፈስ የተሰቃየው ወንድማችን | ስለ መምህር ግርማ ምስክርነት | መምህር ተስፋዬ አበራ #ebs 🚩💥😱😭 https://youtu.be/-6nuu674dqA?si=nE4eORBmsW5DqaCA

እንኳን ለጾመ ፍልሰታ በሰላም በጤና አደረሳችሁ፤ አደረሰን! ጾሙን ጾመን ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ተቀብለን ለድኅነት እንድንበቃ፤ የእመቤታችንን ረድኤት በረከት እንድናገኝ አምላካችን እግዚአብሔር ይ
እንኳን ለጾመ ፍልሰታ በሰላም በጤና አደረሳችሁ፤ አደረሰን! ጾሙን ጾመን ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ተቀብለን ለድኅነት እንድንበቃ፤ የእመቤታችንን ረድኤት በረከት እንድናገኝ አምላካችን እግዚአብሔር ይርዳን፡፡ የእግዚአብሔር አብ ጸጋ፣ የእግዚአብሔር ወልድ ቸርነት፣ የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አንድነት፣ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት፣ የቅዱሳን ጸሎትና ምልጃ ከሁላችንም ጋር ይሁን አሜን #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

የመምህር ተስፋዬ ጥብቅ መልዕክት ለወንዶችና ለሴቶች || 3ቱ ወንዶች ከሴቶች የሚጠሏቸው ጸባይና ባሕሪይ || የዛር መንፈስ ደዌ ወይም በሽታ ሆኖ ሲቀመጥ 😱💥🚩 https://youtu.be/fjY_gBZH8oA

"ትጾማላችሁ ሰይጣን ግን አይበላም፤ በርትታችሁ ትደክማላችሁ ሰይጣን ግን ከቶ አይተኛም፤ ሰይጣንን የምትበልጡበት ብቸኛው መለኪያ ትህትናን በመያዝ ነው። ምክያቱም ሰይጣን ትህትና የለውምና።" (ኢትዮጵያዊው ቅዱስ ሙሴ) "በሕይወት ጉዳዮች ላይ ብዙ አታንጸባርቁ። ስለ ምንም ነገር አትጨነቁ። ሸክማችሁን ሁሉ በእግዚአብሔር ላይ ጣሉ እርሱም ይደግፋችኋል።" (ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድሪያ) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

#መዝሙረ_ዳዊት_116_(1-19) እግዚአብሔር የልመናዬን ድምፅ ሰምቶአልና ወደድሁት። ጆሮውን ወደ እኔ አዘንብሎአልና በዘመኔ ሁሉ እጠራዋለሁ። የሞት ጣር ያዘኝ፥ የሲኦልም ሕማም አገኘኝ፤ ጭንቀትንና መከራን አገኘሁ። የእግዚአብሔርንም ስም ጠራሁ። አቤቱ፥ ነፍሴን አድናት። እግዚአብሔር መሓሪና ጻድቅ ነው፥ አምላካችንም ይቅር ባይ ነው። እግዚአብሔር ሕፃናትን ይጠብቃል፤ ተቸገርሁ እርሱም አዳነኝ። ነፍሴ ሆይ፥ ወደ ዕረፍትሽ ተመለሺ፥ እግዚአብሔር መልካም አድርጎልሻልና፤ ነፍሴን ከሞት፥ ዓይኔንም ከእንባ፥ እግሬንም ከመሰናከል አድኖአልና። በሕያዋን አገር በእግዚአብሔር ፊት እሄዳለሁ። አመንሁ ስለዚህም ተናገርሁ፤ እኔም እጅግ ተቸገርሁ። እኔም ከድንጋጤዬ የተነሣ። ሰው ሁሉ ሐሰተኛ ነው አልሁ። ስላደረገልኝ ሁሉ ለእግዚአብሔር ምንን እመልሳለሁ? የመድኃኒትን ጽዋ እቀበላለሁ፥ የእግዚአብሔርንም ስም እጠራለሁ። በሕዝቡ ሁሉ ፊት ስእለቴን ለእግዚአብሔር እፈጽማለሁ። የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው። አቤቱ፥ እኔ ባሪያህ ነኝ፥ ባሪያህ ነኝ፥ የሴት ባሪያህም ልጅ ነኝ፤ ሰንሰለቴን ሰበርህ። ለአንተ የምስጋና መሥዋዕትን እሠዋለሁ፥ የእግዚአብሔርንም ስም እጠራለሁ። በሕዝቡ ሁሉ ፊት ስእለቴን ለእግዚአብሔር እፈጽማለሁ፥ በእግዚአብሔር ቤት አደባባይ፥ ኢየሩሳሌም ሆይ፥ በመካከልሽም። ሃሌሉያ #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

የመምህር ግርማ ፈተናዎች በእንባ የተናገሩት || ወታደሩ ጠንቋዩ ይሉኛል || መቋጠሪያው የሱዳን አስማት ነው || መምህር ግርማ ክህነት የላቸውም #ebs 💥😭😱 https://youtu.be/nUMf2d4Zypo

#Ethiopia | እንኳን ለጾመ ፍልሰታ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን ሱባኤው ከልባችን እግዚአብሔርን የምንፈልግበት ጸሎታችን ለሕሙማን ምሕረት ለምድራችን ሰላም የሚያወርድ ያድርግልን አሜን። የቅዱሳን መላእክትና የነቢያት ሐዋርያት የጻድቃን ሰማዕታት እንዲሁም የሰው ልጆች ጸሎት ሁሉ ወደ ሥላሴ መንበር የሚያሳርጉልን ካህናተ ሰማይ ናቸው። አብዛኞቻችን ግን አናውቃቸውም። ለምን? አንድ መልእክት በማታውቀው ሰው ልትልክ ትችላለህን ? እኔ ግን እልሃለሁ ጸሎታችን የሚያሳርጉልን ካህናተ ሰማይ ናቸው። ከሥላሴ መንበር ለሰው ልጅ የምሕረት ትእዛዝ ተቀብለው ወደ ቅዱሳን መላእክትና ነቢያት ሐዋርያት ጻድቃን ሰማዕታት የሚያወርዱ ካህናተ ሰማይ ናቸው። ድርሳነ ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ በግእዝና በአማርኛ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓትና ደንብ ጠብቆ ለመጀመርያ ጊዜ ታተመ። ኪሩቤል ሱራፌል ዘወትር ሳያቋርጡ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር ጸባዖት ፍጹም ምሉእ ሰማያት ወምድረ እያሉ እግዚአብሔርን ያመሰግናሉ። አራቱ እንስሳና ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ኪሩቤል /አራቱ እንስሳ የሥላሴ መንበር ይሸከማሉ። ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ የሥላሴ ዙፋን ያጥናሉ። ይህ ድርሳን በእግዚአብሔር ፈቃድ ከብዙ ድካም በኋላ በእግዚአብሔር እርዳታ በቅዱሳን ጸሎት ለኅትመት በቅቷል። ስለሆነም ገዝታችሁ የሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይና የአራቱ እንስሳ ረድኤት በረከት ተካፋይ ትሆኑ ዘንድ በትሕትና እናሳውቃለን። በእውነት በሁሉም ሊቃውንት እጅ በየጉባኤ ቤቱ ፣ መምህራን ፣ ሰንበት ትምህርት ቤትና ምእመናንም ሊኖራቸው የሚገባ ታላቅ መጽሐፍ ነው ። 📌 አሳታሚ የደብረ ሰላም ፀፀራ ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ / ተምቤን ዓብይ ዓዲ/ መጽሐፉ ለማግኘት በ 0915551515 ወይም 0915551525 በመደወል ማግኘት ትችላላችሁ አድራሻ መርካቶ ቅዱስ ራጉኤል ቤተ ክርስቲያን 1ኛ ፎቅ 🛑 ግእዝ መጻሕፍት መደብር ድርሳነ ካህናተ ሰማይና የተለያዩ ገድላትና ድርሳናት የጸሎት መጻሕፍት ያገኛሉ ድርሳነ ካህናተ ሰማይ በሁሉም የክልል ከተሞችና መጻሕፍት መደብሮች እና በመጻሕፍት አዛሪዎች ያገኝታል። የሃያ አራቱ ካህናትና የአራቱ እንስሳ ጸሎትና በረከት ከሁላችን ሕዝበ ክርስቲያን ጋር ይሁን አሜን። https://www.facebook.com/100038756600865/posts/1270043344297540/?app=fb ሼር እንዲያደርጉልን በቅዱሳን መላእክት በካህናተ ሰማይ ስም እንጠይቃለን

#መዝሙር_90(91)_1-16)) ልዑል መጠጊያ የሚኖር ሁሉን በሚችል አምላክ ጥላ ውስጥ ያድራል። እግዚአብሔርን። አንተ መታመኛዬ ነህ እለዋለሁ፤ አምላኬና መሸሸጊያዬ ነው፥ በእርሱም እታመናለሁ። እርሱ ከአዳኝ ወጥመድ ከሚያስደነግጥም ነገር ያድንሃልና። በላባዎቹ ይጋርድሃል፥ በክንፎቹም በታች ትተማመናለህ፤ እውነት እንደ ጋሻ ይከብብሃል። ከሌሊት ግርማ፥ በቀን ከሚበርር ፍላጻ፥ በጨለማ ከሚሄድ ክፉ ነገር፥ ከአደጋና ከቀትር ጋኔን አትፈራም። በአጠገብህ ሺህ በቀኝህም አሥር ሺህ ይወድቃሉ፤ ወደ አንተ ግን አይቀርብም። በዓይኖችህ ብቻ ትመለከታለህ፥ የኃጥኣንንም ብድራት ታያለህ። አቤቱ፥ አንተ ተስፋዬ ነህና፤ ልዑልን መጠጊያህ አደረግህ። ክፉ ነገር ወደ አንተ አይቀርብም፥ መቅሠፍትም ወደ ቤትህ አይገባም። በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋልና፤ እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል። በተኵላና በእባብ ላይ ትጫማለህ፤ አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ። በእኔ ተማምኖአልና አስጥለዋለሁ፤ ስሜንም አውቆአልና እጋርደዋለሁ። ይጠራኛል እመልስለትማለሁ፥ በመከራውም ጊዜ ከእርሱ ጋራ እሆናለሁ፤ አድነዋለሁ አከብረውማለሁ። ረጅምን ዕድሜ አጠግበዋለሁ፥ ማዳኔንም አሳየዋለሁ። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ነ የኾነ ጉደይ ነው እንዲሁም እኛም ወደዚህ ጊዜያዊ ሕይወት የገባነው ከዚያ በላይ ስለ ኾነ ጉዳይ ነው፤ ይኸውም ዘላለማዊ ሕይወት ነው። ወታደር ወደ ቤቱ መመለስን በደስታ እንደሚያስብ ኹሉ፤ ክርስቲያኖችም የሕይወታቸውን መጨረሻና ወደ አባታቸው ዓለም ወደ መንግሥተ ሰማያት መመለሳቸውን ሳያቋርጡ ያስባሉ።" ብሎ በምሳሌ ጥሩ አድርጎ በሕሊናችን ውስጥ የሕይወትን ዓላም በሥዕል መልክ ይቀርጽብናል። (St. Nicholas of Serbia, Thoughts on Good and Evil)። ◈ ሌላው የሕይወት ዓላማ ምስጋና ነው። ምስጋና ቅዱሳን መላእክትን የምንመስልበት፣ የእግዚአብሔርን ቸርነት የምናደንቅበት፣ ፍቅሩን እያሰብን የምንመሰጥበት የሕይወት ዓላማ ነው። ታላቁ ምስጋና በእያንዳንዳችን ገቢራዊ ሕይወት እግዚአብሔር እንዲታይ የምናደርግበት የየዕለት ሕይወት ያልተቋረጠ ምስጋና ነው። በሰማይ ላይ ፀሐይ እንደሚወጣ በእውነተኛ ክርስቲያን ሰውነትም ፀሐየ ጽድቅ ክርስቶስ ይወጣል። በብዙ አለማስተዋልና ተስፋ መቍረጥ ተቀጥቅጠው ሊወድቁ ያሉትንም እግዚአብሔር በእውነተኛ ምስጋናችን በኩል ኾኖ ወደ ራሱ ይጠራቸዋል። እውነተኛ የክርስትና ሕይወት ያልተቋረጠ የምስጋና ሕይወት ነው። ስለዚህ በዚህ ውስጥ ያለ ሰው በራሱ ሕይወት ተስፋ የመቍረጥ በሽታን አያኖርም። እግዚአብሔር ዓይነ ልቡናችንን ይክፈትልን ከክፉ ኹሉም ይጠብቀን አሜን። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

#ለምን_ተፈጠርኩኝ?? ◈ የተፈጠርንበትን መሠረታዊ ዓላማ በአግባቡ መረዳት። ቢያንስ በመሠረታዊነት የተፈጠርነው ስለ ሦስት ጒዳዮች ነው ማለት ይቻላል። እኒህም፦ ፍቅር፣ ቅድስናና ምስጋና ናቸው። የእግዚአብሔር አንድነቱ ከሦስትነቱ የተስማማው በእርሱ ዘንድ ባለ ዘላለማዊ (Eternal) በኾነ ፍቅር ነው። እኛንም የፈጠረን አንዳች የኾነ ነገር ከእኛ ለማግኘት ብሎ አይደለም። ይልቅስ ለእኛ ካለው ጥልቅ የኾነ ፍቅር የተነሣ በቸርነቱ ፈጠረን። አዳምን ሲፈጥር በጎኑ ሔዋንን የተከለው ስለ ፍቅር ነው። ኋላም ከአዳም ጎን ሔዋንን ያስገኘው ዓለም እግዚአብሔር በሰጠን ፍቅር ተጠቅሎ በአንድነት ይኖር ዘንድ ለማድረግ ነው። አዳም ሔዋንን ይህቺ አጥንቷ አጥንቴ፣ ሥጋዋ ሥጋዬ ነው፤ ከወንድ ተገኝታለችና ሴት ትባል ማለቱ የፍቅርን ትርጒም ሲገልጥ ነው። ፍቅር ማለት ራስን በሌላ ውስጥ ማግኘት ወይም ራስን ለሌላ መሥዋዕት አድርጎ ማቅረብ ነውና። በዚህም መሠረታዊ ምክንያት የሕይወት አንዱ ዓላማ ፍቅር ነው። ራስን መጥላት፣ በራስ ላይ ያልተገባ ውሳኔን መወሰን ይህን የፍቅር እውነተኛና ተፈጥሮአዊ መንገድ የሚጻረር አጋንንታዊ ነው። ሶሎሞን በመኃልየው "የውዴ ዓላማ በእኔ ላይ ፍቅር ነው" (መኃ 2፥10) እንዳለው፤ ከዚህ ውጭ ኾነን መኖርን መምረጥ የለብንም። የሕይወት ትርጒም ወደ ምሬት የሚገለበጥብን ይህን ጉዳይ ሳንረዳ እንዲሁ ዝም ብለን በሥጋዊ ሐሳብ ተወጥረን ስለምንኖ ነው። በሕይወታችን ፍቅር ምን ያህል እንደ ተገፋችና ጥላቻ እንደ ሠለጠነች የምንረዳው ራሳችንን ለማጥፋት እንኳን ድፍረት እስከማግኘት መድረሳችንን ልብ ስንል ነው። ውድ ወንድም እኅቶቻችን ሆይ! አምላክ ሰው ኾኖ በግርግም መወለድን ስለምን የፈቀደ ይምሳላችኋል? ከፍቅር ወጥተን በጥላቻ መኖር የጀመርነውን እኛን ወደ ቀደመው የፍቅር አኗኗር ለማምጣት አይደለምን? በቃና ዘገሊላ ውኃውንስ ወይን ያደረገው በሕይወታችን የጠፋውን ወይን የተባለ ፍቅርን ሊሰጠን የመጣ መኾኑን እንድንረዳ አይደለምን? እንግዲያውስ ጥላቻን ተውትና ወደ ፍቅር ተነጠቁ። ◈ ትክክለኛ በኾነ መንገድ የሕይወትን ዓላማ መረዳት ራስን ከማጥፋት ይልቅ ራስን ወደ መጠበቅ ይመራናል። የሞስኮው ፊላሬት የሕይወትን ዓላማ አስመልክቶ፦ "እያንዳንዱ ክርስቲያን ለራሱ ቅዱስ ለመኾን አስፈላጊና አበረታችን ነገር መፈለግ አለበት። ያለ ተጋድሎና ቅዱስ የመኾን ተስፋ የምትኖር ከኾነ፤ አንተ ክርስቲያን የኾንኸው በስም ብቻ ነው እንጂ በባሕርይው አይደለም። ነገር ግን ከቅዱስነት ውጭ ኾኖ ማንም ሰው ጌታን ሊያየው አይችልም፤ ይኸውም ማለት ዘለዓለማዊ ክብር ሊያገኙ አይችሉም ማለት ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ የመጣው ኃጥአንን ሊያድን ነው ማለት ተገቢ ነው። (1ጢሞ 1፥15) ነገር ግን ኃጢአተኛ ኾነን ሳለ የዳንን እንደ ኾነ አድርገን ካሰብን ራሳችንን እናታልላለን። ኢየሱስ ክርስቶስ ኃጥአንን ያደነው ቅዱሳን የመኾኛ መንገዱን በመስጠት ነውና።" ይላል። (St. Philaret of Moscow, Sermon of September 23, 1847)። ይህ የሊቁ አገላለጽ መኖር የሚገባን ቅዱሳንን ለመኾን መኾኑን በአጽንዖት የሚያሳስብ ነው። ክርስቶስ አምላካችን ሰው ኾኖ የተገለጠበት መሠረታዊ ምክንያትም እኛን ከኃጢአት አውጥቶ ወደ ቅድስና ለማስገባት ነውና። "ከእኔ ተማሩ" ብሎ መናገሩ በወንጌል መዘገቡ የእርሱን የአርአያነት ሥራ መሠረት አድርገን እንድንቀደስ ሲጋብዘን ነው። ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ፦ "ክፉ አኗኗርህን የምትተውና ወደ እግዚአብሔር የምትመለሰው ቅጣትን ከመፍራት የተነሣና ከቅጣት ለማምለጥ ብቻ ስትል ካልኾነ፣ ወይም ደግሞ የመልካምን ነገር ዋጋ ለማግኘት ብቻ ስትል (እንደ ምንደኛ) ከማድረግና የመልካም ምግባር ሕይወትን በሒሳባዊ ስሌትና ጥቅምን በሚያብሰለስል ራስ ወዳድ ሕሊና የምትለውጥና የምትነግድ ከመኾን ነጻ መውጣት እውነተኛ ፍጹምነት ይህ ነው። ኹሉም ነገር ለኛ የተዘጋጀና የተጠበቀልን ስለ መኾኑ የተነገረንን ተስፋ አምነህና ተማምነህ የሚያጨንቅህና የሚያሳስብህ ነገር ኹሉ ከእግዚአብሔር ፍቅር እንዳትለይ ብቻ ሊኾን ይገባል፤ የሕይወት ታላቁ መዳረሻና የዳርቻ ፍጻሜ ከኾነው በእግዚአብሔር ፍቅር ውስጥ ከመኖርና በእርሱ የተወደደ ከመኾን የሚበልጥ አንዳችም ነገር የሌለ መኾኑን አስተውለህና ተረድተህ ብትኖር ታላቁ ፍጹምነት ማለት ይህ ነው።" እያለ እንዴት መኖር እንዳለብን ይመክረናል። (ያረጋል አበጋዝ (ዲ/ን)፣ መድሎተ ጽድቅ ቅጽ አንድ፣ 2007 ዓ.ም፣ ገጽ 116-117)። የሕይወት መዳረሻ ሊኾን የሚገባው ቅዱስ ጎርጎርዮስ እንዳለው በእግዚአብሔር ፍቅር ውስጥ መኖር ነው። የተፈጠርነው ስለ ፍቅር እንደ ኾነ ኹሉ ልንኖርም የሚገባን ስለ ፍቅርና በፍቅር ነው። ክርስቶስን እኛን እስከ መስቀል ሞት የወደደን እኛ እርስ በእርሳችን በፍጹም እንዋደድ ዘንድ ነው። ◈ ሰማዕቱ ኦንፊራይ ጋጋሉክ ቅድስና ኹላችንም የተጠራንለት የሕይወት ዓላማ መኾኑን ሲገልጽ፦ "ቅድስነት ማግኘት አንዳንድ ሰዎች እንደሚያስቡት የመነኮሳት ጒዳይ ብቻ አይደለም። ቤተሰብ ያሏቸው በዚህ ዓለም በተለያዩ ሞያዎች የሚኖሩ ሰዎች በሙሉ ለቅድስና ተጠርተዋል። ስለ ፍጽምናና ቅድስና የተሰጡ ትእዛዛት የተሰጡት ለመነክሳት ብቻ ሳይኾን ለሕዝብ ኹሉ ነውና።" ይላሉ። (Hieromartyr Onuphry Gagaluk)። ስለዚህ ኹላችንም የተጠራነው ለቅድስና መኾኑን ልናስተውል ይገባል። ውድ ወንድሜ ሆይ አንተ የተጠራኸው ለቅድስና መኾኑን አስተውል። ወጥረው የያዙህ እና ራስህን ወደ ማጥፋት ገፍተው የሚወስዱ ጒዳዮች ላይ ከምታተኩር ይልቅስ ስለ ሕይወትህ መቀደስ አስብ። በዚህ ዓለም ምንም ነገር አሌተሳካልኝም አትበል፤ የሕይወት ዋና ዓላማው መቀደስ ነውና፥ አኹን ከዚህ ሰዓት ጀምረህ ወደ ቅድስና መግባት እንደምትችል አስተውል። እኔ ረክሻለሁኝ ክፉን ነገር ማቆም አልችልም አትበል ይልቅስ በመስቀል ላይ በሕይወት መጨረሻ ላይ ወደ በጎነት የተቀየረው የቀኙኝ ሽፍታ አስበው። በመጨረሻዋ ሰዓት ወደ መልካምነት ሲመጣ ጌታም በፍቅር እንደ ተቀበለው አስተውል። አንተም እንዲህ መኾን የምትችል መኾንህን ከልብህ አምነህ አሐዱ ብለህ ጀምር። ◈ ቴኦፋን እንዲህ ይላል፦ "የሕይወታችን ሥሙር መጨረሻው ከእግዚአብሔር ጋር በአንድነት መኖር ነው። የእግዚአብሔር ልጅ ሥግው የኾነው በኃጢአት ምክንያት ውድቀን ያጣናትን ከእግዚአብሔር ጋር የነበረችንን አንድነት ሊመልስል ነው። የእግዚአብሔር ልጅ በኾነው በኢየሱስ ክርስቶስ ከአብ ጋር ኅብረት ወደማድረግ እንገባል፤ ስለዚህም የሕይወትን ዓላማ እናገኛለን።" ይላል። (St. Theophan the Recluse, Letters to various people, 24)። እንግዲህ ይህ ሊቅ ደግሞ የሕይወት ዓላማው ከእግዚአብሔር ጋር የሚኖረንን ኅብረት ማግኘት ነው። ከእግዚአብሔር ከተለየን ከእውነተኛ የሕይወት ዓላማ ውጭ ኾነናል ማለት ነው። በምንም መንገድ ቢኾን ከእርሱ እቅፍ ልንወጣ አይገባንም። እግዚአብሔር ኹል ጊዜም አብረነው እንድንኾን ይፈልጋል። ኃጢአተኛ ነኝና እንዴት ከእርሱ ጋር መኖር እንችላለሁኝ አትበል፤ ይልቅስ ከእርሱ ጋር መኾንን ከውስጥህ ፈልጋት ያሌ እርሱ ራሱ ከኃጢአትህ አንጽቶ ካንተ ጋር መኾኑን ይገልጽልሃል። የሰርቢያው ኒቆላስ ደግሞ "ሰዎች ወደ ጦርነት የሚገቡት በጦርነቱ ለመደሰት ሳይኾን ከጦርነቱ ለመዳን እንደ ኾነ ኹሉ እኛም ወደዚህ ዓለም የገባነው በዚህ ዓለም ለመደሰት ሳይኾን ከዚህ ዓለም ለመዳን ነው። ሰዎች ወደ ጦርነት የሚገቡት ከጦርነቱ በላይ ስለ ኾ

ለጾመ ፍልሰታ 5 የመጻሕፍት ጥቆማዎች
+5
ለጾመ ፍልሰታ 5 የመጻሕፍት ጥቆማዎች

መዝሙር፡ 112፡(113) ሃሌ፡ ሉያ። የእግዚአብሔር፡ ባሪያዎች፡ ሆይ፥ አመስግኑት፥ የእግዚአብሔርንም፡ ስም፡ አመስግኑ። ከዛሬ፡ ዠምሮ፡ እስከ፡ ዘለዓለም፡ ድረስ፡ የእግዚአብሔር፡ ስም፡ ቡሩክ፡ ይኹን
መዝሙር፡ 112፡(113) ሃሌ፡ ሉያ። የእግዚአብሔር፡ ባሪያዎች፡ ሆይ፥ አመስግኑት፥ የእግዚአብሔርንም፡ ስም፡ አመስግኑ። ከዛሬ፡ ዠምሮ፡ እስከ፡ ዘለዓለም፡ ድረስ፡ የእግዚአብሔር፡ ስም፡ ቡሩክ፡ ይኹን። ከፀሓይ፡ መውጫ፡ ዠምሮ፡ እስከ፡ መግቢያው፡ ድረስ፡ የእግዚአብሔር፡ ስም፡ ይመስገን። እግዚአብሔር፡ በአሕዛብ፡ ዅሉ፡ ላይ፡ ከፍተኛ፡ ነው፥ ክብሩም፡ ከሰማያት፡ በላይ፡ ነው። እንደ፡ አምላካችን፡ እንደ፡ እግዚአብሔር፡ ማን፡ ነው፧ በላይ፡ የሚኖር፤ በሰማይና፡ በምድር፡ የተዋረዱትን፡ የሚያይ፤ ከአለቃዎች፡ ጋራ፡ ከሕዝቡም፡ አለቃዎች፡ ጋራ፡ ያኖረው፡ ዘንድ፡ ችግረኛን፡ ከመሬት፡ የሚያነሣ፥ ምስኪኑንም፡ ከፋንድያ፡ ከፍ፡ ከፍ፡ የሚያደርግ፤ መካኒቱን፡ በቤት፡ የሚያኖራት፥ ደስ፡የተሠኘችም፡ የልጆች፡ እናት፡ የሚያደርጋት። ሃሌ፡ ሉያ። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

የአዳኝ ወርቁ ጌጣጌጥ አብዝተን እንድንወድ የሚያደርግ የዛር መንፈስ | እንሾሽላ መመቅና አጋንንታዊ አሰራሩ https://youtu.be/Qdvd2S_1zRg?si=16MAKKLpdBDMVgWt

አጋንንትን የሚያቃጥል የምስጋና የአምልኮት ስግደት በተግባር የአምልኮት ስግደት ተግባራዊ ክርትና #ebs #ethiopia #በማለዳ_ንቁ #eotc 🙏😱💥 https://youtu.be/sMxwqtXd4gw

የላይቪ ቆይታችን የሚገርም ውይይትና ትምህርት ላመለጣችሁ ተከታተሉ! "ከማይግረን የተፈወስኩት በበገና ድምጽ ነው" | የሽንቁሩ ቅዱስ ሚካኤል ተዓምር 2 Haile Gebriel Reacts19 - በማለዳ ንቁ is live! 💥🚩😱 https://www.youtube.com/live/wDgkegdh-lI?si=maR2z2iCLV7oSTPC

የአምልኮት ስግደት በተግባር እንስገድ | ሦስቱ የስግድት አይነቶች | የአምልኮት ስግደት እንዴት እንስገድ? #ebs #ethiopia@haileG2239  💥🚩 https://youtu.be/hy3TRk8oiec

የአምልኮት ስግደት በተግባር እንስገድ | ሦስቱ የስግድት አይነቶች | የአምልኮት ስግደት እንዴት እንስገድ? #ebs #ethiopia@haileG2239  💥🚩 https://youtu.be/hy3TRk8oiec

🙏 እንኳን ለአምላካችን ለአባታችን ለመድኃኔዓለም ክርስቶስ በዓለ ስቅለት ወርሃዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። 🙏 ውድ ቤተሰቦቼ ኢትዮጵያዊያን ኤርትራውያን ወዳጆቼ ዛሬ እግዚአብሔር ቢፈቅድ ከቀ
🙏 እንኳን ለአምላካችን ለአባታችን ለመድኃኔዓለም ክርስቶስ በዓለ ስቅለት ወርሃዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። 🙏 ውድ ቤተሰቦቼ ኢትዮጵያዊያን ኤርትራውያን ወዳጆቼ ዛሬ እግዚአብሔር ቢፈቅድ ከቀኑ 11:00 ሰዓት ላይ በዩቱብ የላይቪ (Live) ፕሮግራም ይኖረናል። በዚህ መርሐግብር ተዓምራትና ተሞክሮዎችን እንመለከታለን፣ ጥያቄዎችን እንመልሳለን እንወያያለን። 🙏 ከዚህ ሰዓት ጀምሮ ጥያቄ ካላችሁ በኮሜንት መጻፋችሁን እንዳትረሱ። ገጠመኞችም ካላችሉ ጻፉ። ለብዙ ሰዎች ያስተምራሉ የምትሉትን ጥያቄ ላኩልኝ። መልካም ቀን ይሁንልን። እንበርታ አሁኑኑ! ቻናሉን ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ 🙏🙏