fa
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

رفتن به کانال در Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

کانال Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 380 مشترک است و جایگاه 5 588 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 193 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 380 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 10 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 43 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -3 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 23.36% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 9.42% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 592 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 449 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 23 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 11 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 380
مشترکین
-324 ساعت
-27 روز
+4330 روز
آرشیو پست ها
ሥርዐተ ማኅሌት ዘወርኀ ጽጌ (‹ዘላይ ወዘታች› ቤት) (#፪ኛ_ዙር_ዓመት_፫ኛ-ሳምንት_ዘጥቅምት_፲፮) በዓለ ኪዳነ ምሕረት፡፡ ✤ ልዩ አዋጅ ዘወርኃ ጽጌ ✤  የማኅሌቱ ሥርዐት የላይ ቤት (የጎንደር መካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም አብነት) እና የታች ቤት (የጎንደር ደብረ ኀይል ዑራኤል ወደብረ ጥበብ በዓታ ለማርያምን አብነት) የሚያደርግ ሲኾን፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ የማኅሌት ቁመትም የላይ ቤትን አብነት የተከተለ ሲኾን፤ የዚቁ ወረብ ግን የደብሩን የራሱን (የሸዋን) የተከተለ ነው፤  የላይ ቤት ቁመት የሚቆሙ አድባራት ዘግምጃ ቤት የሚለውን እንዲከተሉ፤ የታች ቤትን ቁመት የሚቆሙ አድባራት ዘበዓታ የሚለውን እንዲከተሉ እያሳሰብን፡፡ የዚቁ ወረብን ግን የቀጨኔ ደብረ ሰላም የቤቱን ቀለም አስቀድመን ቀጥሎ ደግሞ ዓዲ (ወይም) በማለት የጎንደርን ስላስቀመጥነው እንደ ደብራችሁ ይትበሃል መርጣችሁ እንድትጠቀሙበት ኹሉንም አስቀምጠነዋል፡፡ #የጥቀምት_16_የማኅሌተ_ጽጌ_ወረቦች_፤ በሊቀ ጕባኤ ደምፀ አንበርብር፣ በሊቀ ጠበብት ኤርምያስና በደብራችን ሊቃውንት፡፡ 3.1. ቀስተ ደመና ማርያም keste demenna maryam 2) 2 ናሁ አስተርአየ 3.2. ትመስል እምኪ ማርያም timesil emeki 3.3. እምኵሉ ዕለት ሰንበተ አክበረ emkulu elet senbete akbere 3.4 ንዒ ርግብየ(፪) ምስለ ሚካኤል (እንዘ ተሐቅፊዮ 3ኛ ሳምንት) 3.5 ፀምር ፀዓዳ ዘምንክር አዳዊት (የደብራችን ዜማ፤ ወደፊት የሚጫን) 3.6 ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ(፪) እምዕንቈ ባሕርይ 3.7.1 ነገሥት ይትቀነዩ ለኪ(የደብራችን ዜማ፤ ወደፊት የሚጫን) 3.7.2.1. ይትባረክ ጽጌኪ ማርያም yitbarek tsgeki 1 3.7.2.1. ይትባረክ ጽጌኪ ማርያም yitbarek tsgeki 2 3.8.1. ብክዩ ኅዙናን ሐልየክሙ ስደታ bikiyu hizunan 1 3.8.2. ብክዩ ኅዙናን ሐልየክሙ ስደታ bikiyu hizunan 2 በሚከተለው የቴሌግራም አድራሻችን ያገኛሉ፤ https://t.me/medihanaelem (በእኛ ደብር ብቻ ያሉ ቀረጻዎችን ብቻ እንዳይሆኑብን፤ በየደብራችሁ ያሉትን በድምፅ የተቀዱ ሥርዐተ ማኅሌቶችን በውስጥ መስመር ብትልኩልን ደስ ይለናል፡፡)

ጥቅምት 14፤ ሥርዐተ ማኅሌቱን እነሆ ብለናል፤ በተለይም በደብራችን የሚባሉትን የደብሩን ቀለሞች (ወረቦች ጭምር አካተን አቅርበንላችኋል፡፡) ቅዱስ ገብረክርሰቶስ በዓለ እረፍቱ፤ በጋዛ ምድር ኢትዮጵያ
+7
ጥቅምት 14፤ ሥርዐተ ማኅሌቱን እነሆ ብለናል፤ በተለይም በደብራችን የሚባሉትን የደብሩን ቀለሞች (ወረቦች ጭምር አካተን አቅርበንላችኋል፡፡) ቅዱስ ገብረክርሰቶስ በዓለ እረፍቱ፤ በጋዛ ምድር ኢትዮጵያዊውን ጃንረባ ባኮስን ያጠመቀው ረድኡ ሐዋርያ ቅዱስ ፊሊጶስ ዕረፍቱ ነው፡፡ አቡነ አረጋዊ የተሠወሩበት፤ ቅዱስ ሙሴ እግዚአብሔር በዓለ ዕረፍታቸው ነው፡፡

#ሰበር_ዜና_ቅዱስ_ሲኖዶስ_መደበኛ_ስብሰባውን_አቋረጠ_፤ ለ3ት ቀናት (ከጥቅምት 13-16) በጸሎት፣ በምሕላና ሐዘን ስለ ሀገር ሰላም ሁላችንም በአንድነት ለአምላካችን እንድንጸልይ ትዕዛዝ አስተላልፏ
+2
#ሰበር_ዜና_ቅዱስ_ሲኖዶስ_መደበኛ_ስብሰባውን_አቋረጠ_፤ ለ3ት ቀናት (ከጥቅምት 13-16) በጸሎት፣ በምሕላና ሐዘን ስለ ሀገር ሰላም ሁላችንም በአንድነት ለአምላካችን እንድንጸልይ ትዕዛዝ አስተላልፏል፡፡ ፠ በዓመት 2ት ጊዜ ከሃገር ውስጥና ከውጭ ያሉ ጳጳሳት የሚሳተፉበት የቅ/ሲኖዶስ ምልዓተ ጕባኤ (በጥቅምት 12 በሐዋርያው ቅ/ማቴዎስ በዓለ ዕረፍትና በርክብ ካህናት /ትንሣኤ በዋለ በ25ኛው ቀን/ የሚደረግ ሲሆን)፤ የ2012 ዓ.ም. ስብሰባውን ትናንት የጀመረ ቢሆንም በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ስብሰባውን አቋርጧል፡፡ ፠ ቤተ ክርስቲያንና ምእመናን፣ የአክራሪዎች እና ነውጠኞች ሰለባ እየኾኑ፤ እየተቃጠሉና እየተገደሉ፤ አስከፊ እልቂት እያንዣበበባቸው፤ አንሰበሰብም፥ ልጆቻችን ያሉበት ሔደን እዚያው አብረን እንቃጠላለን፥ እንሞታለን፡፡ /ብፁዓን አባቶች/ ፠ ቅ/ሲኖዶስ ዛሬ ኀሙስ፣ ጥቅምት 13 ቀን 2012 ዓ.ም. ረፋድ ላይ፣ በወቅታዊ አገራዊ ጉዳይ አስቸኳይ መግለጫም ሰጥቷል፡፡ በመግለጫውም፤ ፠ ሐሰተኛ ትርክቶች (ምክንያታዊ ባልኾኑ ጉዳዮች መነሻነት፤ ከእውነታ የራቁ፣ የሕዝቡን የአንድነትና የአብሮነት ባህል የሚጎዱ፣ ታሪክን የሚያፋልሱ)፤ የጸጥታ ኀይሎች ቅድመ ግጭትን መሠረት ያደረገ መከላከል ላይ ትኩረት ባለመስጠታቸውም ለግጭት መንሥኤ በመሆናቸውና ግጭቶች እየተስፋፉ ይገኛል፡፡ ፠ የፖለቲካ ኀይሎች፣ የብዙኀን መገናኛዎች፣ የሶሻል ሚዲያው ተጠቃሚዎች እንዲሁም ምሁራንና የመንግሥት የሥራ ሓላፊዎች፣ ብሔርንና ሃይማኖትን መሠረት ካደረጉ የትንኮሳ ቃላት ተቆጥበው፣ ከልዩነትና ግጭት ይልቅ ለሀገራዊ አንድነትና ተግባቦት የድርሻቸውን እንዲወጡ ቅ/ሲኖዶስ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡ የአባቶቻችን አምላክ ስለ አባቶቻችን ብሎ በመልካም መንገድ ይምራን፡፡ (የቀጨኔ ደ/ሰ/መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ.ክ. ፍኖተ ሕይወት)

#ሐዋርያው_ቅዱስ_ፊልጶስ_ ** በጋዛ ምድር ኢትዮጵያዊውን ጃንረባ ባኮስን ያጠመቀው ረድኡ ሐዋርያ ቅዱስ ፊልጶስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ✤ ለእኛ ለኢትዮጵያውያን ባለውለታችን (በእግዚአብሔር ፈቃድ ሰማያዊውም
+3
#ሐዋርያው_ቅዱስ_ፊልጶስ_ ** በጋዛ ምድር ኢትዮጵያዊውን ጃንረባ ባኮስን ያጠመቀው ረድኡ ሐዋርያ ቅዱስ ፊልጶስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ✤ ለእኛ ለኢትዮጵያውያን ባለውለታችን (በእግዚአብሔር ፈቃድ ሰማያዊውም ሆነ ምድራዊውን ውለታ የዋለልን) የኾነውና ለመጀመሪያ ጊዜ በሐዲስ ኪዳን የእግዚአብሔርን ቃል የተናገረን፤ የክርስትና ጥቀምት አባትና አጥማቂያችን ከ72ቱ አርድዕት አንዱ የኾነው ቅዱስ (ሐዋርያው) ፊልጶስ #በሀገራችን__ብቸኛ_በኾነውና በአ.አ ኮልፌ አጠና ተራ በሚገኘው ቤ.ክ. #ደብረ_ምጥማቅ-ቤ.ክ በዓለ ዕረፍቱ ይከበራል፡፡ " እነሆ በውሀ እንዳልጠመቅ የሚከለክለኝ ምንድነው? " የሐዋርያት ሥራ ፰÷፴፮ **በኢትዮጵያ ብቸኛ የሆነውና በአዲስ አበባ የሚገኘው ደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ቤ.ክ የተመሠረተው በ3ኛው ፓትርያርክ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ሲሆን፤ የቅዱስ ፊልጶስ ክብረ በዓል በዓመት 2ት ጊዜ ነው፤ #ጥቅምት 14 በዓለ ዕረፍቱ #የካቲት 20 ቅዳሴ ቤቱ ነው ‹‹የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሩአችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ፥ የኑሮአቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታቸው ምሰሉአቸው።"ዕብ. 13፥7 ፠፠፠ ‹‹ደብሩሰ ለቅዱስ ፊልጶስ ትመስል ደብረ ሲና፤ ወሀደረ ላዕሌሃ እግዚአብሔር ሐፁር የዐውዳ ወጽጌረዳ በትምዕርተ መስቀል፡፡›› #አድራሻ_- ኮልፌ አጠና ተራ ወደ፡ሎሚ ሜዳ በሚወስደው መንገድ ኢንዱስትሪ መንደር ሳይደርሱ ፠1. ከመርካቶ በባስ ቁጥር 69 ጠሮ በሚወስደው መንገድ፣21 ልኳንዳ ወርደው ወደ ቀድሞ 04 ቀበሌ ፠2. ከአየር ጤና እና ዙሪያው በባስ ቁጥር 87 አጠና ተራ ወርደው የቀለበት መንገድ የእግረኛ መሻገሪያ ተሻግረው ባለው አስፋልት ቀጥታ በመሄድ ያገኙታል ፠3. ከቡራዩ አስኮ አካባቢ ለምትመጡ በባስ ቁጥር 28 አጠና ተራ ወርደው በቀኝ በኩል ባለው አስፋልት ቀጥታ በመሄድ ያገኙታል

#ዳሕምሞ_ #ደብረ_ዳሞ_ መላእክትም ለአረጋዊ እንደባልንጀራ አንደ ጓደኛ ሆኑት፤ እሳቸውን ለመጐብኘትና በረከት ለማግኘት አባቶች ብቻ ሳይሆኑ ንጉሡ አጼ ገብረመስቀልም ወደእሳቸው ይመጣ ነበር፡፡ እሱም እሰከዛሬ ምስክር ሁኖ የሚገኘውንና በእመቤታችን ስም የተሰየመውን ድንቅ ገዳም ሲያንጽ ለእንሳሳቱ መመላለሻ እንዲሆን ተራራን አሠራ፤ ሕንጻው ቅዱስ ያሬድ በተገኘበት ተመረቀች፤ ኋላ ግን ንጉሡ ከአረጋዊ ተባርኮ ሲመለስ ‹‹ተራራውን ላፍርሰው፤ ወይስ ልተወው?›› አለ፤ አቡነ አረጋዊም በግዕዙ ‹‹#ዳሕምሞ_›› አሉት፡፡ በአማርኛ ቋንቋ ‹‹የሰራኸውን ደረጃ ናደው ፥ አፍርሰው እንጂ አትተወው›› ማለት ነው፡፡ በዚህም ምክንያት አካባቢው ዳሞ ገዳሙ ደግሞ ደብረዳሞ ተባለ፡፡ አቡነ አረጋዊም ንጉሡን ‹‹ስለዘንዶው ጅራት ፈንታ ሰዎች ይወጡበት ዘንድ ገመድ አብጅ፡፡ ለልጅ ልጅ መታሰቢያ እንዲሆንና ይህን ድንቅ ሥራ እያየ በፍጥረቱ ሁሉ አንደበት እግዚአብሔር ይመሰገን ዘንድ፡፡›› አሉት፤ ለመወጣጫ ይሆን ዘንድ ገመድ ተሰራለት፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ገመዱ የታሠረበት ግንድ እስካሁን ከ1500 ዓመታት በላይ አለ፤ ኋላ በ13ኛው ክፍለ ዘመን ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ለ12 ዓመታት በደብረ ዳሞ ቆይተው በዚሁ ገመድ ሲወርዱ ነው ሰይጣን ቀንቶ ገመዱን ቢበጥስባቸው እግዚአብሔር አምላክ ክንፍ የሰጣቸው፡፡ ደብረዳሞ ዙርያው ገደል ሆኖ የጠረጴዛ ቅርጽ ያለው ያለው አምባ ሲሆን 500*1000 ሜትር የሚሆን ስፋት አለው፡፡ ከባህር ወለልም በላይ 2216ሜ. ከፍ ይላል፡፡ ወደ ገዳሙ መውጣት አና መውረድ የሚቻለው 16ሜ. በሚረዝመው በአምሳለ ዘንዶ በተሰራው ገመድ ብቻ ነው፡፡ ንጉሡም ከተራራው እንደወረደ እንደታዘዘው አፈረሰ፡፡ አሁን የምናየው ዓይነት ገመድንም አዘጋጅቷል፤ የገመዱም ስመ ‹‹ዘንዶ›› ይባላል፡፡ በዚህ ገዳም ሴቶች በአፀደ ሥጋ እያሉ አይገቡም፤ ካረፉ በኋላ ግን እንደ አባ ጳኩሚስ ገዳምና ሥርዓት ከተከዜ ማዶ ከሚኖሩ የሴት መነኮሳት መካከል አንዲቱ የሞተች እንደሆነ ወደ ወንድሞች መነኰሳት አምጥተው በነሱ ዘንድ በሚገኘው የመቃብር ቦታ ይቀብሯቸው ነበር፡፡ በዚህም የተነሳ የአቡነ አረጋዊ እናት የነበረችው ልጂ በሕፃንነቱ ሳለ መመንኰሱን አውቃ ከልጇ ሕይወቱን ተምራ ገና ከመጀመሪያ ወደ አባ ጳኵሚስ ገዳም ሄዳ መንኵሳ ነበርና በቅድስና በትሕትና ደናግሉ በፍቅር ስታስተዳድር ኖራ መንፈሳዊ ግዳጇን በጐ አገልግሎቷን ፈጽማ ጥር 4 ቀን ስታርፍ ለመቀበሪያዋ ይሆን ዘንድ አባታችን አቡነ አረጋዊ ባሰራላት አዲስ መቃብር ተቀብራለች፡፡ /ከቀ.ደ.ሰ መድኀኔ ዓለም ወደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ. ፍኖተ ሕይወት ሰሌዳ መጽሔት የተወሰደ::/

፠*፠ #አቡነ¬_አረጋዊ (#ዘሚካኤል)#ወቅዱስ_ሙሴ_ብእሴ_እግዚአብሔር #አቡነ¬_አረጋዊ (#ዘሚካኤል) ትውልዳቸው ሮም ሲሆን እግዚአብሔርን ከሚፈሩ ከአባታቸው ይስሐቅና ከእናቸው እድና የተገኙ የቅዱሳን ፍሬ ናቸው፤ ወንድሞቹም ቴዎድሮስ እና ገብረ አምላክ ይባላሉ፡፡ የቀድሞው ስማቸው ዘሚካኤል ነበር፡፡ “አረጋዊ” የተባሉት ኢትዮጵያ ከመጡ በኋላ ነው፡፡ በእድሜ ልጅ ሲሆኑ በመንፈሳዊ ሕይወታቸውና ሥራቸው አዋቂ ስለነበሩ አረጋዊ ብለዋቸዋል፡፡ ወላጆቻቸው ቅዱሳት መጻሕፍትን እያስተማሩ አሳደጉት፤ እሱም በመንፈስ ቅዱስ ኀይል እየጸናና እየበረታ ሄደ፡፡ ዕለት ዕለት ጧትና ማታም ወደቤተክርስቲያን እየሄደ ጸሎት ከመጸለይ አያቋርጥም ነበር፡፡ እድሜውም ለጋብቻ ሲደርስ አባትና አናቱ ያገባ ዘንድ ሚስት አጩለት፡፡ እሱ ግን ፈጽሞ እምቢ አለ፤ ከሕፃንነቱ ጀምሮ በመንፈስ ቅዱስ እየተቃኘ የምንኵስና ሕይወትን ለመኖር ፈልጓልና፡፡ ከብዙ ዘመንም በኋላ የምንኵንስና ሕይወትን ለመኖር ወደ አባ ጳኩሚስ ዘንድ ሄደ፤ ወደ ገዳሙም በገባ ጊዜ አንድ መነኵሴ አገኙትና ‹‹ልጄ ሆይ ከወዴት መጥተሃል እነሆ አንተ ሕፃን እንደሆንክ እመለከታለሁና›› አሉት፡፡ እሱም አመጣጡ ከሮም እንደሆነና ከአባ ጳኵሚስ ዘንድ የሚፈልገው ነገር እንዳለ ነገራቸው፡፡ እሳቸውም ነገሩን ከሰሙ በኋላ ወደ አባ ጳኩሚስ ዘንድ ወሰዱት፡፡ አባ ጳኩሚስም በአየው ጊዜ ከመንበሩ ተነስቶ በፍፁም ፍቅር አቅፎ ሳመው የእግዚአብሔር ጸጋ በእሱ ላይ አድሯልና፡፡ ከዚያም ቀጥሎ ስለምን ጉዳይ ወደ እሱ እንደመጣ ጠየቀው፡፡ አባ ዘሚካኤልም ‹‹እንደአንተ እንደ አባቴ መነኵሴ እሆን ዘንድ መጥቻለሁ›› አለው፡፡ አባ ጳኩሚስም ‹‹ልጄ ሆይ አንተ የንጉሥ ልጅ እንደመሆንህ መጠን የመንግሥቱ ወራሽ ነህና መንኵሰህ ለመኖር እንደምን ይቻልሃል?›› ሲል መለሰለት፡፡ አባ ዘሚካኤል ግን የምድር መንግሥት ኀላፊ ጠፊ እንደሆነ ያውቃልና ከዓለም ንግሥና ይልቅ ዘለዓለማዊ መንግሥትን ይወርስ ዘንድ እንደሚሻ ያመነኵሰውም ዘንድ አጥብቆ ጠየቀው፡፡ አባ ጳኩሚስም ፈተናን ፈትኖት መቋቋም የሚችል ከሆነ እንደሚያስገባው ነግሮ የተለያዩ ፈተናዎችን ፈትነው፡፡ አባ ዘሚካኤልም የተባለውን የታዘዘውን ሁሉ በትጋት ፈጸመ፡፡ አባ ጳኵሚስም ስለሃይማኖቱ ጽናት ስለጠባይና ስለቅንነቱ እጅግ አድርጐ ወደደው፡፡ ከዚያም አስኬማው ወይም ቆቡ ላይ ወደ እግዚአብሔር ጸልዮ አመነኰሰው፤ ስሙንም ዘሚካኤል ብሎ ጠራው፤ በዚህ ጊዜ እድሜው 14 ዓመት ነበር፡፡ አባ ዘሚካኤል አስኬማ ካደረገ በኋላም በታላቅ ትጋቱ በጸሎቱና በጾሙ አባ ጳኵሚስ ተደነቀ፡፡ ስለሱም ዝናው በየሀገሩ ሁሉ እስከ አባቱ አገር ሮም ድረስ ተሰማ፡፡ አባ ዘሚካኤል ገና በሕፃንነቱ የምንኵስና ማዕረግ መቀበሉን ከሰሙ በኋላ ወደ እሱም 8 ቅዱሳን የመጡ ነበሩ፡፡ እነሱም፦ አባ ሊቃኖስ ከቁስጥንጥንያ፣ አባ ይምዓታ ከሀገረ ቁስያ፣ አባ ገሪማ ከሮም፣ ከአንፆኪያ አባ ድሕማ፣ ከቂልቅያ አባ ጉባ፣ ከእስያ አባ አፍጼ፣ ከሮሚያ አባ ጴንጠሌዎን፣ ከቂሳርያ አባ አሌፍ ነበሩ፡፡ እነሱም አባ ጳኵሚስ የምንኵስናውን አፅፍ አጐናፀፏቸውና አመነኮሷቸው፡፡ ለእያንዳንዳቸውም ስማቸውን ሰየሟቸው፡፡ እኒህም አባቶች ስለትዕግስት፣ አርምሞ፣ ትህትና፣ ስለሥርዐተ ማኀበር አመሠራረት ከአባ ጳኵሚስ ዘንድ ተማሩ፡፡ ከዚህ በኋላ በዚያ ገዳም ለብዙ ዓመታት በፍቅር በአንድነት ከአባ ቴዎድሮስ ጋር ተቀመጡ፡፡ በዚህን ጊዜ ግን አባ ጳኩሚስ አርፈው አባ ቴዎድሮስ ተተክተው ነበር፡፡ እነዚህም አባቶች ወደየሃገራቸው ሄደው ማስተማርና ሃይማኖትን ማስፋፋት እንዳለባቸው ተስማምተው ወደየሀገራቸው ተመለሡ፡፡ አባ ዘሚካኤል ግን በዚያው ቆየ፡፡ እሱ ልቡን የነካችዉ ዜናዋንም የሰማላት ሃገር ነበረችና፡፡ ይህቺውም ሃገራችን ኢትዮጵያ ነበረች፡፡ እሱም ማንም ሰው ሳያውቅና ሳያየው ከሁለቱ ደቀመዛሙርቱ ጋር ቅዱስ ሚካኤል እየመራቸው መጥተው ጐብኝተዋታል፡፡ ያለመምህራንና ያለአስተማሪ ያመነች የዚህችን ሀገረ እምነቷንና ሥነስርዐቷን ተመልክቶ ተደነቀ፡፡ እነዚያን 8 መነኰሳትም ከያሉበት ስለሃገሪቷ እየነገረ ጠራቸው የሚገርመው ግን እነሱም ስለዚህች ሀገር እንደሰሙ ያለምንም ማመንታት መጥተዋል፡፡ እነሱም ሕዝቡን እንደሰሙት አገኙት፡፡ አባ ዘሚካኤል አቡነ አረጋዊ የሚለውን ስያሜ ያገኙት ኢትዮጵያ ከመጡ በኋላ ትህትናቸውና ታዛዥነታቸው እሳቸው ሲመነኩሱ ገና ሕፃን ነበሩ ስራቸው ግን የአረጋውያን ነበርና አንተስ ሐፃን አይደለህም የልጅ አዋቂ ነህ ሲሉ አረጋዊ አሏቸው፡፡ አቡነ አረጋዊ በኢትዮጵያ ሲኖሩ በሄዱበት ስፍራ ብቻቸውን የሚፀልዩበትን ቦታ ሁል ጊዜ ይፈልጉ ነበር፡፡ አንድ ቀንም በመንገድ እየሄዱ ሳሉ ትልቅ ተራራን (ደብረ ዳሞን) ተመለከቱ፤ ከሦስተኛው ቀን በኃላም የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል መጥቶ ‹‹አንተ እግዚአብሔር ያከበረህ ቅዱስ ሆይ ምን ያስጨንቀሃል›› አለው፡፡ አባታችንም አቡነ አረጋዊም ‹‹ከዚህች ተራራ ላይ ወጥቼ ስለኃጥያቴ እናዘዝና እለማመን ስለበደሌም ይቅርታን እጠይቅ ዘንድ እወዳለሁ›› አለው፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም እንዲፀልይና ታላቅ ዘንዶም ወደርሱ እንደሚላክለት ነገረው፡፡ በሦስት ሰዓትም ዘንዶው መጣ፤ አባታችንም የዘንዶውን ጅራት ይዘው ወደላይ ወጡ ብቻቸውን አልነበሩም፡፡ ዘንዶው እንዳያስደነግጣቸውና እንዳይጐዳቸው ሰይፍን ይዞ ቅዱስ ሚካኤል ይጠብቃቸው ነበር እንጂ፡፡ አባታችን አቡነ አረጋዊም የእርጅና ዘመናቸው በደረሠ ጊዜ እግዚአብሔር ወደእርሱ በመንፈቀሌሊት ተገልጾ ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡ ይኸውም ‹‹መታሰቢያህን ያደርግ በጸሎትህም የተማመነውን ሁሉ እኔ በመላእክት ፊት ሞገስን ቧለሟልነትን እሰጠዋለሁ፤ በእውነተኛ ሀይማኖት ሁሉ የገድልህን መጽሐፍ የጻፈ፤ ያጻፈ፤ የተረጐመ እኔ ስሙን በሕይወት መጽሐፍ እጽፈዋለሁ፤ ይህ ሁሉ ላደረገም እስከ 14 ትውልድ ድረስ እምርልሀለሁ›› አላቸው፡፡ ከዚህም በኋላ አባታችን አልሞተም በዓመቱ "ሞትን የማይቀምሱ አሉ፡፡" ብሎ እንደተናገረው /ማቴ 16 ፥ 28/ ጥቅምት 14 ቀን 558 ዓ/ም ተሠወረዋል፡፡ ከጻድቁ አባት በረከት ይክፈለን፤ በቃልኪዳናቸው ይጠብቀን፤ አሜን፡፡ **#ቅዱስ_ሙሴ_ብእሴ_እግዚአብሔር_በዓለ_ዕረፍታቸው_፡፡ ታሪኩ ከሙሽራው ቅዱስ ገብረ ክርስቶስና ከቅዱስ ቶማስ ዘቶርማቅ ጋር ተመሳሳይ የሆነው የእግዚአብሔር ሰው የተባለ የቅዱስ ሙሴ ዕረፍቱ ነው፡፡ /ከቀ.ደ.ሰ መድኀኔ ዓለም ወደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ. ፍኖተ ሕይወት ሰሌዳ መጽሔት የተወሰደ::/

ጥቅምት 14፤ ** #ቅዱስ_ገብረክርሰቶስ_(#አብደል_መሲህ_) #በዓለ_እረፍቱ_፤ በጎ ሥራን ከሚሠሩ፤ እግዚአብሔርን ከሚፈሩ ከቊስጥንጥንያው ንጉሥ ቴዎዶስዮስና ከመርኬዛ ልጅ የላቸውም ነበርና ኢየሩሳሌም ድረስ ሂደው በስዕለት ያገኙት ታላቅ አባት ነው፡፡ ስሙንም ቤተሰቡ አብደል መሲህ ብለው ሰየሙት፤ (አብደል ማለት አገልጋይ ማለት ሲሆን መሲህ ማለት ክርስቶስ ማለት ነው፡፡ የስሙ ትርጓሜውም ገብረ ክርስቶስ (የክርስቶስ ሥራ) ማለት ነው፡፡ እድሜውም ለትምህርት ሲደርስ የቤተክርስቲያንንና ሥጋዊ ትምህርትን አስተማሩት፤ አድጎም በጎለመሰ ጊዜ የሮሜውን ንጉስ ልጅ አጭተው እንደሥርዓቱ አጋቡት። እሱ ግን በምድራዊ ሕይወት ከመደሰት ይልቅ በሰማይ ስለሚያገኘው ነገር አብዝቶ ይናፍቅ ነበርና በጋብቻ ከመኖር ይልቅ ምንኵስናን ይወድ ነበርና በሰርጉ ዕለትም እኩለ ሌሊት በሆነ ጊዜ ሙሽራው ገብረክርስቶስ ተነስቶ ወደ ሙሽራይቱ ሔዶ እጇንም ይዞ ከእርሷ ጋር ቃልኪዳን አደረገ፤ ከዚያም የሃይማኖት ጸሎትን አድርሶ ለእርሷም ምን አይነት ሕይወት መኖር እንደሚፈልግ አስረድቷት የተሞሸረበትን ልብስ ከላዩ አውልቆ የግምጃ ልብስን ለብሶ ለመሄድ ተነሳ፡፡ ሙሽራይቱም ‹‹እኔን ለማን ትተወኛለህ?›› ብላ አልቅሳ ጠየቀችው፡፡ እርሱም ‹‹በእግዚአብሔር ዘንድ እተውሻለሁ፤ እኔም ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስን ልከተለው እሄዳለሁ፤ የአባቴ መንግስት ኃላፊ ነውና፡፡ አንቺም መሀላሽን አስቢ፡፡›› አላት፡፡ ያን ጊዜ መሃላዋን አስባ ዝም አለች። ከቤቱ ተነስቶ ወጣ፤ በመርከብ ከሚጓዙ መንገደኞች ጋር ያመት መንገድም ወደሚሆን አርመንያም ተጓዘ። በነጋም ሰዓት አባትና እናቱ ሙሽራው ልጃቸውን ለማግኘት ወደ ሰርጉ አዳራሽ ገቡ፤ እንዳሰቡት ግን ሙሽራው ልጃቸውን አላገኙትም፤ ይልቁንም ሙሽሪቷን እያለቀሰች አገኟት እንጂ፡፡ እነሱም አጥብቀው በጠየቋት ሰዓት መሐላን አስምሏት በሌሊት እንደሄደ ነገረቻቸው፤ ታላቅ ለቅሶን አለቀሱ። ይፈልጉት ዘንድም ንጉሥ አባቱ አምስት መቶ አገልጋዮችን ላከ፡፡ ለድሆችና ለምስኪኖችም ምጽዋት ያደርጉ ዘንድ ብዙ ገንዘብን ሰጣቸው ገብረክርስቶስ ግን በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም በተሰራች አርመንያ ሀገር በምትገኝ በአንዲት ቤተክርስቲያን ደጅ መኖር ጀምሮ ነበር፡፡ አባቱ የላካቸው ሁለቱ አገልጋዮችም ከዚያ ደርሰው ስለርሱ መርምረው ነበር፤ ወሬውን ግን ማግኘት ተሳናቸው፡፡ ለድሆችም ምጽዋትን ተቀብሏል ግን እንደማንኛውም የኔቢጤ ስለመሰላቸው ማወቅ ተስኗቸው ነበር፡፡ በዚህችም ቦታ ማንም እሱ የንጉሥ ልጅ፤ ቅዱስ መሆኑን ሳያውቅ 15 ዓመት ኖረ፡፡ እመቤታችን ለአንድ ቄስ ተገልጻ ገብረ ክርስቶስን ወደ ቤ/ን ያስገባው ዘንድ አዘዘች፤ ገብረክ ርስቶስም ይህን ባወቀ ጊዜ በሌሊት ተነስቶ በእመቤታችን ስዕል ፊት ‹‹እመቤቴ ሆይ የተሰወረ ሥራዬን አንቺ ለምን ገለጥሽ አሁንም ወደ ሚሻለኝ ምሪኝ›› ብሎ ስዕሏን ተሳልሞ በሌሊት ወጥቶ ወደ ባህሩ ወደብ ደረሰ፡፡ ወደሌላ ሃገርም ሊሄድ ወዶ በመርከብ ተሳፈረ ግን በእግዚአብሔር ፈቃድ ከአባቱ አገር ደረሰ እሱም እናትና አባቴ ለኔ የፈለጉትን እየሰጡኝ ለነሱ ምጽዋት ይሆንላቸው ዘንድ በደጃቸው ልኑር ብሎ በፈቃዱ ወደ እነርሱ ሄደ፡፡ የእነርሱን መዳን ሽቷልና ፊቱ በጣም ተለውጧልና ከቤተሰቦቹም ይሁን ከገረዶቻቸው መሃል ማንም ያወቀው አልነበረም ከውሾቹ በቀር፡፡ ለአባቱም እኔ መጻተኛ ነኝና በቤተ መንገሥትህ ደጅ ፊት ለፊት እንዳትረሳኝ ጎጆ ሥራልኝና ልኑር አለው፤ አባቱም የልጁን ኹኔታ አስቦ እኔም ልጄ እንዲሁ አይደል ብሎ ፈቀደለትና መኖር ጀመረ፡፡ የቤተ መንግሥቱ ባለሟሎችና እንዲንከባከቡት የታዘዙት ሠራተኞች ግን ሲገቡና ሲወጡ ሽታው እንዳያስጨንቀን ይህን ምስኪን አስውግዱልን እያሉ ወጭትና ድስትም እያጠቡ በላዩ ይደፉበት ነበር፡፡ ውሾችም እንዲናከሱበትና እንዲበሉት የሥጋ ትርፍራፊ ይጥሉበት ነበር፡፡ ውሾች ግን ቁስሉን ይልሱለት ነበር፡፡ ቅዱስ አባ ገብረ ክርስቶስም ጊዜ እየረዘመ በሄደ ጊዜ የባሮቹ በደል እየበዛ ሲመጣ (መቋቋም ስላቃተው ሳይሆን ለእነሱ በደል እንዳይሆንባቸው ሲል) ወደ እግዚአብሔር ይወስደው ዘንድ ለመነ፡፡ ከዚያም ታሪኩን ከመጀመሪያ እስከመጨረሻው ጽፎ በእጁ ይዟት አረፈ፤ የነገሩትን የማይረሳ የለመኑትን የማይነሳ ፈጣሪም እንደፈለገ ነፍሱን ከሥጋው ለየለት፡፡ ለሱም ስሙን ለሚጠራ መታሰቢያውንም ለሚያደርግ ቃልኪዳን ሰጠው፡፡ የዕረፍት ቀኑም እሑድ ነበርና ሕዝቡ ሁሉና ካህናቱ ከሊቀጳጳሳቱ ጋር በቅዳሴ ጊዜ በቤተክርስቲያን ውስጥ ሳሉ ‹የእግዚአብሔርን ሰው በንጉሡ በቴዎዶስዮስ ቤት ፈልጉት› የሚል ቃል ከሰማይ ሰሙ በዚያን ጊዜ ሂደው በአረፈበት ቦታ አገኙት፡፡ በእጁም ውስጥ የተጨበጠ ክርታስን አዩ፡፡ ሊወስዷትም ሽተው መውሰድ ተሳናቸው በአንድነትም በጸለዩ ጊዜ እጁ ተፈትታ ወስደው አነበቧት፡፡ አባትና እናቱም ልጃቸው እንደሆነ አወቁ ታላቅ ጩኸትም ሆነ መሪር ልቅሶንም አለቀሱ አክብረውም በጥምቀት 14 በእረፍቱ ቀን ቀበሩት መቃብሩም በሽተኞችን ሁሉ በመፈወስ ድንቅ የሆኑ ብዙ ተዓምራቶችን የሚያደርግ ሆነ ከጻድቁ ረድኤት በረከት ያሳትፈን፡፡ /ከቀ.ደ.ሰ መድኀኔ ዓለም ወደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ. ፍኖተ ሕይወት ሰሌዳ መጽሔት የተወሰደ/

#የአቡነ_አረጋዊ_የበሶ_እምነት_፤ በዓመት አንድ ጊዜ ጥቅምት 14 በቅዱስ ገብረ ክርስቶስ አቡነ አረጋዊና ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር ክብረ በዓል በሚከበረርባቸው አብያተ ክርስቲያንት ላይ በሶ ይሰጣል፤
+7
#የአቡነ_አረጋዊ_የበሶ_እምነት_፤ በዓመት አንድ ጊዜ ጥቅምት 14 በቅዱስ ገብረ ክርስቶስ አቡነ አረጋዊና ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር ክብረ በዓል በሚከበረርባቸው አብያተ ክርስቲያንት ላይ በሶ ይሰጣል፤ ይኸውም የበሶ እምነት ለብዙ ችግሮች ፈውስ ነው፡፡ በሶ የአቡነ አረጋዊ እምነት የኾነበት ምክንያትም በታላቁ ገዳም በደብረ ዳሞ የመናንያኑ ምግብና ወደዚሁ ቦታ ለሚሄዱ ምዕመናንም እንደ እምነት ተደርጎ የሚሰጥ በመኾኑ ነው፡፡ *** +++ #የቅዱስ ገብረ ክርስቶስ አቡነ አረጋዊና ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር ክብረ በዓል ከሚከበርባቸው ቦታዎች መካከል ዐበይቶቹ፤ ፠ በደብረ ዳሞ፣ ፠ በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም፣ (የቅዱስ ገብረ ክርስቶስ፣ አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር ታቦት ከጥንት ጀምሮ በድርብነት ይገኛል) (ደብራችን መጀመሪያ ሲመሠረት ይቀድሱና ያወድሱ የነበሩት የደብረ ዳሞ ገዳም መነኰሳት ናቸው፡፡ የቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ክብረ በዓል በደብራችን ሲከበር 100 ዓመታት ሞልቶታል፤ እንኳን ክብረ በዓል የቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ማኅበር እንኳን 100 አካባቢ አስቈጥሯል፡፡) ፠ በደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ (አለርት ሆስፒታል አጠገብ፤ ወደ አለም ባንክ መስመር) ፠ በመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ (የአቡነ አረጋዊ ታቦት በድርብነት ይገኛል) ፠ በሽሮ ሜዳ መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን (የአቡነ አረጋዊ ታቦት በድርብነት ይገኛል) ፠ በደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤ.ክ. (የአቡነ አረጋዊ ታቦት በድርብነት ይገኛል) ፠ በጎንደር አቡነ አረጋዊ ቤ.ክ. (ብሉኮ አካባቢ)

ጥቅምት 12፤ የሐዋርያውና ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ በዓለ ዕረፍቱ ነው፤ ከቅዱስ ማቴዎስ ረድኤት በረከት ይክፈለን፡፡
+1
ጥቅምት 12፤ የሐዋርያውና ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ በዓለ ዕረፍቱ ነው፤ ከቅዱስ ማቴዎስ ረድኤት በረከት ይክፈለን፡፡

ሥርዐተ ማኅሌት ዘወርኀ ጽጌ (‹ዘላይ ወዘታች› ቤት) (፪ኛ ዙር ዓመት፤ ፪ኛ ሳምንት፥ዘጥቅምት ፱) በዓለ እስጢፋኖስ ካልዕ ወቶማስ ሰማዕት ዘመርዓስ፡፡ ለቡ! (ልዩ ማስታወሻ) ፠ የደብራችሁ የአቋቋም
+4
ሥርዐተ ማኅሌት ዘወርኀ ጽጌ (‹ዘላይ ወዘታች› ቤት) (፪ኛ ዙር ዓመት፤ ፪ኛ ሳምንት፥ዘጥቅምት ፱) በዓለ እስጢፋኖስ ካልዕ ወቶማስ ሰማዕት ዘመርዓስ፡፡ ለቡ! (ልዩ ማስታወሻ) ፠ የደብራችሁ የአቋቋም ይትበሃል እንደ ቀጨኔ ደብረ ሰላም የላይ ቤት የሆነ፤ ‹‹ዘግምጃ ቤት›› የሚለውን ተመልከቱ፡፡ ፠ የደብራችሁ የአቋቋም ይትበሃል የታች ቤት ከሆነ ‹‹ዘበዓታ›› የሚለውን ተመልከቱ፡፡

ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያንችንን ጉዳይ በተመለከተ በየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል መልአከ ሰላም ሰ/ት/ቤት ጥቅምት 9 ከቀኑ 9፡30 ጀምሮ በሰ/ትቤቱ አዳራሽ እንወያይ፤ በርኩሳን መናፍስት የሚመሩ ቤተ
+1
ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያንችንን ጉዳይ በተመለከተ በየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል መልአከ ሰላም ሰ/ት/ቤት ጥቅምት 9 ከቀኑ 9፡30 ጀምሮ በሰ/ትቤቱ አዳራሽ እንወያይ፤ በርኩሳን መናፍስት የሚመሩ ቤተ ክርስቲያንን ለማዳከም ቀን ከሌት የሚደክሙበት ወቅት በመሆኑ ከመቼውም በላይ በየሰ/ት/ቤቶቻችን ቅድሚያ በመስጠት ልንወያይና ልንመካከር ይገባልና፡፡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በማስተዋል መንገድ ይምራን፡፡

ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያንችንን ጉዳይ በተመለከተ በየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል መልአከ ሰላም ሰ/ት/ቤት ጥቅምት 9 ከቀኑ 9፡30 ጀምሮ በሰ/ትቤቱ አዳራሽ እንወያይ፤ በርኩሳን መናፍስት የሚመሩ ቤተ
+1
ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያንችንን ጉዳይ በተመለከተ በየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል መልአከ ሰላም ሰ/ት/ቤት ጥቅምት 9 ከቀኑ 9፡30 ጀምሮ በሰ/ትቤቱ አዳራሽ እንወያይ፤ በርኩሳን መናፍስት የሚመሩ ቤተ ክርስቲያንን ለማዳከም ቀን ከሌት የሚደክሙበት ወቅት በመሆኑ ከመቼውም በላይ በየሰ/ት/ቤቶቻችን ቅድሚያ በመስጠት ልንወያይና ልንመካከር ይገባልና፡፡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በማስተዋል መንገድ ይምራን፡፡

፠፠ #አቡነ_በጸሎተ_ሚካኤል_ አንጦንስ መቃርስን፤ መቃርስ ጳኩሚስን፤ ጳኩሚስ ቴዎድሮስን፤ ቴዎድሮስ አረጋዊን፤ አረጋዊ ማትያስን፤ ማትያስ መድኃኒነ እግዚእን፤ መድኃኒነ እግዚእ ዮሐኒን፤ ዮሐኒ ኢየሱስ
+2
፠፠ #አቡነ_በጸሎተ_ሚካኤል_ አንጦንስ መቃርስን፤ መቃርስ ጳኩሚስን፤ ጳኩሚስ ቴዎድሮስን፤ ቴዎድሮስ አረጋዊን፤ አረጋዊ ማትያስን፤ ማትያስ መድኃኒነ እግዚእን፤ መድኃኒነ እግዚእ ዮሐኒን፤ ዮሐኒ ኢየሱስ ሞዐን፤ ኢየሱስ ሞዐም ትምህርትን ከምግባር ጋር ያስተማራቸውን 800 የሚኾኑ ንቡራነ እድ መነኰሳትን ወልዷል፤ በመላ ሃገሪቱም አሰማርቷል፤ ከእነዚህም ውስጥ አንዱና ዋነኛው አቡነ በጸሎተ ሚካኤል (የደብረ ጎል ገዳምን ያስፋፉ) ናቸው አቡነ በጸሎተ ሚካኤልም ከአባታቸው ማርቆስና ከእናታቸው እግዚእ ክብራ ዛሬ መስከረም 6 ተፀነሱ፡፡ በተወለዱም ጊዜ በቤታቸው ውስጥ ቀስተ ደመና ተተክሎ የታየ ሲሆን አስቀድሞ መልአኩ ስሙን እንዳወጣለት ‹‹በጸሎተ ሚካኤል›› ተብለው ተሠየሙ፡፡ እርሳቸውም በርካታ ቅዱሳንን የወለዱ ወላዴ አእላፍ ሲሆኑ፤ ከወለዷቸው ልጆች መካከል አንዱና ዋነኛው ከልጅነት ጀምሮ በአርድዕትነት (በተላላኪነት) ያገለገሏቸውና ትምህርትን ያስቀሰሟቸው አቡነ ተክለ ሃይማኖት ናቸው፡፡

ወተቀበልዎ መላእክት በስብሐት ወበማኅሌት፤ ወአብዕዎ ኢየሩሳሌም ሰማያዊተ አብዕዎ ገብረ ሕይወት፡፡ እንኳን #ለአቡነ_ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ_በዓለ_ዕረፍት_በሰላምና_በጤና_አደረሳችሁ፡፡ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (አቦ፥ አቡዬ)፤ * እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ብርሃነ ዓለም የኾኑ፤ * እንደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ጸጋንና ክብርን የተሞሉ፤ * ኰከበ ገዳም፥ መናኔ ዓለም፥ ምድራዊ መልአክ፤ * ስማቸውን ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ያወጣላቸው፤ * በአክናፈ መባርቅት ተጭነው የሚጓዙ፤ * 60 አናብስትና 60አናብርት ይታዘዙላቸው የነበሩ፤ የእግራቸው ትቢያ ለአራዊቶቹ ምግብ የኾነላቸው፤ * ለብዙ አእላፍ ቅዱሳን ወላዴ የኾኑና በረከትን የሰጡ ታላቅ አባት (ለአብነትም፤ ለቅዱስ ላሊበላ፥ ለአቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ፥ ለአባ አንበስ ዘደብረ ሐዘሎ፥ ለአባ ብንያም ዘግብፅ) ፠፠፠ #ምድረ_ከብድ_፤ /ዝ_ምድር_ክቡድ_ውእቱ_/ ፤ #ዝቋላ (#ዝ_ቆላ)  ምድረ ከብድ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ ለመጀመሪያ ጊዜ ያረፉባት ቦታ ናት፤ ቀጥሎ ወደ ደብር ቅዱስ #ዝቋላ (#ዝ_ቆላ) ለጸሎት ሂደው ለሃገራችን ኢትዮጵያና ለዓለማችን ምሕረትና በረከትን ከአምላካችን ለ100 ዓመታት በባሕር ውስጥ ሆነው ለምነዋል፤ *ወደ ምድረ ከብድ ተመልሰው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል፤ ቊራም በሰይጣን ተመስሎ መጥቶ ዓይናቸውም ቢያጠፋውም ከ7 ሱባዔያት በኋላ ሊቀ መላእክት ሚካኤልና ገብርኤል ዓይናቸውን መልሰውላቸዋል፡፡ *ወደ ዝቋላ በመመለስም አጋንንትም ከምድረ ዝቋላ አጥፍተዋል፤ ፠ እንደገና ወደ ምድረ ከብድ ተመልሰው በነበሩበት ጊዜ ታላላቆቹና በአንበሳ ዘባን ላይ የሚሄዱት #አቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ ፣ #አባ_አንበስ_ዘደብረ_ሐዘሎ_አፋር)፣ #አባ_ብንያም_ዘግብፅ ከአባታችን ቡራኬ ለመቀበል መጡ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ተሰውረው ነበርና፤ የአቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ አናብስት የ3ቱን አባቶች አናብስት በሉባቸው፤ በ7ኛው ቀን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ተገልጠው የኾነውን ነገር በማየት የተበሉትን አናብስት እንዲመልሱ የራሳቸውን አናብስት አዘዟቸው መልሰውም እንደነበሩ በተዓምራት አስነስተው ሰጧቸው፤ በደመና ጠቅሰው ቅዱስ ፋኑኤል 3ት ሰማያዊ ኅብስትና 3ት ጽዋዕ ይዞ ለእንግዶቻቸው ይዘው ሠረገላ በሚባለው ዋሻ አመጡላቸውና ሰጥተው ሸኟቸው፤ እነዚህን ቅዱሳን በሸኙ በ7ኛው ቀን ወደ ተለያዩ ሃገራት ሄደው አስተምረዋል፡፡ ፠ እድሜያቸው ረዥም እንደመሆኑ፤ ቅዱሱ ንጉሥ አፄ ላሊበላን ጨምሮ ሌሎችም ቅዱሳን ወደ ርሳቸው እየመጡ በረከትን ተቀብለዋል፡፡ ፠#በግብፅ_300_ዓመታት_፥ #በኢትዮጵያ_ምድር_ላይ_262_ዓመታት (በዋነኛነት #በምድረ_ከብድና_በዝቋላ_ ቢኖሩም ሌሎችም የመሠረቷቸውና የኖሩባቸው ገዳማት አሉ፤ ለአብነትም ደቡብ ወሎ የሚገኘውን #ገዘዛ_አቦን_ መጥቀስ ይቻላል) ፠ በድምሩ 562 ዓመታት ከኖሩ በኋላ በንጉሥ ሕዝብናኝ(እንድርያስ) ዘመነ መንግሥት፤ መጋቢት 5 ቀን ቅዳሜ ለእሑድ አጥቢያ ብዙ ቃል ኪዳንን ጌታችን ሰጣቸው፥ 12 አክሊላትንም አቀዳጃቸው፤ የነበሩባት ምድረ ከብድ ገዳም ግን ራደች፥ ተንቀጠቀጠች፥ በብርሃንም ተጥለቀለች፤ ዝቅ እያለችም መንሸራተት ጀመረች፤ ጌታችንም አንቺ መሬት ሆይ ጽኚ ይህንን ኹሉ ስለቻልሽ ምድር ክቡድ /ኋላ ምድረ ከብድ/ ተብለሽ ተጠሪ አላት፤ የጻድቁም ነፍስ ከሥጋቸው ከሌሊቱ 6 ሰዓት ተለየች፡፡ ፠ ይህችውም ምድረ ከብድ ጻድቁ የኖሩባትና የቀደሱባት፥ የመሠረቷትና ያነፅዋት፣ ሠራዊተ መላአክት የከተሙባት፣ ታላላቅ አበው መጥተው በረከት ከአባታችን የተቀበሉባት፣ አርምሞና ጸጥታ የማይለያት፤ አጸዷና ቅጥሯ ልቡናን የሚመስጥ፤ ከአ.አ 125 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ ናት፡፡ አምላከ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ረድኤት፥ በረከትን ይክፈለን፡፡ (ሥርዐተ ማኅሌቱን የኢንተርኔት አቅርቦት በሌለባቸው ቦታዎች አድርሱልን፤ በተለይም ወደ ምድረ ከብድ፥ ዝቋላ፥ ገዛዛ አቦና ሌሎች የአባታችን ክብረ በዓል በሚከበርባቸው አድባራትና ገዳማት ያላችሁ አድርሱልን፡፡) /የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

#አብርሃ_ወአጽብሃና_4ቱ ቅዱሳን ነገሥታት እስከ አሁን ድረስ በኢትዮጵያ ከነገሡ ነገሥታት የሚለዩበት ነገር አለ ይኸውም፤ ክህነትን ከንግሥና፥ ቅድስናን ከንጽሕና ጋር አንድ አድርገው በመያዝ (እንደ
+1
#አብርሃ_ወአጽብሃና_4ቱ ቅዱሳን ነገሥታት እስከ አሁን ድረስ በኢትዮጵያ ከነገሡ ነገሥታት የሚለዩበት ነገር አለ ይኸውም፤ ክህነትን ከንግሥና፥ ቅድስናን ከንጽሕና ጋር አንድ አድርገው በመያዝ (እንደ ካህኑ መልከጼዴቅ፣ አፄ ገብረመስቀል፣ አፄ ቴዎድሮስ ቀዳማዊ፣ …) እግዚአብሔርንም ሰውንም ያገለገሉ ናቸው፤ ከዚህም በተጨማሪ ቅድስናን ከሐናፄ ቤተመቅደስነት ጋር ደርበው የያዙም ጭምር ናቸው፡፡ በዚህም በንግሥናቸው ሀገርን በመልካም ሥራና በቅድስና ከማስተዳደራቸው በተጨማሪ ቅዱሳን ጻድቃን ሆነው እግዚአብሔርን በብዙ ድካም በመልካም ተጋድሏቸው ያገለገሉና አገልግሎታቸውም ሆነ ቅድስናቸው በእግዚአብሔር ዘንድ የተመሰከረላቸው፤ ጽላት የተቀረጸላቸው፥ ገድል የተጻፈላቸው፤ (ገድላቸውና ትሩፋታቸው፣ ምግባር ሃይማኖታቸው እጅግ ድንቅ የኾኑ) ቅዱሳን ናቸው፡፡ ዛሬ ጥቅምት 4 ቀን 364 ዓ/ም አጽብሐ ጥቅምት 4 ቀን 379 ዓ/ም በሞተ ሥጋ አርፈዋል፡፡ ክብረ በዓላቸው በትግራይ ባለ ውቅር ገዳማቸው፤ በአዲስ አበባ ደግሞ፤ * * በደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊ **በየካ ተራራ ዋሻ ተክለ ሐይማኖት **በአያት ቅዱስ ፋኑኤል ቤተክርስቲያን፡፡

#አቡነ_በርተሎሜዎስ_ዘደብረ_ዘመዳ፤ ፠ተወልደው ያደጉት በ13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በሸዋ ቡልጋ፤ በጥራ መረዋ አካባቢ ነው፡፡ ለአቅመ አዳም ሲደርስ ሚስት አጭተው ቢያጋቡትም፤ እንደ ድሜጥሮስ ንጽሕናውን ጠብቆ ለጥቂት ጊዜያት ከቆየ በኋላ ወግር ወደሚባል ተራራ ሂዶ 40 ቀን ሱባዔ ገባ፡፡ ሱባዔውን እንደጨረሰም ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ገባ፡፡ ፠ በደብረ ሊባኖስ ገዳምም ከታላቁ ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የምናኔ ሕይወትን ተማሩ፡፡ ፠ምንኵስናን ከጓደኛቸው ከኤዎስጣቴዎስ ጋር አበአንድነት የተቀበሉትም ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት ሲሆን፤ ከትግራይ ወሰን እስከ አንገት ያለውን እንዲያስተምሩም በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ተልከዋል፡፡ ፠ ወደ እንፍራንዝ (ጣና) ከጌርሎስ ከአኖሬዎስ ልጅ ዘንድ ሄደው ሰነበቱና ወደ ሃገራቸው ተመለሱ፡፡ ፠ ክርስትናን ለማስፋት ተመርጠው ከተሾሙ ዓበይት ንቡራነ ዕድ አንዱ ሲሆኑ፤ የተሾሙበት ሃገረ ስብከታቸውም በቆባ፣ የጠጠርና የኮረም ኤጲስ ቆጶስ ሆነው ነው፡፡ በተለይም በወሎና በአፋር ድንበር አካባቢ ወንጌልን በትጋት አስተምረዋል፡፡ ፠ 12ቱ ንቡራነ ዕድ ከያሉበት ሃገር ወደ ደብረ ሊባኖስ በመምጣጥ ወር ወር የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን አጽም ያጥኑ ነበር፤ የጻድቁ ዘቡነ በርተሎሜዎስ የማዕጠንት ተራቸውም በወርኃ ጳጕሜን ነበር፡፡ ፠ አፄ ዐምደ ጽዮን የአባቱን ሚስት በማግባቱ ቅዱሳኑና ግብጻዊው ጳጳስ አቡነ ያዕቆብ በመቃወማቸው፤ በአፄ ዐምደ ጽዮንና በልጁ በአፄ ሰይፈ አርዕድ መሰደድ ደረሰባቸው፤ አቡነ በርተሎሜዎስም ከጳጳሰ ጋር ወደ ግብጽ መሰደድ ጀመሩ ነገር ግን፤ አቡነ ያዕቆብ ለአቡነ በርተሎሜዎስ ጽላተ ማርያምን ሰጥተው እንዲመለሱ አደረጓቸው፤ አቡነ በርተሎሜዎስም ጽላተ ማርያምን በደብረ ዘመዳ በክብር አስቀመጣት፡፡ ፠ በ14ኛው መቶ ክ/ዘ ጥቅምት አርፈው በደብረ ዘመዳ ገዳም ዐጽማቸው በክብር አርፏል፡፡ #ደብረ_ዘመዳ_ማርያም_አቡነ_በርተሎሜዎስ_ገዳም (#ደብረ_ዠመዳ) ገዳሙ የሚገኘው ወሎ ላስታ ውስጥ ሲሆን የመሠረቷት አቡነ በርተሎሜዎስ ናቸው፡፡ በዚህ ገዳም እንደ አኵሱምና ደብረ ሊባኖስ ሰዐታትና ማኅሌት ሁልጊዜም ይቆምባታል፡፡ በዚህ ገዳም በርካታ ጥንታውያንና ድንቅ የሆነ ቅርሶች አሉ፤ ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ የሳላት የእመቤታችን ስዕል የምትገኘውም በዚሁ ገዳም ሲሆን፤ መልኳ የሚቀያየርና ቅዱስ ዮሐንስ የሚባል ደግ ሰው ነው ወደዚህ ገዳም ያመጣት፡፡ ** ገዳሙ የሚጠበቀው በዋነኛነት እንደ ነብር ባሉ የዱር አራዊት ነው፡፡ ፠፠፠የደብረ ዘመዳ ዓመታዊ ክብረ በዓል የሚከበረው በጥቅምት 4 በአቡነ በርተሎሜዎስ በዓለ ዕረፍታቸው ቀን ነው፡፡ ፠፠፠ ታላቁ ገዳም ደብረ ዘመዳ የሚገኘው፤ ሰሜን ወሎ ዋጃ ከተማ ከተደረሰ በኋላ የተወሰኑ ሰዓታት የእግር ጕዞ በመጓዝ ነወ፡፡ ከጻድቁ ከአቡነ በርተሎሜዎስ ረድኤት በረከት ይክፈለን፤ አሜን፡፡ /ምንጭ፤ ገድለ አቡነ በርተሎሜዎስ የብራና፤ የአማርኛ የቤ/ክ መዝገበ ቃላት፣ ዶ.ር ሥርግው ሐብለ ሥላሴ፣ ዝክረ ቅዱሳንና ከገድላት አንደበት የፊት ገጾች፡፡) /የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/