cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

𝚂𝚎𝚢𝚏𝚎𝚕𝙸𝚜𝚕𝚊𝚖 ሰይፈል ኢስላም!

قال ابن تيمية -رحمه الله-: {قوام الدين كتاب يهدي وسيف ينصر وكفى بربك هادياونصيرا} مجموع الفتاوى [10/13] ጠቃሚ መረጃዎችን ለማግኘት በሚመችዎ የማህበራዊ ሚድያ ይከታተሉኝ!👇 https://heylink.me/AzizoSocialLinks.com/

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
326
مشترکین
+224 ساعت
+107 روز
+4730 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

ሀዋሳ ከተማ ሀምዛ መስጂድ ህጋዊ መስጂድ ቦታ ላይ ቸርች እንገነባለን ባሉ ህገወጥ ሰዎች ምክንያት ውጥረት መፈጠሩ ተገለፀ! ... (ሀሩን ሚዲያ ደቡብ ስቱዲዮ፦ ግንቦት 3/2016) ... በሲዳማ ክልል ሀዋሳ ከተማ በተለምዶ ቡና ቅምሻ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኘው ሀምዛ መስጂድ ህጋዊ መስጅድ ቦታ ላይ ቸርች እንገነባለን ባሉ በህገወጥ ሰዎች ምክንያት ውጥረት መፈጠሩን የሀዋሳ ከተማ እስልምና ጉዳዪች ምክር ቤት ዋና ጸኃፊ  ለሀሩን ሚዲያ ደቡብ ስቱድዮ ገልፀዋል። ... ኃሊፊው እዳሉት የመስጂዱን መግቢያና መውጫ በአጥር ዘግተውብናል ይህ የሆነው ደግሞ መስጂዱ በ2003 ዓ.ል ህጋዊ የይዞታ ማረጋገጫ ተሰጥቶን የተገነባ ቢሆንም በመስጂዱ ቅርብ ርቀት ላይ የግለሰብ ቤት ተከራይተው ሸራ በመወጠር ቸርች ከፍተውብን እኛ ለክፍለከተማው ማዘጋጃ ቤትና ለጸጥታ አካላት በተደጋጋሚ አመልክተን ምንም አይነት ምላሽ በማጣችን ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት ወስደነው ሳለ ዛሬ ግንቦት 3/2016 ዓል እለተ ቅዳሜ በህቡዕ ተደራጅተው በመምጣት የመስጂዳችንን መግቢና መውጫ የሆነ ህጋዊ ቦታ ዘግተው እያጠሩብን ሲሆን ለጸጥታ አካላትም ስልክ ብንደውልም ሊመጡልን አልቻሉም ያሉን ሲሆን ... ሀሩን ሚዲያ ደቡብ ስቱድዮ ወደ ቀበሌው ሰላምና ጽጥታ ኃላፊ ወደ ሆኑት አቶ በቀለ ደውለን ስለጉዳዪ ጠይቀናቸዋል እሳቸው ከጸጥታ አካላት ጋር በመሆን ስፍራው ላይ እንደሚገኙና የሚታጠረውን አጥር አስቁመው የማዘጋጃውን ስራ አስኪያጅ ደውለው እስኪመጣ እየጠበቁ እንደሆነ ተናግረዋል። ... ስለታሰሩት ሙስሊሞች ጉዳይ ስንጠይቃቸው ባለፈው ነው የሴፍቲ ታንክ ከፕላን ውጭ እየቆፈሩ ነው በሚል በተፈጠረ ግርግር ታስረው ወዲያው እንድለቀቁ ተደርጓል በማለት የገለጹልን ሲሆን በመጨረሻም እኛ ለየትኛውም ወገን ሳናዳላ የህብረተሰቡን ሰላም ለመጠበቅ ከምንግዜውም በላይ እንሰራለን ብለውናል። ... በአሁኑ ሰዓት ከፍተኛ ውጥረት የነገሰ ስለሆነ የሚመለከተው አካል ችግራችንን አውቆ አፋጣኝ ምልሽ እንዲሰጠን እንጠይቃለን በማለት የአካባቢው ሙስሊሞች ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። ... ©ሀሩን ሚዲያ
نمایش همه...
በህንድ የአእምሮ ጤና እክል ያለባት ወጣት መለኮታዊ ኃይል አላት በሚል በመመለክ ላይ ትገኛለች በታሚል ናዱ ግዛት የሂንዱ ከተማ በሆነችው ቲሩቫናማላይ ውስር ሚስጥራዊ ኃይል አላት የተባለችው ግለሰብ የአእምሮ የጤና ችግር ላይ ብትሆንም የሕንድ ማህበረሰብን ግን እያመለካት ይገኛል። ህንዳውያን በርከት ያሉ አምላክ እና አማልክቶች ያሏቸው ሲሆን የሂንዱ አማልክቶች ሚስጥሮች እና እውነተኛ ህይወት ላይ በርካታ አወዛጋቢ ጉዳዮች ይነሳሉ። ከነዚህ መካከል ቶፒ አማ የምትባለው ኮፍያ የምታደርገው ሴት ብዙ ጊዜ ‘ሲድዳ’ እየተባለች በቅፅል ስም ትጠራለች። ይህችው ግለሰብ አዳኛችን ናት በማለት መመለክ ላይ ትገኛለች። አማኞች ፍፁም የሆነች ብሩህ ፍጡር ናት ይሏታል። ነገር ግን ዓለማዊ አመለካከት ላላቸው ሰዎች የህክምና እርዳታ የምትፈልግ የአእምሮ እክል ያለባት ሴት ናት። ለአማኞች የሚታየቸው በቲሩቫናማላይ ጎዳናዎች ውስጥ ስትንቀሳቀስ ማንም በማይረዳው ጥንታዊ የታሚልኛ ቋንቋ ስትናገር ሲያዩ፣ ሌሎች ደግሞ ቤት የሌላት ምስኪን ሴት ያለ አላማ ስትቅበዘበዝ እና ስታጉረመርም ትውላለች ይላሉ። ሁሉም ነገር የአመለካከት ጉዳይ በመሆኑ ልዩነቶች መስተናገዳቸው ግድ ሆኗል።ቶፒ አማ የቲሩቫናማላይ ምልክት ከመሆኗ እና ብዙ ተከታዮችን ከመሳቧ በፊት የነበራት ህይወት እንቆቅልሽ ሆኖ በመቆየቱ ለታዋቂነቷ ትልቅ አስተዋፅኦ አበርክቷል። ሁለት ወጥ ቃላቶችን እንኳን በአንድ ላይ አሰካክታ መናገር አለመቻሏን መለኮታዊ ኃይል ቢኖራት ነው ብለው ህንዳውያኑ እንዲያስቡ አስገዷቸዋል። በህንዳውያኑ የማህበራዊ ድህረ ገፅ ተጠቃሚዎች ዘንድ ቶፒ አማ ከተማዋን እየዞረች የጠጣችውን የቡና ትራፊ የተባረከ መስዋዕት ነው በማለት ሰዎች አንስተው ሲቀምሱ ይታያል። በሌላ በኩል ይህችኑ ሴት የአዕምሮ ጤና ችግር ያለባት ፣ የቆሸሸ ልብስ የለበሰች ፣ ሰውነቷ ከመታጠብ የራቀ እና በአንዳች እክል ውስጥ እንዳለች ማስተዋል ይችላል። አንድ የኤክስ ተጠቃሚ ባጋራው ፅሁፍ አንዳንዶች በአእምሮ ህመም እየተሰቃየች ነው ብለው የሚያስቡ እና እርዳታ ትሻለች የሚል ሰዎች ቢኖሩም ስለ እርሷ ውዳሴ የሚያቀርቡና የሚዘምሩ በርካቶች መሆናቸውን ፅፏል።ጥልቅ የሆነ መንፈሳዊ ጥበቧ ካልተገለጠልህ እሷን ማግኘት የሚችሉት የታደሉት ብቻ ናቸው ሲሉም አማኞች ይደመጣሉ። አስደናቂው ጉዳይ የአእምሮ እክል ላይ የምትገኘው ቶፒ አማ በአብዛኛው አምላኪዎቿን ችላ ብላ የእለት ውሎዋብ ስታሳልፍ አንዳች ምስጢራዊ ኃይል እየተገለጠላት ነው ብለው የሚያስቡ አሉ። በዚህም የተነሳ በሄደችበት ቦታ ሁሉ በርካቶች ይከተሏታል። በስምኦን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
نمایش همه...
በኢንዶኔዥያ በጥሎሽ የሚሰጥ ሀብትን ለማግኘት ሲል ሴት በመምሰል ጋብቻ  የፈፀመው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ በሀሰተኛው ጋብቻ የተታለለው ወጣት ከተጋቡ ከ12 ቀናት በኃላ ሚስት ብሎ ያገባት እንስት ወንድ መሆኑን ማወቁ ድንጋጤ ፈጥሮበታል። በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ የኢንዶኔዥያ መገናኛ ብዙሃን የ26 ዓመቱን ወጣት  ያጋጠመውን እንግዳ ጉዳይ በፊት ገፃቸው ይዘው ወጥተዋል። በዚህም ካገባት ከ12 ቀናት በኃላ ማስቴ ያላትን እንስት ወንድ ሆና መገኘቷን ተከትሎ ጉዳዩን ወደ ፖሊስ ወስዶታል። ወጣቱ ከሙሽራዋ ጋር በኢንተርኔት አማካኝይመት ነው የተገናኙት የተባለ ሲሆን በኢንተርኔት የጀመረውን ትውውቅ ለማዳበር በማለት በአካል ይገናኛሉ። ኤኬ የተባለው ወጣት ታድያ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲያያት ወድያውኑ በፍቅር እንደወደቀ ይገልፃል። እራሷን አዲና ካንዛ አዛህራ በማለት ያስተዋወቀችው ሴት ሁል ጊዜ ሂጃብ ተጠቅማ ፊቷን ለመደበቅ ትሞክር እንደነበረ ይገልፃል ቢሆንም ግን ሀይማኖታዊ እንጂ የሆነ ለመደበቅ የፈለገችው ነገር እንዳለ በፍፁም እንዳልጠረጠረ ይገልፃል። በዚህም ዓይናፋርነቷ የበለጠ ይሳባል። ትልቁን ጥያቄ ለማቅረብ ብዙ ጊዜ አልወሰደበትም ለትዳር ጠየቃት አዲናም ተቀበለች ነገር ግን እናቷ ስለሞተች እና አባቷ ለረጅም ጊዜ በአጠገባ ስላልነበሩ ትዳራቸው በሕግ አካል እንዲመዘገብ እንደማትፈልግ ትነገረውና በሰርጋቸው ቀን የምትጠራው የቅርብ ቤተሰብ እንደሌላትም ታሳውቀውቃለች። በመጨረሻም ሁለቱ የፍቅር ወፎች የዋንጉንጃያ መንደር የሃይማኖት መሪ ባደረጉት ልዩ ሥነ ሥርዓት ላይ ተጋቡ ጥሎሹም በ5 ግራም ወርቅ ነበር ተብሏል። ነገር ግን እንስቷ ካጋብቻው በኃላም ቢሆን ፊቷን ከአዲሱ ባለቤቷ እንኳን ሳይቀር ደበቀች በትውልድ መንደሩ ካሉት ቤተሰቦቹ እና ጓደኞቹ ጋርም ለመገናኘት ፈቃደኛ ሳትሆን ቀረች። በዚህም ኤኬ ቅሬታዎችን ማሰማት ጀመረ ይህንን ቅሬታውን የሰሙት ቤተሰቦቹም አዲሷን ሚስቱን ለመመርመር ወሰኑ። በምርመራቸውም የለም ያለችው አባቷ መኖሩን አረጋገጡ እሱም ሴት ሳትሆን ወንድ መሆኑን ይነግራቸዋል። በዚህ ጉዳይን ወደ ህግ ይወስዱታል  ወንጀለኛውንም በወንጀለኛ መቅጫ ህግ አንቀጽ 378 ክስ ይመሰርቱበታል፤ ክሱን እየተመለከተ የሚገኘው ፍርድ ቤቱ እስከ አራት ዓመት በእስር ቤት ውስጥ የመቆየት አደጋ ሊያጋጥመው ይችላል ተብሏል። በሚሊዮን ሙሴ #ዳጉ_ጆርናል
نمایش همه...
ከአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ አውጥቷል! ... (ሀሩን ሚዲያ ፦ሚያዝያ 30/2016) ... ሀገራችን ኢትዮጵያ ብዝሀ ሀይማኖትና ብዝህ ብሄሮች በአንድ ላይ ተሰባስበዉ የሚኖሩባት የጋራ ቤታችን መሆኗ ሁላችንም የሚያኮራ እና በባለቤትነት ስሜት የምንኖረዉ ጸጋችን ነዉ፡፡ በሀገር ግንባታ ሂደት የተለያዩ ብሄሮችና እምነቶች በመደጋገፍ የጋራ ጠላት በገጠማቸዉ ጊዜ አብረዉ በመቆም በጋራ ደማቸዉን አፍስሰዋል፤ አጥንታቸዉን ከስክሰዋል! የተለያዩ እምነቶች በሰላምና በችግር ጊዜ አብረዉ በመቆም ለሀገር መጽናት ዉድ ዋጋ ከፍለዉ የጋራ የሆነችን ሀገራችንን አስረክበዉናል፡፡ እኛ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችም የዚህ የጋራ ታሪክ ወራሽ በመሆናችን አባቶቻችን በከፈሉት ዉድ ዋጋ እና ባስረከቡን ሀገር እኛ ልጆቻቸዉ ኩራት ይሰማናል፡፡የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ክልላችን ያለበትን ሁኔታ በመረዳት አባባሽ ሁኔታዎችን እና መንገዶችን በመተዉ ለክልላችን ሰላምና መረጋጋት የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ይገኛል፡፡ ከፍተኛ ምክር ቤቱ የአማራ ክልል ሙስሊሞችን ሁለንተናዊ ዉክልና ወስዶ እንደሚንቀሳቀስ አንድ ተቋም የክልሉን ተጨባጭ ሁኔታ ከግምት ዉስጥ ያስገባ እጅግ ጥንቃቄ የተሞላበት አካሄድን በመምረጥ ለክልሉ ሰላምና ልማት የተሻለዉን መንገድ መርጦ ሰላምና መረጋጋት ለመፍጠር አስፈላጊዉን ሁሉ በማድረግ ላይ ያለ ተቋም ነዉ፡፡በተለያዩ ቡድኖች አማካኝነት በሚነሳ ግጭት ሁሉንም ወገናችን የከፋ ዋጋ እያስከፈለዉ እንደሆነ ብንረዳም በልዩ ሁኔታ ደግሞ በሙስሊሞች ላይ እየደረሰ ያለዉ ግፍ፣ መፈናቀል፣ ዘረፋ፣ መታገትና መገደል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ በመሄድ ላይ ይገኛል፡፡ የክልሉ መጅሊስ የምእመኑን ስቃይና እንግልት፣ ግድያ፣ የመስጅዶችና ሀሪማዎች መቃጠልና መነጠቅ፤ የምእመኑን መፈናቀል በየጊዜዉ እየተከታተለና እየመዘገበ ማስረጃ እያደራጀ ለሚመለከታቸዉ አካላት መረጃ እየሰጠ የመጣ ቢሆንም ሁኔታዎች እየተሻሻሉ ይመጣሉ በሚል እምነት በሆደ ሰፊነት በመታገስ የሀገርን ህልዉና ትልቁ ግብና የክልላችን ልማት አማራጭ የሌለዉ ጉዳያ በማድረግ ለሚፈጠሩት ችግሮች ሁሉበቅርበት ካሉ ከሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላት ጋር በመነጋገርና በመወያየት የእርምት እርምጃ እንዲወስድ በማሳሰብ ከዚህ ደርሷል፡፡ በተለይም ሙስሊሞች በዲሞግራፊ እና በፖለቲካ ሚና አናሳ ናቸዉ ተብሎ በታሰቡባቸዉ ቦታዎች በጅምላ መፈናቀል፤ መገደል፣ ማሳደድ፣ ሀብትና ንብረታቸዉን መንጠቅና ማዉደሙ እየተባባሰ መጥቷል፡፡ ሙስሊም በዝ እንደሆኑ በሚታመንባቸዉ አካባቢዎች ላይ ደግሞ በእጅ አዙር የብሄር ግጭት መነሻነት በሚመስል መልኩ ሁለንተናዊ ቀዉስን በመፍጠር መስጅዶችን! ሀሪማዎችን እና ሀይማኖት መሪዎችን ትኩረት ያደረገ ጥቃት ይፈጸማል። በተለያዩ አካባቢዎች በአንዳንድ "የሀይማኖት አስተማሪዎች ሃላፊነት የጎደለዉ ስብከት አብሮ የኖረን ህዝብ አሳዛኝ በሆነ መልኩ እምነትን መሰረት ያደረገ ጥቃት እንዲፈጸም ምክንያት ሆኗል፡፡ምንም እንኳን ከላይ የገለጽናቸዉ ለሀይማኖታችን ቀናኢ ነን ብለዉ የሚያስቡ አንዳንድ ግጭት አምጭ እና አባባሻ ግለሰቦች መሰል እኩይ ተግባር ቢፈጽሙም ሰፊዉ የሌላ ሀይማኖት ተከታይ ወገናችን ዛሬም ቢሆን ለሙስሊም ወገኖቹ አለኝታ በመሆን በአብሮነት እንደሚኖር የታወቀ ሀቅ ነዉ፡፡ይህ በእንዲህ እንዳለ በተለያዩ የሀይማኖት ተቋማት ዉስጥ ባሉ የሀይማኖት አባቶች' በማህበራዊ ሚዲያ በሚደረጉ ቅስቀሳዎች በሙስሊሞች ላይ ጥቃት የሚያነሳሳ እጅግ አደገኛ ቅስቀሳ፣ ፕሮፖጋንዳና ስብከት በማናለብኝነት ሲደረጉ ቆይተዋል፡፡ ይህም የክልሉን ሙስሊሞች በተናጠልም፣ በቡድንም፣ እንደማህበረሰብም ለከፍተኛ ጥቃቶች በተደጋጋሚ ሲጋለጡ እያስተዋልን ነዉ፡፡የክልሉ ሙስሊሞች ለዘመናት ትዉልዶቻቸዉን ካስቀመጡባቸዉ ይዞታዎቻቸዉና እርስቶቻቸዉ ታሪካዊና ማንነታቸዉን ካበቀሉበት የትዉልድ ቀያቸዉና ክልላቸዉ በየጊዜዉ በሚነሱ አሻጥሮች ቀጥተኛ የማፈናቀል ጥቃቶች እንዲሰደዱ ሲደረግ ክልላቸዉን ጥለዉ የት እንዲሄዱ እንደተፈለገ ግራ ያጋባል፡፡ በደቡብ ጎንደር ዉሻ ጥርስ ሀሪማ፣ በማእከላዊ ጎንደር ፉርቃና ደልዳሊት ሀሪማ፣ አምባገር ሀሪማ፣ እንዲሁም መስጅዶች ላይ ጥቃት የደረሰ ሲሆን ሰባህ ሀሪማ በ2012 ቤተ-ክርስቲያን ተስርቶበታል በተጨማሪም በአዊ ዞን በዚገም ወረዳ መስጅዶች ተቃጥለዋል በተጠቀሱት አካባቢዎች በሚገኙ ሙስሊሞች ላይም ከዚህ በፊት ይደረግ የነበረዉ እገታና ዘረፋ በጊዜ ማስቆም ባለመቻሉ ሁኔታዉ አድጎ ቀያቸዉን ለቀዉ እንዲወጡ እየተደረጉ መሆኑን እያየን እየሰማን ነዉ፡፡ በኦሮሚያ ልዩ ዞን የተፈጠረዉን ሁኔታ በቅርብ እየተከታተልን ሲሆን በሌሎች ሀሪማዎች ላይ ተመሳሳይ ስጋቶች እንዳሉ እንዲታወቅ እንፈልጋለን፡፡ በተጨማሪም በደቡብ ጎንደር ዞን በአምበሳሜ (ደራ) ወረዳ ወፍ አርግፍ ቀበሌ ከ800 መቶ ዓመት በላይ እድሜ ያለዉ ጥንታዊ መስጅድና የሙስሊሞች መካነ-መቃብር በአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም  ቢሮ በቅርስነት የተመዘገበዉን ቦታ በማፍረስ የአካባቢዉን ሙስሊም በማፈናቀል ቦታዉን ቤተ-ክርስቲያን የሰሩበት መሆኑን ስንሰማ በሀገሪቱ ያሉ አማኞች እንዲያዉቁትና መንግስትም ሆነ ቤተ-ክርስቲያኗ በዚህ ጉዳይ ላይ አስቸኳይ እልባት እንዲሰጥ ለመጠየቅ እንወዳለን፡፡ ይህ ሁሉ ጥቃት ሲፈጸም በርካታ ሀይሎች እጃቸዉ እንዳለበት እንረዳለን፡፡የህዝባችን ደህንነትና የሰላም ዋስትና በማረጋገጥ በኩል መንግስት እየወሰደዉ ያለዉ ሰላም የማስከበር እርምጃ የሚበረታታ ቢሆንም ነገሮችን በሰላም ለመፍታት በሚያደርገዉ ሆደ ሰፊነትና ታጋሽነት እድሉን ለተጨማሪ ጥፋት የሚጠቀሙ የተወሰኑ ሀይሎች የመንግስትን መዋቅር እና ማህበረሰቡ በአመኔታ የሰጣቸዉን ስልጣን ለአጥፊዉ ቡድን አላማ እስከመጠቀም የደረሱበት ሁኔታ እንዳለ ተስተዉሏል፡፡ በዚህም መንግስት ታችኛዉን መዋቅር መፈተሸ እንዳለበት ለማስታወስ እንወዳለን፡፡ በመሆኑም የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ይህ ነገር እየተባባሰ ከዚህም በላይ በሀገርም ሆነ በምእመኑ ላይ ከፍተኛ የሂወት፤ የቁስና የስነ-ልቦና ጉዳት ከማድረሱ በፊት በአስቸኳይ እንዲቆም እንጠይቃለን፡፡ ይህንን ዘረፋ ስቃይና እንግልት፤ እገታ፣ መገደልና መፈናቀል በጽነ- እናወግዛለን፡፡ከዚህም በላይ ይህን እኩይ ተግባር ለማስቆም መንግስት፤ ሰላማዊዉ የክልሉ ህዝባችን፣ የሌላ እምነት ተከታይ ወገኖቻችን፤ የሀይማኖት አባቶች እንዲሁም ጉዳዩ የሚመከታችሁ አካላት በሙሉ የበኩላችሁን ድርሻ እንድትወጡ ወገናዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ይህ ሰላማዊ ዜጎች ላይ ያነጣጠረ ግፍ እና ግድያ ለዘመናት አብሮና ህብረት ፈጥሮ የኖረዉን ህዝባችንን አብሮ'ነት ለማናጋት የታሰበ ስለሆነ በጋራ እንድንታገለዉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ በክልላችን የሚገኙ መሳጅዶች የጁምዓ መልእክቶቻችሁን በዚሁ ችግርና መከራ ዉስጥ ስላሉት ወገኖቻችን በማድረግ ለደረሰብንና እየደረሰብን ለሚገኘዉ መከራም ሰደቃ በማዉጣት በየመስጅዱ አቅመ ደካሞችን በማገዝ እንዲሆን በተጨማሪም በግፍ ለተገደሉ ደረሳዎችና ምእመናን ሶላተል ጋይብ እንዲሰገድላቸዉ እንደ አካባቢያችን ተጨባጭ ሁኔታ ይፈጸም ዘንድ ጥሪ እናቀርባለን፡፡በIዚህ መከራና እንግልት መሀል ለሞቱ ወገኖታችን አሏህ ጀነትን እንዲወፍቃቸዉ እየለመንን፤ ለቤተሰቦቻቸዉ ሶብርን(መጽናናትን) እንመኛለን፡፡ የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮችን ምክር ቤት
نمایش همه...