fa
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

رفتن به کانال در Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

کانال Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 378 مشترک است و جایگاه 5 573 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 194 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 378 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 06 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 32 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -4 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 22.44% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 9.50% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 449 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 461 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 20 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 07 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 378
مشترکین
-424 ساعت
-257 روز
+3230 روز
آرشیو پست ها
‹‹እንበይነ አውሎጊስ ለዳንኤል አመ አርአዮ ስቅለተ፤ ከመ እገሪሁ ሰዓምኪ ወሰአልኪዮ ምሕረተ፡፡ ለተአምረ ሣህል ወልድኪ በእንተ ፍቅረ ሰብእ ዘሞተ፤ እንዘ ታዘክሪዮ ድንግል ይምሐረኒ ሊተ፤ ከናፍሪሁ ጽጌ አንኂ ስዕመተ፡፡›› ፠ #አባ_ዳንኤል_፤ እንጀራን ዓሣንም ቢሆን ማርንም ዘይትንም ቢሆን ከብቻው ቅጠል በቀር ሳይቀምስ ፵ ዓመት ተኩል በአስቄጥስ ገዳም ኖረ፡፡ ዜናውም በአስቄጥስ ገዳምና በዓለም ሁሉ ተሰማ፥ የነገሥታት ልጆችም ወደ እርሱ እየመጡ እየተባረኩ ይሄዱም ነበር፤ ግማሾቹም በዚያው ይመነኵሱ ነበር፡፡ ከብዙ ዘመንም በኋላ መነኰሳትን የሚፈትን የመመካት ጾር (‹‹በገዳም ውስጥ እንደእኔ ትርሕምትን ገንዘብ ያደረገ ይኖር ይሆን?›› የሚል) መጣበት፡፡ ይህ ፈተና አንድ ጊዜ ታላቁን ቅዱስ አባ መቃርስን በፈተነው ጊዜ ሰውን የሚወድ ቸሩ አምላካችን አባ መቃርስን ወደ ከተማ እንዲኼድና የወንድማማች ሚስቶችን ኹነው ልጆቻቸውን እያሳደጉ በከተማ ከሚኖሩት ኹለት ገድለኛ እናቶች እንዲማርና ጾሩ እንዲጠፋለት አድርጓል። አሁንም ይህ ታላቅ ቅዱስ አባ ዳንኤል የመጣበትን ጾር ቢመለከት መልአከ እግዚአብሔር ተገለጠና ወንድሜ፣ ቸሩ አምላካችን ክርስቶስ እንዲህ ያለውን የመመካት ከትሕትናና ከፍቅር በቀር አይወድምና ተው አለው። ፠ አባ ዳንኤልም ጌታዬ ይህን እንድተውና ጦሩም እንዲጠፋልኝ ከኔ የሚበልጥ ጻድቅ አሳየኝ አለው፡፡ መልአኩም በሮሜና በቊስጥንጥንያ የነገሠ ንጉሥ ኹኖ ሳለ ነገር ግን በገድሉ ጽኑዕ ታጋይ ተጋዳይ መነኰስ የሆነውን #የጻድቁን_አኖሬዎስን_ ነገር ነገረው። አባ ዳንኤልም ይህን ሲሰማ በምድር ላይ ተደፋና በራሱ ላይ አመድ ነስንሶ አለቀሰ፤ በኋላም ይህን ገድለኛ ንጉሥ ሊያየው ወደደና ጸለየ፡፡ ‹‹ንጉሥ አኖሬዎስም የመነኰሳትን ሥራዎች ሁሉ ስለሚሠራ ከልብሰ መንግሥቱ ሥር በሥጋው ላይ ማቅ ይለብስ ነበር›› ተብሎ የተመሠከረለት ነው፡፡ ፠ ብርህት ደመናም አባ ዳንኤልን መጣችለትና ተጭኖ ወደ ሮሜው ንጉሥ ዘንድ ኼደ፡፡ እንደደረሰም አገልጋዩን ጠርቶ እባክህ ወንድሜ ንጉሡን ማግኘት እሻለሁና የሚያገናኘኝን መኰንን አገናኘኝ አለው፡፡ እርሱም እኔ ባስገባህስ አትገባምን? አለው፤ እግዚአብሔር ይባርክህ ልጄ አስገባኝ አለው፤ አባቴ ሆይ ግን ምድራዊ የሆነ ሟች ፈራሽ ንጉሥን ስለምን ማየትን ወደድህ አለው፣ እርሱም ቸሩ ጌታዬ ስላዘዘኝ እንጂ ነው አለው፤ በኋላም ቆየኝ ለጌታዬ የሚሻውን ገዝቼ ልምጣ ብሎ ወጣና ጥቂት ጨው አምባሻና እና መጻጻ ገዝቶ መጣ፡፡ ይህንም ይዞ አምባሻ ጨው መጻጻና የጎመን ቅጠልም ገዝቶ ወደ ጌታው ወደ ንጉሡ እና ወደ ንጉሡ መምህር አባ አውሎጊስ ዘንድ ገባ፣ አባ ዳንኤልንም በውጭ ተወው፡፡ ንጉሡም ረዳቱን አንተ አላዋቂ ነህን? ስለምን አባ ዳንኤልን በአፍአ ተውኸው አለውና ከመምህሩ ከአውሎጊስ ጋራ ወጣ፡፡ ለአባ ዳንኤልም ሰገዱለት፡፡ ሰላምታም ተሰጣጥተው ወደ ቤተ መንግሥት አስገቡትና በአንድነት ተቀመጡ፡፡ ፠ ዘጠኝ ሰዓትም በሆነ ጊዜ ለማዕድ ሲሰየሙ አባ ዳንኤል እንዳይታመም ፈርቶ ጌቶቼ እንጀራን ባለመብላቴ በእኔ ላይ አታጒረምርሙ፣ እንዳልታመም ፈርቼ ነው አላቸው። ጸሎትንም ጸለዩ፣ ከዚህም በኋላ ንጉሥ አኖሬዎስ አባ ዳንኤልን ስለአመጣጡ መረመረው፣ አባ ዳንኤልም የሚቻልህስ ከሆነ ከንጉሡ ዘንድ አስገባኝ፣ በጌታ ክርስቶስ ትእዛዝ መጥቻለሁና አለው፣ ነገ አስገባሃለሁ አለው፡፡ በማግስቱም አኖሬዎስ ዐይን የሚበዘብዝ ልብሰ መንግሥቱን ለብሶ በዙፋኑ ላይ ተቀመጠ፣ አባ ዳንኤልንም ንጉሡን በዙፋኑ ላይ ሆኖ ባየው ጊዜ ከግርማው የተነሣ አይቶት በታላቅ ፍርሃት ውስጥ ሆኖ ከእግሩም በታች ሰገደለትና አስገቡት ባየውም ጊዜ ፈርቶ ተንቀጠቀጠ፣ ረዳቱም መፍራቱን አይቶ ወደ ማደሪያው መለሰው፡፡ ንጉሡም ችሎቱን ሲጨርስ ልብሰ መንግሥቱን ጨርሶ ልብሰ ምንኲስናውን ለብሶ ወደ አባ ዳንኤል መጣ፣ እርሱም ወንድሜ ሆይ በልቤ ያለውን ነግሬው ወደ ቦታዬ እመለስ ዘንድ ወደ ንጉሡ ለምን አላስገባኸኝም አለው፡፡ አኖሬዎስም አባቴ ሆይ አልገባህምን? ለዚህች ምድር ንጉሥ ብለው የሰየሙኝ እኔ ነኝ አለው፤ አባ ዳንኤልን በሰማ ጊዜ ከእግሩ በታች ሰገደለትና አኗኗሩን ሁሉ ይነግረው ዘንድ በጌታችን ስም አማጸነው፤ አኖሬዎስም በእጅ ሥራው ሰሌን በመታታት ሸጦ ፈጽሞ ከሚያገኘው በቀር ሳይበላ ሳይለብስ ፵ ዓመታት እንደሆነው፣ የሚተርፈውንም ለድኆች እንደሚሸጥ፣ ምግቡም እንጀራና ጨው ቅጠል መጻጻም እንደሆነ፣ የማንንም ገንዘብ ለመቀማት እንዳልደፈረ፣ ድንግልናውንም መጠበቁን ነገረው። ** አባ ዳንኤልም ከእግሩ በታች ሰገደለትና አባቴ በአንተ ላይ ስለተመካሁ ይቅር በለኝ አለው። ከዚህም በኋላ አባ ዳንኤል ፈጽሞ እያዘነ ወደ ቦታው ተመለሰ። ከኹለት ወራትም በኋላ ጻድቁ ንጉሥ አኖሬዎስ ከመምህሩ ተማክሮ መንግሥቱን ጥሎ ወደ አባ ዳንኤል ኼደ። መልአከ እግዚአብሔርም ተሸክሞ አደረሰው። እነርሱም በአንድነት ሲጋደሉ በፍቅር ኑረዋል፡፡ ፠ ደናግል ወደሚኖሩበት ገዳም አንድ የወንበዴዎች አለቃ ሰይጣን አነሳስቶት ወደ ገዳሙ በአባ ዳንኤል ተመስሎ ቆቡን ደፍቶ በሩን አንኳኳ፤ ደናግላኑም ሊዘርፋቸው መምጣቱን ምንም ባለማወቅ ይልቁንም አባ ዳንኤል መጣ ብለው በሩን ከፈቱለትና አስገቡት፤ እግሩንም አጥበው ለበረከት ብለው የእግሮቹን ዕጣቢ በፊታቸው ላይ ረጩት፤ ከመካከላቸውም አንዷ ዐይነ ሥውር ነበረችና ዐይኗ ወዲያው በራላት፤ በዚህም ደናግሉ እጅግ ተደስተው ‹‹አባ ዳንኤል አንተ ንዑድ፥ ክቡድ ነህ›› ብለው ሰገዱለት፡፡ ይህን ጊዜ የሽፍቶቹ አለቃ በጣም ደንግጦ በመጸጸት ወደ አባ ዳንኤል ዘንድ ሄዶ ያደረገውን ሁሉ በመናገር ንስሓ ገባ፡፡ መንኵሶም በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመረ፡፡ ተአምራት እስከማድረግ ደርሶ በሰላም ዐረፈ፡፡ እንዲሁም መምህሩ አውሎጊስና ረዳቱ ቅዱሱ አባ ዳንኤልም ተጋድሏቸውን ፈጽመው በዚህችው ቅድስት እለት በአንድነት አረፉ፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን፡፡ /የቀ.ደ.ሰ. መድኀኔ ዓለምና ደ.ት.ቅ. ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት/

#ለ2ት #ዓለም_ሰዎች (በገዳም ለሚኖሩም በዓለምም ለሚኖሩ) #ትምህርት_የሚሆኑ_አባቶች፡፡ #አባ_ዳንኤል_ገዳማዊ_ንጉሡ_ጻድቁ_አኖሬዎስና_አውሎጊስ ታሪካቸው እጅጉን ከመሚሰጠውና ከጀመሩት ሳይጨርሱት ከማያቋርጡት በስንክሳር ላይ ከተጻፉት መካከል አንዱ ዛሬ ግንቦት 8 በዓለ ዕረፍቱ የሚታሰበው፤ የከበረና የተቀደሰ፥ የገዳማውያን መብራት #አባ_ዳንኤል_ገዳማዊ_ነው፡፡ ‹‹አባ ዳንኤል ዘደብረ ሲሐት›› (ገዳመ ሲሐትን ለብዙ ዘመን ተጋድሎባታል፤ ብዙ ቅዱሳን ደቀመዛሙርትን ወልዶባታልና) ‹‹አባ ዳንኤል ዘገዳመ አስቄጥስ›› (በአስቄጥስ ገዳም አበ ምኔት ሆኖ ተሹሞ እልፍ አእላፍ መነኰሳትን በጽድቅ መንገድ መርቷልና) #አባ_ዳንኤል፤ ፠ በትውልድ ግብጻዊ ሲሆን ወደ ገዳም የገባው ገና በወጣትነቱ ሲሆን ዘመኑም በዘመነ ጻድቃን (በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን) ነው፡፡ ፠ ቀን ቀን መነኰሳቱን ሲናዝዝ ፥ ድውያንን ሲፈውስ ፥ ሥርዐተ ገዳምን ሲቈጣጠር ይውላል፡፡ ከብዙ የቅድስና ዓመታት በኋላም ከትጋቱ የተነሳ ለምግብና ለእንቅልፍ ጊዜ አልነበረውም፤ ስለዚህ ሲመሽ ደግሞ ጭው ወዳለውና ስውራን ወደ ሚገኙበት በርሃ ይወርዳል፡፡ ሙሉውን ሌሊትም የተሰወሩ አባቶችን ሲፈልግ ያድር ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት የብዙ ስውራንን ገድል የጻፈ ሲሆን፤ ባረፉ ጊዜም ገንዞ በመቅበር በረከታቸውን ተሳትፏል፡፡ ፠ እርሱ ገንዞ ቀብሮ፤ ዜናቸውን ከጻፈላቸው ሥውራን ቅዱሳንም እንደ አብነት እሥራኤላዊቷን ቅድስት ዓመተ ክርስቶስን (መላ ሰውነቷን ጠጉሯ የሸፈናትና ለ38 ዓመት ራቁቷን በሥውር የኖረች) እንዲሁም ስሟን እንጣልዮስ አስብላ የነበረች ቅድስት በጥሪቃ ንግሥትን (መንግሥቷን ትታ በሥውር የኖረች፤ ወንድ መስላ ኖራ ስታርፍ ሴት መሆኗ የታወቀውን) መጥቀስ እንችላለን፡፡ ፠ ራሳቸውን የተናቀ አድርገውና ሰውረው የሚኖሩትን የሚያከብር ነበር፤ ለምሳሌ በሴቶች ገዳም እብድ ናት ተብላ በበር የተጣለችውን ቅድስት አናሲማን ፤ በእስክንድርያ ከተማ ሊቀ ዻዻሳቱ ሳይቀር ‹‹እብድ ነው›› ብለው የናቁትን ከዝሙት ጦር በመሸሽ ራሱን እብድ ያደረገውን ቅዱስ ምሕርካን እብድ ሳይሆኑ ራሳቸውን የሠወሩ ቅዱሳን መሆናቸውን ገልጧል፡፡ ፠ በሐዋርያዊነቱም በጊዜው ጦማረ ልዮን የሚባል የኑፋቄ ደብዳቤ ይላክ ነበርና ለዚህ ኬልቄዶናዊ ኑፋቄ በትጋት ምላሽ ይሰጥ ነበር፡፡ አንድ ቀንም በንጉሥ ትዕዛዝ ኑፋቄው በእርሱ ገዳም ሊነበብ ሲል ቅዱሱ ከወታደሩ ቀምቶ ስለ ቀደደው ለሞት እስኪደርስ ደብድበውታል፡፡ ፠*፠ አውሎጊስ የሚባለል የወፍጮ ድንጋይ እየወቀረ (እየጠረበ) በመሸጥ ለድኆችና ጦም አዳሪዎች የሚመጸውት ጻድቅ ሰው ነበር፡፡ አባ ዳንኤልም የአውሎጊስን መልካም ሥራ ተመልክቶ እጅግ ደስ ብሎት ለአውሎጊስ የሀብቱን መጠን እንዲጨምርለትና ይበልጥ እንዲመጸውት በማሰብ ወደ እግዚአብሔር በጸሎት አሳሰበ፡፡ ለአውሎጊስም ዋስ ሆነውና ሀብቱ ተጨመረለት፥ ብዙ ወርቅንም አገኘ፡፡ አንድ ቀን የሚወቅረውን ድንጋይ ሲፈነቅል በሸክላ ዕቃ የተደፈነ ሙሉ ወርቅ አገኘ፡፡ ወደ ቊስጥንጥንያም ከተማ ሄዶ ለንጉሡ አስረከበና የንጉሡ የሠራዊት አለቃ ሆኖ ተሾመ፡፡ ከተሾመም በኋላ የቀድሞውን የጽድቅ ሥራውን ተወ፡፡ አባ ዳንኤልም ስለ እርሱ ሰምቶ ሊያየው ቢሄድ በፈረስ ላይ ተቀምጦ በሠራዊት ታጅቦ በትዕቢት ተመልቶ አገኘው፡፡ ክፉ የትዕቢት መንፈስ አድሮበት ነበርና፡፡ አባ ዳንኤልም አውሎጊስ ሀብት እንዲያገኝ በመለመኑ አዘነ፡፡ በሌሊትም የአውሎጊስ ነፍስ በእርሱ ምክንያት እንደጠፋች ራሱ አባ ዳንኤልም ሲሰቀልና እመቤታችን ስለ እርሱ ስትማልድ ራእይ አየ፡፡ ከእንቅልፉም በነቃ ጊዜ የአውሎጊስ ሀብት እንዲጠፋና ወደ ቀደመ ግብሩ እንዲመለስ በጾም በጸሎት ሱባዔ ያዘ፡፡ መልአክም ተገልጦለት በእግዚአብሐር የፍርድ ሂደት ውስጥ ጣልቃ በመግባቱ ከገሠጸው በኋላ አውሎጊስም ምሕረት እንደሚያገኝ ነገረው፡፡ አውሎጊስን የሾመው ንጉሥም ሞተና ሌላ ንጉሥ ነገሠ፡፡ አውሎጊስንም ንብረቱን ሁሉ ቀምቶ ነፍሱንም ለመግደል አሳደደው፡፡ አውሎጊስም ነፍሱን ለማዳን ሽሽቶ ወደ ሀገሩ በመግባት የቀድሞ ሥራውን መሥራት ጀመረ፡፡ ነዳያንንም እንደ ዱሮ መመገብ ጀመረ፡፡ ፠ ይህንን ታሪክ በተመለከተ ሊቁና የወርቃማው ዘመን ወርቃማው ደራሲ ከሚባሉት አንዱ የሆነው አባ ጽጌ ድንግል ማኅሌተ ጽጌ ድርሰቱ እንዲህ ሲል እመቤታችንና ከልጇ አውሎጊስን የተዋሰውን አባ ዳንኤልን እንዳስማረችው አመስጥሮ አስቀምጦልናል፡፡

‹‹ ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተ ክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡›› ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት በጥር ፲፯/፳፻፲፪ ዓ.ም በቀ
+1
‹‹ ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተ ክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡›› ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት በጥር ፲፯/፳፻፲፪ ዓ.ም በቀ/ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለም ቤ/ክ በሥርዐተ ተክሊል ጋብቻሽን የፈጸምሽው የሰ/ት/ቤታችን አባል እኅታችን፤ #አለምነሽ_ዳምጣቸው_ከምስጋናው_በላይ ጋር የፈጸማችሁትን ጋብቻ፤ የይስሐቅንና የርብቃን ጋብቻ የባረከ አምላክ፤ የትዳር ሕይወታችሁን ይባርክላችሁ፥ ያጣምራችሁ፥ ያዋሕዳችሁ፤ እመብርሃን በአማላጅነቷ አትለያችሁ፤ ቅዱስ ገብርኤል ከፊት ይምራችሁ ከኋላ ይከተላችሁ፡፡ ✤ ‹‹ጌታን እንዲወዱና በአካልም ይሁን በመንፈስ በባሎቻቸው ደስ እንዲሰኙ ለእህቶች ንገራቸው፡፡ ልክ እንደዚሁ ጌታ ቤተ ክርስቲያንን እንደወደደ ሚስቶቻቸውን እንዲወዱ ለወንድሞች በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ንገራቸው፡፡›› ቅዱስ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ ለፖሊካርፐስ በላከው መልእክቱ ✤ ከተጋባችሁ በኋላ ባልና ሚስት አንድ አካል ናችሁ እንጂ ሁለት ስላይደላችሁ በፍጹም ልባችሁ እርስ በእርሳችሁ ተፋቀሩ፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ሌላ ወንድ ወይም ሌላ ሴት አትፈልጉ ይልቁንም በተቻላችሁ መጠን አንዳችሁ ሌላውን ደስ አሰኙ፤ በመረዳዳትና በፍጹም ፍቅር ኑሯችሁን ሁሉ አሳምሩ፡፡>> ኢትዮጵያዊው ፈላስፋ ዘርአያዕቆብ፡፡ /ከቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤#ክፍል#፮_ (#የሰይጣን_ኀይል_በምን_እንደሚደክም፤ #ሰው_በሰራው_ኀጢአት_ተጠያቂው_ራሱ_እንጂ_ሰይጣን_እንዳልሆነ፤ #ሰይጣን_ሰዎችን_ፈጣሪያቸውን_እንዴት_ባለ_መንገድ_እንደሚያስክዳቸው፤ #አንድን_ኀጢአት_ያለፈን_ሰው_በሌላ_ኀጢአት_እንደሚፈትኑት፤ አባ ጳውሊ፤ ኃይላችሁ በምን ይደክማል? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ #ከፍቅር፥ ከትዕግሥት፥ ከጾም፥ ከጸሎት፥ ከመታዘዝ፥ ከትጋሃ ሌሊትና ከመሳሰሉት ትሩፋቶች ሁሉ ጋር ኃይላችን የሚደክመው #በትሕትና ነው አለው፡፡ እኛ በፍጥረታት ሁሉ ላይ ጭንቅ የሆነ መከራ ከማምጣት ቸል አንልም አንቦዝንም፡፡ በሚቻለን ሁሉ እንፈትናቸዋለን አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ አንተ እንደምትለኝ ከሆነስ ሰዎች ምንም ኃጢአት የለባቸውም፡፡ ኃጢአትስ የሚሆንባችሁ የክፋትንና የርኵሰትን ሥራ በምታሠሯቸው በአንተና በወገኖችህ ላይ ነው አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ እኔ የንግድ ቤቱ ነኝ፡፡ በእኔ ዘንድም ብዙ የሚሸጡ የኃጢአት ዕቃዎች አሉኝ፡፡ የንግድ ቤቱንም በር እከፍታለሁ፡፡ ሁሉም እንደየፍላጎቱ የሚሻውን ይገዛል፡፡ ስለዚህ #ሰው ሁሉ በራሱ ፍላጎት የሚበድል ከሆነ እርሱ በሠራው ኃጢአት እኔ ስለ እርሱ አልጠየቅም፤ ኃጢአትም የለብኝም አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ አንተ የተረገምህ! የንግድ ቤትህ እንዳይከፈት እግዚአብሔር ይቅር አይበልህ፡፡ ፈጽመህም መሸጥ እንዳትችል የንግድ ቤትህ ይዘጋ፤ ይፍረስ አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አንተ ክፉ ሽማግሌ ያለ በደሌ ስንት ጊዜ ትረግመኛለህ፡፡ ሌሊቱን ሙሉ ከአንተ ጋር በመሆኔ ሃይሌን አደከምከኝ፤ ሰውነቴንም አሠቃየሃት፡፡ ስለዚህ እሄድ ዘንድ ተወኝ አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ ሰዎች ፈጣሪያቸውን እንዲክዱ የምታደርገው በምን መንገድ እንደሆነ እስኪ ዳግመኛ ንገረኝ አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ በዚህ ዓለም የማደርገውን ሁሉ ነገርሁህ፡፡ #መጀመሪያ ልጆች የወላጆቻቸውንና የአሳዳጊዎቻቸውን ምክር እንዳይሰሙ፣ ለቃላቸውም እንዳይታዘዙና ከእናንተ ይልቅ በእውቀት እኛ እንበልጣለን፣ እኛ እናውቃለን እንዲሉ እናደርጋቸዋለን፡፡ ##ዳግመኛም ወላጆቻቸውንና በዕድሜ የሚበልጧቸውን እንዲሳደቡ እናደርጋቸዋለን፡፡ /፪ጢሞ.፫:፪/፡፡ በዚህ ምክንያት የቤተሰብ ፍቅር እናሳጣቸዋለን፡፡ በሄዱበት ሁሉ እየተረገሙ ይኖራሉ፡፡ ###ከዚህ በኋላ በዝሙት፥ በክህደት፥ የምንዝር ጌጥን በመውደድ፥ በስካር፥ በስርቆት፥ ነፍስን በመግደል እንዲወድቁ እናደርጋቸዋለን፡፡ በመጨረሻም ተስፋ ቆርጠውና አእምሮ አጥተው ቊጥር የሌለው ኃጢአትን እንዲሠሩ እናደርጋቸዋለን አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ በዕድሜ ያረጀ ዘመኑም የተቃረበና ሥጋውም የደከመ ሽማግሌ ኃይሉ ይደክማልና በምን ትፈትኑታላችሁ? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ እኛ በሽማግሌዎች ብዙ ምክንያት እናገኛለን፡፡ ስንፍና እናመጣባቸዋለን፤ ጾምንና ጸሎትን እንከለክላቸዋለን፡፡ ዘመናቸውን እስኪረግሙና ራሳቸውን እስኪያጠፉ ድረስ የሚያደርስ ጭንቀትና ጥርጣሬን እናመጣባቸዋለን፡፡ ክፉ ሐሳብንና ገንዘብ መውደድንም እናመጣባቸዋለን፡፡ ተስፋ መቁረጥን ሰላም ማጣትን በውስጣቸው እናደርጋለን፡፡ ከልባቸው የኅሊና ጸሎትን፥ ከአንደበታቸው ምስጋናን እናጠፋባቸዋለን፡፡ ለልጆቻቸው፥ ለዘመዶቻቸው፥ ለሚረዷቸው፥ ለሚቀርቧቸው ሁሉ ሁከተኞች እንዲሆኑ እናደርጋቸዋለን አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ ዳግመኛ እንዲህ ብሎ ጠየቀው፤ አንተ የተረገምክ ከእናንተ እያንዳንዳችሁ ሰው ሁሉ በፍትወት ተማርኮ ኃጢአትን እንዲሠራ ለማድረግ ሁላችሁም የተሰለፋችሁ አይደለምን? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አዎ ሁላችንም #ሰውን በኃጢአት ምኞት ተማርኮ እንዲወድቅ ለማድረግ የተሰለፍን ነን፡፡ ብዙዎችንም እናስታቸዋለን፤ በኃጢአት ላይ ኃጢአት እንዲሠሩ እናደርጋቸዋለን፡፡ ዳግመኛም #ከአጠመድነው ወጥመዳችን አምልጦ የወጣውን ሰው በሌላ በታላቅ የኃጢአት ወጥመድ እንዲወድቅ አጥብቀን እንዋጋዋለን አለው፡፡ #ለሰው በሚፈልገው ተመስለው በምትሐት እንደሚገለጹ፤ የሰይጣናት አሳሳች መሆናቸው ለጥቂት ደጋጎች እንጂ (በመጨረሻ በሥራቸው) እንጂ ለሁሉ እንደማይታወቁ፤ በገዳም የሚኖሩትን በምን እንደሚዋጋቸውና እንደሚያሸነፉት፤ ከሰው ልጆች የሚፈራቸውና የማይፈራቸውን .… ክፍል ፯.… ይቀጥላል ነገ ይጠብቁን/ #በፌስቡክ_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://t.me/medihanaelem

፠ #የ2012 ዓ.ም. #የርክበ_ካህናት_የቅዱስ_ሲኖዶስ_ጕባኤ_ውሳኔ፤ ፩ኛ) በቫይረሱ የተጠቁትን ምሕረት እንዲሰጥልን፥ እስካሁን ያልተያዙትን እንዲጠብቅልን ተማኅጽኖውን ለእግዚአብሔር አቅርቧል ያቀርባ
+3
፠ #የ2012 ዓ.ም. #የርክበ_ካህናት_የቅዱስ_ሲኖዶስ_ጕባኤ_ውሳኔ፤ ፩ኛ) በቫይረሱ የተጠቁትን ምሕረት እንዲሰጥልን፥ እስካሁን ያልተያዙትን እንዲጠብቅልን ተማኅጽኖውን ለእግዚአብሔር አቅርቧል ያቀርባልም፤ ፪ኛ) ካህናትና ምዕመናን እንደ አንድ ልብ መካሪ፥ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ በመሆን በቤተ ክርስቲያንም ሆነ በቤታቸው የሚያደርጉትን ጸሎት አጠናክረው እንዲቀጥሉ፤ ፫) ምዕመናን ከቤተ ክርስቲያን ተለይተው መኖር ስለማይችሉ በሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች አስተናጋጅነት ጥንቃቄ በተመላ መልኩ (የሃይማኖት አባቶችና የጤና ባለሙያዎች በሚሰጡት ምክርና መንግሥትም በሚሰጠው መመሪያ መሠረት) መንፈሳዊ ተግባራትን በቤተ ክርስቲያን እንዲያከናውኑ፤ ፬) ያለው ለሌለው በማካፈል መንፈሳዊ ትሩፋት እንድንሠራ፤ ፭) በአሁን ጊዜ ያሉ የፖለቲካ ድርጅቶች ከሁሉም በፊትና በላይ ለሃገራዊ ሰላምና ሕዝባዊ አንድነት በጋራ እንዲቆሙ፤ ፮) ለሕዳሴ ግድብ የሚደረገው ሕዝባዊ አንድነትና ተሳትፎ እንዲቀጥል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

ሰበር ዜና፤ #የተዘጉ_የቤተ_ክርስቲያን_በሮች_እንዲከፈቱ_ቅዱስ_ሲኖዶስ_ወሰነ፡፡ ዛሬ ረቡዕ ግንቦት 5 የርክበ ካህናት ስብሰባውን እያደረገ የሚገኘው ቅዱስ ሲኖዶስ የተዘጉ የቤተ ክርስቲያን በሮች ተከ
+2
ሰበር ዜና፤ #የተዘጉ_የቤተ_ክርስቲያን_በሮች_እንዲከፈቱ_ቅዱስ_ሲኖዶስ_ወሰነ፡፡ ዛሬ ረቡዕ ግንቦት 5 የርክበ ካህናት ስብሰባውን እያደረገ የሚገኘው ቅዱስ ሲኖዶስ የተዘጉ የቤተ ክርስቲያን በሮች ተከፍተው መንፈሳዊ አገልግሎቱ በፀረ ኮቪድ-19 የጥንቃቄ ተግባራት እየተመራ እንዲፈጸም አዘዘ፡ • ጠቅላይ ቤተ ክህነት ከመንግሥት ጋራ በመነጋገር ትእዛዙን እንዲያስፈጽም መመሪያ ሰጠ፤ • አገልግሎቱን በጥንቃቄ ተግባራቱ መሠረት ለማስፈጸም አጥቢያዎች ሓላፊነቱን ይወስዳሉ፤ • የሰንበት ት/ቤቶችን በማስተባበር፣ መንፈሳዊ አገልግሎቱ በአግባቡ እንዲከናወን ያደርጋሉ፤ • ጥምቀቱ፣ ቊርባኑ፣ ተክሊሉ፣ ፍትሐቱ ርቀትን ጠብቆ በተገቢ የልኡካን ቁጥር ይፈጸማል፤ • ቅዱስ ሲኖዶሱ፥ የቤተ ክርስቲያን በር በግድ እየተዘጋ በፖሊስ የሚደረገውን ጥበቃ ተችቷል፤ ቋሚ ሲኖዶሱ፥ “በስሜ የተደረገ እንጂ የእኔ ውሳኔ አይደለም፤” ብሏል፤ • የጠቅላይ ቤተ ክህነት ፀረ ኮቪድ-19 የተስፋ ልኡክ ዐቢይ ግብረ ኀይል፣ ሪፖርቱን ለምልዓተ ጉባኤው አቅርቧል፤ • አስቸኳይ ዐዋጁን በማስፈጸም ሰበብ፣ ፖሊስ፣ በአገልጋይ ልኡካንና ምእመናን ላይ ጥቃቶችንና ማጥላላቶችን መፈጸሙ ቅዱስ ሲኖዶሱን አሳዝኗል፤ • ማንም እገዛ ሳይጠይቃቸው በበሯ ቆመው እየተሳደቡና እየደበደቡ ከፍተኛ የኀይል ርምጃ መውሰዳቸው ሳያንስ፣ ሥርዐተ አምልኮዋን የሚያጥላሉ የሌላ እምነት ተከታይ ፖሊሶችም እንዳሉበት በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡ ፠ አብያተ ክርስቲያናት ይትረኃዋ (ቤተ ክርስቲያኖች ይከፈቱ) /ሃይማኖተ አበው/ ፠ ኢይትዓጸዉ አናቅጽኪ፡፡ (ደጆችሽ አይዘጉ) /ት.ኢሳ. 60/ /ምንጭ፤ ሐራ ዘተዋሕዶ/ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ት

#ርክብ_ካህናት (#ዕለተ_ጥብርያዶስ፤ #ዳግሚት_ዕለተ_አግብኦተ_ግብር፤ የሃገራችን የቅዱስ ሲኖዶስ መሰብሰቢያ ቀን)፤ #ረቡዕ_ግንቦት_5 ርክበ ካህናት የሁለት ቃላት ጥምረት ሲኾን እነዚህም፤ **1ኛ. ረክብ የሚለው ቃል ተራከበ ተገናኘ ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ትርጕሙም ማግኛ፣ መገኛ፣ መገናኛ ማለት ነው፡፡ /ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ገጽ ፰፴፩/፡፡ **2ኛ. ክህነት የሚለው ቃል ከዲቁና ጀምሮ እስከ ከጵጵስና ድረስ ያሉትን መዓርጋት (በጥቅሉ ዲያቆናትን፣ ቀሳውስትንም ኾነ ጳጳሳትን) የሚያጠቃልል ስያሜ ነው፤ ካህን (ነጠላ ቍጥር) ሲኾን ካህናት ደግሞ (ብዙ ቍጥር) ነው፤ ብዙ ጊዜ ግን ይህን ባለማወቅ ካህናት የሚለውን ለቀሳውስት ብቻ መጠሪያ ሲኾን እናያለን፤ አለማወቅ ነው! (ለምሳሌ በቅዳሴ መጨረሻ ላይ ዲያቆኑ በእደ …… ካህን ይባርከነ ቢል ለኹሉም ያስኬዳል፥ ሰዋስዉም ያዛል፥ ሥርዐቱም ይኸው ነው፤ ነገር ግን ዛሬ ዛሬ በእደ … ካህን ይባርከነ በማለት ፈንታ በእደ ብፁዕ ፓትርያርክ፣ በእደ ብፁዕ ሊቀ ጳጳስ፣ በእደ ቆሞስ …. ሲባል ይታያል፤ መስተካከል ያለበት ጉዳይ ነው፡፡) ርክበ ካህናት ማለትም የአባቶች ካህናት (ማለትም በጵጵስና ማዕረግ ያሉ /ኤጲስ ቆጶሳት፣ ጳጳሳት፣ ሊቃነ ጳጳሳትና ርዕሰ ሊቃነ ጳጳስን ያጠቃለለ (የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት) ጕባኤ፤ የካህናት መገኛ፥ መገናኛ ጉባኤ (መሰባሰቢያ፣ መወያያ) ማለት ነው፡፡ በዓሉ በየዓመቱ የትንሣኤ በዓል በዋለ በ፳፭ኛው ቀን ሁልጊዜ በዕለተ ረቡዕ ይውላል፤ ወሩና የሚውልበት ቀን ግን በኢየዓርግና በኢይወርድ (በባሕረ ሓሳብ የበዓላትንና የአጽዋማትን) ቀመር ተከትሎ የሚወጣ ስለኾነ ከፍና ዝቅ ይላል፡፡ የአጽዋማትና የበዓላት ቀመር በቅዱስ ድሜጥሮስ አማካኝነት ከመዘጋጀቱ በፊት (ዐቢይ ጾም ሰኞ፣ ስቅለት ዓርብ፣ ትንሣኤ እሑድ፣ ርክበ ካህናት ረቡዕ፣ ዕርገት ሐሙስ፣ ጰራቅሊጦስ እሑድ እንዲሆን ከመደረጉ በፊት) ርክበ ካህናት በየዓመቱ ግንቦት ፳፩ ቀን ይውል ነበር /መጽሐፈ ግጻዌ ግንቦት ፳፩/፡፡ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጐ ከተነሳ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ በየጸጋቸው መጠን እየተገለጠ ያጽናናቸው፥ ያጸናቸው፥ ያስተምራቸው፥ ይባርካቸውም ነበር፤ ጌታችን እስከ ዕርገቱ ባሉ ፵ ቀናትም መጽሐፈ ኪዳንን፣ ትምህርተ ኅቡዓትን፣ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንን አስተምሯቸዋል፤ በልቡናቸውም አሳድርድሮባቸዋል፡፡ ፠ በመጽሐፍ ቅዱስ በዮሐንስ ወንጌል፤ ከዕርገቱ አስቀድሞ ጌታ ለደቀ መዛሙርቱ ፫ ጊዜ በጕባኤ መገለጡ ተዘግቦ ይገኛል፡፡ እነዚህም፤ 1ኛ. የትንሣኤ (ዮሐ. 20፥19) 2ኛ. የአግብኦተ ግብር (ዳግም ትንሣኤ) /ዮሐ. 20፥:26/ 3ኛ. የጥብርያዶስ፤ (ዮሐ. 21፥1) ለድንግል ማርያም ግን በኹሉም እለታት መገለጡን አበው ያስተምራሉ፡፡ በጥብርያዶስ ባሕርም ከዐሥራ አንዱ ቅዱሳን ሐዋርያት ጋር ምሳ በልቷል፡፡ የርክበ ካህናት በዓል መነሻም ጌታችን ለሦስተኛ ጊዜ ከተገለጠበት ከጥብርያዶስ ባሕር ካለው ታሪክ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ በዚህች ዕለት በቅዱስ ዼጥሮስ መሪነት ሐዋርያቱ ወደ ጥብርያዶስ ባሕር ሔዱ፡፡ አሶችን ሊያጠምዱም በብዙ ደከሙ፤ ነገር ግን ጌታችን በረድኤት አብሯቸው አልነበረምና አንዳች አሣ በመረባቸው ሊገባ አልቻለም፡፡ ማጥመድ (አስተምሮ ከክህደት ወደ ሃይማኖት፤ ከኀጢአት ወደ ጽድቅ መመለስ) የሚቻለው በረድኤተ እግዚአብሔር እንጂ በእውቀት ብዛት ወይም በአንደበተ ርቱዕነት ብቻ አይደለምና፡፡ ሲነጋ ግን መድኀኒታችን ወደ ቅዱሳን ደቀ መዛሙርቱ መጣ፤ በጥብርያዶስ ባሕር ዳርቻም ቆሞ ታያቸው፤ ከሚወደው ደቀ መዝሙሩ ከቅዱስ_ዮሐንስ በቀር ጌታችን መሆኑን ያወቀው ግን አልነበረም፡፡ ቸሩ አባት ‹‹ልጆቼ! አንዳች የሚበላ ነገር አላችሁ?›› ሲል ጠየቀ፤ ‹‹ጌታ ሆይ! የለም›› አሉት፡፡ ‹‹የለንም›› ብሎ የሌለንን ነገር በጌታ ፊት ማመኑ እጅግ መልካም ነው፤ ምክንያቱም ያጣነውን ነገር ሊሰጠን፥ የጎደለንን ሊሞላልን፥ የጠፋብንን ሊጠቁመን ቸርነቱ ብዙ ነውና፡፡ ያን ጊዜ ሐዋርያቱን መረባቸው በመርከብ ቀኝ እንዲጥሉ አዘዛቸው፡፡ እነርሱም በደስታ ጣሉ፤ በአግራሞት እስኪሞሉ ድረስ መረባቸውን መሳብ አቅቷቸው ሊቀደድ እስኪደርስ ድረስ 153 ዓሦች ተያዙላቸው፡፡ ያን ጊዜም የሚወደው ደቀ መዝሙሩ ቅዱስ ዮሐንስ ጌታችን መኾኑን ለቅዱስ ዼጥሮስ ‹‹ጌታ እኮ ነው›› አለው፤ ሽማግሌው ቅዱስ ግን ራቁቱን ነበርና ወደ ባሕሩ ተወረወረ፡፡ ከአፍታ በኋላም ጌታችን ከሐዋርያቱ ጋር በድጋሚ (ለ፪ኛ ጊዜ) ለምሳ ተቀመጠ፤ ባርኮ ሰጥቶ ልባቸውን ሊያጸና አብሯቸው በላ፡፡ በዚያች ሰዓት ቅዱስ ዼጥሮስን ፫ ጊዜ ‹‹ትወደኛለህን?›› ሲል ጠየቀው፤ ቅዱሱ አረጋዊም እየደጋገመ ‹‹ለሊከ ተአምር ከመ አነ አፈቅረከ (እንድወድህ አንተ ታውቃለህ)›› ሲል መለሰ፡፡ ጌታም በበጐች ሐዋርያት (ካህናት)፤ በጠቦቶች አርድእት (ዲያቆናት)፤ በአባግዕት ፴፮ቱ ቅዱሳት አንስት (ምዕመናን ወምዕመናት) ላይ ሁሉ እረኛ እንዲሆን ሾመው፡፡ ይህ ምሥጢር ለጊዜው ጌታችን ሐዋርያትን፣ ሰብዐ አርድእትንና ሠላሳ ስድስቱን ቅዱሳት አንስት በአጠቃላይ መቶ ሃያውን ቤተሰብእ እንዲጠብቅና እንዲከባከብ ቅዱስ ጴጥሮስን ማስጠንቀቁን፤ ፍጻሜው ግን የቤተ ክርስቲያን አባቶች (ጳጳሳት) መምህራንንና መላው ሕዝበ ክርስቲያንን እንዲጠብቁና እንዲያስተዳድሩ በእግዚአብሔር መሾማቸውን የሚያስረዳ ትርጕም አለው /ዮሐ.፳፩፥፩-፲፯ (አንድምታ ትርጓሜ)/፡፡ ቀጥሎም የቅዱስ ጴጥሮስን የሰማዕትነቱን ምሥጢር ገልጦለት ‹‹ተከተለኝ›› (ለጊዜው በእግር፤ በኋላ ግን በግብር ምሰለኝ) ብሎታል፡፡ ወልደ ነጐድጓድ ወፍቊረ እግዚእ ቅዱስ ዮሐንስም ሞትን እንደማይቀምስ እንዲሁ ተናግሮለታል:: ፠ ጌታ ለሐዋርያት በአንድነት የተገለጠባትን ይህች ቀን እነዚህ ሁሉ ተግባራት የተከናወኑባት ናትና (የትንሣኤ በዓል ፳፭ኛ ቀን) መሠረት በማድረግ፤ የኋላ ሊቃውንት በየዓመቱ የትንሣኤ በዓል በዋለ በ፳፭ኛው ቀን ዐራቱ ሊቃነ ጳጳሳት የሚሰበሰቡበት የካህናት መገናኛ ቀን ርክበ ካህናት ይሁን ብለው ወስነዋል፡፡ ከዚህ በኋላ ርክበ ካህናት በዓለ ትንሣኤ በዋለ በ፳፭ኛው ቀን፣ በበዓለ ሃምሳ እኩሌታ በዕለተ ረቡዕ ይዘከራል፤ በያዝነው ዓመት በ፳፻፲፪ ዓ.ም የትንሣኤ በዓል ከተከበረበት ዕለት (ሚያዝያ ፲፩ ቀን) ጀምሮ ብንቈጥር ፳፭ኛው ቀን ግንቦት ፭ ቀን ይኾናል፡፡ በመኾኑም የዘንድሮው ርክበ ካህናት ግንቦት ፭ ቀን በዕለተ ረቡዕ ይውላል ማለት ነው፡፡ ይህ በዓል ከቅዱሳን ሐዋርያት ጀምሮ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሲያስተዳድሩ የቆዩ አባቶቻችን ጌታንና ደቀ መዛሙርቱን አብነት በማድረግ በጋራ በመሰባሰብ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን የተቀላጠፈ አገልግሎት እንደዚሁም ለምእመናን አንድነትና መንፈሳዊ ዕድገት የሚበጁ መንፈሳውያን መመሪያዎችን የሚያስተላልፉበት እለት ነው፡፡ *** ይህንን የጌታችን ትእዛዝና የሐዋርያትን ሥልጣነ ክህነት መሠረት በማድረግ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በዓመት ሁለት ጊዜ ጉባኤ ያደርጋል፤ ፠ ፩ኛ. የመጀመሪያው ጉባኤ ጥቅምት ፲፪ ቀን (የቅዱስ ማቴዎስ በዓለ ዕረፍት) ሲሆን፣ ፠ ፪ኛ. የትንሣኤ በዓል በዋለ በ፳፭ኛው ቀን የሚደረገው ይህ ርክበ ካህናት ነው፡፡ ከላይ በተጠቀሱት ዕለታት በዋዜማው ሁሉም ጳጳሳት ከየሃገረ ስብከታቸው በመንበረ ፓትርርኩ በምትገኘው ቤተ ክርስቲያን ተሰብስበው የመሐረነ አብ ጸሎት ይደርሳል በነጋታው ጕባኤው ይካሄዳል፡፡ የቀ.ደሰ.መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት

የመርካቶ ደብረ ኃይለ ቅዱስ ራጕኤል አንቀጸ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት አድራሻ ከዚህ የሚከተለው ስለሆነ እንድትጠቀሙበት እነሆ ብለናል፡፡ የፌስ ቡክ ገጽ፤ https://www.facebook.com/
የመርካቶ ደብረ ኃይለ ቅዱስ ራጕኤል አንቀጸ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት አድራሻ ከዚህ የሚከተለው ስለሆነ እንድትጠቀሙበት እነሆ ብለናል፡፡ የፌስ ቡክ ገጽ፤ https://www.facebook.com/sundayschoolofSR/ የቴሌግራም ገጽ፤ https://t.me/Anqetseberhansundayschool የዩቲዩብ ገጽ፤ አንቀጸ ብርሃን ሚዲያ Anqetse berhan media (https://www.youtube.com/channel/UCj5T3d_1kE4BFizwS12ompQ

ሰይጣን በአባ ጳውሊ ተገዝቶ ሳለ ያወጣው ምሥጢር #ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (#ተዋስኦተ_ጳውሊ_ምስለ_ሰይጣን)፤ #ክፍል#፭_ ++አባ ጳውሊ፤ የወገኖችህ ቊጥራቸውና ስማቸው እንዲሁም በዚህ ዓለም የምትታዩት ብዛታችሁ ምን ያህል እንደሆነ እውነቱን ትነግረኝ ዘንድ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ባየኸው በፈጣሪ ስም አምልሐለው አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ነገዳችን ብቻ ነው እንጂ ቊጥራችን አይታወቅም አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ በአኗኗራችሁ ከእናንተ የበላይ አለቃ አለን አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አዎን አለ ፤ ታላቁ አለቃ እኔ ነኝ አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ ከእናንተ ወገን በክፋትና በማሳት ከወገን ወገን፥ ከሰይጣን ሰይጣን የሚበላለጥ አለን? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አዎን አለ አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ ከሰው ወገን ዘመድ ወዳጅ አለህን? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አዎን አለኝ አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ አንተ የረከስክ ነህና ወዳጅህ ማነው? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ #የእግዚአብሔርን ሕግ ትቶ ኃጢአትን የሚሠራ ነው አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ ስለምጠይቅህ ነገር ምንም እንዳትሸሽገኝ በመስቀል ላይ በተሰቀለው በጌታ ስም አምዬሃለው አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አንተ ክፉ ሽማግሌ ከአንተ የተነሳ ወዮልኝ ፤ ከሥራዬ ምንም የምደብቅህ የለኝምና በዚህ ቅዱስ ስም አታቃጥለኝ ዝም በል አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ አንተ ከክብርህ የተዋረድክና የተረገምህ! #ክፉ ሥራህን ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው እስኪ ንገረኝ አለው፡፡ ሰይጣን፤ አንተ ሽማግሌ ብዙዎች እኔ እንደማስታቸውና እንደማልጠቅማቸው አያውቁምና ሥራዬን አትነግርብኝምን? አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ የምጠይቅህን ክፉ ሥራህን ንገረኝ እንጂ እኔ እንዳልናገር የማዘዝ ሥልጣን የለህም አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ከቸርነቱ ያርቃቸው ዘንድ አምላካቸውን ሐሰተኛ አድርገው እስኪያዩትና ፣ እስኪነቅፉት እስኪሰድቡትም ድረስ ሐሰትን እናስተምራቸዋለን፡፡ ዳግመኛም የማስተዋል አእምሮን በመንሳት የነቀፋና የስድብ መንፈስ ከልባቸውና ከአፋቸው እንዳይጠፋ እናደርጋለን አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ አንተ የተረገምክ እንዲህ በማድረግህ #ምን ትጠቀማለህ? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ እናንተን ከዘለዓለም ሕይወት ማጥፋትና በገሃነም እሳት ማቃጠል ነው እንጂ የምጠቀመው ጥቅም የለኝም አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ በውኑ ገሃነም የሚባል ቦታ አለን? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አዎ ገሃነመ እሳት አለ፡፡ በዚያ መጽናናት የሌለው ልቅሶ፥ ጥርስ ማፋጨት እንዲሁም የማያንቀላፋ ትል፥ ታላቅ ስቃይና የማይቋረጥ ልቅሶ ድቅድቅ ጨለማ አለ፡፡ ኑሯችን በዚያ ነው አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ አንተ ከክብርህ የተዋረድክ፤ በገሃነመ እሳት እንደምትቀጣ የምታውቅ ከሆነ ለምን ንስሐ አትገባም!? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ #ንስሐ እንዳልገባ #የሚጸጸት ልብ የለኝም አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ እግዚአብሔር መሐሪና ይቅር ባይ ነውና ከለመንከው ይሰጥሃል!! አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ ለዚህ ሥራ ዕድል የለንም አለው፡፡ አባ ጳውሊ፤ ከእናንተ በዚህ በክፉ ሥራችሁ የበላይ አለቃ አለን? አለው፡፡ ዲያብሎስ፤ አዎን አለ፤ በጨለማ ሠራዊት ላይ ታላቁ አለቃ እኔ ነኝ፡፡ እኔ ሰይጣናትን ሁሉ ሰውን ለማሳት በየቦታው እልካቸዋለሁ፡፡ ከአጋንንት ጭፍራና ከወገኖቼ መካከል ከእኔ የሚከፋ የለም፡፡ ከእኛ መካከል ሰዎች ዝሙትንና ስርቆትን፥ ቂምና ስካርን ይህን የመሰለ ኃጢአት እንዲሠሩ የሚያደርጉ እጅግ የከፉ ጨካኝ አጋንንት አሉ አለው፡፡ #የሰይጣን ኀይል በምን እንደሚደክም፤ ሰው በሰራው ኀጢአት ተጠያቂው ራሱ እንደሆነ፤ ሰይጣን ሰዎችን ፈጣሪያቸውን እንዴት ባለ መንገድ እንደሚያስክዳቸው፤ አንድን ኀጢአት ያለፈን ሰው በሌላ ኀጢአት እንደሚፈትኑት፤ ለሰው በሚፈልገው ተመስለው በምትሐት እንደሚገለጹ … ክፍል ፮.… ይቀጥላል ነገ ይጠብቁን/ #በፌስቡክ_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://t.me/medihanaelem

‹‹ ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተ ክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡›› ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት በሚያዝያ ፲፰/፳፻፲፪ ዓ.ም
+1
‹‹ ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተ ክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡›› ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት በሚያዝያ ፲፰/፳፻፲፪ ዓ.ም በደ/ኃይል ቅዱስ ራጕኤል ወኤልያስ ቤ/ክ ጋብቻችህን የፈጸማችሁት የሰ/ት/ቤታችን አባላት፤ #ሳሙኤል_እሸቴ_ከሃገሬ_ብሩ ጋር የፈጸማችሁትን ጋብቻ፤ የይስሐቅንና የርብቃን ጋብቻ የባረከ አምላክ፤ የትዳር ሕይወታችሁን ይባርክላችሁ፥ ያጣምራችሁ፥ ያዋሕዳችሁ፤ እመብርሃን በአማላጅነቷ አትለያችሁ፤ ቅዱስ ገብርኤል ከፊት ይምራችሁ ከኋላ ይከተላችሁ፡፡ ✤ ‹‹ጌታን እንዲወዱና በአካልም ይሁን በመንፈስ በባሎቻቸው ደስ እንዲሰኙ ለእህቶች ንገራቸው፡፡ ልክ እንደዚሁ ጌታ ቤተ ክርስቲያንን እንደወደደ ሚስቶቻቸውን እንዲወዱ ለወንድሞች በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ንገራቸው፡፡›› ቅዱስ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ ለፖሊካርፐስ በላከው መልእክቱ ✤ ከተጋባችሁ በኋላ ባልና ሚስት አንድ አካል ናችሁ እንጂ ሁለት ስላይደላችሁ በፍጹም ልባችሁ እርስ በእርሳችሁ ተፋቀሩ፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ሌላ ወንድ ወይም ሌላ ሴት አትፈልጉ ይልቁንም በተቻላችሁ መጠን አንዳችሁ ሌላውን ደስ አሰኙ፤ በመረዳዳትና በፍጹም ፍቅር ኑሯችሁን ሁሉ አሳምሩ፡፡>> ኢትዮጵያዊው ፈላስፋ ዘርአያዕቆብ፡፡ /ከቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/

#ልደታ_ለማርያም ምሥራቀ ምሥራቃት ሙፃአ ፀሐይ እግዝእትነ ዘመና ሙዳይ፤ ተወልደት ዮም ዳግሚት ሰማይ፡፡ ፠ #የግንቦት_ልደታ_ለማርያም_ክብረ_በዓልና_የእመቤታችን_በዓላት በቀደመዉ ዘመን በዘመነ ብሉይ ‹‹የቤተ መቅደስ መታደስ በዓል›› ይከበር እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳል፡፡ ይህ በዓል እስከ ጌታችን ዘመንም ይከበር ነበር፡፡ /ዮሐ. 10፥22/ በሐዲስ ኪዳን እውነተኛ የእግዚአብሔር ማደሪያ ቤተ መቅደስ ለሆነችዉ እመቤታችን በስሟ በዓል ሊደረግላት ይገባል፤ ‹‹የጻድቅ መታሰቢያ ለዘላለም ይኖራል›› እንዳለ ቅዱስ ዳዊት መዝ. 111፥7 በተአምረ ማርያም ላይ በዝርዝር እንደተቀመጠዉ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም 33ት በዓላት አሏት፡፡ ከእነዚህ በዓላት ሁሉ አስበልጣ የምትወደዉ በዓለ ልደቷን እንደሆነ በአጼ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመነ መንግሥት ከዐረብኛ ወደ ግእዝ በተተረጎመዉ እመቤታችን በተለያዩ ሀገራት ያደረገቻችዉን ገቢረ ተአምራት በኢትዮጵያ ከተፈጸሙት ጋር አካቶ የያዘው ተአምረ ማርያም በዝርዝር ያስረዳል፡፡ ፠ #ልደቷ_መጽሐፍ_ቅዱስ_ላይ_ከሌለ_ተቀባይነት_እንዴት_ይኖረዋል? በመጽሐፍ ቅዱስ ያልተካተቱና ምሉዕነት የሌላቸዉ ታሪኮች በአዋልደ መጻሕፍት እንደሚሟሉ ራሱ መጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳል ለምሳሌ ስለ ቅዱስ ዳዊት የሚናገረዉ መጽሐፈ ዜና መዋዕል ‹‹የንጉሡም የዳዊት የፊተኛዉና የኋለኛዉ ነገር በነቢዩ በናታን ታሪክ እንዲሁም በባለ ራእዩም በጋድ ታሪክ ላይ ተጽፏል›› ይላል፡፡ 1ኛ ዜና 29፥29 ፠ #የእመቤታችን_የልደቷ_ታሪክ የእመቤታችን ወላጆች በአብዛኛዉ አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ‹‹ሐና››ና ኢያቄም/ዮአኪን በሚለዉ ስም የሚጠሩ ሲሆን ሐና በቤተልሔም ተወልዳ እንዳደገች ታሪክ ያስረዳል፡፡ በናዝሬት ገሊላ ለመሥዋዕት የሚሆኑ በጎች የሚያቀርብ እንዲሁም እረኛ የነበረዉን ኢያቄምንም አግብታለች፡፡ ቅድስት ሐና ወደ ቤተ መቅደስ ስትሔድ እርግብን አይታ ታለቅስ ነበር፡፡ ከብዙ ልመና በኋላ ቅድስት ድንግል ማርያምን ግንቦት አንድ ቀን በደብረ ሊባኖስ ወልደዋል፡፡ ስለ ሐና መካንነት ወደ ቤተ መቅደስ ሄደዉ መባዕ ሲያቀርቡ ካህኑ ያልተቀበላቸዉ መሆኑን በብስራተ መልአክ ልጅ እንደሚወልዱ እንደተነገራቸዉ በእኛ ቤተ ክርስቲያን የሚተረከዉና በሌሎች ኦርቶዶክሳዊያን አብያተ ክርስቲያናት የሚነገረዉ ታሪክ ተመሳሳይ ነዉ፡፡ ፠ #እመቤታችን_የት_ተወለደች? እመቤታችን ስለተወለደችበት ስፍራ በዓለም የተለያዩ ሐሳቦች ይስተጋባሉ፡፡ ሌላዉ ቀርቶ በዶግማ አንድነት ባላቸዉ አኃት አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ በእንዲህ ዓይነት ታሪክ ነክ ጉዳዮች ላይ ልዩነት መኖራቸዉ የተለመደ ክስተት ነዉ፡፡ የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ሁለት ሐሳቦች የሚያነሱ ሲሆን፤ አንደኛዉ ‹‹ድንግል ማርያም ብስራተ መልአክ በሰማችበት ናዝሬት ተወልዳለች›› የሚል ነዉ፡፡ ሁለተኛዉ ሐሳብ ደግሞ ‹‹ከሦስተኛዉ ክ/ዘመን ወዲህ የማርያም መግቢያ ተብሎ በሚታወቀዉ ከኢየሩሳሌም የቅድስት ሐና የክሩሲድ ቤ/ክ በታች ነዉ የተወለደችዉ የሚል ነዉ፡፡ የግብጽ ስንክሳር የእመቤታችን የትዉልድ ስፍራ በናዝሬት ነዉ ይላል፡፡ የኢትዮጵያ ስንክሳር ግን በቀደምትነታቸዉ ተጠብቀዉ የቆዩ ከመሆናቸዉ አንጻር ተአማኒነታቸዉ የጎላ መሆኑን ያሳያል፡፡ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት የእመቤታችን የትዉልድ ስፍራ ሊባኖስ የተባለዉ ተራራማ ሀገር ነዉ፡፡ ሊባኖስ ከገሊላ በስተ ሰሜንና ከፊንቄ በስተምስራቅ ይገኛል፡፡ ‹‹ሙሽራየ ሆይ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነይ›› መኃ. 4፥7 የሚለዉ ቃለ ትንቢት ምሥጢርም የአመቤታችን መካነ ልደት የሊባኖስ ተራራ ስለመሆኑ የሚያጠይቅ እንደሆነ ምስክርነታቸዉ የታመነ የቤተ ክርስቲያን ሊቃዉንት ያስረዳሉ፡፡ ፠ #የልደታ_ለማርያም_በዓል_መቸ_ነዉ? እንደተወለደችበት ሥፍራ የእመቤታችን የልደት ቀን እንዲሁ አወዛጋቢ ነዉ፡፡ በ6ኛዉ ና7ኛዉ መቶ/ክ/ዘመን ነዉ የሚሉ የተለያዩ ሃሳቦች የተጻፉ ሲሆን Encyclopaedic of Christian antiquities ደግሞ በ431 ዓ/ም ከተካሄደዉና ንስጥሮስ ከተወገዘበት ከጉባኤ ኤፌሶን በኋላ ነዉ ይላል፡፡ በዓለም ቅዱሳንን የሚያከብሩ አብያተ ክርስቲያናት የቅዱሳንን በዓለ እረፍታቸዉን የሚያከብሩ ሲሆን ልደታቸዉ የሚከበረዉም በሦስተኛ ደረጃ የመጥምቀ መለኮት ቅ/ ዮሐንስ፤ በሁለተኛ ደረጃ የእመቤታችን ቅ/ድንግል ማርያም ልደት ነዉ፡፡ በአንደኛ ደረጃ ለስም አጠራሩ ክብር ይግባዉና የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ነዉ፡፡ የአመቤታችን ልደት በምዕራባዊያን አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ኬ.ክ በመጋገር፡ የአመቤታችን ትንሽ ሀዉልት በማቆም ዐስር ሻማዎችን በማብራት ያከብራሉ፡፡ #የድንግል_ማርያም_ልደት_ለምን_ይከበራል? * ስለ መጥምቁ ዮሐንስ ልደት በመልአኩ ቅ/ገብርኤል አንደበት‹‹በመወለዱ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል›› በማለት ተነግሯል (ሉቃ 1-14)፤ ምክንያቱም ቅ/ዮሐንስ የጌታ መንገድ ጠራጊ፥ የአዋጅ ነጋሪ በመሆኑ ነዉ፡፡ የቅዱስ ዮሐንስ መወለድ ለብዙዎች ደስታ ምክንያት ከሆነ፤ የድንግል ማርያም ልደትማ ምንኛ የሚያስደስት ይሆን!?፡፡ስለሆነም ከጌታ ቀን ቀጥሎ የምንደሰትበት ትልቁ ቀን የእርሷ የልደት ቀን ነዉ፡፡ * የቀርጤሱ ቅ/እንድርያስ ስለ ከበረ ልደቷ እንዲህ ብሏል ‹‹ይህ በዓል በሐዲስና በብሉይ ኪዳን መካከል መገኛ ሆነ፡፡ ምሳሌዎቹ በእዉነታ፣ አሮጌዉ በአዲስ ቃል ኪዳን ተተኩ፡፡ ፍጥረት ሁሉ በደስታ ይዘምራል የዚህን ቀንም ደስታ ይካፈላል፡፡ ይህ መቅደሱን የሰራበት ዕለት ነዉ፡፡ ይህ ዕለት ትልቅ ሕንፃ የታነጸበትና ፍጡር የፈጣሪ ማደሪያ ለመሆን የተዘጋጀበት ዕለት ነዉ፡፡››ብሏል * እመቤታችን ለፀሐዩ መምጣት የተዘረጋች ሰማይ፤ በቅድመ አያቶቿ በነ ቴክታና ጰጥሪቃ ሕልም እንደታየችዉ በሌሊት የምታበራ ጨረቃ፤ የብሉይ ኪዳን ማብቂያ የሐዲስ ኪዳን መጀመሪያ ናትና ልደቷ ለሰዉ ልጅ ሁሉ ደስታ ነዉ፡፡ * ነቢያት በብዙ ሕብረ አምሳል የተናገሩላት ‹‹መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራራዎች ናቸዉ››፤ ‹‹ከእሴይ ስር በትር ትወጣለች አበባዋም ከግንዱ ይወጣል››፤ ‹‹ሙሽራየ ሆይ ከሊባኖስ ነይ››፤ …. ብለዉ የተናገሩላት ቅ/ድ/ማርያም ልደቷ የትንቢታቸዉ ፍፃሜ ነዉና ታላቅ ደስታቸዉ ደስታችንም ነዉ፡፡ (መዝ. 86፥1፣ ኢሳ. 11፥1፣ መኃ. 4፥7) * በዓለም ላይ የብዙ ታዋቂ ሰዎች ልደት ከሞቱም በኋላም ጭምር በታላቅ ድምቀት ይከበራል፤ ታዋቂ ያልሆኑ ሰዎች ልደትም እንዲሁ ይታሰባል፡፡ ለሰዉ ልጅ መዳን ምክንያት የሆነች የአምላክ እናት የተወለደችበት ቀን ግን ምንኛ ሊከበር ይገባዉ ይሆን! ፠ #የግንቦት_ልደታ_በዓል_አከባበር ሐናና ኢያቄም ከአይሁድ ለማምለጥ ተሰደዉ በአድባረ ሊባኖስ ስር እመቤታችንን ወለዱ በወቅቱ ከቤት የወጡት ለሽሽት ነበርና ስንቅ ስላልያዙ ምግባቸዉ ‹‹ንፍሮና ጥራጥሬ›› ነበር፡፡ ይኼንን ትዉፊት በመያዝ በዓሉ ከቤት ዉጭ ንፍሮ እየተበላ ይከበራል፡፡ ሆኖም ግን በበጎ ነገሮች ሰበብ ክፉ ዓላማዉን ማስፈጸም የሚፈልገዉ ዲያቢሎስ በማር መሃል መርዝን ከሚጨምርባቸዉ መንፈሳውያት በዓላት አንዱ የግንቦት ልደታ የእመቤታችን በዓል ነዉ፡፡ አንዳንዶች በድፍረት ለአድባር ለዉጋር ነዉ ፣ቆሌዉን ለመለመን ነዉ፣ እያሉ ንፍሮ የሚበትኑ፣ ፈንድሻ የሚጥሉ፣ ቡና የሚረጩ፣ ቂቤ የሚቀቡ፣ የከብት ደም የሚያፈሱ፣ እነዚህ በእርግጥም ጣዖት አምላኪዎች ናቸዉ፡፡ /የቀ.ደ.ሰ. መድኀኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/

#ልደታ_ለማርያም ምሥራቀ ምሥራቃት ሙፃአ ፀሐይ እግዝእትነ ዘመና ሙዳይ፤ ተወልደት ዮም ዳግሚት ሰማይ፡፡ ፠ #የግንቦት_ልደታ_ለማርያም_ክብረ_በዓልና_የእመቤታችን_በዓላት በቀደመዉ ዘመን በዘመነ ብሉይ ‹‹የቤተ መቅደስ መታደስ በዓል›› ይከበር እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳል፡፡ ይህ በዓል እስከ ጌታችን ዘመንም ይከበር ነበር፡፡ /ዮሐ. 10፥22/ በሐዲስ ኪዳን እውነተኛ የእግዚአብሔር ማደሪያ ቤተ መቅደስ ለሆነችዉ እመቤታችን በስሟ በዓል ሊደረግላት ይገባል፤ ‹‹የጻድቅ መታሰቢያ ለዘላለም ይኖራል›› እንዳለ ቅዱስ ዳዊት መዝ. 111፥7 በተአምረ ማርያም ላይ በዝርዝር እንደተቀመጠዉ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም 33ት በዓላት አሏት፡፡ ከእነዚህ በዓላት ሁሉ አስበልጣ የምትወደዉ በዓለ ልደቷን እንደሆነ በአጼ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመነ መንግሥት ከዐረብኛ ወደ ግእዝ በተተረጎመዉ እመቤታችን በተለያዩ ሀገራት ያደረገቻችዉን ገቢረ ተአምራት በኢትዮጵያ ከተፈጸሙት ጋር አካቶ የያዘው ተአምረ ማርያም በዝርዝር ያስረዳል፡፡ ፠ #ልደቷ_መጽሐፍ_ቅዱስ_ላይ_ከሌለ_ተቀባይነት_እንዴት_ይኖረዋል? በመጽሐፍ ቅዱስ ያልተካተቱና ምሉዕነት የሌላቸዉ ታሪኮች በአዋልደ መጻሕፍት እንደሚሟሉ ራሱ መጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳል ለምሳሌ ስለ ቅዱስ ዳዊት የሚናገረዉ መጽሐፈ ዜና መዋዕል ‹‹የንጉሡም የዳዊት የፊተኛዉና የኋለኛዉ ነገር በነቢዩ በናታን ታሪክ እንዲሁም በባለ ራእዩም በጋድ ታሪክ ላይ ተጽፏል›› ይላል፡፡ 1ኛ ዜና 29፥29 ፠ #የእመቤታችን_የልደቷ_ታሪክ የእመቤታችን ወላጆች በአብዛኛዉ አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ‹‹ሐና››ና ኢያቄም/ዮአኪን በሚለዉ ስም የሚጠሩ ሲሆን ሐና በቤተልሔም ተወልዳ እንዳደገች ታሪክ ያስረዳል፡፡ በናዝሬት ገሊላ ለመሥዋዕት የሚሆኑ በጎች የሚያቀርብ እንዲሁም እረኛ የነበረዉን ኢያቄምንም አግብታለች፡፡ ቅድስት ሐና ወደ ቤተ መቅደስ ስትሔድ እርግብን አይታ ታለቅስ ነበር፡፡ ከብዙ ልመና በኋላ ቅድስት ድንግል ማርያምን ግንቦት አንድ ቀን በደብረ ሊባኖስ ወልደዋል፡፡ ስለ ሐና መካንነት ወደ ቤተ መቅደስ ሄደዉ መባዕ ሲያቀርቡ ካህኑ ያልተቀበላቸዉ መሆኑን በብስራተ መልአክ ልጅ እንደሚወልዱ እንደተነገራቸዉ በእኛ ቤተ ክርስቲያን የሚተረከዉና በሌሎች ኦርቶዶክሳዊያን አብያተ ክርስቲያናት የሚነገረዉ ታሪክ ተመሳሳይ ነዉ፡፡ ፠ #እመቤታችን_የት_ተወለደች? እመቤታችን ስለተወለደችበት ስፍራ በዓለም የተለያዩ ሐሳቦች ይስተጋባሉ፡፡ ሌላዉ ቀርቶ በዶግማ አንድነት ባላቸዉ አኃት አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ በእንዲህ ዓይነት ታሪክ ነክ ጉዳዮች ላይ ልዩነት መኖራቸዉ የተለመደ ክስተት ነዉ፡፡ የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ሁለት ሐሳቦች የሚያነሱ ሲሆን፤ አንደኛዉ ‹‹ድንግል ማርያም ብስራተ መልአክ በሰማችበት ናዝሬት ተወልዳለች›› የሚል ነዉ፡፡ ሁለተኛዉ ሐሳብ ደግሞ ‹‹ከሦስተኛዉ ክ/ዘመን ወዲህ የማርያም መግቢያ ተብሎ በሚታወቀዉ ከኢየሩሳሌም የቅድስት ሐና የክሩሲድ ቤ/ክ በታች ነዉ የተወለደችዉ የሚል ነዉ፡፡ የግብጽ ስንክሳር የእመቤታችን የትዉልድ ስፍራ በናዝሬት ነዉ ይላል፡፡ የኢትዮጵያ ስንክሳር ግን በቀደምትነታቸዉ ተጠብቀዉ የቆዩ ከመሆናቸዉ አንጻር ተአማኒነታቸዉ የጎላ መሆኑን ያሳያል፡፡ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት የእመቤታችን የትዉልድ ስፍራ ሊባኖስ የተባለዉ ተራራማ ሀገር ነዉ፡፡ ሊባኖስ ከገሊላ በስተ ሰሜንና ከፊንቄ በስተምስራቅ ይገኛል፡፡ ‹‹ሙሽራየ ሆይ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነይ›› መኃ. 4፥7 የሚለዉ ቃለ ትንቢት ምሥጢርም የአመቤታችን መካነ ልደት የሊባኖስ ተራራ ስለመሆኑ የሚያጠይቅ እንደሆነ ምስክርነታቸዉ የታመነ የቤተ ክርስቲያን ሊቃዉንት ያስረዳሉ፡፡ ፠ #የልደታ_ለማርያም_በዓል_መቸ_ነዉ? እንደተወለደችበት ሥፍራ የእመቤታችን የልደት ቀን እንዲሁ አወዛጋቢ ነዉ፡፡ በ6ኛዉ ና7ኛዉ መቶ/ክ/ዘመን ነዉ የሚሉ የተለያዩ ሃሳቦች የተጻፉ ሲሆን Encyclopaedic of Christian antiquities ደግሞ በ431 ዓ/ም ከተካሄደዉና ንስጥሮስ ከተወገዘበት ከጉባኤ ኤፌሶን በኋላ ነዉ ይላል፡፡ በዓለም ቅዱሳንን የሚያከብሩ አብያተ ክርስቲያናት የቅዱሳንን በዓለ እረፍታቸዉን የሚያከብሩ ሲሆን ልደታቸዉ የሚከበረዉም በሦስተኛ ደረጃ የመጥምቀ መለኮት ቅ/ ዮሐንስ፤ በሁለተኛ ደረጃ የእመቤታችን ቅ/ድንግል ማርያም ልደት ነዉ፡፡ በአንደኛ ደረጃ ለስም አጠራሩ ክብር ይግባዉና የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ነዉ፡፡ የአመቤታችን ልደት በምዕራባዊያን አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ኬ.ክ በመጋገር፡ የአመቤታችን ትንሽ ሀዉልት በማቆም ዐስር ሻማዎችን በማብራት ያከብራሉ፡፡ #የድንግል_ማርያም_ልደት_ለምን_ይከበራል? * ስለ መጥምቁ ዮሐንስ ልደት በመልአኩ ቅ/ገብርኤል አንደበት‹‹በመወለዱ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል›› በማለት ተነግሯል (ሉቃ 1-14)፤ ምክንያቱም ቅ/ዮሐንስ የጌታ መንገድ ጠራጊ፥ የአዋጅ ነጋሪ በመሆኑ ነዉ፡፡ የቅዱስ ዮሐንስ መወለድ ለብዙዎች ደስታ ምክንያት ከሆነ፤ የድንግል ማርያም ልደትማ ምንኛ የሚያስደስት ይሆን!?፡፡ስለሆነም ከጌታ ቀን ቀጥሎ የምንደሰትበት ትልቁ ቀን የእርሷ የልደት ቀን ነዉ፡፡ * የቀርጤሱ ቅ/እንድርያስ ስለ ከበረ ልደቷ እንዲህ ብሏል ‹‹ይህ በዓል በሐዲስና በብሉይ ኪዳን መካከል መገኛ ሆነ፡፡ ምሳሌዎቹ በእዉነታ፣ አሮጌዉ በአዲስ ቃል ኪዳን ተተኩ፡፡ ፍጥረት ሁሉ በደስታ ይዘምራል የዚህን ቀንም ደስታ ይካፈላል፡፡ ይህ መቅደሱን የሰራበት ዕለት ነዉ፡፡ ይህ ዕለት ትልቅ ሕንፃ የታነጸበትና ፍጡር የፈጣሪ ማደሪያ ለመሆን የተዘጋጀበት ዕለት ነዉ፡፡››ብሏል * እመቤታችን ለፀሐዩ መምጣት የተዘረጋች ሰማይ፤ በቅድመ አያቶቿ በነ ቴክታና ጰጥሪቃ ሕልም እንደታየችዉ በሌሊት የምታበራ ጨረቃ፤ የብሉይ ኪዳን ማብቂያ የሐዲስ ኪዳን መጀመሪያ ናትና ልደቷ ለሰዉ ልጅ ሁሉ ደስታ ነዉ፡፡ * ነቢያት በብዙ ሕብረ አምሳል የተናገሩላት ‹‹መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራራዎች ናቸዉ››፤ ‹‹ከእሴይ ስር በትር ትወጣለች አበባዋም ከግንዱ ይወጣል››፤ ‹‹ሙሽራየ ሆይ ከሊባኖስ ነይ››፤ …. ብለዉ የተናገሩላት ቅ/ድ/ማርያም ልደቷ የትንቢታቸዉ ፍፃሜ ነዉና ታላቅ ደስታቸዉ ደስታችንም ነዉ፡፡ (መዝ. 86፥1፣ ኢሳ. 11፥1፣ መኃ. 4፥7) * በዓለም ላይ የብዙ ታዋቂ ሰዎች ልደት ከሞቱም በኋላም ጭምር በታላቅ ድምቀት ይከበራል፤ ታዋቂ ያልሆኑ ሰዎች ልደትም እንዲሁ ይታሰባል፡፡ ለሰዉ ልጅ መዳን ምክንያት የሆነች የአምላክ እናት የተወለደችበት ቀን ግን ምንኛ ሊከበር ይገባዉ ይሆን! ፠ #የግንቦት_ልደታ_በዓል_አከባበር ሐናና ኢያቄም ከአይሁድ ለማምለጥ ተሰደዉ በአድባረ ሊባኖስ ስር እመቤታችንን ወለዱ በወቅቱ ከቤት የወጡት ለሽሽት ነበርና ስንቅ ስላልያዙ ምግባቸዉ ‹‹ንፍሮና ጥራጥሬ›› ነበር፡፡ ይኼንን ትዉፊት በመያዝ በዓሉ ከቤት ዉጭ ንፍሮ እየተበላ ይከበራል፡፡ ሆኖም ግን በበጎ ነገሮች ሰበብ ክፉ ዓላማዉን ማስፈጸም የሚፈልገዉ ዲያቢሎስ በማር መሃል መርዝን ከሚጨምርባቸዉ መንፈሳውያት በዓላት አንዱ የግንቦት ልደታ የእመቤታችን በዓል ነዉ፡፡ አንዳንዶች በድፍረት ለአድባር ለዉጋር ነዉ ፣ቆሌዉን ለመለመን ነዉ፣ እያሉ ንፍሮ የሚበትኑ፣ ፈንድሻ የሚጥሉ፣ ቡና የሚረጩ፣ ቂቤ የሚቀቡ፣ የከብት ደም የሚያፈሱ፣ እነዚህ በእርግጥም ጣዖት አምላኪዎች ናቸዉ፡፡

#ልደታ_ለማርያም ምሥራቀ ምሥራቃት ሙፃአ ፀሐይ እግዝእትነ ዘመና ሙዳይ፤ ተወልደት ዮም ዳግሚት ሰማይ፡፡ ፠ #የግንቦት_ልደታ_ለማርያም_ክብረ_በዓልና_የእመቤታችን_በዓላት በቀደመዉ ዘመን በዘመነ ብሉይ ‹‹የቤተ መቅደስ መታደስ በዓል›› ይከበር እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳል፡፡ ይህ በዓል እስከ ጌታችን ዘመንም ይከበር ነበር፡፡ /ዮሐ. 10፥22/ በሐዲስ ኪዳን እውነተኛ የእግዚአብሔር ማደሪያ ቤተ መቅደስ ለሆነችዉ እመቤታችን በስሟ በዓል ሊደረግላት ይገባል፤ ‹‹የጻድቅ መታሰቢያ ለዘላለም ይኖራል›› እንዳለ ቅዱስ ዳዊት መዝ. 111፥7 በተአምረ ማርያም ላይ በዝርዝር እንደተቀመጠዉ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም 33ት በዓላት አሏት፡፡ ከእነዚህ በዓላት ሁሉ አስበልጣ የምትወደዉ በዓለ ልደቷን እንደሆነ በአጼ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመነ መንግሥት ከዐረብኛ ወደ ግእዝ በተተረጎመዉ እመቤታችን በተለያዩ ሀገራት ያደረገቻችዉን ገቢረ ተአምራት በኢትዮጵያ ከተፈጸሙት ጋር አካቶ የያዘው ተአምረ ማርያም በዝርዝር ያስረዳል፡፡ ፠ #ልደቷ_መጽሐፍ_ቅዱስ_ላይ_ከሌለ_ተቀባይነት_እንዴት_ይኖረዋል? በመጽሐፍ ቅዱስ ያልተካተቱና ምሉዕነት የሌላቸዉ ታሪኮች በአዋልደ መጻሕፍት እንደሚሟሉ ራሱ መጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳል ለምሳሌ ስለ ቅዱስ ዳዊት የሚናገረዉ መጽሐፈ ዜና መዋዕል ‹‹የንጉሡም የዳዊት የፊተኛዉና የኋለኛዉ ነገር በነቢዩ በናታን ታሪክ እንዲሁም በባለ ራእዩም በጋድ ታሪክ ላይ ተጽፏል›› ይላል፡፡ 1ኛ ዜና 29፥29 ፠ #የእመቤታችን_የልደቷ_ታሪክ የእመቤታችን ወላጆች በአብዛኛዉ አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ‹‹ሐና››ና ኢያቄም/ዮአኪን በሚለዉ ስም የሚጠሩ ሲሆን ሐና በቤተልሔም ተወልዳ እንዳደገች ታሪክ ያስረዳል፡፡ በናዝሬት ገሊላ ለመሥዋዕት የሚሆኑ በጎች የሚያቀርብ እንዲሁም እረኛ የነበረዉን ኢያቄምንም አግብታለች፡፡ ቅድስት ሐና ወደ ቤተ መቅደስ ስትሔድ እርግብን አይታ ታለቅስ ነበር፡፡ ከብዙ ልመና በኋላ ቅድስት ድንግል ማርያምን ግንቦት አንድ ቀን በደብረ ሊባኖስ ወልደዋል፡፡ ስለ ሐና መካንነት ወደ ቤተ መቅደስ ሄደዉ መባዕ ሲያቀርቡ ካህኑ ያልተቀበላቸዉ መሆኑን በብስራተ መልአክ ልጅ እንደሚወልዱ እንደተነገራቸዉ በእኛ ቤተ ክርስቲያን የሚተረከዉና በሌሎች ኦርቶዶክሳዊያን አብያተ ክርስቲያናት የሚነገረዉ ታሪክ ተመሳሳይ ነዉ፡፡ ፠ #እመቤታችን_የት_ተወለደች? እመቤታችን ስለተወለደችበት ስፍራ በዓለም የተለያዩ ሐሳቦች ይስተጋባሉ፡፡ ሌላዉ ቀርቶ በዶግማ አንድነት ባላቸዉ አኃት አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ በእንዲህ ዓይነት ታሪክ ነክ ጉዳዮች ላይ ልዩነት መኖራቸዉ የተለመደ ክስተት ነዉ፡፡ የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ሁለት ሐሳቦች የሚያነሱ ሲሆን፤ አንደኛዉ ‹‹ድንግል ማርያም ብስራተ መልአክ በሰማችበት ናዝሬት ተወልዳለች›› የሚል ነዉ፡፡ ሁለተኛዉ ሐሳብ ደግሞ ‹‹ከሦስተኛዉ ክ/ዘመን ወዲህ የማርያም መግቢያ ተብሎ በሚታወቀዉ ከኢየሩሳሌም የቅድስት ሐና የክሩሲድ ቤ/ክ በታች ነዉ የተወለደችዉ የሚል ነዉ፡፡ የግብጽ ስንክሳር የእመቤታችን የትዉልድ ስፍራ በናዝሬት ነዉ ይላል፡፡ የኢትዮጵያ ስንክሳር ግን በቀደምትነታቸዉ ተጠብቀዉ የቆዩ ከመሆናቸዉ አንጻር ተአማኒነታቸዉ የጎላ መሆኑን ያሳያል፡፡ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት የእመቤታችን የትዉልድ ስፍራ ሊባኖስ የተባለዉ ተራራማ ሀገር ነዉ፡፡ ሊባኖስ ከገሊላ በስተ ሰሜንና ከፊንቄ በስተምስራቅ ይገኛል፡፡ ‹‹ሙሽራየ ሆይ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነይ›› መኃ. 4፥7 የሚለዉ ቃለ ትንቢት ምሥጢርም የአመቤታችን መካነ ልደት የሊባኖስ ተራራ ስለመሆኑ የሚያጠይቅ እንደሆነ ምስክርነታቸዉ የታመነ የቤተ ክርስቲያን ሊቃዉንት ያስረዳሉ፡፡ ፠ #የልደታ_ለማርያም_በዓል_መቸ_ነዉ? እንደተወለደችበት ሥፍራ የእመቤታችን የልደት ቀን እንዲሁ አወዛጋቢ ነዉ፡፡ በ6ኛዉ ና7ኛዉ መቶ/ክ/ዘመን ነዉ የሚሉ የተለያዩ ሃሳቦች የተጻፉ ሲሆን Encyclopaedic of Christian antiquities ደግሞ በ431 ዓ/ም ከተካሄደዉና ንስጥሮስ ከተወገዘበት ከጉባኤ ኤፌሶን በኋላ ነዉ ይላል፡፡ በዓለም ቅዱሳንን የሚያከብሩ አብያተ ክርስቲያናት የቅዱሳንን በዓለ እረፍታቸዉን የሚያከብሩ ሲሆን ልደታቸዉ የሚከበረዉም በሦስተኛ ደረጃ የመጥምቀ መለኮት ቅ/ ዮሐንስ፤ በሁለተኛ ደረጃ የእመቤታችን ቅ/ድንግል ማርያም ልደት ነዉ፡፡ በአንደኛ ደረጃ ለስም አጠራሩ ክብር ይግባዉና የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ነዉ፡፡ የአመቤታችን ልደት በምዕራባዊያን አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ኬ.ክ በመጋገር፡ የአመቤታችን ትንሽ ሀዉልት በማቆም ዐስር ሻማዎችን በማብራት ያከብራሉ፡፡ #የድንግል_ማርያም_ልደት_ለምን_ይከበራል? * ስለ መጥምቁ ዮሐንስ ልደት በመልአኩ ቅ/ገብርኤል አንደበት‹‹በመወለዱ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል›› በማለት ተነግሯል (ሉቃ 1-14)፤ ምክንያቱም ቅ/ዮሐንስ የጌታ መንገድ ጠራጊ፥ የአዋጅ ነጋሪ በመሆኑ ነዉ፡፡ የቅዱስ ዮሐንስ መወለድ ለብዙዎች ደስታ ምክንያት ከሆነ፤ የድንግል ማርያም ልደትማ ምንኛ የሚያስደስት ይሆን!?፡፡ስለሆነም ከጌታ ቀን ቀጥሎ የምንደሰትበት ትልቁ ቀን የእርሷ የልደት ቀን ነዉ፡፡ * የቀርጤሱ ቅ/እንድርያስ ስለ ከበረ ልደቷ እንዲህ ብሏል ‹‹ይህ በዓል በሐዲስና በብሉይ ኪዳን መካከል መገኛ ሆነ፡፡ ምሳሌዎቹ በእዉነታ፣ አሮጌዉ በአዲስ ቃል ኪዳን ተተኩ፡፡ ፍጥረት ሁሉ በደስታ ይዘምራል የዚህን ቀንም ደስታ ይካፈላል፡፡ ይህ መቅደሱን የሰራበት ዕለት ነዉ፡፡ ይህ ዕለት ትልቅ ሕንፃ የታነጸበትና ፍጡር የፈጣሪ ማደሪያ ለመሆን የተዘጋጀበት ዕለት ነዉ፡፡››ብሏል * እመቤታችን ለፀሐዩ መምጣት የተዘረጋች ሰማይ፤ በቅድመ አያቶቿ በነ ቴክታና ጰጥሪቃ ሕልም እንደታየችዉ በሌሊት የምታበራ ጨረቃ፤ የብሉይ ኪዳን ማብቂያ የሐዲስ ኪዳን መጀመሪያ ናትና ልደቷ ለሰዉ ልጅ ሁሉ ደስታ ነዉ፡፡ * ነቢያት በብዙ ሕብረ አምሳል የተናገሩላት ‹‹መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራራዎች ናቸዉ››፤ ‹‹ከእሴይ ስር በትር ትወጣለች አበባዋም ከግንዱ ይወጣል››፤ ‹‹ሙሽራየ ሆይ ከሊባኖስ ነይ››፤ …. ብለዉ የተናገሩላት ቅ/ድ/ማርያም ልደቷ የትንቢታቸዉ ፍፃሜ ነዉና ታላቅ ደስታቸዉ ደስታችንም ነዉ፡፡ (መዝ. 86፥1፣ ኢሳ. 11፥1፣ መኃ. 4፥7) * በዓለም ላይ የብዙ ታዋቂ ሰዎች ልደት ከሞቱም በኋላም ጭምር በታላቅ ድምቀት ይከበራል፤ ታዋቂ ያልሆኑ ሰዎች ልደትም እንዲሁ ይታሰባል፡፡ ለሰዉ ልጅ መዳን ምክንያት የሆነች የአምላክ እናት የተወለደችበት ቀን ግን ምንኛ ሊከበር ይገባዉ ይሆን! ፠ #የግንቦት_ልደታ_በዓል_አከባበር ሐናና ኢያቄም ከአይሁድ ለማምለጥ ተሰደዉ በአድባረ ሊባኖስ ስር እመቤታችንን ወለዱ በወቅቱ ከቤት የወጡት ለሽሽት ነበርና ስንቅ ስላልያዙ ምግባቸዉ ‹‹ንፍሮና ጥራጥሬ›› ነበር፡፡ ይኼንን ትዉፊት በመያዝ በዓሉ ከቤት ዉጭ ንፍሮ እየተበላ ይከበራል፡፡ ሆኖም ግን በበጎ ነገሮች ሰበብ ክፉ ዓላማዉን ማስፈጸም የሚፈልገዉ ዲያቢሎስ በማር መሃል መርዝን ከሚጨምርባቸዉ መንፈሳውያት በዓላት አንዱ የግንቦት ልደታ የእመቤታችን በዓል ነዉ፡፡ አንዳንዶች በድፍረት ለአድባር ለዉጋር ነዉ ፣ቆሌዉን ለመለመን ነዉ፣ እያሉ ንፍሮ የሚበትኑ፣ ፈንድሻ የሚጥሉ፣ ቡና የሚረጩ፣ ቂቤ የሚቀቡ፣ የከብት ደም የሚያፈሱ፣ እነዚህ በእርግጥም ጣዖት አምላኪዎች ናቸዉ፡፡ እኛም ከእንደዚ ዓይነቶቹ አሰናካዮች በመለየት ይኼንን ታላቅ በዓል በተገባና በተረዳ ነገር እንድናከብረዉ የእመቤታችን ረድኤት በረከት አይለየን፡፡