fa
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

رفتن به کانال در Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

کانال Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 413 مشترک است و جایگاه 5 577 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 192 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 413 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 13 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 71 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -3 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 25.53% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 9.38% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 933 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 446 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 23 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 14 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 413
مشترکین
-324 ساعت
+357 روز
+7130 روز
آرشیو پست ها
እንኳን ለቅዱስ እግዚአብሔር አብና ለእልፍ አእላፋት፥ ትዕልፊት አእላፋት (ለቅዱሳን መላእክት በዓለ ሢመት)፤ በሰላምና በጤና አደረሰን፤ አደረሳችሁ፡፡ (ከእልፍ አእላፋት አለቃዎች ስሞች በጥቂቱ)፡፡ ጸሎትነ ትብጻሕ (ሰላም ለክሙ) ለመላእክተ ምሕረት፤ ፨ ሚካኤል ወገብርኤል፥ ፨ ሱራፌል ወኪሩቤል/፬ቱ እንስሳ/፥ ፨ ዑር(ራ)ኤል ወሩፋኤል /፳፬ቱ ካህናተ ሰማይ/፥ ፨ ሱርያል ወፋኑኤል፥ ፨ አፍኒን ወራጕኤል፥ ፨ ሳቁኤል ወአቅናኤል፥ ፨ ብርናኤል ወሱባኤል፥ ፨ ፍናኤል ወሰላታኤል፥ ፨ ሰዳካኤል ወኤልናኤል፥ ፨ አናንኤል ወኢየሩማኤል፥ ፨ ግርማኤል ወድርማኤል ፥ ፨ ድማህኤል ወአድማኤል፥ ፨ ሙራኤል /ምናቴር አብያቴር/፥ ፨ ሱታ(ስቱ)ኤል ወሱርያል፤ ……. ፎቶዎቹ፤ ክብረ በዓሉ ከሚከበርባቸው ቦታዎች ጥቂቶቹ፤ …. 1. ግሸን ደብረ ከርቤ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ (መስቀሉ የሚገኝበት)፤ 2. ጠዳ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ (ጎንደር፤ ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ)፤ 3. ጎርዶማ እግዚአብሔር አብ ቤተክርስቲያን (በሰሜን ሸዋ)፤ 4. ደብረ ሲና ቅዱስ እግዚአብሔር አብ (አዲስ አበባ)፤ 5. ቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤ.ክ (አዲስ አበባ) 6. ቦሌ ቡኒ ደብረ ቤቴል ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤ.ክ (አዲስ አበባ) /የቀ.ደ.ሰ መድኀኔ ዓለም ወደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

መንበረ ክብር ደብረ ታቦር ቅዱስ ሚካኤል ወአቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም /ኋላ ወቅድስት አርሴማ በሚል እየተጠራ የሚገኝ/፤ (በቀጨኔ አዲሱ ገበያና በእንጦጦ መሃል ጉብታ ላይ የሚገኝ)፤ የታላቁ ደብር የቀጨኔ መድኀኔ ዓለም አፅመ ርስት (ከ108 ዓመታት በፊት መጀመሪያ የተወደሰበት፥የተሠለሰበት ቦታ)፨ እውነትም ደብረ ታቦር፤ ከየትኛውም የአዲስ አበባ ቦታ በቀንም ኾነ በማታ ጉብ ብሎ የሚታይ፨

ኅዳር 12 ለሰው ወገን የሚያዝንና የሚራራ፥ በእግዚአብሔር የጌትነት ዙፋን ፊት ሁልጊዜ ለምስጋና የሚቆም፥ ለፍጥረት ሁሉ የሚማልድ፥ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በዓለ ሢመቱና እስራኤላውያንን በባሕረ ኤርትራ ያሸገረበት በዓል ነው፡፡ (እንኳን አደረሳችሁ) በዓለ ሢመቱ፤ ሚካኤል ማለት ማን እንደ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡ በእለተ እሁድ ካለመኖር ወደ መኖር የመጣ ሲሆን እርሱም የነገደ ኃይላት አለቃቸው ነው በተጨማሪም ከሳጥናኤል ውድቀት በኋላ የአጋእዝትን ነገድም በአለቅነት ደርቦ የያዘ ሲኾን፡፡ ለ100ውም(99ኙም) ነገደ መላእክት አለቃቸውም ነው፡፡ ቅዱስ ሚካኤል ለሰው ልጆች ምሕረትን ከኅዳር 12 (በዓለ ሢመቱ) ጀምሮ እስከ 13 (የአእላድ መላእክት) በዓል ድረስ ከአምላኩ ምሕረትን የሚለምንበት ነው፡፡ በዚህ ቀን የሚከበረው እስራኤልን ከግብጽ ባርነት እያመራቸው ማውጣቱን ለማዘከር ነው፡፡ ይህም የሆነው ያዕቆብ በረሃብ 70 ኹኖ ወደ ግብፅ ከወረደ በኋላ በ215 ዓመታት (አብርሃም ወደ ግብፅ በተሰደደ በ430 ዓመታት) በኋላ፤ የዮሴፍን ዝና ያልሰማ ፈርኦን በግብፅ ነገሠ፡፡ እስራኤል ከእኛ ይልቅ በዝተዋል ጠላቶቻችን ቢነሱብን ተደርበው ያጠፉናል በማለት አገዛዝ አጸናባቸው ፍርድ አጓደለባቸው፡፡ የእስራኤል ሴቶች ልጅ ሲወልዱ ወንድ ከሆነ እንዲገደል በማረግ መከራ አጸናባቸው፡፡ 430 ዘመን በባርነት ከቆዩ በኋላ ከእብራውያን ወገን የሆነችው ራሔል ጭቃ እያቦካች ምጥ በያዛት ጊዜ እንዲያሳርፉዋት ጠየቀች ግብጻውያን ግን የሕፃናቱ ደም ጡቡን ያጠነክራል ርገጭ አሉዋት፡፡ ከመሐጸኗ የወጡ ሁለት መንትያ ልጆቿን እያየች ከጭቃ ጋር ረገጠች፡፡ ራሔልም አለቀሰች ስለ ልጆቿም መጽናናትን እንቢ አለች፡፡ የእስራኤል ንጉሥ ሆይ የሆነብንን እይ ስትል ራሷን ይዛ ታለቅስ ጀመር እንባዋንም ወደ ሰማይ ንጉሥ ወደ እግዚአብሔር ረጨች፡፡ የራሔል እንባ የሕዝበ እስራኤል ሁሉ ጩኸት እሮሮ ይዛ ቅድመ እግዚአብሔር ደረሰች፡፡ “. . . ራሔል ስለ ልጆችዋ አለቀሰች የሉምና ስለ ልጆችዋ መጽናናት እንቢ አለች” /ኤር 31፥5፤ ማቴ 2፥17/ እንዲል፡፡ ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር ሙሴን አስነሳና፤ በሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል መሪነት፤ 10 ተዓምራትን በምድረ ግብፅ በ11ኛ ተዓምር ደግሞ በኅዳር 12 (ፈርዖንን ከነሠራዊቱ በኤርትራ ባሕር አስጥሞ) በማድርግ ወደ ተስፋይቱ ምድረ መራቸው፡፡ ባሕረ ኤርትራን እስራኤላውያን እንደተሻገሩም የእስራኤል ልጆች የሙሴ የአሮን እኅት ማርያም ከበሮ እየመታች ንሴብሆ ለእግዚአብሔር ስቡሐ ዘተሰብሐ እግዚአብሔር ተዋጊ ነው ስሙም እግዚአብሔር ነው እያሉ ጠላታቸውን የመታላቸውን እነሱንም በተአምራቱ ያሻገራቸውን ከጠላታቸው እጅ ያዳናቸውን እግዚአብሔርን አመሰገኑ፡፡ ከዚህ በኋላ መጋቢ ብሉይ ቅዱስ ሚካኤል እየመራቸው መና ከሰማይ እያወረደላቸው ውሃ ከጭንጫ እያፈለቀላቸው ቀኑን በደመና ሌቱን በብርሃን መርቷቸው አርባ ዘመን ተጉዘው የቃል ኪዳን አገራቸው ምድረ ርስት ከነዓን ገብተዋል፡፡ /ዘጸ 15/ ከሙሴ በኋላ እስራኤልን የመራው ነቢዩ ኢያሱም እስራኤልን በሚመራበት ጊዜ ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል እስራኤልን ይረዳቸው ነበር፡፡ ከጠላቶቻቸው ጋር ሲዋጉም ሰልፉን ይመራ የነበረው ቅዱስ ሚካኤል ነበር፡፡ ለምሳሌ እስራኤላውያን ከኢያሪኮ አጠገብ በነበሩበት ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል ተገልጦ ኢያሱን አነጋግሮታል፡፡ ኢያሱ በኢያሪኮ አጠገብ ሳለ ቀና ብሎ ሲመለከት የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ የያዘ አንድ ሰው ከፊቱ ቆሞ አየ፤ ኢያሱም ወደ እርሱ ቀርቦ “ከእኛ ወገን ነህ ወይስ ከጠላቶቻችን?” ሲል ጠየቀው፡፡ እርሱም “አይደለሁም ነገር ግን የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ በመሆኔ መጥቻለሁ” ብሎታል /ኢያሱ 5፥13-15/፡፡ ይህ የተመዘዘ ሰይፍ ይዞ ከኢያሱ ፊት ለፊት የቆመው መልአክ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡ ይህን ለአብነት አነሣን እጅ እስራኤል በሚበድሉበት ጊዜ ሁሉ ወደ እግዚአብሔር የሚማልድላቸው ይህ ታላቅ መልአክ መጋቢ ብሉይ ቅዱስ ሚካኤል ነበር፡፡ እግዚአብሔር አምላክ በእደ መልአኩ ይጠብቀን፤ ከበዓሉ በረከት ይክፈለን፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

ኅዳር 9፤ የሠለስቱ ምዕት ክብረ በዓል ነው፡፡ ሐመረ ኖኅ ሠለስቱ ምዕት ቤ.ክ፤ በሃገራችን በሠለስቱ ምዕት (በ31ቱ ሊቃውንት ስም) ብቸኛ የሆነውና ከ310 ዓመታት በፊት በአፄ ቴዎፍሎስ (ስመ መንግሥት አጽራር ሰገድ) ታንጾ የነበረ ሲኾን ንጉሡ ሲያንጹትም የሠለስቱ ምዕት የአእላፍ መላእክትና የነቢያት ቤተ ከርስቲያን አድርገው ነው፤ ድርቡሽ ጎንደርን ከ129 ዓመታት በፊት በወረረ ጊዜ ጠፍ ኹኖ ቆይቶ በ2007 ዓ.ም. ቤተ ክርስቲያኑ ድጋሚ ተሠርቶ፤ እነሆ ዘንድሮ ለ5ኛ ጊዜ ተከብሮ ውሏል፡፡ ይህ ቤተ ክርስቲያን ታላቅ ጕባኤ ቤትም ሲኖረው፤ ቀድሞ የ4ቱ ጕባኤያት ዋና ማስመስከሪያ ኹኖ ቆይቷል፤ ከአፄ ኀይለ ሥላሴ ዘመን ጀምሮ በኢትዮጵያ ደረጃ የመጻሕፍተ መነኰሳት ዋና ማስመስከሪያ ኹኖ ይገኛል፡፡ /ፎቶ ላይ የምትመለከቱት የሠለስቱ ምዕት የመጻሕፍተ መነከኰሳት ጕባኤ ቤት በእሳት አደጋ በተቃጠለበት ወቅት፤ በጎንደር የሚገኙ የመጻሕፍተ ብሉያት፣ የመጻሕፍተ ሐዲሳት፣ የመጻሕፍተ ሊቃውንት የማጽናኛና የምክክር መርሐ ግብር እያካሄዱ የሚያሳይ ነው፡፡)

ለተዝካረ አበው /ኅዳር ፰/ (በታላቁ ገዳም በዋልድባ/ዋሊ/ ብቻ በዛሬው ዕለት ለሚደረገው የአበው መታሰቢያ አደረሳችሁ፨ በኢትዮጵያ በብቸኝነት ጌታችን በመሠረተው በዚህ በታላቁ ገዳም በዋልድባ ብቻ ከሚደረጉ ሥርዐቶች መካከል አንዱና ከቀድሞ አባቶች ሲወርድ ሲዋረድ ከመጣው መካከል፤ የወጣ ሳይገባ፥ የገባ ሳይወጣ (መርፌም ቢኾን ከሱባዔው በፊት ወደ ገዳሙ ካልገባ ሱባዔው እስኪያልቅ ጥቅም ላይ አይውልም)፨ የ158 ቀናት ሱባዔ ይደረጋል፤ (ከ143 ቀናት በኃዋላ ዛሬ ኅዳር ፰ በተዝካረ አበው ቀን በማኅበር ደረጃ ቢሰባሰቡም መልሰው እስከ ኅዳር ፳፬ ወደ ሱባዔ ገብተው በ፳ወ፬ቱ ካህናተ ሰማይ ትልቁ ሱባዔ ያበቃል፨ በእነዚህ ቀናት ከቀባሪ በስተቀር ወደ ገዳሙ መግባትም አይቻልም፨ ፠፠ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ከአበው አንድነት፥ ከአቡነ ሳሙኤል ልጅነት፥ ከገዳመ ዋሊ ረድኤት በረከት ይክፈለን፨ /ከዋልድባ ዋሊ ገጽ የተወሰደ/

ኅዳር ፯ ዕፁብ ድንቅ የኾነ ተዓምራትን የሚሠሩት (እንጨቱ ጸበላቸው ውስጥ ሲገባ መቁጠሪያ የሚያደርጉት፤ በፎቶ የምታዩት)፤ ፻ ትውልድ የሚያስምሩት፤ በደንጊያ ሠረገላነት የሚጓጓዙት ከ፯ቱ ቅዱሳን ዘጋሥጫ አንዱ የኾኑት አባ ገብረ እንድርያስ በዓለ ዕረፍታቸው ነው፨ ቦታቸውን ክርስቲያን የኾነ ኹሉ ሊያየው የሚገባም ነው፤ እንዲሁም የሊቀ ስማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቅዳሴ ቤቱ ነው፨ ✤✣✤ ጻድቁ አቡነ ገብረ እንድርያስ ዘወለቃ፤ ✤አባታቸው ተንስአ ክርስቶስ፥ እናታቸው አርሴማ ሲባሉ፥ የትውልድ ሀገራቸው ወሎ፥ ቦረና፥ ጋሥጫ ሲኾን የቀድሞ ስማቸው ንፍታሊም ይባል ነበር። ✤ ለትምህርት ሲሄዱ መምህራቸው ብዙሃኑን የምታድን ጻድቅ ትሆናለህ ብለው ትንቢት የተናገሩላቸው ሲኾን፤ የጻሕፍትን ትርጓሜ በደንብ ካስተማሯቸው በኋላ ንፍታሊም ይባል የነበረውን የቀድሞ ስማቸውን ለውጠው ገብረ እንድርያስ አላቸው። ✤ ጻድቁ በአቡነ ከማ ገዳም ለረጅም ጊዜ በታላቅ ተጋድሎ አገልግለዋል፤ ብዙ አባቶች ሱባኤ በሚይዙበት በስኮሩ ስላሴ ቤተክርስትያን ጸሎት ሲያደርጉ ቅዱስ ኡራኤል በወርቅ ጽዋ ማየ ሕይወት አጠጥቷቸዋል። ✤ ጻድቁ አባታችን ሙታንን በማስነሳት ና ድውያንን በመፈወስ ብዙ ተአምራትን ሲያደርጉ ኖረዋል። ✤ ጻድቁ ዐርብ ዐርብ የጌታችንን ቅዱስ ሥጋውን ና ክቡር ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም ይመላለሱ የነበረው በአየር ላይ ድንጋዩን እንደ ሰረገላ ዋርካውን እንደ ጥላ ይጠቀሙበት ነበር። ይህ ሰረገላ የሆነው ድንጋይ በገዳማቸው ይገኛል። ✤ ጻድቁ አባታችን እግዚአብሄር ኀጥአንን እንዲምርላቸው ርቀት ወንዝ ከተሰኘው ቦታ በአንገታቸው ላይ በጣም ትልቅ ድንጋይ እየተሽከሙ ይጸልዩ ነበር። በዚህም ይጸልዩበት በነበረው ወንዝ ውስጥ በተአምራት መቁጠርያ የሚሰራ ጸበል ፈለቀላቸው፤ ጠበላቸው ውስጥም እንጨት ሲነከርበት እንጨቱ በተአምራት መቁጠሪያ ሆኖ ይወጣል፤ ይኸውም መቁጠሪያ ለብዙ ሕመሞች መድኀኒት ነው፡፡ ✤ ✤ ✤ ዛሬ ቅዱስ ሲኖዶስ ስለ ሃገራችን ሰላም የ፩ ሱባዔ ምሕላ እንዲደረግ ያወጀው ማብቂያው ነው፤ አቡነ ገብረ እንድርያስና ሊቀ ሰማዕቱ ስለ ሃገራችን በተቀበሉት ቃል ኪዳን ሰላምና ጤና ያውርዱልን፤ ጠላታችንን ከሃገራችን ያባርሩልን፨ ✤ እባካችሁ ዝም አትበሉን እናንት ገዳማት! ዕድሜ ጠገቦቹ የዘመን አዝማናት፡፡ እነ አባ ያዕቆብ እነ ደብረ ጽጌ፤ እነ ቦሎ ዋሻ እነ ደብረ ሐይጌ፤ እነ ፍልፍሌ ጸዓዳ እነ ጅቦ ዋሻ፤ እነ ደብረ ቆዘት እነ ጊዮርጊስ ዋሻ፤ ታሪካችሁን ንገሩን እንያዝ ማሰታወሻ፤ ድንገት ብትጠፉብን እንዲሆን ማልቀሻ፡፡ ደብረ ቆዘት ጠርተን ገብረክረስቶስ አልን፤ የገዛዛን ታሪክ ለላሊበላ ሰጠን ፤ ደበረ ከረቤ ብለን አባ ያዕቆብ አልን፤ የወለቃ ጉዳይ ለዘካርያስ ሰጠን፡፡ እነ ደብረ ሐይጌ እነ ጅቦ ዋሻ፤ የያጌ ጌጦች የታሪክ መናገሻ፤ የጎለሌው ዋሻ የተባለከው ፍልፍሌ፤ የቦሎ ቤቴክስያን የጉርባው ቀበሌ፤ የጊዮርጊስ ዋሻ ነአኩቶ ድድምቱ ፤ እስኪ ተናገሩ የታሪክ እውነቱ፡፡ ማን እንበላችሁ የመጠርያ ስማችሁ፤ እነማን ነበራችሁ የታለ ገድላችሁ? ያሁኑ ስማችሁስ ማን ሰየመላችሁ? * (በደቡብ ወሎ ወግዲ ወረዳ ለሚገኙ ከዘመናት ብዛት በመፈራረስ እና በመጥፋት ያሉ ታሪካቸው በአግባቡ ያልታወቁ 13 ጥንታዊያን ፍልፍል አብያተ ክርስቲያናት፡፡ 2001 ዓ.ም) /ከዋልድባ ዋሊ ገጽ የተወሰደ/

ኅዳር 5፤ አባ ዮሐኒ ወአሞኒ፤ ዘገዳመ ዓሣይ፤ ቆላ ተንቤን (ከአስቴር ማስታወሻ /ከዋልድባ ዋሊ ገጽ/ የተወሰደ) አባ ዮሐኒ በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን መግቢያ ላይ በትግራይ ተንቤን አውራጃ በሀገረ ሰላም ቀበሌ የተወለደ ቅዱስ ነው፡፡ በዚያን ዘመን ሥርዓተ ምንኵስና ወደ ኢትዮጵያ ባይገባም አበው በምናኔ በበረሃ ይኖሩ ነበር፡፡ ከ4ኛው መ/ክ/ዘ በፊት (ሥርዓተ ምንኵስና ወደ ሀገራችን የገባው በኢትዮጵያ በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ /ከአባ መቃርስ ወደ አባ ጳኵሚስ፤ ከአባ ጳኵሚስ ወደ አባ ቴዎድሮስ፤ ከአባ ቴዎድሮስ ወደ አባ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞ) ቢሆንም የብሕትውና ኑሮ ግን በሀገራችን ከዚያም ቀድሞ እንደነበረ ከሚጠቁሙን ዋነኛ ነገሮች አንዱ የገዳመ ዓሣ/ይ/ ታላላቅቆች የኾኑ ቅዱሳን አባቶቻችን ቅዱሳን አባ አሞኒ እና አባ ዮሐኒ ዋነኞቹ ናቸው፡፡ ገዳሙ ከ1600-1800ዓመታትን ያስቈጠረ ውቅር(ፍልፍል) ቤተክርስቲያኝ ሲኾን፤ ገዳሙ ያለበት ተራረ ብቻውን ከ20ደቂቃ በላይ ያስጕዛል፤ እንደ ደረጃ ያሉ፥ ሠርጥ የኾኑና አንድ ድልድይን ካለፉ በኋላ ገዳመ ዓሣን እንዲኹም ወደ ላይ ተጨማሪ የ5 ደቂቃ ተራራ ሲወጡ አባ ዮሐኒ በሕፃንነታቸው (ከተወለዱባት እለት ጀምሮ እስከ 3 ዓመት እስከሚሞላቸው) ያደጉባን ትንሽ ዋሻ ያገኛሉ፤ የአባ አሞኒና የአባ ዮሐኒ ታሪክም ከአባ መሪና ጋር በተወሰነ መልኩ ይመሳሰላል፤ ………. ለማንኛውም ከዚህ በታች ታሪኩ ይተረካል………፡፡ አባ ዮሐኒ ከመወለዱ በፊት፤ የእናቱ ባል የተንቤን ሹም ስለበር ለዘመቻም /ለንግድም/ ይላሉ ኖባ ወደሚባል አገር ሔዶ ለሰባት ወር ያህል ዘገየ፤ ታናሽ ወንድሙም ወንድሜ ዘገየ ከእንግዲህ ወዲህ አይመለስም /ሞቷልም ይላሉ/ ስለዚህ ሚስት ትሆኚኝ ዘንድ ነዪ ቃል ኪዳን እንግባ አላት፤ እሷም የባሏ ታናሽ ወንድምና በቤቷ ውስጥ ያሳደገችው ነበረና እንዴት ደፈርከኝ ብላ ተቆጣች፤ እርሱም ተቆጥቶ ደረሰባትና ጸነሳ ወንድ ልጅ ወለደች፡፡ በወለደችበት ቀንም ከብዙ ምርኮ ጋር ባሏ ወደ አገሩ ተመለሰ፤ ወደ ቤቱም በገባ ጊዜ ሚስቱ ከቤት የለችም ነበርና ሚስቴ ወዴት ሔደች ብሎ ጠየቀ፡፡በቤቱ ውስጥ ያለ አንድ ሕፃን ባለቤትህ ታማለች አለው፤ ባለቤቷም በሽታዋ ምንድን ነው አለው? ያ ሕፃንም ዛሬ ልጅ ወለደች ብሎ መለሰለት፡፡ ይህንንም በሰማ ጊዜ ፈጽሞ ተቆጣ፤ ያ ሐፃንም እየመራው ሚስቱ ወዳለችበት ገባ ይደበድባት ጀመር፡፡ ደብረ ዓሣይ (በቆላ ተንቤን የሚገኝ) በሚባል ገዳም ስሙ አባ አሞኒ ዘናሕሶ የተባለ ገዳማዊ ነበር፤ በዚያ ገዳምም ለሃያ ዓመታት ያህል የቆየ ነው፡፡ የእግዚአብሔር መልአክም አባ አሞኒን ተነስተህ የተንቤን ሹም ወደ ሆነው ሰው ቤት ሂድ ከዚያም እግዚአብሔር የወደደውን ነገር ታገኛለህ አለው፤ አባ አሞኒም የእግዚአብሔር መልአክ እንዳዘዘው ከተራራው(ከገዳሙ) ወርዶ ወደ ተንቤን ሹም ቤት ደረሰ፤ ሚስቱም በቤቷ በር ፊት ለፊት አባ አሞኒን ባየችው ጊዜ ውስጡ ጥበበ እግዚአብሔር ነውና፤ ለባሏ የጸነስኩት ከዚህ መነኵሴ ነው አለችው፡፡ ያን ጊዜም ባሏ በቁጣ ወጥቶ አባ አሞኒን መታው፥ ደበደበው፤ ልጅህን ይዘህ ሒድ ብሎ ሕፃኑን ለአባ አሞኒ ሰጠው፡፡ አባ አሞኒም ሕፃኑ በተወለደበት ቀን በልብሱ አቀፈው፤ ወደ ገዳሙ (ደብረ ዓሣይ) ወስዶ እኔ ጡት የለኝ! ብሎ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፤ ከገደሉ ጀርባ እንደ መቃብር አስመስሎ ምድርን ቆፈረና፤ ለሕፃኑ የሰሌን ቅጠልን አንጥፎ በዚያ አስቀመጠው፥ ድንጋይም ከደነ፤ እግዚአብሔር ከወደደ ያድንህ፣ ይህቺ ጉድጓድ እናትህ ትሁን ብሎ ከዚያ ትቶት ወደ በዓቱ ሔደ፡፡ በነጋውም ማልዶ ወደዚያ ሕፃን ገሠገሠ፤ ፌቆ/ሚዳቋ የምትመስል/ ከጉድጓዱ ድንጋዩን አስወግዳ ተንበርክካ ስታጠባው አያት፤ ፌቆዋም አባ አሞኒን ባየችው ጊዜ ከጉድጓዱ ውስጥ ሸሸች፤ አባ አሞኒም ያን ሕፃን ደስተኛ ሆኖ ዓይኖቹን ባየ ጊዜ የተደነቀው ቅዱስ አሞኒ ሕጻኑን "ዮሐኒ" ሲል ስም አወጣለት፤ ትርጕሙም ወላጆችህ ወይም አሳዳጊዎችህ አራዊት ናቸው እንደ ማለት ነው:: አባ አሞኒም ይህን ዕፁብ ድንቅ ሥራ ..................... ቀሪውን ታሪክ ሳምንት ይጠብቁ ........

አክሊለ በረከቱ ለጊዮርጊስ፥ ወትምክህተ ቤቱ ለክፍለ ያዕቆብ፨ (የተፈጸመ ናሁ ማኅሌተ ጽጌን የኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ ሊቀ ካህናት ኀይለ ሥላሴ ዘማርያምና የደብራችን አስተዳዳሪ መልአከ ሰላም ፍቅረ ማርያም ምሕረቱ እየመሩት፨

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት - آمار و تحلیل کانال تلگرام @finotehiwott