fa
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

رفتن به کانال در Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

کانال Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 371 مشترک است و جایگاه 5 624 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 193 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 371 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 21 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -34 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 2 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 22.49% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 7.98% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 457 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 226 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 22 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 22 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 371
مشترکین
+224 ساعت
+327 روز
-3430 روز
آرشیو پست ها
እንኳን አደረሳችኁ "#ታኅሣሥ ፳፰፤ #ልደተ_እግዚእነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ፡፡ #በአዲስ_አበባ_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_#የጌታችን_ልደት_የበዓለ_ወልድ_የገና_ክብረ_በዓል_የሚከብርባቸው ፳፰ ገዳማትና አድባራት፡፡ ክብረ በዓሉ የሚከበርበት ምክንያት፤ የጌታችንና የአምላካችን የመድኀኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት፤ ልዩ ማስታወሻ፤  ከቅዱሳንም ሆነ ከእመቤታችን በላይ የጌታችን በዓል ከዋለ የጌታችን በዓል በዋነኛነት ስለሚከበር፤ ጾምም ከሆነ ጾሙ ቀርቶ በዓል ስለሚደረግ፤ በዓላቸው በዚህ ቀን የኾኑ ቅዱሳን በዓላቸው በሌላ ቀን ቅያሬ ሲከበር ነገር ግን በቦታቸው ላይ የጌታችን ልደት በልዩ ሁኔታ ይከበራል፡፡ ነገር ግን የጌታችን ልደት፤ ከ9ኙ ዐበይት የጌታችን በዓላት አንዱ በመኾኑ፤ በሁሉም ገዳማትና አድባራት ዋይዜማ ተዚሞ፥ ማኅሌት ተቁሞ፥ ሰዐታት ተቁሞ፥ ኪዳን ተደርሶ፥ ቅዳሴ ተቀድሶ ይከበራል፡፡ #በመዲናችን_በአዲስ_አበባ_የሚከብርባቸው_፰ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. አዲስ አበባ መካነ ሥላሴ ቅዱስ በዓለ ወልድ (አዲስ አበባ ላይ በ1883 ዓ.ም. የተመሠረተ፤ ነገር ግን ታቦቱ ቀድሞ የነበረና ከ600 ዓመታት በላይ ታሪክ ያለው) አድራሻ፤ አራዳ ከተማ ክፍለ ከተማ፤ 4ኪሎ ታክሲ፤ ከፒያሳ → አራት ኪሎ ፪. ለቡ ደብረ ታቦር በዓለ ወልድና አበ ብዙኃን አብርሃም ገዳም አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ለቡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ለቡ ፫. ጽርሐ ንግሥት ቅድስት ሐና ቤ/ክ አድራሻው፤ ሐና፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሐና፡፡ ፬. አንቀፀ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (የቅዱስ ላሊበላ ታቦት በድርብነት ይወጣል) አድራሻ፤ የካ_ክፍለ_ከተማ፥ ራስ ካሣ ታክሲ፤ ከ4 ኪሎ →  ፈረንሳይ →  አንቀጸ ምሕረት (ራሳ ካሣ ሚካአል) ፭. ፊሊዶሮ መድኀኔዓለም ቅዱስ ላሊበላ፡፡ አድራሻው፤ ፊሊዶሮ፡፡ ታክሲ፤ ከመርካቶ → ኮልፌ(ፊሊዶሮ)፡፡ ፮. አዲስ አምባ ደብረ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕትና ደብረ ፍስሐ ቅዱስ ገብርኤል አድራሻው፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ሳሪስ አዲስ ሰፈር፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሳሪስ አዲስ ሰፈር፡፡ ፯. መካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል (ቅዱስ በዓለ ወልድ በድርብነት ይከብራል) አድራሻው፤ መካኒሳ፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መካኒሳ ፰. ኮልፌ ቀራንዮ (ታቦት ማደርያ) ደብረ ተአምራት ዳግማዊ ጻድቃኔ ማርያም፡፡  (ቅዱስ በዓለ ወልድ በድርብነት ይከብራል) አድራሻ፤ ዘነበወርቅ ታቦት ማደሪያ ጀርባ፤ ከዘነበወርቅ ወደ ታቦት ማደሪያ በሚወስደው መንገድ ላይ፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ →  ጦር ኃይሎች →  ዘነበ ወርቅ፡፡ #በሃገራችን_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከብርባቸው_፳፩ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. ቤተልሔም፥ እስራኤል፥ ኢየሩሳሌም (ጌተችን የተወለደባት) አድራሻ፤ እስራኤል፥ ኢየሩሳሌም፤ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ቦሌ አየር መንገድ (በአውሮፕላን) → እስራኤል ፪. ማኅበረ ሥላሴ ገዳም (የሺዎች ገዳም)፤ (ለመጀመሪያ ጊዜ ጌታ በተወለደባት ዕለት የጌታችን መወለድ በኢትዮጵያ የተበሠረባት) አድራሻ፤ ምዕራብ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ቋራና (መተማ) ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ጎንደር → ሸዲ/መተማ/ ፫. ደብረ ሮሐ ላስታ ቅዱስ ላሊበላ (ዳግማዊት /አምሳለ/ ኢየሩሳሌም) አድራሻው፤ ሰሜን ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ላስታ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ላሊበላ ፬. መንበረ ልዑል ደብረ መጕና አቡነ አብሳዲ ወቅድስት ኪዳነ ምሕረት ወማኅበረ በኵር ገዳም፡፡ አድራሻ፤ ምዕራብ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ትራንስፖርት፤ ከጎንደር ከተማ → ዳንሻ መስመር ላይ → በበው የምትባል መንደር ላይ ተወርዶ → የእግር ጕዞ ፭. ዞዝ አንባ አቡነ አብሳዲ (ቅዱስ ላሊበላ ከፈለፈላቸው አንዱ) አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ በለሳ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ማክሰኚት → በለሳ (ዞዝ አንባ) ፮. ምድረ ከብድ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አድራሻ፤ ጉራጌ ስልጤ ሃገረ ስብከት፥ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ምደረ ከብድ ፯. ርዕሰ አድባራት አደባባይ ኢየሱስ ቤ.ክ.፤ /ጽላቱ ከደበቡ ኢትዮጵያ የሄደ፥ እጅግ ጥንታዊ ታሪክ ያለው፥ ኋላ ላይ ቊጥሩ ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ የሆነ/ አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፥ አራዳ፥ ጃንተከል ወርካ ጋር ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቱቡስ ተራ → ጎንደር ፰. ደብረ ስብሐት ቀሃ ኢየሱስ፤ (ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ፤ የጎንደር ላይ ቤት አቋቋም ትምህርት ቤት ማስመስከርያ) አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፥ ጥምቀተ ባሕሩ አጠገብ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቱቡስ ተራ → ጎንደር ፱. አለም ገና ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (በድርብነት ይከብራል)፤ አድራሻ፤ ምዕራብ ሸዋ ሃገረ ስብከት ፥ አለም ገና ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → አለም ገና፡፡ ፲. ገፈርሳ(ታጠቅ) በዓለ ወልድ ወአቡነ ሳሙኤል ወአቡነ ኪሮስ፤ አድራሻው፤ ምዕራብ ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ገፈርሳ ትራንስፖርት፤ ከመርካቶ አውቶቡስ ተራ → ታጠቅ ወይም መናገሻ የሚል ትራንስፖርት ይዘው ገፈርሳ ድልድዩ ጋር በዓለ ወልድን ያገኛሉ፡፡ ፲፩. አሸዋ ሜዳ ቤሮ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ላሊበላ ቤተክርስቲያን፤ አድራሻ፤ ምዕራብ ሸዋ ሃገረ ስብከት ፥ ወልመራ ወረዳ፥ (አዲስ ዓለም አካባቢ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ → አምቦ (አዲስ ዓለም) ፲፪. ቂልጠፋት በዓለ ወልድ አድራሻ፤ ጉራጌና ስልጤ ሃገረ ስብከት፥ እንደጋይ ወረዳ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ጉራጌ ፲፫. ጉንችሬ በዓለ ወልድ፤ አድራሻ፤ ጉራጌና ስልጤ ሃገረ ስብከት፥ እነሞር ወረዳ) ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ጉራጌ ፲፬. ደብረ ገሊላ ቅዱስ በዓለ ወልድ ወሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን፤ አድራሻ፤ አሜሪካ ሃገረ ስብክት፥ ሲያትል ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ቦሌ አየር መንገድ (በአውሮፕላን)→ አሜሪካን (ሲያትል) ፲፭. ሆሳዕና ደብረ ምሕረት ቅዱስ በዓለ ወልድ፤ አድራሻ፤ ጉራጌ ሀገረ ስብከት፤ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ሆሳዕና ፲፮. ቡኢ ደብረ ሰላም በዓለ ወልድ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ደቡብ ሃገረ ስብከት፥ ቡኢ፤ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ቡኢ ፲፯. ባሕር ዳር በዓለ ወልድ (በዐለ እግዚአብሔር) ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ባሕር ዳር ሃገረ ስብከት፥ ባሕር ዳር ከተማ፥ ቀበሌ 13፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር፡፡ ፲፰. ወለንጪቲ ጨመሪ በዓለ ወልድ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ደቡብ ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ወለንጪቲ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ወለጪቲ፡፡ ፲፱. ወንዶ ገነት በዓለ ወልድ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ሳዲማ ሃገረ ስብከት፥ ወንዶ ገነት፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ወንዶ ገነት፡፡ ፳. ደብረ ምሕረት ዱና በዓለ ወልድ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ዱና፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አውቶቡስ ተራ → ዱና፡፡ ፳፩. ደብረ ገነት በዓለ ወልድ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤  ሃገረ ስብከት፥ ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አውቶቡስ ተራ → ደብረ ገነት፡፡ -- ፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/    #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram...

እንኳን ለአምላካችንና ፈጣሪያችን ቅዱስ አማኑኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላምና በጤና አደረሰን ፥ አደረሳችሁ፡፡ ክብረ በዓሉ ከሚከበርባቸው ገዳማትና አድባራት ዐበይቶቹ (እናንተም የምታውቋቸውንና በአቅራቢያችሁ ያሉትንከነፎቷቸው ጨምሩበት) ፠ ኦፍና አማኑኤል፤ መርሐ ቤቴ፥ አለም ከተማ፤ በ4ኛው ክፍለ ዘመን የተመሠረተ ጥንታዊ ቤ.ክ. ፠ ኤነር አማኑኤል፤ ምድረ ጕራጌ፤ እጅግ በጣም ጥንታዊ ገዳም ፠ ደብረ መንክራት በጎል ሰከበ ሚጣቅ ቅዱስ አማኑኤል፤ ከደብረ ብርሃንና አንኮበር መሃል ላይ የሚገኝ፤ በንጉሥ ሣህለ ሥላሴ የተመሠረተ፤ እጅጉን በጣም ፈዋሽ የኾነ ጠበል የሚገኝበትና የቅዱሳን መናኸሪያ የኾነ፡፡ ፠ ጫገል ቅዱስ አማኑኤል /በደብረ ሊባኖስ ገዳም ከሚተዳደሩ አብያተ ክርስቲያናት አንዱ/ ፠ ደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል፣ አዲስ አበባ፤ መርካቶ መሳለሚያ ፠ ባሶ ወረዳ ጣፎ ደብረ ሰላም ቅዱስ አማኑኤል ቤተክርስቲያን፤ ከጢያ ከተማ ወደ አጠገብ የሚገኝ፡፡

እንኳን አደረሳችኁ "#ታኅሣሥ ፳፱፤ #ልደተ_እግዚእነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ፡፡ #በአዲስ_አበባ_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_ #የጌታችን_ልደት_የበዓለ_ወልድ_የገና_ክብረ_በዓል_የሚከብርባቸው ፳፱ ገዳማትና አድባራት፡፡ ክብረ በዓሉ የሚከበርበት ምክንያት፤ የጌታችንና የአምላካችን የመድኀኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት፤ ልዩ ማስታወሻ፤  ከቅዱሳንም ሆነ ከእመቤታችን በላይ የጌታችን በዓል ከዋለ የጌታችን በዓል በዋነኛነት ስለሚከበር፤ ጾምም ከሆነ ጾሙ ቀርቶ በዓል ስለሚደረግ፤ በዓላቸው በዚህ ቀን የኾኑ ቅዱሳን በዓላቸው በሌላ ቀን ቅያሬ ሲከበር ነገር ግን በቦታቸው ላይ የጌታችን ልደት በልዩ ሁኔታ ይከበራል፡፡ ነገር ግን የጌታችን ልደት፤ ከ9ኙ ዐበይት የጌታችን በዓላት አንዱ በመኾኑ፤ በሁሉም ገዳማትና አድባራት ዋይዜማ ተዚሞ፥ ማኅሌት ተቁሞ፥ ሰዐታት ተቁሞ፥ ኪዳን ተደርሶ፥ ቅዳሴ ተቀድሶ ይከበራል፡፡ #በመዲናችን_በአዲስ_አበባ_የሚከብርባቸው_፰ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. አዲስ አበባ መካነ ሥላሴ ቅዱስ በዓለ ወልድ (አዲስ አበባ ላይ በ1883 ዓ.ም. የተመሠረተ፤ ነገር ግን ታቦቱ ቀድሞ የነበረና ከ600 ዓመታት በላይ ታሪክ ያለው) አድራሻ፤ አራዳ ከተማ ክፍለ ከተማ፤ 4ኪሎ ታክሲ፤ ከፒያሳ → አራት ኪሎ ፪. ለቡ ደብረ ታቦር በዓለ ወልድና አበ ብዙኃን አብርሃም ገዳም አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ለቡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ለቡ ፫. ጽርሐ ንግሥት ቅድስት ሐና ቤ/ክ አድራሻው፤ ሐና፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሐና፡፡ ፬. አንቀፀ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (የቅዱስ ላሊበላ ታቦት በድርብነት ይወጣል) አድራሻ፤ የካ_ክፍለ_ከተማ፥ ራስ ካሣ ታክሲ፤ ከ4 ኪሎ →  ፈረንሳይ →  አንቀጸ ምሕረት (ራሳ ካሣ ሚካአል) ፭. ፊሊዶሮ መድኀኔዓለም ቅዱስ ላሊበላ፡፡ አድራሻው፤ ፊሊዶሮ፡፡ ታክሲ፤ ከመርካቶ → ኮልፌ(ፊሊዶሮ)፡፡ ፮. አዲስ አምባ ደብረ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕትና ደብረ ፍስሐ ቅዱስ ገብርኤል አድራሻው፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ሳሪስ አዲስ ሰፈር፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሳሪስ አዲስ ሰፈር፡፡ ፯. መካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል (ቅዱስ በዓለ ወልድ በድርብነት ይከብራል) አድራሻው፤ መካኒሳ፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መካኒሳ ፰. ኮልፌ ቀራንዮ (ታቦት ማደርያ) ደብረ ተአምራት ዳግማዊ ጻድቃኔ ማርያም፡፡  (ቅዱስ በዓለ ወልድ በድርብነት ይከብራል) አድራሻ፤ ዘነበወርቅ ታቦት ማደሪያ ጀርባ፤ ከዘነበወርቅ ወደ ታቦት ማደሪያ በሚወስደው መንገድ ላይ፡፡ ታክሲ፤ ከፒያሳ →  ጦር ኃይሎች →  ዘነበ ወርቅ፡፡ #በሃገራችን_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከብርባቸው_፳፩ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. ቤተልሔም፥ እስራኤል፥ ኢየሩሳሌም (ጌተችን የተወለደባት) አድራሻ፤ እስራኤል፥ ኢየሩሳሌም፤ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ቦሌ አየር መንገድ (በአውሮፕላን) → እስራኤል ፪. ማኅበረ ሥላሴ ገዳም (የሺዎች ገዳም)፤ (ለመጀመሪያ ጊዜ ጌታ በተወለደባት ዕለት የጌታችን መወለድ በኢትዮጵያ የተበሠረባት) አድራሻ፤ ምዕራብ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ቋራና (መተማ) ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ጎንደር → ሸዲ/መተማ/ ፫. ደብረ ሮሐ ላስታ ቅዱስ ላሊበላ (ዳግማዊት /አምሳለ/ ኢየሩሳሌም) አድራሻው፤ ሰሜን ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ላስታ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ላሊበላ ፬. መንበረ ልዑል ደብረ መጕና አቡነ አብሳዲ ወቅድስት ኪዳነ ምሕረት ወማኅበረ በኵር ገዳም፡፡ አድራሻ፤ ምዕራብ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ትራንስፖርት፤ ከጎንደር ከተማ → ዳንሻ መስመር ላይ → በበው የምትባል መንደር ላይ ተወርዶ → የእግር ጕዞ ፭. ዞዝ አንባ አቡነ አብሳዲ (ቅዱስ ላሊበላ ከፈለፈላቸው አንዱ) አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ በለሳ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ማክሰኚት → በለሳ (ዞዝ አንባ) ፮. ምድረ ከብድ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አድራሻ፤ ጉራጌ ስልጤ ሃገረ ስብከት፥ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ምደረ ከብድ ፯. ርዕሰ አድባራት አደባባይ ኢየሱስ ቤ.ክ.፤ /ጽላቱ ከደበቡ ኢትዮጵያ የሄደ፥ እጅግ ጥንታዊ ታሪክ ያለው፥ ኋላ ላይ ቊጥሩ ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ የሆነ/ አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፥ አራዳ፥ ጃንተከል ወርካ ጋር ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቱቡስ ተራ → ጎንደር ፰. ደብረ ስብሐት ቀሃ ኢየሱስ፤ (ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ፤ የጎንደር ላይ ቤት አቋቋም ትምህርት ቤት ማስመስከርያ) አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፥ ጥምቀተ ባሕሩ አጠገብ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቱቡስ ተራ → ጎንደር ፱. አለም ገና ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (በድርብነት ይከብራል)፤ አድራሻ፤ ምዕራብ ሸዋ ሃገረ ስብከት ፥ አለም ገና ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → አለም ገና፡፡ ፲. ገፈርሳ(ታጠቅ) በዓለ ወልድ ወአቡነ ሳሙኤል ወአቡነ ኪሮስ፤ አድራሻው፤ ምዕራብ ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ገፈርሳ ትራንስፖርት፤ ከመርካቶ አውቶቡስ ተራ → ታጠቅ ወይም መናገሻ የሚል ትራንስፖርት ይዘው ገፈርሳ ድልድዩ ጋር በዓለ ወልድን ያገኛሉ፡፡ ፲፩. አሸዋ ሜዳ ቤሮ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ላሊበላ ቤተክርስቲያን፤ አድራሻ፤ ምዕራብ ሸዋ ሃገረ ስብከት ፥ ወልመራ ወረዳ፥ (አዲስ ዓለም አካባቢ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ → አምቦ (አዲስ ዓለም) ፲፪. ቂልጠፋት በዓለ ወልድ አድራሻ፤ ጉራጌና ስልጤ ሃገረ ስብከት፥ እንደጋይ ወረዳ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ጉራጌ ፲፫. ጉንችሬ በዓለ ወልድ፤ አድራሻ፤ ጉራጌና ስልጤ ሃገረ ስብከት፥ እነሞር ወረዳ) ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ጉራጌ ፲፬. ደብረ ገሊላ ቅዱስ በዓለ ወልድ ወሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን፤ አድራሻ፤ አሜሪካ ሃገረ ስብክት፥ ሲያትል ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ ቦሌ አየር መንገድ (በአውሮፕላን)→ አሜሪካን (ሲያትል) ፲፭. ሆሳዕና ደብረ ምሕረት ቅዱስ በዓለ ወልድ፤ አድራሻ፤ ጉራጌ ሀገረ ስብከት፤ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ሆሳዕና ፲፮. ቡኢ ደብረ ሰላም በዓለ ወልድ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ደቡብ ሃገረ ስብከት፥ ቡኢ፤ ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ → ቡኢ ፲፯. ባሕር ዳር በዓለ ወልድ (በዐለ እግዚአብሔር) ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ባሕር ዳር ሃገረ ስብከት፥ ባሕር ዳር ከተማ፥ ቀበሌ 13፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር፡፡ ፲፰. ወለንጪቲ ጨመሪ በዓለ ወልድ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ደቡብ ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ወለንጪቲ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ወለጪቲ፡፡ ፲፱. ወንዶ ገነት በዓለ ወልድ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ሳዲማ ሃገረ ስብከት፥ ወንዶ ገነት፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ወንዶ ገነት፡፡ ፳. ደብረ ምሕረት ዱና በዓለ ወልድ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤ ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ ዱና፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አውቶቡስ ተራ → ዱና፡፡ ፳፩. ደብረ ገነት በዓለ ወልድ ቤ.ክ.፤ አድራሻ፤  ሃገረ ስብከት፥ ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. አውቶቡስ ተራ → ደብረ ገነት፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/    #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram...

የቀኝ ጌታ ዮሐንስ ቀብር ተፈጸመ #በየኔታ_ቀጸላ_ፈንቴ_የተደረገ_ቅኔ '' ተፈነወ ዮሐንስ መንገለ ኤፌሶን መቃብር ፥ ከመ ይንሥኡ ሕዝብ  ዘሙሴ  ፥በዘዮሐንስ ትምህርት  አምጣነ በጽሐየ ኤፌሶን መቃብር ፥ ወኢታፈቅር እንከ ለዝንቱ ዓለመ ሄኖክ ሕይወት ፥ ኦ አእሩግ ወሕፃን ፥ ይቤ ዮሐንስ ዘከመ ሰማዕት ያፈቅሮ እግዝእነ ሞት ። '' አባታችን ቀኝ ጌታ ዮሐንስ በትሩፋት አገልግሎት ማኅሌቱን ደከመኝ ሳይሉ ቤተ መቅደስ አስቀድሞ ከመከፈቱ  እስከ ቅዳሴ ፍጻሜ ጠንቅቀው የሚያገለግሉ  ትጉህ አገልጋይ ነበሩ ።

ሥርዓተ ግብዓተ መሬታቸው ዛሬ ቀን 23 / 0 4 /2016 ዓ.ም ፤ በደብራችን በቀጨኔ ደብረሰላም መድኀኔዓለም ከ5 – 6 ይፈጸማል ::

#ዜና_እረፍት ወኢትጸመም ሞቶ ለዘ ተልአከከ .... ( ያገለገለህን ሰው ሞት ቸል አትበል ሲራክ 38 ÷ 16 በ ቀ/ደ/ሰ/መድኀኔዓለም ወደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ለረጅም ዓመታት አገልጋይ የ
+3
#ዜና_እረፍት ወኢትጸመም ሞቶ ለዘ ተልአከከ .... ( ያገለገለህን ሰው ሞት ቸል አትበል  ሲራክ 38 ÷ 16 በ ቀ/ደ/ሰ/መድኀኔዓለም ወደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ለረጅም ዓመታት አገልጋይ የነበሩት የደብራችን አገልጋይ  ቀኝ ጌታ ዮሐንስ ከዚህ ዓለም ድካም  በሥጋ ሞት ተለይተውናል። ለደብራችን አገልጋዮች፣ ለቤተሰቦቻቸው ፣ ለሰንበት ት/ቤቱ አባላትና ለምእመናን መድኀኔዓለም መጽናናትን ያድልልን።      ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት

እንኳን አደረሳችኁ በዓለ_ልደቱ_ለሐዲስ_ሐዋርያ_ፀሐይ_ማር_አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት አቡነ ተክለ ሃይማኖት ታኅሣሥ 24 1196 ዓም በሰሜን ሸዋ ቡልጋ ጽላልሽ እቲሣ ተወልደው በአጠገቡ በምትገኛዋ ደብረ አጋዕዚት ክርስትና_ተነሡ፡፡ #አባታቸው ቅዱስ ጸጋ ዘአብና እናታቸው ቅድስት እግዚእ ኀረያ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሲያስተምሯቸው በአካባቢያቸው ደግሞ በዘመኑ የነበሩ ልጆች ይማሩ የነበረውን ፈረስ መጋለብን፣ ቀስት መወርወርን፣ እርሻንና አደንን አስተምረዋቸዋል፡፡ #በ7ት ዓመታቸው ከግብፃዊው ጳጳስ አቡነ ቄርሎስ ዲቁናን ከተቀበሉ በኋላ እግዚአብሔር በክህነት ሕዝቡን እንዲያገለግሉ መረጣቸው፡፡ ከዮዲት ጉዲት በኋላ ሃገራችን ሰሜኑና ደቡቡ ተቆራርጧል፤ የሐሳብን ልዕልና የሚያመጣው የመንፈስ ልዕልና ተዳክሟል፡፡ ለዚህም ኢትዮጵያን የሚዋጅ ሐዲስ ሐዋርያ ያስፈልግ ነበርና አምላካችን አቡነ ተክለ ሃይማኖትን ጠራ፡፡ #አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቅስናን ከአቡነ ቄርሎስ ተቀብለው በጽላልሽ አካባቢ በክህነት ከአባታቸው ጋር አገልግለዋል፡፡ አባታቸው ሲያርፉ በወንጌሉ ማንም ሊከተለኝ የሚወድድ ቢኖር  ያለውን ሁሉ ትቶ መስቀሉን ተሸክሞ ይከተለኝ ያለውን በመከተል ሀብታቸውን ለድኾች መጽውተው በሸዋና በዳሞት በስብከተ ወንጌል አገለገሉ፡፡ ከዚያም፤ #በመጀመርያ ደቡብ ወሎ ቦረና ላይ ገዳማቸውን ደብረ ጎል ገድመው ወደሚገኙት ታላቁና ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን ወደኾኑት ጻድቅ አባት አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ገብተው ዐሥር ሁለት ዓመታት በትምህርትና በሥራ (በአርድእትነት) አሳልፈዋል፡፡ በዚያም ዋሻ ፈልፍለው አስደናቂ ሕንፃ ሠርተው ነበር፡፡ #በ1216 ዓ.ም. አካባቢ ወደ ሐይቅ እስጢፋኖስ ገሳም ገብተዋል፤ በዚሁ ገዳምም ከመመንኰሳቸው በፊት ሰባት ዓመት ከመነኰሱም በኋላ ሦስት ዓመት በድምሩ ለ10 ዓመታት በትምህርት፣ በእደ ጥበብ ሥራ፣ በአገልግሎትና ሥርዓተ ምንኩስናን እያጠኑ ቆይተዋል፡፡ #ከሐይቅ ወጥተው በዘመኑ በሥርዐተ ምንኩስናና በትምህርት ብሎም በጥበበ እድ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ወደ ነበረው ወደ ደብረ ዳሞ በመሄድ በየገዳሙ አበምኔት ከሆኑት ከአቡነ ዮሐኒ ዘንድ መንፈሳዊ ትምህርት ፣ ሥርዐተ ምንኩስናና ጥበበ እድ ሲማሩ ለ12 ዓመታት ቆዩ ፡፡ ያነጹት ፍልፍል ድንጋይ ዋሻ፣ መጻሕፍት ሲጽፉ ቀለማቸውን ያስቀምጡባቸው የነበሩትን ሽንቁሮች ዛሬም በደብረ ዳሞ ማየት ይቻላል፡፡ #በደብረ ዳሞ የነበራቸውን ቆይታ ጨርሰው በገመድ ሲወርዱ ሰይጣን በቅንዐት መጥቶ ገመዱን በጠሰባቸው እግዚአብሔር አምላክ በዚህ ወቅት የሚበሩበትን እንደ መላእክት ክንፍ ሰጣቸው፡፡ #ለአምስት ዓመታት #አኵስምን_ዋልድባን እንዲሁም ሎሎች የትግራይ ገዳማትን እየተዘዋወሩ ሲመለከቱ ቆዩ #ከሸዋ በወጡ በሃያ ሁለት ዓመት (እድሜያቸው ሃምሳ ሁለት ሲሆን) ለበለጠው ክብር እና ርእይ በግብጽ በኩል ወደ ኢየሩሳሌም ተሻገሩ፡፡ #ከኢየሩሳሌም ሲመለሱ በሐይቅ በኩል አድርገው ደብረ ጎልን ተሳልመው በሚዳ እና በመርሐ ቤቴ በኩል ወደ ሸዋ በመምጣት ከዮዲት ዘመን በኋላ በመንፈሳዊ ሕይወት የተጎዳውን ሸዋን እና ደቡብ ኢትዮጵያን በመዘዋወር ለዐሥር ዓመታት ያህል አስተምረዋል፡፡ #አቡነ ተክለ ሃይማኖት ተግተው በማስተማራቸው የተኛው ሁሉ ነቃ፣ የደከመው በረታ፣ የጠፋውም ተገኘ፡፡ ሐዋርያትን ለማፍራት እንዲችሉ አንድ ገዳም ለመመሥረትና ደቀ መዛሙርትን ለማስተማር አሰቡ፡፡ እናም ወደ ደብረ አስቦ ገዳም ገቡ ፡፡ ቦታውን አስተካክለው እና ከደብረ ዳሞ እና ከሐይቅ የተከተሏቸውን ጥቂት ደቀ መዛሙርት ይዘው በደብረ ሊባኖስ ገዳም ልክ እንደ ሐይቅ እስጢፋኖስ ሁሉ ሦስቱን ነገሮች ያካተተ አገልግሎት ጀመሩ፡፡ ምንኩስና፣ ትምህርትና ሥራ፡፡ መነኮሳቱ መንፈሳዊ ትምህርት ይማራሉ፤ በሕገ ገዳም ይመራሉ፤ ለራሳቸው እና ለአካባቢው ሕዝብ ርዳታ የሚሆን እርሻ ያርሳሉ፡፡ #ደቀ መዛሙርትን አፍርተው፣ ገዳማቸውን አደራጅተው፣ ስብከተ ወንጌልንም አስፋፍተው ካደላደሉ በኋላ በሕይወታቸው የመጨረሻ ዓመታት ወደ ደብረ አስቦ ዋሻ ገብተው በአንድ እግራቸው በጾም እና በጸሎት ተወሰኑ፡፡ #አገልግሎታቸውን ፈጽመው ነሐሴ 24 ቀን 1297 ዓ.ም. በ99 ዓመታቸው ዐረፉ፡፡ ✤✤ #እቲሣ_ገዳም_ #በቅዱሳን ነገሥታት አብርሃ ወአጽብሃና አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን የተመሠረተ፤ ሲመሠረትም በታቦተ ኢየሱስና አርባዕቱ እንስሳ ነው፤ #ሊቀ ካህናት አበይድላ ከአኵስም 300 ታቦታትና 300ካህናት ይዞ መጥቶ በጽላልሽ የተቀመጠባት ናት፤ #ፀሐይ አቡነ ተክለሃይማኖት የተወለዱባት (የተወለዱባት ጠፍጣፋ ደንጊያ አሁንም በቦታው አለች)፣ #አባታቸውና ጸጋ ዘአብና እናታቸው እግዚእኀረያ የተወለዱበት፤ ኋላም ክብሩ አጽማቸው ያረፈበት ነው፡፡ #ቅዱስ ያሬድ 3 ዓመት ጸልዮባታል፤ #ቅዱስ ላሊበላ 7 ዓመት ጸልዮባታል፤ #ተሰዓቱ ቅዱሳን 20 ዓመት የጸለዩበት፤ #ሐርቤ በሚባለው ቦታ ላይ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ 7 ዓመት ጸልየውበታል፤ #ታቦተ ጽዮን 12 ዓመት (ከ9ሺህ ሕዝብ) ጋር መጥታ ኖራበታለች፤ #በአምሳለ ሲዖል የተሠራ አስደናቂ የጨለማ ዋሻ ያለበት ነው፤ #ብዙ የታሪክ ቅርስ ያለበት ነው፤ #በቅዱስ ሚካኤልና ጸጋ ዘአብ ቤተ ክርቲያን ውስጥ ካየን በኋላ፤ እዚሁ ቦታ በሚገኘው ፈዋሽ ጠበል ተጠምቀንና ጠጥተን ጕዟችንን ወደ ቦታው ከአ.አ በቅርብ ርቀት በደብረ ብርሃን መንገድ አሌልቱ ከተማ ላይ በመታጠፍ ይገኛል፡፡ #ሥርዐተ_ማኅሌቱን እንደየደብራችሁ ይትበሃል እንድትጠቀሙበት (በላይ ቤትና በታች ቤት) (#ዘአባጃሌ_ተክለ_ሃይማኖትና_ዘአደባባይ_ተክለሃይማኖት) አዘጋጅተነዋል፡፡ ጸሎትና በረከታቸው ፤ ረድኤትና ምልጃቸው በመላው ሕዝበ ክርስቲያንና በቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ሁሉ አድሮ ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/    #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot      www.finotehiwotsundayschool.com #ኢትዮጵያውያን_ቅዱሳን