fa
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

رفتن به کانال در Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

کانال Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 411 مشترک است و جایگاه 5 577 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 191 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 411 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 11 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 64 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 24 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 24.26% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 9.47% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 737 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 458 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 23 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 12 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 411
مشترکین
+2424 ساعت
+237 روز
+6430 روز
آرشیو پست ها
ከግንቦት 7-11 በመካኒሳ ምዕራፈ ጻድቃን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤ/ክ ኆኅተ ጽድቅ ሰ/ት/ቤት #ዐውደ_ርዕይ_በእንተ_ቅዱስ_ያሬድ_ወቤተ_ክርስቲያን::

#በሃገር_አቀፍ_ደረጃ_ለመጀመሪያ_ጊዜ_ሊቁን_በሊቁ_ቀን_እንዘክረው_፡፡ በሃገር አቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ፤ ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅን በሊቁ ቅዱስ ያሬድ በዓለ ስዋሬ ግንቦት 11 ቀን (በቅ/ዮሐንስ አፈወርቅ በዕረፍቱ ዋዜማ) እንዘክረው፡፡ ➊ የት፤ በመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅ/ጊዮርጊስ ሰ/ት/ቤት አዳራሽ ➋ ሰዐቱ፤ በ7፡30 ➋ ምን ይቀርባል? "ጋብቻና ቤተሰባዊ ሕይወት በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ" የሚል ጥናታዊ ጽሑፍ፤ በመምህር ግርማ ባቱ ➍ ከጥናታዊ ጽሑፉ በኋላ ውይይት በቀሲስ ጥላሁን ታደሰ:: #፠በአብዛኛው ኪዳንና ተዓምር በየዕለቱ በሚደርሰባቸው ገዳማትና አብያተ ክርስቲያናት ‹‹እሰግድ ለኪ፥ እሰግድ ለኪ፥ እሰግድ ለኪ ወእዌድሰኪ … ›› የሚለውን የእመቤታችን ድርሳኑን በየቀኑ የምንሰማውን) የደረሰ፤ ፠እጅግ በጣም ብዙ የኾኑ ድንቅ የኾነ መጻሕፍትን እጁን እስኪያመውና እጁን በክር አሥሮ የጻፈ፤ ፠ኍልቈ መሳፍርት የሌላቸውን መልእክታት የከተበ ፠ ጳውሎስን የተካ ሰባኪ፤ ለአንዲት እናት ሳይቀር ጕኤ ዘርግቶ፥ አትሮኖስ አቁሞ የሚያስተምር ትጉህ አስተማሪ፤ ፠ በፓትርያርክነት ቤተ ክርስቲያንን የመራና ያስተዳደረ፤ ፠ ጠቢብ፣ መናኝ፣ ጳጳስ፣ ፈላስፋ፣ መምህር፣ ሰባኪ፣ ጸሐፊ፣ …………… ……… ……… ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄድ እንደመሆኑ እንዳያመልጣችሁ፤ አዳራሹም ስለሚጠብብ ከሰዐቱ ቀድማችሁ መገኘትን አትዘንጉ!! ****ከሃገር ውጭ ላላችሁ በ‹‹EOTC>> ይተላለፋልና በዛ ተመልከቱ፤ ምንም እንኳን በአካል እንደመገኘት ባይሆንም!!!!

፠የልደታ ለማርያም በዓል መቸ ነዉ? እንደተወለደችበት ሥፍራ የእመቤታችን የልደት ቀን እንዲሁ አወዛጋቢ ነዉ፡፡ በ6ኛዉ ና7ኛዉ መቶ/ክ/ዘመን ነዉ የሚሉ የተለያዩ ሃሳቦች የተጻፉ ሲሆን Encyclopaedic of Christian antiquities ደግሞ በ431 ዓ/ም ከተካሄደዉና ንስጥሮስ ከተወገዘበት ከጉባኤ ኤፌሶን በኋላ ነዉ ይላል፡፡በዓለም ቅዱሳንን የሚያከብሩ አብያተ ክርስቲያናት የቅዱሳንን በዓለ እረፍታቸዉን የሚያከብሩ ሲሆን ልደታቸዉ የሚከበረዉም በሦስተኛ ደረጃ የመጥምቀ መለኮት ቅ/ ዮሐንስ፤በሁለተኛ ደረጃ የእመቤታችን ቅ/ድንግል ማርያም ልደት ነዉ፡፡በአንደኛ ደረጃ ለስም አጠራሩ ክብር ይግባዉና የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ነዉ፡፡ የአመቤታችን ልደት በምዕራባዊያን አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ኬ.ክ በመጋገር፡የአመቤታችን ትንሽ ሀዉልት በማቆም ዐስር ሻማዎችን በማብራት ያከብራሉ፡፡ ፠የድንግል ማርያም ልደት ለምን ይከበራል? & ስለ መጥምቁ ዮሐንስ ልደት በመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል አንደበት‹‹በመወለዱ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል››በማለት ተነግሯል(ሉቃ 1-14)ምክንያቱም ቅ/ዮሐንስ የጌታ መንገድ ጠራጊ የአዋጅ ነጋሪ በመሆኑ ነዉ፡፡የቅዱስ ዮሐንስ መወለድ ለብዙዎች ደስታ ምክንያት ከሆነ የድንግል ማርያም ልደት ምንኛ የሚያስደስት ይሆን፡፡ስለሆነም ከጌታ ቀን ቀጥሎ የምንደሰትበት ትልቁ ቀን የእርሷ የልደት ቀን ነዉ፡፡ & የቀርጤሱ ቅ/እንድርያስ ስለ ከበረ ልደቷ እንዲህ ብሏል‹‹ይህ በዓል በሐዲስና በብሉይ ኪዳን መካከል መገኛ ሆነ፡፡ ምሳሌዎቹ በእዉነታ፣ አሮጌዉ በአዲስ ቃል ኪዳን ተተኩ፡፡ ፍጥረት ሁሉ በደስታ ይዘምራል የዚህን ቀንም ደስታ ይካፈላል፡፡ ይህ መቅደሱን የሰራበት ዕለት ነዉ፡፡ ይህ ዕለት ትልቅ ህንፃ የታነጸበትና ፍጡር የፈጣሪ ማደሪያ ለመሆን የተዘጋጀበት ዕለት ነዉ፡፡››ብሏል & እመቤታችን ለፀሐዩ መምጣት የተዘረጋች ሰማይ፡በቅድመ አያቶቿ በነ ቴክታና ጰጥሪቃ ህልም እንደታየችዉ በሌሊት የምታበራ ጨረቃ የብሉይ ኪዳን ማብቂያ የሐዲስ ኪዳን መጀመሪያ ናትና ልደቷ ለሰዉ ልጅ ሁሉ ደስታ ነዉ፡፡ & ነቢያት በብዙ ሕብረ አምሳል የተናገሩላት‹‹መሰረቶቿ የተቀደሱ ተራራዎች ናቸዉ››‹‹ከእሴይ ስር በትር ትወጣለች አበባዋም ከግንዱ ይወጣል››‹‹ሙሽራየ ሆይ ከሊባኖስ ነይ›.ብለዉ ተናገሩላት ቅ/ድ/ማርያም ልደቷ የትንቢታቸዉ ፍፃሜ ነዉና ታላቅ ደስታቸዉ ነዉ፡፡(መዝ86-1 ኢሳ 11-1) & በዓለም ላይ የብዙ ታዋቂ ሰዎች ልደት ከሞቱም በኋላም ጭምር በታላቅ ድምቀት ይከበራል ታዋቂ ያልሆኑ ሰዎች ልደትም እንዲሁ ይታሰባል ለሰዉ ልጅ መዳን ምክንያት የሆነች የአምላክ እናት የተወለደችበት ቀን ምንኛ ሊከበር ይገባዉ ይሆን! ፠የግንቦት ልደታ በዓል አከባበር በቤተ ክርስቲያናችን ትዉፊት መሰረት ሃና እና ኢያቄም ከአይሁድ ለማምለጥ ተሰደዉ በአድባረ ሊባኖስ ስር እመቤታችንን ወለዱ በወቅቱ ከቤት የወጡት ለሽሽት ነበርና ስንቅ ስላልያዙ ምግባቸዉ‹‹ንፍሮና ጥራጥሬ›› ነበር፡፡ይኼንን ትዉፊት በመያዝ በዓሉ ከቤት ዉጭ ንፍሮ እየተበላ ይከበራል፡፡ሆኖም በበጎ ነገሮች ሰበብ ክፉ ዓላማዉን ማስፈጸም የሚፈልገዉ ዲያቢሎስ በማር መሃል መርዝን ከሚጨምርባቸዉ መንፈሳዊያት በዓላት አንዱ የግንቦት ልደታ የእመቤታችን በዓል ነዉ፡፡አንዳንዶች በድፍረት ለአድባር ለዉጋር ነዉ፣ቆሌዉን ለመለመን ነዉ፣ እያሉ ንፍሮ የሚበትኑ፣ቡና የሚረጩ፣ቂቤ የሚቀቡ፣የከብት ደም የሚያፈሱ፣ እነዚህ በእርግጥም ጣዖት አምላኪዎች ናቸዉ፡፡ እኛም ከእንደዚ ዓይነቶቹ አሰናካዮች በመለየት ይኼንን ታላቅ በዓል በተገባና በተረዳ ነገር እንድናከብረዉ የ እመቤታችን ረድኤት በረከት አይለየን፡፡ #ፎቶው_ላይ_የምትመለከቷቸው_አብያተ_ክርስቲያናት፤ 1)፠፠፠፠መናገሻ ጋራ ልደታ ለማርያም፤ በአፄ ይስሐቅ ዘመን የተመሠረተች፤ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በመስቀላቸው የባረኳት፣ ግማደ መስቀሉ ያረፈባት፤ በድርሳነ ራጕኤል ላይ የተጠቀሰች ገዳም፡፡ 2)፠፠፠ጎንደር መካነ ስብሐት ልደታ ቤተ ክርስቲያን፡፡ * ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዷ የኾነች፤ አጸዷ ውጡ ውጡ የማያሰኝ ፍጹም መንፈስን፣ ነፍስንና ሥጋን የመመሰጥ ኃይል ያለው ቦታ ነው፡፡ * በስዕለት ሰሚነቷ የአፄ ዮስጦስንም ስዕለት ስለሰማቻቸው፤ አድረሺኝ (ቢያደርሰኝ ቢያደርሳችሁ እየተባለ ዛሬ ሞላው ጎንደር በፍልሰታ ማብቂያ የአድርሺኝ ስዕለቱን እንዲያወጣ መሠረት የኾነች ቤተ ክርስቲያን፡፡ * የ4ቱ ጕኤያት (መጻሕፍተ ትርጓሜያት፤ ብሉያት፣ ሐዲሳት፣ ሊቃወንትና መነኮሳት) ማስመስከሪያ የነበረች፤ አሁንም ይህንን ጕባኤ ለማስጀመር በሒደት ላይ የምትገኝ፡፡ * የታች ቤት ትርጓሜ ጀማሪና መምህር የኾኑት ሊቁ ዐራት ዐይና መምህር ኤስድሮስ ጕባኤ ከፍተው አትሮኖስ ዘርግተው ወንበር ተክለው ያስተማሩባት፤ ውዳሴ ማርያም ዘኀሙስ ‹‹ዳዊት ከቤተ ልሔም ውኃ ምንጭ ይጠጣ ዘንድ ፈለገ… የሚለውን ሲያትቱ ይህችው የቤተ ልሔም ውኃ እንደ ጎንደር መካነ ስብሐት ልደታ ማርያም ጠበል ነች፤ ያቺ የቤተ ልሔም ውኃ ጽምአ ዳዊትን ታረካ ነበርና (አርክታለች)፤ ይህች የልደታ ጠበል ምዕመናንን ከጤና ጽምእ ታረካለችና ትፈውሳለችና፤…. እያሉ ያነሷት፡፡ ዛሬም ድረስ ይህች የልደታ ጠበል በፈዋሽነቷ የታወቀችና ብዙ ሕሙማንን የሚፈወሱባት ናት፡፡ * በርካታ ለሃራችንና ለዓለማችን ትላልቅ ሥራን የሠሩ ሊቃውንትን ያፈራች፡፡ * የጎንደር ልደታ በደርቡሽ ጎንደር ስትቃጠልና ስትፈራርስ የመጀመሪያ ቤተ ክርስቲያኗም ፈርሷል (የመጀመሪያው ፎቶ የሚያሳየው ደርቡሾች ካፈረሱት የተረፉት አምዶችን ነው)፡፡ ፠፠፠፠3) አዲስ አበባ ማኅደረ ስብሐት ልደታ፤ በ1916ዓ.ም. የተመሠረተች፡፡ ፠፠፠፠4መቀሌ ልደታ ለማርያም ቤ.ክ. ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ ሐመር 20ኛ ዓመት ቁጥር 1 (የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት)

እመቤታችን እግዝትእነ ማርያም የተወለደችበት እለት በአባት እናቷ ቤት ፍስሃ ደስታ ተደረገበት ቤቱንም ብርሃን መላው በስምንተኛውም ቀን ""ማርያም"" ብለው አወጡላት::ስለምን ማርያም ብለው አወጡላት ቢሉ፤ እነሆ በዚህ አለም ከሚመገቡት ሁሉ ምግብ ለአፍ የሚጥም ለልብ የሚመጥን "ማር" ነው፤ በገነትም በሕይወት የተዘጋጁ ጻድቃን ቅዱሳን "ያም" የሚባል ምግብ አላቸው፡፡ ከዚህ ሁሉ የበለጥሽ የከበርሽ ነሽ ሲሉ ስለዚህ "ማርያም" ብለው አወጡላት:: የእመቤታችን ማርያም ስም ተነቦ ሳይተረጎም ይቀር ዘንድ አይገባምና:-""ማ"" ማለት ማህደረ መለኮት: ""ር"" ማለት ርግብየ ይቤላ: ""ያ"" ማለት ያንቀዓዱ ኃቤኪ ኩሉ ፍጥረት:""ም"" ማለት ምስሃል ወምስጋድ ወምስትሥራየ ኃጥያት ማለት ነው:: አንድም "ማርያም" ማለት ልዩ ከጣዖት፣ ክብርት እምፍጥረታት፣ ንጽህት እምሃጥያት፣ መልክ ከደም ግባት የተሰጣት ማለት ነው፡፡ ዳግመኛም "ማርያም" ማለት ተፈስሂ ቤተ ይሁዳ ወተሃሠዪ ቤተ እስራኤል ማለት ነው:: አንድም "ማርያም" ማለት መርሕ ለመንግስተ ሰማያት ማለት ነው፡፡ ይህስ እንዴት ነው ቢሉ ፡- እነሆ ዛሬ በዚህ አለም ለዕውር መሪ በትር እንዲሰጡት ሁሉ እርሷም በጣዕመ ፍቅሯ የሰውን ሁሉ ኃጥያት ክፋት ፍቃ ከልጇ ከወዳጇ አስታርቃ ከገሃነመ እሳት አውጥታ መንግስተ ሰማያት የምታስገባ ስለሆነች ስለዚህ መርሕ ለመንግስተ ሰማያት አሏት:: አንድም ማርያም ማለት ሰረገላ ፀሃይ ማለት ነው፤ አንድም ማርያም ማለት ተላኪተ እግዚአብሔር ወሰብእ ማለት ነው፤ አንድም ማርያም ማለት ውብህት (ስጥውት) ማለት ነው:: በዚህ በግንቦት አንድ ቀን እመቤታችን አለምን ልታስምር ከቅድስት ሃና እና ከቅዱስ እያቄም በብዙ ልመና ተገኘች:: የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ፍቅሯ ጣዕሟ በረከቷ ረድኤቷ አማላጅነቷ በእውነት በኛ በምናምን ልጆቿ ላይ ይደርብን:: ፠ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፠ ፠የግንቦት_ልደታ_ለማርያም_ክብረ_በዓል_የእመቤታችን በዓላት በቀደመዉ ዘመን በዘመነ ብሉይ ‹‹የቤተ መቅደስ መታደስ በዓል››ይከበር እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳል፡፡ይህ በዓል እስከ ጌታችን ዘመንም ይከበር ነበር፡፡ (ዮሐ 10-22) በሐዲስ ኪዳን እዉነተኛ የእግዚአብሔር ማደሪያ ቤተ መቅደስ ለሆነችዉ እመቤታችን በስሟ በዓል ሊደረግላት ይገባል‹‹የጻድቅ መታሰቢያ ለዘላለም ይኖራል›› እንዳለ ቅዱስ ዳዊት መዝ 111-7 በተአምረ ማርያም ላይ በዝርዝር እንደተቀመጠዉ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሠላሳ ሦስት በዓላት አሏት ፡፡ከእነዚህ በዓላት ሁሉ አስበልጣ የምትወደዉ በዓለ ልደቷን እንደሆነ በአጼ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመነ መንግስት ከዐረብኛ ወደ ግእዝ በተተረጎመዉ እመቤታችን በተለያዩ ሀገራት ያደረገቻችዉን ገቢረ ተአምራት በኢትዮጵያ ከተፈጸሙት ጋር አካቶ የያዘዉ ተአምረ ማርያም በዝርዝር ያስረዳል፡፡ ፠ልደቷ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ከሌለ ተቀባይነት እንዴት ይኖረዋል? በመጽሐፍ ቅዱስ ያልተካተቱና ምሉዕነት የሌላቸዉ ታሪኮች በአዋልደ መጻሕፍት እንደሚሟሉ ራሱ መጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳል ለምሳሌ ስለ ቅዱስ ዳዊት የሚናገረዉ መጽሐፈ ዜና መዋዕል ‹‹የንጉሡም የዳዊት የፊተኛዉና የኋለኛዉ ነገር በነቢዩ በናታን ታሪክ እንዲሁም በባለ ራእዩም በጋድ ታሪክ ላይ ተጽፏል›› 1ኛ ዜና 29-29 ፠የእመቤታችን ታሪክ የእመቤታችን ወላጆች በአብዛኛዉ አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ‹‹ሀና››እና ኢያቄም/ዮአኪን በሚለዉ ስም የሚጠሩ ሲሆን Hና በቤተልሔም ተወልዳ እንዳደገች ታሪክ ያስረዳል፡፡ በናዝሬት ገሊላ ለመሥዋዕት የሚሆኑ በጎች የሚያቀርብ እንዲሁም እረኛ የነበረዉን ኢያቄምንም አግብታለች፡፡ ቅድስት ሀና ወደ ቤተ መቅደስ ስትሔድ እርግብን አይታ ታለቅስ ነበር፡፡ ከብዙ ልመና በኋላ ቅድስት ድንግል ማርያምን ግንቦት አንድ ቀን በደብረ ሊባኖስ ወልደዋል፡፡ ስለ ሃና መካንነት ወደ ቤተ መቅደስ ሄደዉ መባዕ ሲያቀርቡ ካህኑ ያልተቀበላቸዉ መሆኑን በብስራተ መልአክ ልጅ እንደሚወልዱ እንደተነገራቸዉ በእኛ ቤተ ክርስቲያን የሚተረከዉና በሌሎች ኦርቶዶክሳዊያን አብያተ ክርስቲያናት የሚነገረዉ ታሪክ ተመሳሳይ ነዉ፡፡ ፠እመቤታችን የት ተወለደች? እመቤታችን ስለተወለደችበት ስፍራ በዓለም የተለያዩ ሀሳቦች ይስተጋባሉ፡፡ሌላዉ ቀርቶ በዶግማ አንድነት ባላቸዉ አኃት አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ በእንዲህ ዓይነት ታሪክ ነክ ጉዳዮች ላይ ልዩነት መኖራቸዉ የተለመደ ክስተት ነዉ፡፡የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ሁለት ሀሳቦች የሚያነሱ ሲሆን አንደኛዉ‹‹ድንግል ማርያም ብስራተ መልአክ በሰማችበት ናዝሬት ተወልዳለች››የሚል ነዉ፡፡ሁለተኛዉ ሀሳብ ደግሞ‹‹ከሦስተኛዉ ክ/ዘመን ወዲህ የማርያም መግቢያ ተብሎ በሚታወቀዉ ከኢየሩሳሌም የቅድስት ሀና የክሩሲድ ቤተ ክርስቲያን በታች ነዉ የተወለደችዉ የሚል ነዉ፡፡ የግብጽ ስንክሳር የእመቤታችን የትዉልድ ስፍራ በናዝሬት ነዉ ይላል፡፡የኢትዮጵያ ስንክሳር ግን በቀደምትነታቸዉ ተጠብቀዉ የቆዩ ከመሆናቸዉ አንጻር ተአማኒነታቸዉ የጎላ መሆኑን ያሳያል፡፡በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት የእመቤታችን የትዉልድ ስፍራ ሊባኖስ የተባለዉ ተራራማ ሀገር ነዉ፡፡ሊባኖስ ከገሊላ በስተ ሰሜንና ከፍንቄ በስተ ምስራቅ ይገኛል፡፡‹‹ሙሽራየ ሆይ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነይ››የሚለዉ ቃለ ትንቢት ምስጢርም የአመቤታችን መካነ ልደት የሊባኖስ ተራራ ስለመሆኑ የሚያጠይቅ እንደሆነ ምስክርነታቸዉ የታመነ የቤተ ክርስቲያን ሊቃዉንት ያስረዳሉ፡፡መኃ 4-7 ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ ሐመር 20ኛ ዓመት ቁጥር 1 (የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት)

#ልደታ_ለማርያም ምሥራቀ ምሥራቃት ሙፃአ ፀሐይ እግዝእትነ ዘመና ሙዳይ፤ ተወልደት ዮም ዳግሚት ሰማይ፡፡ ፠ልደቷ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ከሌለ ተቀባይነት እንዴት ይኖረዋል? ፠የእመቤታችን ታሪክ? ፠እመቤታችን የት ተወለደች? ፠የልደታ ለማርያም በዓል መቸ ነዉ? ፠የድንግል ማርያም ልደት ለምን ይከበራል? ፠የግንቦት ልደታ በዓል አከባበር ጴጥርቃ እና ቴክታ የሚባሉ መካን ነበሩና የሚወርሳቸው ልጅ አልነበራቸውም፡፡ ቴክታም ወንድሜ ሆይ አምላከ እስራኤል ለኔ ልጅ ቢነሳኝ አንተም እንደኔው ሆነህ ትቀራለህን? ከሌላ ደርሰህ ውለድ እንጂ ብላ ብታሰናብተው እንደዚ ያለ ነገር እንኳንስ ላደርገው በልቦናዬ እንዳላስበው አምላከ እስራኤል ያውቅብኛል አላት ሕልምን አለሙ፤ ያም ህልም ፈቺ እግዚአብሔር በምሕረቱ አይቷችኋል በሣህሉ መግቧችኋል 7 አንስት ጥጆች መውለዳቹ 7 ሴቶች ልጆች እና የልጅ ልጆች ትወልዳላቹ ከቤታቹ ሰባተኛይቱ ጨረቃ መውለዷ ከሰው የበለጠች ከመላእክትም የከበረች ደግ ፍጥረት ትወልዳላቹ የፀሐይ ነገር ግን አልታወቀኝም አለው፡፡ ከዛም ፀንሳ በ9 ወሯ ሴት ልጅ ወለደች፡፡ ስሟንም ሄሜን ብለው አወጡላት፡፡ ሄሜንም ደርዲ የምትባል ሴት ልጅ ወለደች፤ ደርዲም እንዲሁ ቶና የምትባል ሴት ወለደች፡፡ ቶናም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ሲካር አለቻት፤ ሲካርም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ሴትና አለቻት፡፡ ሴትናም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ሄርሜላ አለቻት፡፡ ሄርሜላም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ንጽህት ቅድስት ክብርት የምትሆን እመቤታችንን የምትወልደውን ሐናን ወለደች:: ከጴጥርቃና ከቴክታ የተወለዱ 67 ወንዶች ልጆች አሉ የእመቤታችን የድንግል ማርያምን ትውልድ ለመቊጠር ትንቢት አልተነገረላቸውም ሱባኤ አልተቆተረላቸውምና አልተፃፈም፡፡ ይህቺም ሃና በሥርዓት በቅጣት አደገች፤ ለአእምሮ ስትበቃ አካለ መጠን ስደርስ ከቤተ መንግስት ወገን ከነቅዱስ ዳዊት ወገን ከሆነው (መጽሃፍ ቅዱስ ይገልጸዋል) ከቅዱስ እያቄም ጋር አጋቧት:: እነዚህ ቅዱሳን እያቄም እና ሃና በአንድነት ተጋብተው ሲኖሩ ልጅ አጡ፡፡ ከእለታት አንድ ቀን ወደ ቤተ እግዚአብሄር ሂደው ሲፀልዩ ሲያዝኑ ዋሉ፡፡ ሃዘናቸው እንዴትስ ነው ቢሉ፤ እያቄም:-"አቤቱ ጌታዬ ያባቶቼ የእስራኤል አምላክ እኔ ባርያህ እለምንሃለው አትጣለኝ፤ አትናቀኝ፤ ፀሎቴን ስማኝ ፈቃዴን ፈጽምልኝ፤ ለአይኔ ማረፊያ ለልቤ ተስፋ የሚሆን የተባረከ ወንድ ልጅ ስጠኝ" ብሎ ሲለምን ዋለ፡፡ ሃናም በበኩሏ "አቤቱ ጌታዬ የአባቶቼ የእስራኤል አምላክ እኔ ባርያህ እለምንሃለው፤ ስማኝ ለአይኔ ማረፊያ ለልቤ ተስፋ የምትሆነኝ የተባረከች ሴት ልጅ የማህፀኔን ፍሬ ስጠኝ" ብላ ስትለምን ዋለች፡፡ እንዲ ብለው ሲያዝኑ ሲጸልዩ ውለው ርግብ ከልጆቿ ጋር ስትጫወት አይታ አቤቱ ጌታዬ ለዚች ግእዛን ለሌላት እንስሳ ልጅ የሰጠህ አምላክ ምነው ለኔ ልጅ ነሳኅኝ ብላ ምርር ብላ አለቀሰች፡፡ እንዲህ ብለው ሲያዝኑ ሲፀልዩ ውለው ከዘካርያስ ከሊቀ ካህናቱ ሄደው አቤቱ ጌታችን ሆይ ወንድ ልጅ ብንወልድ ተምሮ ቤተ እግዚአብሔርን አገልግሎ እንዲኖር እንሰጣለን፡፡ ሴት ልጅም ብንወልድ ማይ ቀድታ መሶብ ወርቅ ሰፍታ መጋረጃ ፈትላ ካህናትን አገልግላ እንድትኖር እንሰጣለን ብለው ስለት ገቡ:: ዘካርያስም እግዚአብሄር ጸሎታችሁን ይስማላቹ ስእለታችሁን ይቀበልላችሁ ጻህቀ ልቦናችሁን ይፈጽምላቹ ብሎ አሳረገላቸው፡፡ ከዚያም በኋላ ቅድስት ሃና እና ቅዱስ እያቄም እለቱን ራእይ አይተው ነገር አግኝተው አደሩ፡፡ ራእዩም እንዴት ነው ቢሉ ኢያቄም 7ቱ ሰማያት እንደ መጋረጃ ተገልጠው ከላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ አላት፡፡ ወፍ የተባለው ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ነጭነቱ ንጽሃ ባህሪው ነው፤ ከላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ ማለቱ፤ የኢያቄምን ባህርይ ባህርይ እንዳደረገው እወቅ ሲል ነው፤ 7ቱ ሰማያት የተባሉ የጌታችን ልዩ ልዩ ባህሪው፤ ምልአቱ፣ ስፍሃቱ፣ ርቀቱ፣ ልእልናው፣ ዕበዩ፣ መንግስቱ ናቸው፡፡ ሃናም እኔም አየሁ አለችው፡፡ ምን አየሽ ቢላት፤ ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማህጸኔ ስትተኛ አየሁ አለችው:: ርግብ የተባለች እመቤታችን ድንግል ማርያም ናት፡፡ ነጭነቷ፤ ንጽህናዋ፣ ቅድስናዋና ድንግልናዋ ነው፡፡ ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ተቀምጣ ከራሴ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማህጸኔ ስትተኛ አየሁ ማለቷ ብስራተ ገብርኤልን በጆሮዋ ሰምታ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታችንን መፀነሷ ነው፡፡ ይህንኑም ራእይ ያዩት ሐምሌ 30 ዕለት ነው:: እነሱም እንዲ ያለ ራዕይ ካየን፡፡ ነገር ካገኘን ብለው ዕለቱን በሩካቤ ሥጋ አልተገናኙም፡፡ ፈቃደ እግዚአብሄር ቢሆን ብለው አዳምንና ሄዋንን ብዙ ተባዙ ምድርንም ምሏት ብሎ ያበሰረ አምላክ ለኛስ ይልክልን የለምን? ብለው ዕለቱን አልጋ ምንጣፍ ለይተው እስከ 7 ቀን ድረስ ለየብቻቸው ሰነበቱ፤ ነሃሴ በባተ በሰባተኛው ቀን ከሰው የበለጠች ከመላእክት የከበረች ዓለሙ ሁሉ ተሰብስቦ ቢመዘን አንድ የራሷን ፀጉር የማያህል ደግ ፍጥረት ትወልዳላችሁና ዛሬ በሩካቤ ሥጋ ተገናኙ ብሏችኅል ጌታ ብሎ መልአኩ ለሃና ነገራት በፈቃደ እግዚአብሔር በብስራተ መልአክ እመቤታችን እግዝእትነ ማርያም እሁድ እለት ተፀነሰች (በኦሪት ስርአት እሁድ ዕለት ባል እና ሚስት መገናኘት ልማድ ነበርና)፡፡ እመቤታችን የተፀነሰች ዕለት አይሁድ ቀንተው ተነሱባቸው ቅናቱ እንዴት ነው ቢሉ፡፡ ሳሚናስ የሚባል የጦሊቅ ልጅ ከኤዶቅ ካጎቱ ቤት ሄዶ ሞተ እነርሱም እንቀብራለን ብለው ባልጋ ይዘው ሲሄዱ ከመንገድ አሳረፉት፡፡ የሃናም የአጎቷ ልጅ ነበርና ለማልቀስ ብትደርስ ዘመዶቿ ሁሉ ተሰብስበው ሲላቀሱ ቆዩአት:፡፡ እርሷም አብራ እየዞረች ስታለቅስ ጥላዋ ቢያርፍበት መግነዝ ፍቱልኝ ሳይል ብድግ ብሎ ተነስቶ ስብሃት ለኪ ማርያም እሙ ለፀሐየ ጽድቅ ለአብ ሙሽራው ለወልድ ወላዲቱ ለመንፈስ ቅዱስ ጽርሃ ቤቱ ተፈስሂ ደስ ይበልሽ ብሎ ሰገደላት፡፡ አይሁድ ከዛ ነበሩና ምነው ሳሚናስ ምን አየህ? ምን ትላለህ? ቢሉት ከዚች ከሃና ማህፀን የምትወለደው ህፃን ሰማይ ምድርን፤ እመቅ አየርን የፈጠረ አምላክን ትወልዳለች እያሉ መላእክት ሁሉ ሲያመሰግኗት ሰማኋቸው እኔንም ያነሳችኝ የፈወሰችኝ ያዳነችኝ እርሷ ናት አላቸው በል ተወው ሰማንህ ብለው ቅናት ጀመሩ፡፡ "እመቤታችን እግዝትእነ ማርያም በተፀነሰች በ9 ወር ከአምስት ቀን የግንቦት መባቻ ዕለት ግንቦት 1 ተወለደች፡፡"

ቅዱስ ማርቆስ በሰማዕትነት ሲያርፍ የ70 ዓመት አረጋዊ ነበረ:: ከ30 ዓመታት በላይ በዘለቀ መዋዕለ ስብከቱ ለዓለም ሁሉ የምስራች የሚሆን የወንጌልን ቃል ከመጻፉ ባሻገር ከሐዋርያዊ ተልዕኳቸው የተነሣ ብርሃናተ ዓለም ከተባሉ ከቅዱስ ጴጥሮስና ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር በብዙ አህጉረ ስብከት ተዘዋውሮ በማስተማሩና ይልቁንም የጥንት ግሪክ ሥልጣኔ ተስፋፍቶባትና የሮማ ሥርወመንግሥት ቁልፍ የፓለቲካና የንግድ መዲና በነበረችው እስክንድርያ በሰማዕትነት እስካረፈባት ቅጽበት ድረስ በአንደበቱም በሕይወቱም በክብሩና በመከራው ሁሉ በማስተማር አይሁድን ከይሁዲነት ወደ ክርስቲያንነት ፥ አረማውያንን ከአምልኮ ጣዖት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር የመለሰ እንዲሁም በጸሎታቸው የሚጠብቁ፥ በትሩፋታቸው የጽድቅን ዋጋ የሚያሰጡ የባሕታውያን አባት አባ ጳውሊን፣ የመነኰሳት አባት አባ እንጦንስን፣ አባ ጳኩሚስ እና አባ ሰራብዮንን፤ መናፍቃንን ተከራክረው የረቱ ሃይማኖትን ያቀኑ ቅዱስ እለእስክንድሮስን ፥ ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊን ፥ ቅዱስ ቄርሎስን፥ ቅዱስ ጢሞቴዎስ ዘአልቦ ጥሪትና ቅዱስ ዲዮስቆሮስን የመሳሰሉ ኦሮቶዶክሳውያን ሊቃውንትንና እስከ ዛሬም መከራ ሳይበግራቸው፥ ሞትና ግርፋታቸውን እንደ ክብር ቈጥረው፥ በሃይማኖታቸው ፀንተው የሚኖሩ የጸኑ ምእመናንን ያፈራች አንፀባራቂ ስም ያላት ኦርቶዶክሳዊትና ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያንን ያቋቋመ ሐዋርያ በመሆኑ ዳግመኛም ከአባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን /4ኛ ክ/ዘ/ እስከ አቡነ ቄርሎስ /20ኛ ክ/ዘ/ ድረስ የኢትዮጵያን ቤተክርስቲያን በክህነት የመገቡ 111 ጳጳሳት ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ ያቋቋማት የዚህችው ቤተክርስቲያን ፍሬዎች በመሆናቸውና ትምህርታችን ከትምህርታቸው ሥርዐታችን ከሥርዓታቸው የተስማማ ፥ የተግባባ በመሆኑ “ማርቆስ አባታችን ፥ እስክንድርያ እናታችን” ማለት በኢትዮጵያውያን ምእመናን ዘንድ የተለመደ ነበር፥ ታሪክ ነውና ዛሬም ቢሆን ቤተክርስቲያናችን ሙሉ በሙሉ ከግብጽ ቤተክርስቲያን ጥገኝነት ተላቃ በኢትዮጵያውያን ጳጳሳት ብትመራም ይህ እውነታ የሚዘነጋ አይደለም:: ምንጭ፤ በመምህር ኅሩይ ኤርምያስ ለለቩርዝቡርግ ቅዱስ ማርቆስ ሰ/ት/ቤት ዓመታዊ በዓል የተዘጋጀ ታኅሣስ ፳፻ወ፬ ዓ.ም. “የአጤ ኃይለ ሥላሴ ታሪክ” ከሚለው መጽሐፋቸው ገጽ 1132 ላይ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት፡፡/ የምትመለከቷቸው ቤተ ክርስቲያናት፤ ሰላ ድንጋይ ቅዱስ ማርቆስ፤ በአፄ ምኒልክና የተሠራና የአቡነ ማቴዎስ መንበረ ጵጵስና የነበረ፤ በልዩ አሠራር በ42 ቆመ ብእሲ (ዐምድ) የታነጸ፡፡ መናገሻ ቅዱስ ማርቆስ፤ በአቡነ ማቴዎስ የተሠራና መንበረ ጵጵስና የነበረ፤ ውጭው ክብ ውስጡ ግን ልዩና ድንቅ በሆነ አሠራርና ሥዕላት የተሞላ፡፡ ጎጃም ደብረ ማርቆስ፤ መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ፤ በአፄ ኀይለ ሥላሴ ከቤተ መንግሥታቸው ላይ ቦታ ቀንሰው ያነጹት ቤ.ክ.

ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ ማርቆስ የሚለው ስም ሦስት ፍቺዎች አሉት ንብ፣ አንበሳና ካህን:: *ንብ የሚለው ፍቺ የተሰጠው ንብ አበባ ካለው ተክል ሁሉ ቀስማ ማር እንድትሠራ እርሱም ቀድሞ ከጌታ ኋላም ከጌታ የተማርኩት ይበቃኛል ሳይል ከሐዋርያት ተምሮ ደገኛይቱን ወንጌልን በማስተማሩና በመጻፉ ነው፤ *አንበሳ መባሉ አንበሳ እንስሳት አራዊትን በክርኑ እንዲሰብር፤ በግብጽ ይመለኩ የነበሩ በእንስሳ አምሳል የተሠሩ ጣዖታትን በወንጌል ቃል ኃይልነት በማጥፋቱ ነው፡፡ *ካህን የሚለው ትርጉም ደግሞ በሐዋ. 14፥13 “ወአምጽኡ ማሬ ዘድዮስ” ተብሎ ከተመዘገበው መጽሐፍ ቅዱሳዊ አሳብ የተወረሰ ነው:: ማርቆስ ከመባሉ በፊት ዮሐንስ ይባል የነበረ ሲሆን ቁጥሩ ከ72ቱ አርድዕት ነው፤ ሐዋ. 12፥12፡፡ አባቱ አርስጦቦሎስ እናቱ ማርያም ይባላሉ:: እናቱ ማርያም በጌታ ትምህርት አምነው ሲከተሉትና ሲያገለግሉት ከነበሩት ደጋግ ሴቶች አንዷ ስትሆን ከጌታ ትንሣኤ በኋላ ቤቷን ለወንጌል አገልግሎት ሰጥታ ሐዋርያት በዚያ ተሰብስበው ለጸሎት ይተጉ ነበር፥ ጌታ ባረገ በ10ኛው ቀን (በተነሣ በ50ኛው ቀን) ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋር በአንድነት ሳሉ መንፈስ ቅዱስን የተቀበሉትም በዚሁ በማርቆስ እናት በማርያም ቤት ውስጥ ነው፡፡ ሐዋ. 2፥1 ፤ 12፥12፡፡ የራሱን ሀገረ ስብከት ይዞ ማስተማር ከመጀመሩ በፊት ቅዱስ ማርቆስ ሐዋርያትን እየተከተለ ይማር ፥ በተልእኮም ይራዳቸው ነበር:: ከቅዱስ ጳውሎስ መጠራት በኋላ ጳውሎስንና አጎቱ በርናባስን ተከትሎ በአንጾኪያ ፤ ቅዱስ ጴጥሮስን ተከትሎ በሮም አስተምሯል፤ እነርሱም በመልእክቶቻቸው “ማርቆስ ሰላም ይላችኋል” እያሉ አንስተውታል:: ሐዋ. 12፥25፣ ቈላ. 4፥10፣ 1ኛ ጴጥ. 5፥13 በሮም ተልእኮው ከቅዱስ ጴጥሮስ ጋር ሳለ ቅዱስ ጴጥሮስ ከፍጹምነት መድረሱን ዐውቆ ጵጵስና ሾሞ ከሀገረ ስብከቱ ግብጽን ከፍሎ አስተምር ብሎ ሰጠው:: እርሱም ሊያስተምር ሄዶ ወደከተማ ሊገባ ሲቃረብ የጫማው ጠፍር ተበጥሶበት አንያኖስ ወደሚባል ጫማ ሰፊ ሄደና ስፋልኝ ብሎ ሰጠው። አንያኖስ ጫማውን ተቀብሎ ሲሰፋ መስፊያው እጁን ወግቶት “ኢስ ታኦስ” ብሎ ጮኸ “አሐዱ እግዚአብሔር” ማለት ነው፤ የጠራኸውን ታውቀዋለህን? አለው፥ ሲሉ ሰምቼ እንጂ ያስተማረኝስ የለም አለው:: ቅዱስ ማርቆስም ፈቃደኛነቱን አይቶ አስተማረው አንያኖስም ከነቤተሰቦቹ አምኖ ተጠመቀ:: ከዚህ በኋላ አንያኖስን አስከትሎ በከተማ እየተዘዋወረ ያስተምር ጀመረ፤ ሕዝቡም ትምህርቱን ሰምተው ፥ ተአምራቱን አይተው አመኑ ተጠመቁ፤ አብያተ ጣዖታቱንም አፈራርሰው አብያተ ክርስቲያናትን ሠሩ። በዚህ ጊዜ የጣዖታቱ አገልጋዮች የለመዱት ቢቀርባቸው በጠላትነት ተነሡበት:: ምእመናኑ ተሰብስበው አባታችን እንድትለየን አንሻም፤ ነገር ግን ገነውተ ጣዖታቱ በጠላትነት ተነሥተውብሀልና ቁጣቸው እስኪበርድ ጥቂት ጊዜ ወደ ሌላ ሥፍራ ሄደህ ቆይ አሉት:: አንያኖስን ኤጲስቆጶስ ልጆቹን ቄስና ዲያቆን አድርጎ ሾሞላቸው፤ በባርቃና በሌሎች 5 አውራጃዎች እየሰበከ ቅዱስ ጴጥሮስን ለመጠየቅ ወደሮም ሄደ፤ በዚያ ሆኖ በስብከቱ ያመኑ የእስክንድርያ ምእመናን የተማሩትን እንዳይዘነጉ የማርቆስ ወንጌል ተብሎ የሚታወቀውን ወንጌል በሮማይስጥ ቋንቋ ጽፎ ልኮላቸዋል:: ዘመኑ ጌታ ካረገ 11ኛው ሲፈጸም 12ኛው ሲጀመር ፥ ቀላውዴዎስ ቄሳር በነገሠ በ4ኛው ዓመት /45-46ዓ.ም. ባለው ጊዜ/ ነው:: ከጥቂት ዓመታት ቆይታ በኋላ ወደ ግብጽ ተመለሰ፥ ምእመናኑ በቊጥር በዝተው፥ በእምነት ጐልምሰው አግኝቷተቸው ደስ ብሎት እያስተማራቸው አብሯቸው ጥቂት ጊዜ ቆየ:: በዓለ ትንሣኤን በሚያከብሩበት ቀን አምልኮ ጣዖት ከስሞ አምልኮተ እግዚአብሔር በመስፋፋቱ ምቀኝነት ያደረባቸው ጣዖታውያን ሊጣሉት መጡ፤ ምእመናኑ አባታችን ሽሽ አሉት፤ እንግዲህስ በጌታዬና በአምላኬ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ስለ ወንጌል ክብር መከራ ልቀበል እንጂ ልሸሽ አይገባኝም አልሸሽም አለ:: እንደ ላም በአንገቱ ገመድ አስረው በረሀ ለበረሀ ሲጐትቱት ዋሉ ፥ ሥጋው በእሾህ በጋሬጣ ተቀረደደ:: ወደጌታ ቢያመለክት ስለተቀበልኸው መከራ ክብርህን ከ12ቱ ደቀመዛሙርቴ ክብር አንድ አድርጌልሀለሁ፤ በስምህ የተማፀነኝንም እምርልሀለሁ ብሎ ቃልኪዳን ገብቶለት ነፍሱን በቃለ አቅርንት፥ በይባቤ መላእክት አሳርጓታል:: በሞቱ ያልረኩት ጣዖታውያኑ ከሞተም በኋላ ሥጋውን ለማቃጠል ሽተው እንጨት ሰበሰቡ የሚያቀጣጥልላቸውን ዝፍትም በከመሩት እንጨት ላይ አርከፈከፉ፤ ጌታ ግን ይህን እንዲያደርጉ ዕድል አልሰጣቸውም ድንገት ታላቅ ነጐድጓድ ሆነ ፥ የተከማቹበት ሥፍራ ተናወጸ፥ የፀሐይም ብርሃን ተሠወረባቸው፤ በዚህ ጊዜ ምን መጣብን ብለው ማቃጠሉን ትተው ሸሽተዋል:: ኋላ ግን ምእመናን በመብረቅ ጸዳል ተከብቦ አግኝተው በክብር ሥጋውን በአሌክሳንድርያ ቀብረውታል:: በዚህ ቦታ ተቀብሮ ለብዙ ዘመን ከቆየ በኋላ በ820 ዓ.ም ሁለት የቬኑስ ነጋድያን አጽሙን በድብቅ ከተቀበረበት አስወጥተው ወደ ቬነስ ነጋድያን አጽሙን በድብቃ ከተቀበረበት አስወጥተው ወደ ቬነስ ወሰዱት በዚህ ከተማ በሚገኘው በቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን አኑረውት ቦታው የበላይ ቅዱስ ሆኖ በክብር ይኖር ነበር። ስለሆነም የግብጽ ቤተ ክርስቲያን እንዲሰጣት በየጊዜው ከመጠየቅ አልቦዘነችም ነበር። ግርማዊ ንጉሠ ነገሥታት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴም የሮማው ርዕሠ ሌቀ ጳጳስ ጳውሎስ 6ኛ ስለፈቀዱ በሞተ በ1900 በተወሰደ 1140 ዓመት ወደ ጥንተ ቦታው ለመመለስ በቃ። አጽሙም ሰኔ 17 ቀን 1960 ዓ.ም ተመለሰ ሲመለስም ጃንሆይም በስፍራው ተገኝተዋል፡፡

እንኳን ደስ አለን፡፡ (በሰንበት ትምህርት ቤታችን ታሪክ 5ት አባላት በአንድ ቀን ጋብቻቸውን የፈጸሙበት ቀን፤ 7ት ተጋቢዎች ደግሞ በደብራችን በአንድ ቀን ሥርዐተ ጋብቻቸውን የፈጸሙበት ዕለት ነው፡፡) /በዕለተ መድኀኔ ዓለም ወበዓለ ዳግም ትንሣኤ ጋብቻችሁን የፈጸማችሁ ወንድሞቻችንና እኅቶቻችን፤ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ በዳግም ምጽአት በቀኝ ያቁማችሁ፡፡/ ‹‹ ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተ ክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡›› ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት በሚያዝያ ፳፯/፳፻፲፩ ዓ.ም. (በዕለተ መድኀኔ ዓለምና በዳግም ትንሣኤ ቀን) ጋብቻችሁን የፈጸማችሁ የደብራችን አገልጋይና ፭ት የሰ/ት/ቤታችን አባላት፤ * #መሪጌታ_ኃይሉ_ለገሠ_ከፍሬሕይወት ጋር #ይደነቁ_ዘነበ_ከከበደ ጋር #ዳንኤል_ንጉሤ_ከሠናይት_አበበ ጋር #ገነት_ዳንኤል_ከቢንያም ኤርምያስ ጋር የፈጸማችሁትን ጋብቻ፤ የይስሐቅንና የርብቃን ጋብቻ የባረከ አምላክ፤ የትዳር ሕይወታችሁን ይባርክላችሁ፥ ያጣምራችሁ፥ ያዋሕዳችሁ፤ እመብርሃን በአማላጅነቷ አትለያችሁ፤ ቅዱስ ገብርኤል ከፊት ይምራችሁ ከኋላ ይከተላችሁ፡፡ ✤ ‹‹ጌታን እንዲወዱና በአካልም ይሁን በመንፈስ በባሎቻቸው ደስ እንዲሰኙ ለእህቶች ንገራቸው፡፡ ልክ እንደዚሁ ጌታ ቤተ ክርስቲያንን እንደወደደ ሚስቶቻቸውን እንዲወዱ ለወንድሞች በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ንገራቸው፡፡›› ቅዱስ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ ለፖሊካርፐስ በላከው መልእክቱ ✤ ከተጋባችሁ በኋላ ባልና ሚስት አንድ አካል ናችሁ እንጂ ሁለት ስላይደላችሁ በፍጹም ልባችሁ እርስ በእርሳችሁ ተፋቀሩ፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ሌላ ወንድ ወይም ሌላ ሴት አትፈልጉ ይልቁንም በተቻላችሁ መጠን አንዳችሁ ሌላውን ደስ አሰኙ፤ በመረዳዳትና በፍጹም ፍቅር ኑሯችሁን ሁሉ አሳምሩ፡፡>> ኢትዮጵያዊው ፈላስፋ ዘርአያዕቆብ፡፡ /ከቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

/በዕለተ መድኀኔ ዓለም ወበዓለ ዳግም ትንሣኤ ጋብቻሽን የፈጸመሽው እኅታችን ትርሲት ጉልላት ከእነባለቤትሽ፤ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ በዳግም ምጽአት በቀኝ ያቁማችሁ፡፡/ ‹‹ ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተ ክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡›› ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት በሚያዝያ ፳፯/፳፻፲፩ ዓ.ም. (በዕለተ መድኀኔ ዓለምና በዳግም ትንሣኤ ቀን) ጋብቻሽን የፈጸመሽው የሰ/ት/ቤታችን አባል፤ * #ትርሲት_ጉልላት_ከግርማ ጋር የፈጸማችሁትን ጋብቻ፤ የይስሐቅንና የርብቃን ጋብቻ የባረከ አምላክ፤ የትዳር ሕይወታችሁን ይባርክላችሁ፥ ያጣምራችሁ፥ ያዋሕዳችሁ፤ እመብርሃን በአማላጅነቷ አትለያችሁ፤ ቅዱስ ገብርኤል ከፊት ይምራችሁ ከኋላ ይከተላችሁ፡፡ ✤ ‹‹ጌታን እንዲወዱና በአካልም ይሁን በመንፈስ በባሎቻቸው ደስ እንዲሰኙ ለእህቶች ንገራቸው፡፡ ልክ እንደዚሁ ጌታ ቤተ ክርስቲያንን እንደወደደ ሚስቶቻቸውን እንዲወዱ ለወንድሞች በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ንገራቸው፡፡›› ቅዱስ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ ለፖሊካርፐስ በላከው መልእክቱ ✤ ከተጋባችሁ በኋላ ባልና ሚስት አንድ አካል ናችሁ እንጂ ሁለት ስላይደላችሁ በፍጹም ልባችሁ እርስ በእርሳችሁ ተፋቀሩ፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ሌላ ወንድ ወይም ሌላ ሴት አትፈልጉ ይልቁንም በተቻላችሁ መጠን አንዳችሁ ሌላውን ደስ አሰኙ፤ በመረዳዳትና በፍጹም ፍቅር ኑሯችሁን ሁሉ አሳምሩ፡፡>> ኢትዮጵያዊው ፈላስፋ ዘርአያዕቆብ፡፡ /ከቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

#ዜና_ዕረፍት ታሪካዊ ነክ በሆኑ ስብከታዊ ትምህርቶቻቸውና ጽሑፎቻቸው እጅጉን የሚታወቁት፤ #ብፁዕ_አቡነ_ገሪማ_(ዶ.ር.) #ሚያዝያ_27_በዕለተ_መድኀኔ_ዓለም_ዐረፉ፤ #የግብዓተ_መሬት_ሥነ_ሥርዐቱም_ረቡዕ_ሚያዝያ_30/2011ዓ.ም. #በቅድስት_ሥላሴ_ቤ/ክ ይካሄዳል፡፡ ከጻፏቸው መጻሕፍት መካከልም፤ *የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየዘመናቱ የሚል መጽሐፍ *ከ30 በላይ የትምህርታዊ ጽሑፎች ያካተተ ስብስብ በ2006 ዓ.ም. የሳተሙት መጽሐፍ *የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ከልደተ ክርስቶስ እስከ ፳፻ በሚለው ድንቅ እስትጉቡእ (ስብስብ) መጽሐፍ ላይ ‹‹የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደርና መንግሥት በየዘመናቱ›› የሚል ጽሑፍ አዘጋጅተዋል፡፡ ብፁዕ አቡነ ገሪማ፣ የተወለዱት በሰሜን ሸዋ በ1937 ዓ.ም. ሲሆን፤ ማዕርገ ዲቁናን ከግብጻዊው አቡነ ቄርሎስ፣ ማዕርገ ምንኵስናን ደግሞ መጋቢት 1973 ዓ.ም. በደብረ ሊባኖስ ገዳም ተቀብለዋል፡፡ በመንፈሳዊ ትምህርት ዜማ፥ ቅኔ፥ አቋቋም ከተለያዩ መምህራን ቀስመዋል፡፡ ዘመናዊ ትምህርታቸውን፤ በሐረር የራስ መኰንን አዳሪ ትምህርት ቤትና የከፍተኛ ኹለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በቅድስት ሥላሴ ትምህርት ቤት ተምረው አጠናቀዋል፡፡ በ1958 ዓ.ም. ለከፍተኛ ትምህርት ከሌሎች አራት የቤተ ክርስቲያን ወጣቶች ጋራ ወደ ሩማንያ ተልከው በታሪክ ትምህርት የማስተርስ ዲግሪ እንዲሁም በነገረ መለኰት የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ተቀብለዋል፡፡ ከጵጵስና በፊት ስማቸው ዶ/ር ግርማ ወልደ ቂርቆስ ነው፡፡ በሓላፊነትና በአገልግሎት ከሠሩባቸው መካከል፣ የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ምክትል አስተዳዳሪና ዋና ጸሐፊ፣ የትምህርት እና ማሠልጠኛ መምሪያ ሓላፊ፣ በብሥራተ ወንጌል ራዲዮ ጣቢያ በመምህርነት ይገኙባቸዋል፡፡ #ጵጵስናን በሦስተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አንብሮተ እድ፣ ሐምሌ 9 ቀን 1973 ዓ.ም. ተቀብለው፤ በሰሜን ሱዳን ካርቱም ኤጲስ ቆጶስነት የተሾሙት ብፁዕ ዶር. አቡነ ገሪማ፣ በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ገዳማት፣ ወደ ኋላም የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ኾነው አገልግለዋል፡፡ #በተለይ በአምስተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ዘመነ ክህነት፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤቱንም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤቱንም (የአመራሩንም የአስፈጻሚውንም) ሓላፊነቶችን ደርበው ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡ እነዚህም የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የልማት እና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን ኮሚሽነር፣ የቅድስት ሥላሴ እና የቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጆች ዲን፣ በመንበረ ፓትርያርኩ የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ቢሮ ዋና ጸሐፊ፣ የምስካየ ኅዙናን መድኀኔዓለም ገዳም ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ፣ የሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ እንዲሁም የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት የውጭ ግንኙነት የበላይ ሓላፊ ሆነው ያገለገሉበበት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ ብፁዕነታቸው ካላቸው መንፈሳዊነትና የዓላማ ጽናት የተነሣ በዕርግና ምክንያት ያጋጠማቸውን ሕመም ተቋቁመው እስከ ማዕዶት ሰኞ ቤተ ክርስቲያንን እያገለገሉ ከቆዩ በኋላ፤ ሕመሙ እያየለባቸው ስለመጣ በቅዱስ ፓትርያርኩ መመሪያ ሰጭነት ሚያዝያ 21 ቀን 2011 ዓ.ም ወደ ባልቻ ሆስፒታል ገብተው ሕክምና እየተከታተሉ ሳለ ሚያዝያ 27 ቀን 2011 ዓ.ም አንቀላፍተዋል፡፡ የብፁዕ አባታችን ቡራኬ ይድረሰን፨