fa
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

رفتن به کانال در Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

کانال Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 382 مشترک است و جایگاه 5 588 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 193 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 382 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 10 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 43 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -3 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 23.36% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 9.42% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 592 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 449 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 23 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 11 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 382
مشترکین
-324 ساعت
-27 روز
+4330 روز
آرشیو پست ها
#የጾመ_ፍልሰታ_ምንባባት_ዘነሐሴ_፮ #የቅዳሴ_ምንባባት † ፩ኛ ቆሮ.፫፥፲-፳፪ ወበከመ ጸጋሁ ለእግዚአብሔር፡፡ † ፩ኛ ጴጥ.፫፥፩-፯ ወከማሁ አንትንሂ አንስት ተኰነና፡፡ † የሐዋ.ሥ.፲፮÷፲፫ ወወፃዕ
#የጾመ_ፍልሰታ_ምንባባት_ዘነሐሴ_፮ #የቅዳሴ_ምንባባት † ፩ኛ ቆሮ.፫፥፲-፳፪ ወበከመ ጸጋሁ ለእግዚአብሔር፡፡ † ፩ኛ ጴጥ.፫፥፩-፯ ወከማሁ አንትንሂ አንስት ተኰነና፡፡ † የሐዋ.ሥ.፲፮÷፲፫ ወወፃዕነ በዕለተ ሰንበት እምአንቀጸ ሀገር፡፡ #ምስባክ_መዝ. ፵፬፥፲፪ ወይሰግዳ ሎቱ አዋልደ ጢሮስ በአምኃ፡፡ ወለገጽኪ ይትመሐለሉ ኵሎሙ አሕዛብ ብዑላነ ምድር፡፡ ኵሉ ክብራ ለወለተ ንጉሠ ሐሴቦን፡፡ (ትርጕም፤ የጢሮስ ልጃገረዶች እጅ መንሻን ይዘው ይሰግዱለታል፤ የምድር ባለጸጎች አሕዛብ ሁሉ በፊትሽ ይማለላሉ፡፡ ለሐሴቦን ንጉሥ ልጅ ሁሉ ክብሯ፡፡) #ወንጌል_ማር.፲፮፥፱-፲፱፤ ወተንሢኦ በጽባሕ በእሑድ ሰንበት፡፡ #ቅዳሴ_ዘእግዝእትነ አው (ግሩም)፡፡ ጐሣዕ ልብየ ቃለ ሠናየ፡፡

#የጾመ_ፍልሰታ_ምንባባት_ዘነሐሴ_፬ #የቅዳሴ_ምንባባት † ሮሜ ፲፪፥፲፮-ፍጻ ወከመዝ ሐልዩ ምስለ ቢጽክሙ፡፡ † ፩ኛ ጴጥ.፭፥፮-፲፪ አትሕቱ እንከ ርእሰክሙ † የሐዋ.ሥ.፲፯÷፳፫ ወበጺሕየ ዝየ ርኢኩ
#የጾመ_ፍልሰታ_ምንባባት_ዘነሐሴ_፬ #የቅዳሴ_ምንባባት † ሮሜ ፲፪፥፲፮-ፍጻ ወከመዝ ሐልዩ ምስለ ቢጽክሙ፡፡ † ፩ኛ ጴጥ.፭፥፮-፲፪ አትሕቱ እንከ ርእሰክሙ † የሐዋ.ሥ.፲፯÷፳፫ ወበጺሕየ ዝየ ርኢኩ ጣዖተክሙ #ምስባክ_መዝ. ፳፥፲፪ እግዚኦ በኃይልከ ይትፌሣሕ ንጉሥ፡፡ ወብዙኀ ይትሐሠይ በአድኀኖትከ፡፡ ፍትወተ ነፍሱ ወሀብኮ፡፡ (ትርጕም፤ አቤቱ በኃይልህ ንጉሥ ደሰታል፤ በማዳንህም እጅግ ተድላ ደስታ ያደርጋል፤ የልቡን ፈቃድ ሰጠኸው፡፡) #ወንጌል_ሉቃስ.፲፬፥፴፩-ፍጻ፤ ወእመኒ ፈቀደ ንጉሥ ይሑር ይጽብአ፡፡ #ቅዳሴ_ዘእግዝእትነ አው (ዘቄርሎስ)፡፡ ጐሣዕ ልብየ ቃለ ሠናየ (ኀቤከ እግዚኦ)

ሳምንታዊ የዐርብ ጕባኤያችን ጾመ ፍልሰታን በማስመልከት ስለ፡፡ #ክብረ_ድንግል_ማርያም በተለያዩ ሊቃውንትና መምህራን›› ትምህርቶች ይሰጣሉ፡፡ የአባ ጊዮርጊስ ድረስት የሆነው #የመሐረነ_አብ_ጸሎት /
ሳምንታዊ የዐርብ ጕባኤያችን ጾመ ፍልሰታን በማስመልከት ስለ፡፡ #ክብረ_ድንግል_ማርያም በተለያዩ ሊቃውንትና መምህራን›› ትምህርቶች ይሰጣሉ፡፡ የአባ ጊዮርጊስ ድረስት የሆነው #የመሐረነ_አብ_ጸሎት /በተለያዩ ገዳማት ከሚደርሱ የመሐረነ አብ ጸሎቶች እንደ ንብ ተቀስሞ የተዘጋጀው/ ይደርሳል፡፡ #140ኛ_ሳምንት_ዐርብ_ነሐሴ_3 /የቀ/ደ/ሰ መድኀኔዓለም ወደ/ት/ቅ/ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት፡፡/

#የጾመ_ፍልሰታ_ምንባባት_ዘነሐሴ_፫ #ነሐሴ_፫#ስምዖን_ዘዓምድ_ወቅድስት_ሶፍያ #የቅዳሴ_ንባብ ፠፩ኛተሰሎ. ፫፥፩-ፍጻሜ ፤ ወሥዒነነ ተዐግሦ አብደርነ ንንበር አቴና፡፡ ፠፩ኛጴጥ. ፫፥፰-፲፭፤ ወዘሰ
#የጾመ_ፍልሰታ_ምንባባት_ዘነሐሴ_፫ #ነሐሴ_፫#ስምዖን_ዘዓምድ_ወቅድስት_ሶፍያ #የቅዳሴ_ንባብ ፠፩ኛተሰሎ. ፫፥፩-ፍጻሜ ፤ ወሥዒነነ ተዐግሦ አብደርነ ንንበር አቴና፡፡ ፠፩ኛጴጥ. ፫፥፰-፲፭፤ ወዘሰ ያፈቅራ ለሕይወት ወይፈቱ ይርአይ ፠ሐዋ.ሥራ ፲፬፥፳-ፍጻሜ፤ ወበሳኒታ ሖረ ምስለ በርናባስ፡፡ #ምስባክ_/መዝ. ፵፬፥፲፪/ ወይሰግዳ ሎቱ አዋልደ ጢሮስ በአምኃ፡፡ ወለገጽኪ ይትመሐለሉ ኵሎሙ አሕዛብ ብዑላነ ምድር፡፡ ኵሉ ክብራ ለወለተ ንጉሠ ሐሴቦን፡፡ #ወንጌል_ሉቃስ.፲፰፥፱-፲፰ ወይቤሎሙ ለእለ ያጽድቁ ርእሶሙ፡፡ #ቅዳሴ_ዘእግዝእትነ_ጐሣዕ_ልብየ_ቃለ_ሠናየ

ሕንጼሃ ለደብረ ጅጅጋ ማርያም፤ (እንኳን ደስ አለን) ልክ የዛሬ ዓመት ሐምሌ ወር ላይ ርኵስ መንፈስ ባደረባቸውና ባነሳሳቸው ሰዎች የጅጅጋ ማርያም መቃጠሏን ዘግበንላችሁ ነበር፡፡ ልክ በዓመቱ ሐምሌ
+3
ሕንጼሃ ለደብረ ጅጅጋ ማርያም፤ (እንኳን ደስ አለን) ልክ የዛሬ ዓመት ሐምሌ ወር ላይ ርኵስ መንፈስ ባደረባቸውና ባነሳሳቸው ሰዎች የጅጅጋ ማርያም መቃጠሏን ዘግበንላችሁ ነበር፡፡ ልክ በዓመቱ ሐምሌ 22 መንፈስ ቅዱስ ባደረባቸውና ባነሳሳቸው ምዕመናንና የሌላም እምነት ተከታዮች አስተዋጽዖ ጭምር ሕንፃዋ ታድሶ ተመርቋል፡፡

#የመጻሕፍት_ማሰባሰቢያ_ሳምንትና_ልዩ_መርሐ_ግብር_ከነሐሴ_1_እስከ_ነሐሴ_11_፡፡ ፠በ1966ዓ.ም. አገልግሎቱን በመጻሕፍት ማስነበብና ማዋስ ለጀመረው አንጋፋ ቤተ መጻሕፍታችን መጻሕፍትን የምናሰባስ
+2
#የመጻሕፍት_ማሰባሰቢያ_ሳምንትና_ልዩ_መርሐ_ግብር_ከነሐሴ_1_እስከ_ነሐሴ_11_፡፡ ፠በ1966ዓ.ም. አገልግሎቱን በመጻሕፍት ማስነበብና ማዋስ ለጀመረው አንጋፋ ቤተ መጻሕፍታችን መጻሕፍትን የምናሰባስብበት ልዩ መርሐ ግብር፡፡ ፠ ከነሐሴ 1 እስከ ነሐሴ 11 የመጻሕፍት ሽያጭና የመጻሕፍት ማሰበብ ይካሄዳል፡፡ #ነሐሴ 11 ዝክረ ቅዱስ ያሬድና ልዩ መርሐ ግብሩ አብሮ ይካሄዳል፡፡ ፠ የመጨረሻ መርሐ ግብሩ #ቅዳሜ_ነሐሴ_11_ቀን_2011_ዓ.ም. ከ11፡30 - 2፡00 ሰዐት በቅዱስ ገብርኤል አዳራሽ ታላላቅ የመጻሕፍት መምህራንና ተጋባዥ እንግዶች በሚገኙበት ይካሄዳል፡፡ ፠#ቅዱስ_ያሬድ_ለቤተ_ክርስቲያናችን_ድንቅና_ዕንቊ_የሆኑ_5ት_መጻሕፍትን_ደርሶ_አብርክቶልናል_እኛስ_ለቤተ_መጻሕፍቶቻችን_ምን_ያህል_መጻሕፍት_አስተዋጽዖ_አድርገናል_??፡፡ ‹‹ስትመጣ …. ይልቁንም በብራና የተጻፉትን አምጣልኝ፡፡›› **ቤተ መጻሕፍታችንን ልዩ ከሚያደርጉት መካከል ማኅበረ ምዕናንንና ማኅበረ ካህናትን ታሳቢ አድርጎ የተደራጀ መሆኑ፡፡

ጾመ ፍልሰታ #ጾም_በሐዲስ_ኪዳን፡- የሐዲስ ኪዳን ጾም ከብሉይ ኪዳን ጾም የተለየ ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን የነበረው ጾም ሥጋዊ ችግርን የሚመለከት ሲኾን፤ በሐዲስ ኪዳን ግን የምንጾመው ለጽድቅ ነው፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተጠመቀ በኋላ የመጀመሪያ ሥራ ያደረገው ጾምን ነው፤ እንደዚሁም ያስተማራቸው ደቀ መዛሙርት ከሥራቸው በፊት ጾምን እንደ ጌታቸው አስቀደሙ፡፡ የሚከተሉት ጥቅሶች በሐዲስ ኪዳን ጾም እንደታዘዘ የሚያመለክቱ ናቸው፡፡ ማር.፱፣፳፱፣ ማር.፪፣፳፣ ማቴ.፮፣፮፣ ሉቃ.፮፣፳፩፣ የሐ.ሥራ.፲፫፣፫፡፡ ስለዚህ ቤተክርስቲያናችን እነዚህን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል አብነት በማድረግ ጾምን በአዋጅ እንድንጾም በቀኖናዋ (በሥርዐቷ) ደንግጋለች፡፡ በቤተክርስቲያናችን የአዋጅ ጾም የሚባሉት ሰባት ናቸው፡፡ እነርሱም፡- 1. ✣ ዐቢይ ጾም (ጾመ ኩዳዴ) 5. ✣ ጾመ ነነዌ 2. ✣ ጾመ ድኅነት (የረቡዕና ዐርብ) 6. ✣ጾመ ጋድ 3. ✣ ጾመ ሐዋርያት (የሰኔ ጾም) 7. ✣ ጾመ ፍልሰታ 4. ✣ ጾመ ነቢያት (የገና ጾም) #ጾመ_ፍልሰታ ፍልሰታ የግእዝ ቃል ነው፤ ፈለሰ ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጕሙም ተለየ፣ ሄደ፣ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ መሄድን ያመለክታል፡፡ ጾመ ፍልሰታ ሐዋርያትን አብነት አድርገን፤ ሐዋርያት የተቀበሉትን በረከት ለማግኘት የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምዕመናን የምንጾመው ታላቅ ጾም ነው። እመቤታችን እንደ ሰው ልማድ ሞትን ትቀምስ ዘንድ ግድ ስለኾነ፤ ጻዕርና ሕማም በሌለበት አሟሟት፤ ዕዝራ በመሰንቆ፥ ዳዊት በበገና እያጫወቷት፤ በተወለደች በ64 ዓመቷ ጥር 21 ቀን በ48 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ አርፋለች። ሐዋርያትም እንደምታርፍ በመንፈስ ቅዱስ ስለተገለጸላቸው ከያሉበት (ከየሀገረ ስብከታቸው) ወደ መኖሪያ ቤቷ (የሐዋርያው ቅድስ ዮሐንስ ቤት) ተሰባስበው ነበር። ነፍሷ ከሥጋዋ እንደተለየች አስከሬኗን ገንዘውና ከፍነው ወስደው ለመቅበር ወደ ጌቴሴማኒ ሲሄዱ አይሁድ ሰምተው መጡና ሐዋርያትን ከበቧቸው። የአይሁድ ተንኮል አስከሬኗን ከሐዋርያት እጅ ቀምተው በእሳት ለማቃጠል ነበር፤ ይህንንም ማድረግ የፈለጉበት ምክንያት፤ የሐዋርያት ትምህርት (የጌታችን ከሞት መነሳትና ለፍርድ ተመልሶ መምጣት)ከአይሁድ አልፎ ዓለም ሁሉ እያመነበት ስለመጣ እመቤታችንም ተነሥታ ዐርጋለች እያሉ ሐዋርያት ያስተምራሉ በሚል ስጋት ነበር። ‹‹የፈሩት ይነግሣል፥ የጠሉት ይወርሳል›› እንዲሉ አበው፤ የእመቤታችን ትንሣኤም ሆነ ዕርገት አይቀሬ ሁኗል። አይሁድ የእመቤታችንን ሥጋ ለመንጠቅ በሞከሩበት ጊዜም ታውፋኒያ የተባለ ጎልማሳ ሰው በጉልበቱና በድፍረቱ በአይሁድ ዘንድ ተመርጦ የእመቤታችንን ሥጋዋ ያረፈበትን ቃሬዛ ከሐዋርያት ነጥቆ መሬት ላይ ለመጣል ሲሞክር፤ የእግዚአብሔር መልአክ በእሳት ሰይፍ ሁሉቱንም እጆቹን ቀንጥሶ (ቆርጦ) ጥሏቸዋል። ነገር ግን ጥፋቱን አውቆ ወዲያው ስለተፀፀተና ይቅርታ ስለጠየቀ በአምላክ ፈቃድ በእመቤታችን አማላጅነት በቅዱስ ጴጥሮስ አማካኝነት እጆቹ እንደገና ተመልሰውለት የእመቤታችንን እመ አምላክነት (የአምላክ እናት መሆኗ)ና ክብርን ለመመስከር በቅቷል። የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋ በመላእክት ተነጥቆ ከተወሰደ በኋላ በገነት ውስጥ በዕፀ ሕይወት ሥር መቀመጡ ከዮሐንስ በስተቀር ለሌሎች ሐዋርያት ለጊዜው ምሥጢር ሆኖባቸው ቆይቶ ነበር። ቆየት ብሎ ግን ሐዋርያው ዮሐንስ ስለእመቤታችን ሥጋ ነገራቸው። ቅዱሳን ሐዋርያትም ለእመቤታችን ካላቸው ክብርና ፍቅር የተነሳ ለምን አልቀበርናትም? ለምንስ የሥጋዋ ምሥጢር ለዮሐንስ ተገልጾ ለኛ ይደበቅብናል? በማለት እያዘኑና እየለመኑ ከጥር 21 አንስተው ለስድስት ወራት ከዐሥር ቀናት ቆይተዋል። ከዚህም በኋላ ከነሐሴ 1 ቀን ጀምረው ሱባዔ ይዘው ለ14 ቀናት እግዚአብሔርን በጾምና በጸሎት ጠየቁት። በመጨረሻም የነገሩትን የማይረሳ፥ የለመኑትን የማይነሳ ልጇ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነሐሴ 14 ቀን ሥጋዋን አምጥቶ ስለሰጣቸው፤ ሳይውሉ ሳያድሩ በዕለቱ በጌቴሴማኒ በታላቅ ክብርና ዝማሬ ቀበሯት። በተቀበረችም በ3ኛው ቀን በነሐሴ 16 ከተቀበረችበት መቃብር ተነሥታ ወዲያውኑ በታላቅ ክብር በመላእክት አጃቢነት ወደ ሰማይ ዐርጋለች። ጥበበኛው ሰሎሞንም “ውዴ እንዲህ ይለኛል ሙሽራዬ ውዴ ሆይ! ተነሺ የእኔ ውብ ሆይ ነዪ አብረን እንሂድ” በማለት አመሣጥሮ የተናገረው በጥበበ እግዚአብሔር ተመርቶ እንደ ክርስቶስ ሆኖ ውዴ ያላት እመቤታችን መሆኗንና ልጇ ተነሥቶ እንደ ዐረገ እሷም መነሣቷንና ማረጓን እንረዳለን። /መሓ.፪፥፲/። እመቤታችን ባረገችበት ጊዜ ሐዋርያው ቶማስ በመንፈስ ቅዱስ ጥበብ በደመና ተጭኖ ከሀገረ ስብከቱ (ሕንድ) ወደ ኢየሩሳሌም ሲመለስ እመቤታችን በመላእክት ታጅባ ወደ ሰማይ ስታርግ ተገናኙ። በዚህ ጊዜ ቶማስ ቀድሞ የልጇን ትንሣኤ ሳላይ አሁንም ደግሞ እርሷን ሳልቀብራት ከትንሣኤዋም ሳልደርስ ቀረሁ ብሎ አዘነ ከደመናው ላይ ሊወድቅም ፈለገ፤ ሆኖም እመቤታችን ዕርገቷን ከእርሱ በቀር ሌሎች አለማየታቸውን ገልጻ አረጋጋችው፤ ዕርገቷንም ለሐዋርያት እንዲነግርና ምልክትና ማስረጃ እንዲሆነው ተገንዛበት የነበረውን ሰበኗን/የከፈን ጨርቅ/ ሰጥታ አሰናበተችው። ቶማስም መሬት ለይ ወርዶ መቀበሯን፣ ትንሣኤዋንና ዕርገቷን ያላወቀ መስሎ ሐዋርያትን ስለ እመቤታችን ሥጋ ጉዳይ ጠየቃቸው፤ እነርሱም ሱባዔ ገብተው እግዚአብሔርን በጸሎት መጠየቃቸውን፣ ከሱባዔያቸው በኋላ የእግዚአብሔር ፈቃዱ ሆኖ ሥጋዋን መላእክት አምጥተው እንደሰጧቸውና እንደቀበሯት አስረዱት። እርሱ ግን ‹‹ሞት በጥር ነሐሴ መቃብር›› እንዴት ሊሆን ይችላል? ሲል ተከራከራቸው። ሐዋርያትም ቶማስን ለማሳመንና ለማሳየት ወደ መቃብሯ ወሰዱት፤ ሆኖም መቃብሯ ባዶ ሆኖ አገኙትና ተደናገጡ፤ በዚህ ጊዜ ቶማስ የሆነውን ሁሉ ገልጾ ለምልክትና ለማረጋገጫ የሰጠችውን ሰበኗን /ተገንዛበት የነበረውን ጨርቅ/ አሳያቸው፤ የራሱን ድርሻም አስቀርቶ አከፋፍሎ ሰጣቸው፤ ዛሬም ካህናት ከእጅ መስቀላቸው ጋር የሚይዙት እራፊ ጨርቅ የሚይዙበት ምክንያት ሐዋርያት የተከፋፈሉት የእመቤታችን ሰበን ምሳሌ ነው። ሐዋርያትም የዕርገቷን ምሥጢር ካመኑ በኋላ ዕርገቷን ለማየት በዓመቱ በተመሳሳይ ሁኔታ እንደገና ከነሐሴ 1 ቀን ጀምረው ለ፪ኛ ጊዜ ሁለት ሱባዔ ገቡ፣ እግዚአብሔርም ልመናቸውን ሰምቶ በነሐሴ ወር በ16ኛው ቀን ጌታችን ሐዋርያትን ወደ ሰማይ አውጥቷቸው እመቤታችንን አግኝተዋት ከሷ ተባርከው በታላቅ ደስታ ወደ ደብረዘይት ተመልሰዋል። በአጠቃላይ የእመቤታችን ለሐዋርያት በተለያዩ ጊዜያት መታየት፣ የሥጋዋና የነፍሷ ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ ፍልሰት ሲባል ከዚህ የተነሣ የነሐሴ ጾም በቤተ ክርስቲያናችን ሥርዐት መሠረት ሐዋርያት ያገኙን በረከት ለማግኘት ጾመ ፍልሰታን እንጾማለን። ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ረድኤት በረከት ይክፈለን፡፡ /የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/ ለሌሎችም እንዲዳረስ የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/publishing_tools/?section=PUBLISHED_POSTS&sort[0]=published_time_descending እንዲሁም የቴሌግራም ገጻችንን https://t.me/medihanaelem

(#እንዲጠይቅላችሁ_የምትፈልጉትን_ጥያቄዎች_በፌስቡክና_ገጻችን_inbox_በቴሌግራም_ላይ_Message_ወይም_በ0922851374_ማሳወቅ_ትችላላችሁ_፡፡) ፌስቡክ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/publishing_tools/?section=PUBLISHED_POSTS&sort[0]=published_time_descending ቴሌግራም፤ FINOTE HIWOT የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት /የቀ/ደ/ሰ መድኀኔዓለም ወደ/ት/ቅ/ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት፡፡/

ልዩ የምክረ አበው መርሐ ግብር፤ ለ4 ሳምንት በተከታታይ ሲሰጥ በቆየው የኦርቶዶክሳዊ የጾታ ትምህርት ላይ ማጠቃለያ በጥያቄና መልስ በሊቃውንት አባቶችና ወንድሞች ትምህርቱና ውይይቱ ይሰጣል፡፡ እንዳያ
+1
ልዩ የምክረ አበው መርሐ ግብር፤ ለ4 ሳምንት በተከታታይ ሲሰጥ በቆየው የኦርቶዶክሳዊ የጾታ ትምህርት ላይ ማጠቃለያ በጥያቄና መልስ በሊቃውንት አባቶችና ወንድሞች ትምህርቱና ውይይቱ ይሰጣል፡፡ እንዳያመልጥዎ!!! እንዳያመልጥዎ!!! #ዐርብ_ሐምሌ_26/2011ዓ.ም. ከቀኑ 11፡30 -2፡00፡፡ (139ኛ ሳምንት የዐርብ ጕባኤ፡፡) በጕባኤው፤ #ስለ_መንፈሳዊ_ሕይወትና_ፈተናዎች #ስለ_እጮኝነት_አመራረጥና_የእጮኝነት_ጊዜ #ስለ_ድንግልና_ሕይወትና_ጋብቻ (#እንዲጠይቅላችሁ_የምትፈልጉትን_ጥያቄዎች_በፌስቡክና_ገጻችን_inbox_በቴሌግራም_ላይ_Message_ወይም_በ0922851374_ማሳወቅ_ትችላላችሁ_፡፡) ፌስቡክ፤ https://www.facebook.com/%25E1%258B%25A8%25E1%2589%2580%25E1%258C%25A8%25E1%258A%2594-%25E1%258B%25B0%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25A8-%25E1%2588%25B0%25E1%2588%258B%25E1%2588%259D-%25E1%2588%2598%25E1%258B%25B5%25E1%258A%2580%25E1%258A%2594%25E1%258B%2593%25E1%2588%2588%25E1%2588%259D%25E1%258A%2593-%25E1%258B%25B0%25E1%2589%25A5%25E1%2588%25A8-%25E1%2589%25B5%25E1%258C%2589%25E1%258 ቴሌግራም፤ FINOTE HIWOT የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት /የቀ/ደ/ሰ መድኀኔዓለም ወደ/ት/ቅ/ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት፡፡/

#ታላቁ_ሰማዕት_ቅዱስ_መርቆሬዎስ፤ የወላጆቹ አገር አስሊጥ የምትባል ስትኾን እርሱ ግን ተወልዶ ያደገው በሮሜ ከተማ ነው፡፡ አያቱና አባቱ ሥራቸው አውሬ ማደን ስለነበር አንድ ቀን እንደልማዳቸው አውሬ ሲያድኑ ከገጸ ከለባት ወገን የሆኑ ሁለት ወንዶች አግኝተዋቸው የመርቆሬዎስን አያት በሉት፡፡ አባቱንም ሊበሉት ሲሉ የታዘዘ መልአክ ከለከላቸው፡፡ ዙሪያቸውንም በእሳት አጥሮ ከበባቸው፡፡ እነርሱም በተቸገሩ ጊዜ ለመርቆሬዎስ አባት ሰገዱለት፡፡ በዚያን ጊዜም እግዚአብሔር ፍጥረታቸውን ወደገራምነት ለወጠውና እንደበጎች የዋሆች ሆነው አብረውት ወደ መንደር ገቡ፡፡ ከዚህም በኋላ ቅዱስ መርቆሬዎስ ተወለደና ስሙ ፒሉፓዴር ተባለ፡፡ የውሻ መልክ ያላቸውም በእርሱ ዘንድ ብዙ ዘመናት ኖሩ፡፡ ከዚህም በኋላ ክርስቲያኖች ሆኑ፡፡ የቅዱስ መርቆሬዎስም ወላጆች አስቀድመው አረማውያን ነበሩና የክርስትና ጥምቀትን በጸጋ ተቀበሉ፡፡ አባቱን ኖህ እናቱንም ታቦት ብለው ሰየሟቸው፡፡ ቀድሞ ፒሉፓዴር የነበረውም ስሙ ተለውጦ መርቆሬዎስ ተባለ፡፡ የውሻ መልክ ያላቸው ግን መልአኩ በተገለጠላቸው ጊዜ እንደነገራቸው ለቅዱስ መርቆሬዎስ አባት የሚታዘዙና የሚያገለግሉ ሆኑ፡፡ ንጉሡም የመርቆሬዎስን አባትና የውሻ መልክ ያላቸውን ዜናቸውን ሲሰማ ወታደሮቹን ልኮ በፊቱ አቆማቸው፡፡ እግዚአብሔርም የቀድሞ ፍጥረታቸውን መልሶላቸው አራዊት አደረጋቸውና ንጉሡን እጅግ አስፈሩት፡፡ ንጉሡም የቅዱስ መርቆሬዎስን አባት የአራዊት ተፈጥሯቸውን ያርቅለት ዘንድ ለመነው፡፡ የቅዱስ መርቆሬዎስም አባት በለመነ ጊዜ ተፈጥሯቸውን መልሶላቸው ገራሞች ሆኑ፡፡ ንጉሡም የመርቆሬዎስን አባት ገዥና የሠራዊቱ አለቃ አድርጎ ሾመው፡፡ የውሻ ፊት ያላቸውም አብረው ያገለግሉት ስለነበር ሁሉም ይፈራው ነበር፡፡ ንጉሡም የመርቆሬዎስን አባት ወደ ጦርነት ከላከው በኋላ ሳይመለስ ስለቀረ ሚስቱን ሊያገባት አሰበ፡፡ የመርቆሬዎስ አባትም የመርዶሳውያን አገሮች ሁሉ ገዢ በነበረው ንጉሥ ተይዞ ቢማረክም ገዥው ክርስቲያን መሆኑን አይቶ አከበረው፡፡ ቆይቶም በሀገሩ ላይ ሾመው፡፡ ሚስቱም ጠፍታ ከሀገሯ ወጥታ ሄዳ ስለነበር ከባሏ ተገናኝተው በዚያው መኖር ጀመሩ፡፡ መርቆሬዎስም አባቱና እናቱ ከሞቱ በኋላ ንጉሡ በአባቱ ፈንታ በመርዶሳውያን አገር ላይ ሾመው፡፡ መርቆሬዎስ መኰንንነት በተሾመም ጊዜ ገጸ ከለባቱ አብረውት ነበሩ፡፡ ለመዋጋትም በወጣ ጊዜ የቀድሞው የአራዊት የሆነ ተፈጥሯቸውን እግዚአብሔር ይመልስለት ስለነበር ማንም አይቋቋመውም ነበር፡፡ ለቅዱስ መርቆሬዎስ ታላቅ የድል አድራጊነት ኃይል ተሰጠውና ዜናው በሁሉም ሀገሮች ተሰማ፡፡ በሮሜ ሀገር ጣዖትን የሚያመልከው ዳኬዎስ የተባለውም ንጉሥ የበርበር ሰዎች ጋር ጦርነት ሊገጥም በወጣ ጊዜ እጅግ ሲበዙበት ፈራ፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስም በጦሩ መሀል የተሳለ ሰይፍ የያዘ የእግዚአብሔርን መልአክ ስላየ ንጉሡን እግዚአብሔር ያጠፋቸዋልና አትፍራ›› አለው፡፡ መልአኩም ሰይፉን ለቅዱስ መርቆሬዎስ ሰጠውና ‹‹ጦርነቱን ድል ባደረግህ ጊዜ እግዚአብሔርን አስበው›› አለው፡፡ ጦርነቱን ድል አድርጎ ሲጨርስም መልአኩ ድጋሚ ተገልጦለት ‹‹ለምን የፈጣሪህን ስም መጥራት እረሳህ?›› አለው፡፡ ከጦርነቱም በኋላ ንጉሥ ዳኬዎስ ለጣዖታቱ ዕጣን በማሳረግ በዓልን አደረገ፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስም በዚያ ስላልተገኘ ለጣዖታቱ ዕጣን በማሳረጉ እንዳልተባበረ ንጉሡ ሲያውቅ መልእክተኞችን ልኮ አስመጣው፡፡ ንጉሡም ‹‹ከእኔ ጋር ለምን አታጥንም?›› ባለው ጊዜ ቅዱስ መርቆሬዎስ ትጥቁንና ልብሱን አውልቆ ከወረወረለት በኋላ ‹‹ክብር ይግባውና አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስን ፈጽሞ አልክደውም፣ ለረከሱ ጣዖቶችህም አልሰግድም›› አለው፡፡ ንጉሡም ተናዶ ልዩ ልዩ በሆኑ ሥቃዮችም እጅግ አሠቃየው፡፡ ንጉሡም ስለ መርቆሬዎስ ብለው የአገሩ ሰዎች እንዳይነሱበት ፈርቶ በብረት ችንካር ቸንክሮ የቀጰዶቅያና የእስያ ክፍል ወደሆነች ወደ ቂሳርያ ከደብዳቤ ጋር ላከው፡፡ በዚያም እጅግ ካሠቃዩት በኋላ ንጉሡ ዳኬዎስ እንዳዘዘ ኅዳር 25 ቀን አንገቱን በሰይፍ ቆረጡትና የሰማዕትነት ተጋድሎውን ፈጸመ፡፡ የሕይወትንም አክሊል ተቀዳጀ፡፡ በዓለሙ ሁሉ አብያተ ክርስቲያናት ታነጹለት፡፡ እግዚአብሔርም ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን በቅዱስ መርቆሬዎስ ስም አደረገ፡፡ ✤ከብዙ ተአምራቱም አንዱ የቂሳርያውን ሊቀ ጳጳስ ባስልዮስን እንዲሁም ጎርጎርዮስን ረድቶ ከሃዲውን ዑልያኖስን የገደለበት ነው፡፡ ዑልያኖስ ነግሦ የክብር ባለቤት ጌታችንን ክዶ ጣዖታትን ማምለክና ክርስቲያኖችን ማሠቃየት ጀመረ፡፡ የቂሳርያው ሊቀ ጳጳስ ባስልዮስም አስተምሮ ሊመልሰው ወደ ንጉሡ ቢመጣ ክብር ይግባውና ዑልያኖስ ጌታችንን ሰድቦ ባስልዮስንም አሰረው፡፡ ባስልዮስም በእሥር ቤት ሳለ በቅዱስ መርቆሬዎስ ሥዕል ፊት ጸለየ፡፡ ሥዕሉም ወዲያው ተሰወረው፡፡ ያንጊዜም ወደ ከሃዲው ንጉሥ ዑልያኖስ ዘንድ ሄዶ በጦር ወግቶ ገደለውና ወዲያው ወደ ቦታው ተመለሰ፡፡ በስዕሉ ላይ ያለው የቅዱስ መርቆሬዎስ ይዞ ከተሳለው ጦር ጫፍ ላይም ደም ይንጠፋጠፍ ነበር፡፡ ቅዱስ ባስልዮስም ከሃዲውን ንጉሥ እንደገደለው ዐውቆ ‹‹የክርስቶስ ምስክር ጌታዬ ሆይ የእውነት ፀር የሆነ ዑልያኖስን ገደልከውን?›› አለው፡፡ ሥዕሉም ያን ጊዜ አዎን እንደሚል ራሱን ዘንበል አደረገ፡፡ ቅዱስ ባስልዮስም ደስ ብሎት እግዚአብሔርን አመሰገነ፡፡ ✤ሌላው ሰማዕት ቅዱስ መርቆሬዎስ በተአምሩ ከእስልምና እምነት መልሶ ክርስቲያን ያደረገው አንድ እስላም ሰው አለ፡፡ ይኸውም የቅዱስ መርቆሬዎስ ቤተ ክርስቲያኑ በተሠራችበት በምስር አገር የሚኖር ከመሳፍንት ወገን የሆነ ወጣት ነበረ፡፡ ከብዙ ሰዎችም ጋር ሆኖ ወደ መሐመድ መቃብር ለመሄድ እንዳሰበ ለአባቱ ሲነግረው ስንቅ ሰንቀው በሰላም ወደ መካ መዲና ሸኙት፡፡ መካ ደርሰውም ሥራቸውም ፈጽመው ወደቤታቸው እየተመለሱ ሰባት ቀን ተጓዙ፡፡ በሌሊትም ሲጓዙ ስለ ሥጋዊ ግዳጁ ያ እስላም ወጣት ከግመል ላይ ወርዶ ለመጸዳዳት ዘወር አለ፡፡ እነርሱም አብሯቸው የሚጓዝ መስሏቸው ስለነበር ባልንጀሮቹም በበረሃው ውስጥ ትተውት ሄዱ፡፡ እርሱም ወዴት እንደሚሄድ ስላላወቀ አራዊትም እንዳይበሉት ፈርቶ እጅግ ደነገጠ፡፡ በዚያም ጊዜ በምስር አገር በአባቱ ቤት አቅራቢያ ያለች የሰማዕቱ የቅዱስ መርቆሬዎስን ቤተ ክርስቲያን አስታውሶ በልቡ ቅዱስ መርቆሬዎስን እንዲያድነው በመለመን ተሳለ፡፡ ወዲያውም ቅዱስ መርቆሬዎስ በፈረሱ ተቀምጦ ወደ እርሱ መጣና ‹‹ከወዴት ነህ? ከዚህ በረሃ ውስጥስ እንዴት ጠፋህ?›› አለው፡፡ ወጣቱ እስላምም የሆነውን ነገረው፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስም ‹‹ና በኋላዬ በፈረሱ ላይ ተፈናጠጥ›› አለውና በአየር ላይ እየበረረ በምስር አገር ወዳለች የቅዱስ መርቆሬዎስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንደ ዐይን ጥቅሻ አደረሰውና እንደተዘጋች በውስጧ አስገባውና ከእርሱ ተሰወረ፡፡ ይህም ወጣት በኋላ አምኖ ተጠምቆ ብዙ ሰማዕትነት ተቀብሏል፡፡ ገዳምም ገብቶ ብዙ ከተጋደለ በኋላ እንደገና ወደ አገሩ ተመልሶ ብዙዎችን ወደ ክርስትና አምጥቷል፡፡ በቅዱስ መርቆሬዎስ ስም ቤተ ክርስቲያን አሠርቶ አበ ምኔትም ሆኖ ብዙ መነኰሳትን አፍርቷል፡፡ /ምንጭ፤ ከገድላት አንደበት/ LIKE & INVITE የፌስ ቡክ ገጻችንን Finote Hiwot ወይም <<የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት››

#ስዕሉ_የሚያሸበሽበው_የቅዱስ_መርቆሬዎስ_ስዕል_፤ በጋሹ አምባ አርማንያ ቅዱስ መርቆሬዎስ (ሰሜን ሸዋ፤ ደብረ ሲና) የሚገኝ፡፡ መርቆሬዎስ መርቆሬዎስ ገባሬ ተአምር፡፡ #ቪዲዮውን_ሁሉም_ሊያየው_የሚገባ_የተዓምር_ተዓምር፡፡ የቻላችሁ በአካል ሰሜን ሸዋ (የ100ብር የትራንስፖርት መንገድ ነው) ሂዳችሁ፤ ያልቻላችሁ ቪዲዮውን እንድታዩት አቅርበንላችኋል፤ ዛሬም ድረስ ተዓምር አድራጊውና በበዓለ መርቆሬዎስ እለት የሚያሸበሽበው የቅዱስ መርቆሬዎስ ስዕል፤ (ቀድሞም ባስልዮስና ጎርጎርዮስ ዑልያኖስ የሚባል ጠላት ሲመጣባቸው ወደ ቅዱስ መርቆሬዎስ ስዕል ጸለዩ፤ ቅዱስ መርቆሬዎስም ከስዕሉ ላይ ወጥቶ ዑልያኖስን ገደለላቸው)፤ ዛሬም ድረስ የቅዱስ መርቆሬዎስ ስዕል ተዓምራትን ያደርጋል፡፡ በጻድቃን ሰማዕታት፤ በመላእክት በእመቤታችን ላይ አድሮ እግዚአብሔር እንደሚመሰገን አስተውሉ፡፡ ✣✤✣ #ቅዱሳት_ሥዕላት_በቅዱሳት_መጻሕፍት -‹‹የስርየት መክደኛ ስራ ፣ ሁለት ኪሩቤልን ከተቀጠቀጠወርቅ ስራ፣ በምስክሩ ታቦት ላይ በሁለቱ ኪሩቤል መካከል መክደኛውም ላይ ሆኜ አነጋግርሃለሁ፡፡›› ዘጸ25፣18-22፤ 37፣7-9 -በቅድስቲቱና በቅድስተ ቅዱሳኑ መካከል መለያ በሆኑት መጋረጃዎች “ብልህ ሠራተኛ እንደሚሠራ ኪሩቤልን አድርጉባቸው” ዘጸ 26፥31፤ 36፣ 8-35፡፡ -እግዚአብሔር ማዘዝ ብቻ ሳይሆን በጥበብና በማስተዋል መንፈሱን እንደመላባቸው፤ የኡሪ ልጅ ባስልኤል፥ የአሂዳምኒክን ልጅ ኤልያብን ዘጸ 31:1-6 -‹‹እስከ መነነቶ ሜልኮል ቅድመ ታቦተ ሕግ ከመ ዘፈነ፣ንጉሠ እስራኤል ኪያኪ ዘጸገየ ሥነ፣ቅድመ ሥዕልኪ ድንግል እዘፍን አነ. . .፤ የዓለም የድኅነት ጌጥ የሆነ ጌታን የወለድሽ እመቤታችን ሆይ አንቺን ያስገኘ የእስራኤል ንጉስ ዳዊት ሚስቱ(ሜልኮል) እስከምትንቀው ድረስ በእግዚአብሔር የቃልኪዳን ታቦት ፊት እንዳመሰገነ እኔም በሥዕልሽ ፊት ቆሜ እዘምራለሁ፤. . .›› ‹‹ኢየኀፍር ቀዊመ ቅድመ ሥዕልኪ ወርኀ ጽጌረዳ አመኀ ኀልቀ . . .፤ማርያም ሆይ የጽጌረዳ ፣የአበባ ወራት ባለፈ ጊዜ ብዙ ምስጋናሽን ሳመሰግን በሥዕልሽ ፊት መቆምን አላፍርም፣ ስምሽን መጥራት የወደቀውን ያነሣል ፣ ኀጥኡንም ጻድቅ ያደርጋልና።›› /አባ ጽጌ ድንግል/ LIKE & INVITE የፌስ ቡክ ገጻችንን Finote Hiwot ወይም <<የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት››

#ወርኀ_ሐምሌ_የሰማዕታት_መታሰቢያ_ወር (ሐምሌ 5 ጴጥሮስና ጳውሎስ፤ ሐምሌ 15 ቂርቆስና ኢየሉጣ፤ ሐምሌ 24 አባ ኖብ ድንግል፤ ሐምሌ 25 መርቆሬዎስ) #ሐምሌ_፳፭_የምናከብረው_ክብረ_በዓል፤ ፨ ታላቁ ሰማዕት (‹‹ካልዕ ሊቀ ሰማዕታት››) ቅዱስ መርቆሬዎስ(ፒሉፓዴር) ዓመታዊ የዕረፍት በዓሉ 1. ✤ታላቁ ሰማዕት ቅዱስ መርቆሬዎስ ልደቱ ሲሆን ድንቅ ተአምር ያደረገበትና ቅዳሴ ቤቱም በዚሁ ዕለት ነው፡፡ እንዲሁም በሐምሌ 25 ዓመታዊ በዓላቸው የኾነ ቅዱሳንም የሚከተሉት ናቸው፡፡ 2. ✤ዳግመኛም ዛሬ ከበሬ ጋር ተጠምደው ሰማዕትነት የተቀበሉት የኢትዮጵያዊው የአቡነ ሕፃን ሞዐ ዕረፍታቸው ነው፡፡ 3. ✤የነቢዩ ሄኖክ ዕርገቱ ነው፡፡ 4. ✤የቅዱስ ጳውሎስ ረዳት የነበረችው የሰማዕቷ የቅድስት ቴክላ ዕረፍቷ ነው፡፡ 5. ✤ሰማዕቱ ቅዱስ ዱማድዮስ ዕረፍቱና ፍልሰተ ሥጋው ነው፡፡ 6. ✤ሰማዕቱ ቅዱስ አበከረዙን ዕረፍቱ ነው፡፡ 7. ✤ሰማዕቷ ቅድስት ኢላርያ ዕረፍቷ ነው፡፡ 8. ✤ሰማዕታቱ ቅድስት ቴክላ እና ቅድስት ሙጊ ዕረፍታቸው ነው፡፡ 9. ✤ሰማዕቱ ቅዱስ እንዲኒና ዕረፍቱ ነው፡፡ 10. ✤ሰማዕቱ አቡነ ይስሐቅ ዕረፍቱ ነው፡፡ 11. ✤የ600 ሰማዕታት መታሰቢያቸው በዓላቸው ነው፡፡ 12. ✤እንዲሁም ዛሬ የ25 ሺህ የአትሪብ ሰማዕታት መታሰቢያቸው ነው፡፡ #በሃገራችን_ከሚገኙ_የቅዱስ_መርቆሬዎስ_ክብረ_በዓል_ከሚከብርባቸው_ዋነኞቹ፡፡ ✥1. ደብረ ጽባሕ ጸዶየ መርቆሬዎስ፤ በአጼ ይኵኖ አምላክ ዘመን የተመሠረተ፡፡ ✥2.ደረስጌ ደብረ ጽዮን ማርያም፤ ‹‹ደጃች ውቤ ደረስጌ ደብረ ጽዮንን በወርቅና በዕንቊ ከመሥራታቸውም በላይ ታቦተ መርቆሬዎስን ማምጣታቸው ተብሎ የሚነገርለት›› ተዓምር አድራጊ ስዕል የሚገኝበት ቤ.ክ (ዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ የነገሠበት)፤ ራስ ደጀን አጠገብ፤ ጃናሞራ (መካነ ሰላም ከተማ) ✥3. ጎንደር ደብረ ፀሐይ ቊስቋም ማርያም፤ የቅዱስ መርቆሬዎስ ታቦት ከጥንት ጀምሮ በድርብነት አለ ✥4. ጋሹ አምባ አርማንያ ቅዱስ መርቆሬዎስ (ሰሜን ሸዋ፤ ደብረ ሲና)፤ ስዕሉ በበዓለ መርቆሬዎስ ቀን የሚያሸበሽበው፡፡ ✥5. ደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኡል (አ.አ)፤ የቅዱስ መርቆሬዎስ ታቦት ከጥንት ጀምሮ በድርብነት አለ ✥6. ደብረ ሲና ቅ.እግዚአብሔር አብ(አ.አ)፤ የቅዱስ መርቆሬዎስ ታቦት ከጥንት ጀምሮ በድርብነት አለ ✥7. አዲስ አበባ ጎፋ ደብረ መዊዕ ቅዱስ መርቆሬዎስ ወዮሐንስ መጥምቅ ቤ.ክ (በአዲስ አበባ በመርቆሬዎስ ስም የጠሰየመ ብቸኛው ቤ.ክ.) LIKE & INVITE የፌስ ቡክ ገጻችንን Finote Hiwot ወይም <<የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት››

‹‹ ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተ ክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡›› ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት በወርኀ ሐምሌ ፯/፳፻፲፩ ዓ.ም. ጋብቻህን በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም የፈጸምከው የሰ/ት/ቤታችን አባል ወንድማችን፤ #ተስፋዬ_ለገሠ_ከመልካም ጋር የፈጸማችሁትን ጋብቻ፤ የይስሐቅንና የርብቃን ጋብቻ የባረከ አምላክ፤ የትዳር ሕይወታችሁን ይባርክላችሁ፥ ያጣምራችሁ፥ ያዋሕዳችሁ፤ እመብርሃን በአማላጅነቷ አትለያችሁ፤ ቅዱስ ገብርኤል ከፊት ይምራችሁ ከኋላ ይከተላችሁ፡፡ ✤ ‹‹ጌታን እንዲወዱና በአካልም ይሁን በመንፈስ በባሎቻቸው ደስ እንዲሰኙ ለእህቶች ንገራቸው፡፡ ልክ እንደዚሁ ጌታ ቤተ ክርስቲያንን እንደወደደ ሚስቶቻቸውን እንዲወዱ ለወንድሞች በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ንገራቸው፡፡›› ቅዱስ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ ለፖሊካርፐስ በላከው መልእክቱ ✤ ከተጋባችሁ በኋላ ባልና ሚስት አንድ አካል ናችሁ እንጂ ሁለት ስላይደላችሁ በፍጹም ልባችሁ እርስ በእርሳችሁ ተፋቀሩ፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ሌላ ወንድ ወይም ሌላ ሴት አትፈልጉ ይልቁንም በተቻላችሁ መጠን አንዳችሁ ሌላውን ደስ አሰኙ፤ በመረዳዳትና በፍጹም ፍቅር ኑሯችሁን ሁሉ አሳምሩ፡፡>> ኢትዮጵያዊው ፈላስፋ ዘርአያዕቆብ፡፡ /ከቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/