fa
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

رفتن به کانال در Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

کانال Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 391 مشترک است و جایگاه 5 600 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 189 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 391 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 26 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 2 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 2 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 20.69% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 10.92% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 180 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 679 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 18 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 27 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 391
مشترکین
+224 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
+230 روز
آرشیو پست ها
መስከረም 8 ፤ 2015 ዓ.ም ፡፡ በስሊሆም የአረጋውያን እና አእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል ፡፡ ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት፡፡

#መስከረም 10 ተቀጸል ጸጌ ፤ #ግማደ_መስቀሉ ከእስክንድርያ በንጉሥ ዳግማዊ ዳዊት አማካኝነት ወደ ኢትዮጵያ የገባበት ቀን ፨ ተቀጸል ጽጌ የሚለውን ምስጢራዊ መዝሙር የጀመረው የዜማና የቅኔ መሰራች የሆነው ቅዱስ ያሬድ ነው፡፡ የመሠረተውም በ6ተኛው መቶ ክፍለ ዘመን #በአጼ #ገብረ_መስቀል ዘመነ መንግሥት ነው የክረምቱና የልምላሜው ጊዜ አልፎ የአበባውና የፍሬው ጊዜ በሚተካበት በመስከረም 25 ቀን ቅዱስ ያሬደ ውደ ንጉሡ ዙፋን ቀረቦ #ተቀጸል_ጽጌ _ገብረ_መስቀል_አጼጌ በማለት ዘምራል ፡፡ ተቀጸል ጽጌ ብዙ ምስጢር ሲኖረው ጽጌ (አበባ) የተባለ የንጉሠ ነገሥቱ #ዘውድ ነው ፤ እግዚአበሔር የንጉሡን ዘመን እንዲባርክለት ዘውዱን እንዲቀድስለት ፤ ተቀጸል ጽጌ አጼጌ ፤ #ንጉሥ_ሆይ_ዘውድን_ተቀዳጅ_እያሉ_ለንጉሡ_ይጸልዩለታል ፡፡ ሌላዉ ትርጓሜ ደግሞ ጽጌ የተባለች #ሃይማኖት ናት ፡፡ በኦሪት ቤተ መቅድስ #ያቁምና #በለዝ የሚባሉ ሁለት አዕማዶች በቀኝና በግራ ተተክለው የቅዱስ #ጴጥሮስና #ጳውሎስ ምሳሌ ሆነው ይኖሩ ነበር፡፡ በሁለቱ አዕማድ ራስ ላይ አንዲት አባባ ተቀርጻ ትታይ ነበር እሷም #የሃይማኖት ምሳሌ ነበረች፡፡ በዚሁ ዕለት በመዘምራኑ የሚነገረው ቀለም ፤ቅዱስ ጴጥሮስና ቅዱስ ጳውሎስ በሃይመኖት እልፍ ክርስቲያኖችን ማፍራታቸውን በጉልህ ያስረዳል፡፡በሃይማኖተ አበው ላይ ፤ አሕዛብ አስተጋብኡ ጽጌ ረዳ ወሦኩሰ ተረፈ በኃበ አይሁድ ( አሕዛብ አበባ ሰበሰቡ እሾህ ግን በአይዱ ዘንድ ቀረ ) ተብሎ ስለተጻፈ ጽጌ የሚለውን ቃል ሃይማኖት ተብሎ እንደሚተረጐም ታሞኖበታል ፡፡ ከዚህም በመነሳት ሊቃውንት መዘምራን ሁል ጊዜ ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ይህን ዝማሬ ለንጉሡ ያቀረባሉ ሊቃነ ጳጳቱም ከቤቱ መንግሥቱ የቀረበላቸውን የተጐነገጐነ አበባ በመስቀላቸው ባርከው ያማረውን አበባ ለንጉሡ #ያድላሉ ከዛም ደግሞ ለሌሎች አገልጋዮች እንደየ ማዕረጋቸው ይታደላል ፡፡ ይህ ስርዓት #ከአፄ_ገብረ_መስቀል ዘመነ መንግሥት እስከ #አፄ_ዳዊት_ዳግማዊ ድረስ በየዓመቱ መስከረም 25 ሲፈጸም ቆይቶ በአፄ ዳግማዊ ዳዊት አማካኝነት ግማደ መስቀሉ መስከረም 10 ወደ ኢትዮጵያ ባስገባበት ቀን እንዲከበር በሊቃውንት ተወስኖ የአፄ መስቀል ( መስቀሉ ወደ ኢትዮጵያ የገባበት )ና የተቀጸል ጽጌ በዓል እስከ ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይል ሥላሴ ድረስ በቤተ መንግሥት እና በቤተ ክህነት ሲከበረ ቆይቶ ኃላ ደግም በቤተ ክህነት እስከ አሁን ድረስ እየተከበረ ይገኛል ፡፡ ለመጨረሻም ጊዜ ለንጉሠ ነገሥቱ የተዘመረው #ለቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሲሆን #ተቀጸል_ጽጌ_ኃይለ_ሥላሴ አጼጌ ተብሎ ተዘመሮ ሲያበቃ ለሊቀ ጳጳሳቱ ድግሞ ጸሎቱን ማቅረብ ቀጥሏል፡፡ በዓሉ በቅድስት ሥላሌ ቤተክርስቲያ አሁን ድረስ ስርዓቱ በዓመት በዓመት መስከረም 10 እየተፈጸመ ይገኛል ፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፨፨፨ ፨፨ #መስቀሉ እንዴት ወደ ኢትዮጵያ እጅ ገባ ?? የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ #አባ ሚካኤል በአሕዛብ ንጉሥ በነበረው መርዋን ታሰሩ ይህ ንጉሥም ክርስቲያኖችን ማሰቃየትም ጀመረ ፡፡ በዘመኑ የነበሩት ንጉሥ አፄ #ሠይፈ አርዓድ የግብጽ ክርስቲያኖች ላይ መከራ እንዳበዛባቸው በሰሙ ጊዜ ፤ ምታ ነጋሪት ክተት ሠራዊት ብለው ወደ ግብጽ ዘመቱ ፡፡ ንጉሡ ከመድረሱም በፊት ደብዳቤ ጻፋ ፤ ሊቀ ጳጳሱን እንዲፈታና ክርስቲያኖችን እንዲተው አስተነቀቁት ፤ ደብዳቤውን ካየ በኃላ እጅግ ፈርቶ ሊቀ ጳጳሱን ከእስራት ፈታቸው ንጉሱም ለበረከት እንዲሆናቸው ከጌታ ወርቅ(የሰበዓ ሰገል ወርቅ ) ጋር እንዲቀመጥ የእጅ መንሻ ወርቅ ለሊቀ ጳጳሱ ላኩላቸው ከዛ ወደ ሃገራቸው ተመለሱ ፡፡ ከዚህ በኃላ እርሳቸው ሞተው የእመቤታቸን ወዳጅ የሆነው ልጃቸው ዳግማዊ ዳዊት ነገሠ ፡ አሕዛቡ ንጉሥ ሞታቸውን በሰማ ጊዜ አባ ሚካኤልን ዳግመኛ አሰራቸው ፤ ከዚያም የሮም የቁስጥንጥንያ የሶርያ የአርመን ፣ የግብፅ ክርስቲያኖች በአንድ ሆነው ለኢትዮጵያው ንጉሥ ለዓጼ ዳዊት፤ የክርስቶስን ሃይማኖት ለማጥፋት የአህዛብ ነገሥታት ቆመዋል የሚል መልእክት ላኩ ፡ ዓጼ ዳዊት ይህን በሰሙ ጊዜ መሃላ በመማፋረሱ ተናደዱ ፡፡መንፈሳዊ ቅንዓትም አድረባቸው፡፡ ክተት ሠረዊት ብለው ለጦር ዘምተው ካርቱም ሲደረሱ #ግዮን (አባይ )ን መልስው ወደ ካሩተም በረሐ ሰደዱት የግብፅ ሰዎች ከእርሱ በቀር የሚጠጡት የለምና ፡፡ የምስሩ ንጉሥ እና መኳኳንንቶች ይህን በሰሙ ጊዜ ያረጉት ስህተት እንደሆነ ተረዱ ደንግጠው ሊቀ ጳጳሱን አባ ሚካኤልን ፈቱዋቸው ከሞት የተረፉትን ምእመናን ነጻ አወጧቸው ፡፡ ለዓለም ክርስቲያኖች ሁሉ ያማልዱት ዘንድ ለመነ። ክርስቲያኖችም ይህንን በሰሙ ጊዜ ነጻ ላወጣቸው ንጉስ አመላካቸውን እግዚአብሔርን አመሰገኑ ፡፡ የግብፁ መኳንንት እጅ መንሻ ወደ ንጉሡ ላኩ ፡ ንጉሥ ዳዊትም ሊቀ ጳጳሱ መፈታታቸውን በሰሙ ጊዜ አስዋን ድረስ ወረዱ ይህም በጊዜው ለኢትዮጵያ እና ለግብጽ የወሰን ድካ የነበረው ነው ፡፡ ሰኔ 10 ቀን ከሊቀ ጳጳሳቱ እና ከመኳኳንንቱ ጋር ተገናኙ ፡፡ የአባይን ውሃ እንዲመልሱላቸው እልፍ ወርቅና ይዘው ቢጠይቋቸው ይህ ለኔ ነፍስ ለማዳን አይጠቅመኝም አሉ ፡፡ እኔ የምፈልገው የጌታቸንን መስቀል ነው አሉ ፡፡ እነርሱም ከተመካከሩ በኃላ መንፈሳዊ ንጉሥ መሆኑን አይተው ይገባዋል አሉ ፡፡ መስቀሉንም አስረከቧቸዉ እርሱን ብቻ ሳይሆን #ሉቃስ የሣላቸውን ሰባቱን #የእመቤታችንን ሥዕሎች ፣ #ዮሐንስ ወንጌላዊ የሣለውን የጌታቸንን #የኵርዓተ ርእሱን ሥዕል ጭምር እንጂ ፡፡ ይህ ሁሉ የሆነው #መስከረም 10 ቀን ነው በዚችም ዕለት በመላው ኢትዮጵያ ብርሃን ሆነ ፤ የኢትዮጵያ ሕዝቦችም መስቀል ኃይልነ መስቀል ጽንዕነ እያሉ ዘመሩ ይህን ልማድ በማድረግ አሁን ድረስ በዓሉ ይከበራል የበዓሉም ስም #አጼ_መስቀል እየተባለ ይጠራል፡፡ ከዚህ ቦኃላ ወደ ጥንት ላማዱ እንዲሄድ የአባይን ወንዝ መለሰው ለግብጻዊያኑ ለቀቁላቸው ፡፡ ከቅዱስ መስቀሉ ረድኤት በረከት ይክፍለን አሜን! /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

መስከረም 7 ፤ በዓለ ዕረፍቱ ለሊቀ ካህናት ዘካርያስ ወልዱ ለበራክዩ፡፡ የእናታችን የቅድስት ሐና በዓለ ልደት ነው ( ታሪኩን የነሐሴ 7 ልጥፍ ላይ ይመልከቱ ) መስከረም 8 ፡ የቅድስት ኤልሳቤጥ ዕረፍት ነው ፡፡ ——— ዕረፍቱ ለሊቀ ካህናት ዘካርያስ በዚህች ካህን የመጥመቀ መለኮት አባት ካህኑ ዘካርያስ ሰማዕትነትን ተቀብሏል ፡፡ የሞቱም ነገር እንዲህ ነው ፡፡ መጥመቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ከተወለደ በኋላ ሄሮድስ ሕፃናትን ማስገደል ጀመረ፡፡ የዘካርያስ ሚስትም ወደ ከተማ ወጥታ ነበርና ስትመለስ አገኛት ኤልሳቤጥም እጅግ አዘና በከተማ የሆነውን ነገር ነገረችው እርሱም ያውቅ ነበርና አውቃለሁ ዘመድሽ ማርያምስ እንዴት ሆና ይሆን አላት እርሳም እጅግ ስለደነገጥኩ አላውቅም አለቸው፡፡እመቤታችን ግን በዚህ ጊዜ ከዮሴፍ እና ከሰሎሜ ጋር ተሰዳ ነበር ፡፡ በእርጅና ጊዜያች ያገኝነውን ትንቢት የተነገረለትን ልጃችምም እንዳይገድሉብን ብላ ፈጽማ አዘነች ዘካርያስም ወደ ዮሐንስ ዙሮ ከዚህ በኃላ አባቴ የሚለኝ የለም ብቻኛ ለጄ አንተ ነህና ብሎ አዘነ እርሷንም ዮሐንስን ይዘሽ ወደ ምድረ በዳ ሒጂ አባቶቻችንን ቀን ከፀሐይ ንዳድ በደመና የሠወራቸው እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ይሆናል ብሎ አጽናናቶ ወደ በርሃ እንድትሸሽ ባርኮ አሰናበታት ፡፡እርሳም የከበረ ዮሐንስን ይዛ ተሰደደች፡፡ የተረገሙ የሄሮድስ ወታደሮችም ሰይፋቸውን ይዘው መጥተው ብላቴናው ወዴት አለ አሉት እርሱም ከእናቱ ጋር እንደተሰደደ እና የተሰደዱበትንም እንደማያውቅ ነገራቸው ፡፡ እነርሱም ልጅህን አምጣ ባይሆን ግን በእርሱ ፈንታ አንተን እንገድልሃለን አሉት ፡፡ እርሱም እውነቱን ነገርኳቹህ አላቸው ፡፡ በዚህ ነገር ምክንያት በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ውስጥ ካህኑ ዘካርያስን በወር ኀ መስከረም ሰባት ቀን አንገቱን ቈርጠው ገደሉት ፡፡ ሥጋውንም በአባቱ በበራክዩ መቃብር ቀበሩት ፡፡ የሊቀ ካህናት ዘካርያስ እና የእናታችን ቅድስት ኤልሳቤጥ እና ቅድስት ሐና ምልጃቸውና ጸሎታቸው አይለየን አሜን ፡፡ share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ትጉህ አገልጋይዋ ዛሬ በዕረፍተ ሥጋ ተለያት፡፡ ለ33 ዓመታት ደብራችንን በትጋት ሲያገልግል የነበረው ዲያቆን ታምሩ ኀይለ ኢየሱስ ተ/ጻድቅ በዛሬው ዕለት ንጋት ላይ ዐረፏል፡፡ ወንድማችን ዲ/ን ታምሩ፤ ፠ የንባብና የጸዋትወ ዜማ (የሰዐታትና የቅዳሴ) ትምህርቱን በታላቁ ገዳም በደብረ ሊባኖስ ተምሮ አጠናቅቋል፡፡ ፠ ወደ ደብራችን እስከ መጣበት ጊዜ ድረስም በደብረ ሊባኖስ ገዳም በሰዐታት ቋሚነት ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ፠ በ1981 ዓ.ም. ወደ ደብራችን መጥቶ ለ2ት ዓመታት በደጅ ጸኚነት ሲያገልግል ቆይቷል፤ ፠ ከ19893 ዓ.ም. በዐረፍተ ሥጋ እስከተለየበት እስከዛሬዋ ቀን ድረስ ንዋያተ ቅድሳትን (ከበሮ፣ ጸናጽል፣ መቋሚያ፣ መጻሕፈትን….) ለአገልግሎት በማቅረብ በብዙዎች ዘንድ ትኩረት የማይሰጠውን፤ ነገር ግን ትልቅ የሆነ የትሕትና አገልግሎትን ዝቅ ብሎ ደከመቸኝ ሰለቸኝ ሳይል፤ ቀን ከሌት፤ ከዕቃ ቤት ወደ ቤተ መቅደስ፥ ከቤተ መቅደስ ወደ ዕቃ ቤት፡፡ ከቤተ ክርስቲያን ለፍታት ወደ ግለሰብ ቤት፥ ከግለሰብ ቤት ወደ ቤ.ክ እያመላለሰ አገልግሏል፡፡  በደብራችን ለ33 ዓመታት በቆየበት ዓመታትም ከተቀጠረበት በተጨማሪ ያለምንም ክፍያ ለትሩፋት፤  በሰዐታት ቋሚነት፣  በደወል ደዋይነት፣  በፍትሐት አገልግሎት፤  እንዲሁም በደብራችን ላሉ አባቶቻችንና ወንድሞቻችን ዲያቆናትን በመታዘዝ አገልግሏል፡፡ ፠ አብዛኛውን ዘመኑንም የኖረው በቤተ ክርስቲያናችን ታዛ (መጠለያ /ገረገራ/) ውስጥ ያለ ምንም አልጋ፣ በወለል ላይ በመተኛት እንደ ገብረ ክርስቶስ ነበር፡፡ ፠ ወንድማችን ዲ.ን ታምሩ በዛሬዋ ዕለት መስከረም 6 ቀን 2015 ዓ.ም. ንጋት ላይ ዐርፏል፡፡ ፠፠፠ ግብዐተ መሬቱም ባደገበት፣ በተማረበትና ባገለገለበት ደብረ ሊባኖስ ገዳም ዛሬ ከቅዳሴ በኋላ ይፈጸማል፡፡ የደብራችን ካህናትም ሽኝት አድርገውለታል፡፡ እግዚአብሔር አምላችን የወንድማችንን ነፍስ በአባቶቻችን በአብርሃም፥ በይስሐቅና በያዕቆብ፤ በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ዕቅፍ ያሳርፍልን፨