fa
Feedback
💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀

💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀

رفتن به کانال در Telegram

💎ሀያዕ ሲወሳ ለሴት ልጅ ጌጧ ነውና ሁሌም አብራ ትወሳለች፣ #ሴት ልጅና #ሀያዕ አብረው የሚኖሩ መቼም የማይነጣጠሉ ጥምሮች ናቸው። 👉 ሴት ልጅ ስትፈጠርም በሀያዕ ዘውድ አሸብርቃ ነው። 💎ይህንን ዘውድ ከራሷ የገፈፈች ሴት ግን ህያው ከሆኑ ሰዎች መሀል እንደምትንቀሳቀስ በድን ትሆናለች።

نمایش بیشتر
9 061
مشترکین
+1324 ساعت
+457 روز
-6430 روز
آرشیو پست ها
እንዲህም ቤት ደስ ይለኛል! ሁለት የሚፋቀሩ ባልና ሚስት ያሉበት...ከረሂሙ ጋር ባላቸው ውብ ግንኙነት የተፋቀሩ...በዛች አራት ማዕዘን ቤታቸው ውስጥ ሌላ ትንሽ አለም የፈጠሩ... ጥ..ል..ቅ ያለ ረጅም ወሬ...ተጨቃጭቀው እዛው ሚስማሙ...እዛው ተጣልተው እዛው የሚታረቁ...ስለነሱ ጉዳይ ማንም ሳያውቅ የሚኖሩ...ውብ የሁለት ጥንዶች ቤት...ትንሽዬ አለም! ሰሜኑን እሱ...ደቡቡን እሷ...ምስራቁን እና ምዕራቡን ፍቅርና መተሳሰባቸው የሞላው...ጥንጥዬ አለም! t.me/abdu_rheman_aman

ዘውታሪ የሆነ ሰላምና መረጋጋት ይኖራችሁ ዘንድ  ሁልጊዜም ፤ በሁሉም ሁኔታ ዉስጥ አላህን አውሱ። ሥሙን በምላሳችሁ አድርጋችሁ ዋሉ። ደስታም ሆነ መልካም ነገር ሁሉ አላህን በማውሳት ዉስጥ ነው የሚገኘው።

🔖እዚህም እዚያም እውር እንዳትሆን ! ቁርኣን ውስጥ ካሉ በጣም አስፈሪ እና አስተማር ከሆኑ አንቀጾች አንዱ የሚከተለው የሱረቱል-ኢስራእ ቁጥር 72 አንቀፅ ነው፤ { وَمَن كَانَ فِے هَـٰذِهِۦۤ أَعۡمَىٰ فَهُوَ فِے ٱلۡـَٔاخِرَةِ أَعۡمَىٰ وَأَضَلُّ سَبِیلࣰا } [سُورَةُ الإِسۡرَاءِ: ٧٢] "በዚህች ዓለም ላይ ሲኖር እውነቱን ከማወቅና ከመከተል ልቡ የታወረ ሰው በመጨረሻው ዓለም (ኣኺራህ) ላይም እውር ይሆናል። ምድር ላይ ሲኖር የሐቅን መንገድ ከሳተው ይልቅም ኣኺራህ ላይ የጀነትን መንገድ ይስታል!" ይህ ችግር እንዳይገጥመን ዲናችንን በሚገባ መማር፣ አላህ እና መልእክተኛው የሚወዱትን አውቀን መተግበር፣ የሚጠሉትንም አውቀን መራቅ ይጠበቅብናል። ግምባር ላይ ያለውን የዓይን ብርሃን ከማጣት ይልቅ የልብን (የዕውቀትና የኢማንን) ብርሃን የማጣት አደጋ ሊያሳስበን ይገባል። منقول

🔖 ዝምታ  ከጥበብ ነው !!      〰️〰️〰️〰️〰️〰️ قال لقمان: يا بني إذا افتخر الناس بحسن كلامهم فافتخر أنت بحسن صمتك.،،،،،،،، ሉቅማነል ሀኪም ለልጁ እንዲህ ሲል መከረው። ልጄ ሆይ❗️ሰዎች በመልካም ንግግራቸው ሲኮሩና ሲጎርሩ ፦ አንተ በመልካም ዝምታህ ኩራባቸው (ብለጣቸው)                 [كتاب روائع الحكمة/٣٤] t.me/https_Asselfya

~ኢላሂ አፈጣጠሬን እንዳሳመርከዉ ስነምግባሬን አሳምርልኝ። ~

"ስትታይ በአድማሱ ላይ ያለች ኮከብ ትመስላለች… ውስጧ ግን ባዶ ነበር… ምግባር አጣሁባት… አብሮ የሚያቆየን ምንም አልነበረም።" አለ…  መልኳን ብቻ አይቶ ካገባት በኋላ… t.me/abdu_rheman_aman

﴿إِنَّ اللَّهَ لا يَظلِمُ النّاسَ شَيئًا وَلكِنَّ النّاسَ أَنفُسَهُم يَظلِمونَ﴾
تلاوة من سورة يونس للشيخ د. عبدالعزيز التركي | عشائيّات ربيع الأول 1447هـ

ነጠላ ሰረዝ ታውቃለህ አይደል? ፅሁፍ ላይ አስፈላጊ ነው። ቃላትን ትለይበታለህ፣ ዝርዝር ሃሳብን ትጠቅስበታለህ። ነገር ግን በድምፅ አታነበውም። ትፅፈዋለህ። እናልህ፤ ህይወትህ ላይ አንዳንድ ሰዎች አሉ፤ ክፉ ደጉን ትለይባቸዋለህ። ትምህርትህ ናቸው። ግን “ምን አሉ?” ብለህ አትጮህም። “በምን አሙኝ?” ብለህ ዋይታህን አታሰማም። ይፃፋሉ፤ ግን አይነበቡም። t.me/abdu_rheman_aman

በመንገድህ ላይ ለጮኸ ውሻ ሁሉ ድንጋይ የምትወረውር ከሆነ ካሰብክበት አትደርስም። so ጉዳት የማያደርሱ ውሻዎችን ባላየ ማለፍ ይልመድብህ። t.me/Abu_lmran_Alaseriy

አቡ ዑበይዳህ ይባላል። ሰሓቢይ ነው። በኸሊፋው ዑመር ግዜ ... አንድ ክፍለ-ግዛት ተሰጥቶት ያስተዳድራል። ታድያ ዑመር አስተዳደሩን ለመፈተሽ ወደርሱ ቤት ሲሄዱ ያዩትን ማመን አቃታቸው። አቡ ዑበይዳ
አቡ ዑበይዳህ ይባላል። ሰሓቢይ ነው። በኸሊፋው ዑመር ግዜ ... አንድ ክፍለ-ግዛት ተሰጥቶት ያስተዳድራል። ታድያ ዑመር አስተዳደሩን ለመፈተሽ ወደርሱ ቤት ሲሄዱ ያዩትን ማመን አቃታቸው። አቡ ዑበይዳህ የሚኖረው በአንድ ክፍል ቤት ነው። ቤቱ ውስጥ የሰይፍ ሰገባ እና የገብስ ኪስ እንጂ ሌላ አጡ፤ ግራ ቢገባቸው ጠየቁት፤ “ይህ ነው ቤትህ?” አቡ ዑበይዳህ መልስ ሰጠ፤ “ዑመር ሆይ! (የዱንያ ቆይታችንኮ) ቀናት ናቸው! ከዚያም እናልፋልን”። ....አዎ! እ ና ል ፋ ለ ን። t.me/abdu_rheman_aman t.me/abdu_rheman_aman

 የቁርአን አንድ ሶስተኛ.mp34.80 KB

~ቅሯት تعدل ثُلث القرآن
~ቅሯት تعدل ثُلث القرآن

📖🕯️ ▫️وَمِنَ اللَّيلِ فَتَهَجَّد بِهِ نافِلَةً لَكَ عَسى أَن يَبعَثَكَ رَبُّكَ مَقامًا مَحمودًا▫️ [الإسراء: ٧٩] وقوله: ﴿ومن الليل فتهجَّدْ به﴾؛ أي: صلِّ به في سائر أوقاته، ﴿ نافلةً لك ﴾؛ أي : لتكون صلاة الليل زيادةً لك في علوِّ القدر ورفع الدرجات؛ بخلاف غيرك؛ فإنَّها تكون كفَّــــارة لسيِّئاته. 📓 تفسير السعدي

እኛ ግን ምን ጎድሎን ነው!? 🪶–የ አቡ ቂላባ ድንቅ ታሪክ– «ደስተኛ ሕይዎት ለመኖር የሚያግዙ ነጥቦች» 📖الوسائل المفيدة للحياة السعيدة ከሚለው የኪታብ ደርስ ላይ የተወሰደ ወንድም አቡ ሱፍያን― =t.me/Sle_qelbachn1

ባልን ወደ ሌላ ሴት አንድከጅል የሚያደርጉ ብዙ ነገሮች አሉ  ከነሱ መካከል:- ለባል አለመዋዋብ፣ ባልን አለማክበር፣ ሁሌ በሆነ ባልሆነው  ሲገባ ሲወጣ መጨቃጨቅ፣ ስራ ውሎ ሲመጣ ፊትን አኮሳትሮ መጠበቅ፣ ሳይዋዋቡ መጠበቅ፣ የሚበላቸውን ምግቦች በፅዳት እና አጣፍጦ አለመስራት፣ ሁሌ አሮጌ ልብስ ለብሶ ዝርፍጥፍጥ እዳሉ ተንጨብርሮ መጠበቅ፣ የራስ ንፅህናና የቤት ንፅህን  አለመጠበቅ። እነዚህ ነገሮች ካሉብሽ ራስሺን ፈትሺ ባልሺ ጥሎሽ ወደሌላ ሳይሄድ!? منقول t.me/https_Asselfya

ይህ ተፈጥሮዬ ነውና ምንም ላደርግ አልችልም።ይህን መጥፎ ባህሪዬን ልቀየረው አልችልም ቻሉት አትበል። ለማንም የማይበገረው አንበሳ እንኳን ቀስ እያደረጉት አስለምደዉት ከሰው ጋ አብሮ እንዲኖር ያደርጉታል። ቁጣህን፣ ትእግስት አልባነትህን ሁሉ ካመንክበት ማስቆም ትችላለህ።

ያረብ ..! ሲትርህን አታንሳብኝ፣ ከዚክርህ አታዘናጋኝ፣ ከዝንጉዎችም አታድርገኝ ። ~

~ከትልልቅ ኢባዳዎች ዉስጥ አላህ ሱብሀነሁ ተአላን የአላማቱን ጌታ መጠባበቅ ነዉ። ~