fa
Feedback
የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን

የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን

رفتن به کانال در Telegram
5 357
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-97 روز
+730 روز
آرشیو پست ها
የባለስልጣኑ የአሰራር ጥራት ቁጥጥር ቡድን የ2018 የቅድመ የዝግጅት ስራዎች ክትትልና ቁጥጥር እያከናወነ ነው፡፡ (ነሃሴ 22 ቀን 2017 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና
+4
የባለስልጣኑ የአሰራር ጥራት ቁጥጥር ቡድን የ2018 የቅድመ የዝግጅት ስራዎች ክትትልና ቁጥጥር እያከናወነ ነው፡፡ (ነሃሴ 22 ቀን 2017 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የአሰራር ጥራት ቁጥጥር ቡድን በማዕከል እና በ9ኙም ቅ/ጽ/ቤት የ2018 በጀት አመት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች አፈጻጸም ክትትልና ቁጥጥር እያከናወነ ነው፡፡ አቶ አምላኩ ተበጀ የባለስልጣኑ የአሰራር ጥራት ቁጥጥር ቡድን መሪ በ2018 በጀት ዓመት የተቋሙን አገልግሎት አሰጣጥ መሰረት ያደረገ ከብልሹ አሰራር የጸዳ ጥራት ያለው የዕውቅናና የምዘና ስርዓትን ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን ገልጸው የመልካም አስተዳደርና ብልሹ አሰራርን በማስወገድ የተሻለ ክትትልና ቁጥጥር በማድረግ ጥራት ያለው የአሰራር ስርዓት በመፍጠር ግልፅና ተአማኒ በማድረግ ተጠያቂነት የሰፈነበት የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት ማስፈን ዋና አላማው መሆኑን ተናግረዋል::

ወ/ሮ ታጋይቱ አባቡ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ እና የጥራት ዘርፍ ሀላፊ እንደተናገሩት መልካም አስተዳደርና አገልግሎት አሰጣጥ ትኩረት ተሰጥቶት የሚሰራና ተቋማችንም ጥራትና ተገቢነትን የሚያረጋግጥ ተቋም እንደመሆኑ የመልካም አስተዳደር እና ብልሹ አሰራር ከኛ ባለፈ በሌሎች አይን በመታየት የሌሎችን ተሳትፎ ተጨምሮበት የሚታዩ ችግሮች ካሉ መፍተሄ እንዲኖረው አላማ ያደረገ መሆኑን ገልጸው ተቀራርቦ በመስራት ለተገልጋዩ ውጤታማ ቀልጣፋ እና አስደሳች አገልግሎት መስጠት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ አቶ አለልኝ ወንዴ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ እና የምዘና ዘርፍ ሀላፊ እንደገለጹት ችግሮችን በማወቅ አስቀድመን መፍታት የምንችለው እንዲሁም የውጤታማነት አቅም የሚኖረን በአብሮነት ስንሰራ ነው በጋራ በማቀድ በጋራ በመስራት የተገልጋዮቻችንን እርካታ እንጨምር ብለዋል፡፡ በመርሀ-ግብሩ ላይም የባለስልጣኑ ባለድርሻ አከላት የተገኙ ሲሆን የመማክርት ጉባኤ በመመስረትና ኮሚቴዎችን በማዋቀር መርሃ-ግብሩ ተጠናቋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

ባለስልጣኑ በ2018 መሪ እቅድ፣የመልካም አስተዳደር ችግሮች ልየታ እንዲሁም የአገልግሎት አሰጣጥ መማክርት ጉባኤ ማቋቋሚያ እና ትግበራ ማኑዋል ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያየ፡፡ (ነሃሴ 22 ቀ
+4
ባለስልጣኑ በ2018 መሪ እቅድ፣የመልካም አስተዳደር ችግሮች ልየታ እንዲሁም የአገልግሎት አሰጣጥ መማክርት ጉባኤ ማቋቋሚያ እና ትግበራ ማኑዋል ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያየ፡፡ (ነሃሴ 22 ቀን 2017 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በ2018 መሪ እቅድ፣የመልካም አስተዳደር ችግሮች ልየታ እንዲሁም የአገልግሎት አሰጣጥ መማክርት ጉባኤ ማቋቋሚያ እና ትግበራ ማኑዋል ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያየ፡፡ አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ በመርሃ-ግብሩ ላይ እንደገለጹት ተቀራርበን አስቀድመን በማቀድ የሚመጡትን ችግሮች በመከላከልና ፍትሃዊ ግልጽነት ያለውና የተሳለጠ አገልግሎት ለመስጠት የመማክርት ጉባኤው አስፈላጊ መሆኑን ገልጸው በጋራ ስንሰራ ውጤት እናመጣለን፣የተገልጋይ እርካታን እናሳድጋለን ስለዚህ በጋራ እንስራ ብለዋል፡፡ አቶ ነብዩ ዳዊት የባለስልጣኑ የእቅድ ዝግጅት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የ2018 በጀት ዓመት መሪ እቅድ እና የአገልግሎት አሰጣጥ መማክርት ጉባኤ ማቋቋሚያ እና ትግበራ ማኑዋል ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን የመማክርት ጉባኤው አላማ፣አስፈላጊነት፣ አደረጃጀትና አሰራር፣የስራ አስፈጻሚ መዋቅራዊ አደረጃጀትና ሀላፊነት፣የማዕከል ተቋማት ተግባርና ሀላፊነት፣ የመማክርት ጉባኤው ተጠሪነት፣የጉባኤው ተግባርና ሀላፊነት፣አጋዥ አካላት፣በየደረጃው የሚቋቋመው የመማክርት ገባኤ የግንኙነት አግባብ፣በመማክርት ጉባኤው የሚቀረጹ የውይይት አጀንዳዎች፣የጉባኤው አቅም ግንባታ ስራዎች እንዲሁም የተጠያቂነት አግባብ በሚሉ ይዘቶች ላይ ዝርዝር ሰነድ አቅርበዋል፡፡

ባለስልጣኑ እየተገነቡ ያሉትን የአቅመ ዳካማ ወገኖች ቤት ግንባታ ክትትል አደረገ፡፡ (ነሀሴ 22 ቀን 2017 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የትም
+4
ባለስልጣኑ እየተገነቡ ያሉትን የአቅመ ዳካማ ወገኖች ቤት ግንባታ ክትትል አደረገ፡፡ (ነሀሴ 22 ቀን 2017 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የትምህርት ማህብረሰብ አካላትን በማስተባበር እያሰራ ያለውን የአቅመ ደካማ ወገኖች ቤት የደረሰበትን የግንባታ ሂደት ክትትል አደረገ፡፡ ባለስልጣኑ ከመደበኛ ስራው ባሻገር ማህበራዊ ሃላፊነትን ከመወጣት አንጻር በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ ዋነኛው የአቅመ ደካማ ወገኖች ቤት ግንባታ በመሆኑ አሁን ያለበት የግንባታ ደረጃ ክትትል የተደረገ ሲሆን ጥሩ የሚባልና በተቀመጠለት የግንባታ ጊዜ የሚጠናቀቅ እንደሆነ ክትትሉ ያመላክታል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

አቶ ካሳ ወዳጅ የቅ/ጽ/ቤቱ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጥና ምርምር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የ2017 በጀት ዓመት የስታንዳርድ ኢንስፔክሽን ትንተና ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን የአጠቃላይ ትምህርት ተቋማት የ2017 ዓ.ም የኢንስፔክሽን ውጤት ንጽጽር፣የስታንዳርዶች አፈጻጸም ፣ የኢንስፔክሽን ትንተና ዋና ዋና ግኝቶች በኢንስፔክሽን ትግበራ ሂደት የታዩ ጥንካሬዎችና ያጋጠሙ ችግሮች እንዲሁም ምክረ ሀሳቦችን ዝርዝር ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን በክፍለ ከተማ ስር ካሉ የመንግስትና መንግስታዊ ያልሆኑ የትምህርት ተቋማት መካከልም 41 ቅድመ አንደኛ ደረጃ 24 አንደኛና መካከለኛ ደረጃ በድምሩ 65 ተቋማት በ2017 ዓ.ም የስታንዳርድ ኢንስፔክሽን የተሰራላቸው መሆኑን ገልጸው በበጀት ዓመቱ የተሻለ የደረጃ መሻሻል መኖሩንም ገልጸዋል ፡፡ አቶ ጌታነህ ባይሌ የእውቅና ፍቃድና እድሳት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የ2018 በጀት ዓመት መሪ አቅድ ያቀረቡ ሲሆን በመጨረሻም ከቤቱ ለተነሱት ሀሳብ አስተያየትና ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥቶበታል በ2017 በጀት ዓመት በኢንስፔክሽን የተሻለ አፈጻጸም ላሳዩ ተቋማት እና ባለሙያዎች የእውቅናና ሽልማት ተሰጥቷቸዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

ለትምህርት ጥራት መሳካት በእውቀት፣በክህሎትና በስነ ምግባር የታነፀ ትውልድ የማብቃት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ሁሉም የድርሻውን በመወጣት ለውጤታማነት መትጋት እንዳለበት ተገለፀ፡፡ (ነሃሴ 22
+5
ለትምህርት ጥራት መሳካት በእውቀት፣በክህሎትና በስነ ምግባር የታነፀ ትውልድ የማብቃት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ሁሉም የድርሻውን በመወጣት ለውጤታማነት መትጋት እንዳለበት ተገለፀ፡፡ (ነሃሴ 22 ቀን 2017 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የቦሌ ቅ/ጽ/ቤት የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት የ2017 ዓ.ም ስታንዳርድ ኢንስፔክሽን ውጤት ትንተና ሪፖርት እንዲሁም የ2018 በጀት ዓመት መሪ እቅድ ለባለድርሻ አካላት አቅርቧል፡፡ ወ/ሮ ሳምራዊት ጌታቸው የቦሌ ቅ/ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ በመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለጹት የትምህርት ስራ የጋራ ሀላፊነት የሚያስፈልገው ጉዳይ ነው፤ ስለዚህ እቅዶቻችንን በጋራ በአብሮነት በእውነተኛነት ለውጤታማነት መስራት ያስፈልጋል በመሆኑም የትኛውም ተቋም የመጪው ጊዜ ከፍታን በማሰብ በአብሮነት በመስራት የተቋማችሁን መሻሻል ልታሳዩ ይገባል ብለዋል፡፡ ወ/ሮ እፀገነት በቀለ የቅ/ጽ/ቤቱ የስነምግባርና ጸረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን በበጀት ዓመቱ ያከናወኗቸውን አበይት ተግባራት አፈፃፀም፣የቁልፍ ተግባራት አፈፃፀም፣የተገኙ ዋና ዋና ውጤቶች፣የነበሩ ጥንካሬዎች እና ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰዱ መፍትሄዎች እንዲሁም የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫ ሪፖርት አቅርበዋል፡፡

(ነሃሴ 22 ቀን 2017 ዓ.ም) ባለስልጣኑ በ2018 መሪ እቅድ፣የመልካም አስተዳደር ችግሮች ልየታ እንዲሁም የመማክርት ጉባኤን ለማቋቋም ከባለድርሻ አካላት ጋር እየተወያየ ነው፡፡ #ፌስቡክ;https
+4
(ነሃሴ 22 ቀን 2017 ዓ.ም) ባለስልጣኑ በ2018 መሪ እቅድ፣የመልካም አስተዳደር ችግሮች ልየታ እንዲሁም የመማክርት ጉባኤን ለማቋቋም ከባለድርሻ አካላት ጋር እየተወያየ ነው፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የክረምት በጎ ፈቃድ አንድ አካል የሆነው የደም ልገሳ መርሃ-ግብር #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

ከዚህ ቀደም ለአይሲቲ ባለሙያ ተወካዮች እና ለሰው ሃይል ባለሙዎች ስልጠናው የተሰጠ መሆኑን አስታውሰው በስልጠናው መሰረትም ወደ ተግባር የተገባ መሆኑንም ጨምረው ተናግረዋል፡፡ነገር ግን ሲስተሙ መጠቀም በሚያስችለው ደረጃ አገልግሎት ላይ ስለልዋለ የክለሳ ስልጠና መሰጠቱ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል፡፡በዚህም መሰረት አጠቃቀሙን እና ሲስተሙን የመሰልጠን ስራ እንደተሰራም ገልጸዋል፡፡በተጨማሪም ሲስተሙ ፈጣን፣ጊዜ ቆጣቢ እንዲሁም የተደራጀ መረጃን ለማግኘትም እንደሚያስችል ጨምረው ተናግረዋል በመሆኑም የሰው ሃይል ዳይሬክቶሬት ትኩረት በመስጠት በስልጠናው መሰረት ወደተግባር በመግባት በሀላፊነት መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

ባለስልጣኑ በተቀናጀ የሰው ሃይል ሲስተም ላይ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ሰጠ፡፡ (ነሀሴ 19 ቀን 2017 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የኢንፎርሜ
+3
ባለስልጣኑ በተቀናጀ የሰው ሃይል ሲስተም ላይ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ሰጠ፡፡ (ነሀሴ 19 ቀን 2017 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዳይሬክቶሬት በተቀናጀ የሰው ሀይል ሲስተም ላይ ለማእከል እና ለ9ኙም ቅ/ጽ/ቤት የሰው ሃይል ባለሙያዎች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ሰጠ፡፡ የባለስልጣኑ የኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ታምራት እንደገለጹት ሲስተሙ በፐብሊክ ሰርቪስ እና በፌደራል ደረጃ ተዘጋጅቶ በከተማ አስተዳደሩ ስርላሉ የመንግስት መስሪያቤቶች በአንድ ቋት ለመጠቀም ታስቦ የተሰራ መሆኑን ገልጸው፡፡

ደም ከሚለግሱት ሰራተኞች መካከል ወ/ሮ ቤተልሄም በእውቀት የባለስልጣኑ የሙያ ብቃት ሰረተፍኬሽን ቡድን መሪ እንደገለጹት ከዚህ ቀደም ባጋጠማቸው የጤና እክል ምክንያት ደም እንደተለገሳቸውና ጤናቸው እንደተመለሰ ገልጸው ዛሬ ደም በመለገሳቸው ደስተኛ እንደሆኑና ደም የለገሱት በደም መፍሰስ ምክንያት በሰዎች ላይ ለሚገጥመው የደም እጦት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማድረግ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

“የሚተካውን ደም በመስጠት የማይተካውን የሰው ልጅ ህይወት እንታደግ” (ነሀሴ 19 ቀን 2017 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በማዕከል እንዲሁም
+8
“የሚተካውን ደም በመስጠት የማይተካውን የሰው ልጅ ህይወት እንታደግ” (ነሀሴ 19 ቀን 2017 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በማዕከል እንዲሁም በቅርንጫፍ ፅ/ቤት ስር ያሉ ሰራተኞች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት የበጎ ፈቃድ መርሃ ግብር የደም ልገሳ አካሄዱ፡፡ አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ እንደገለጹት የሰው ልጅ ገንዘብ ኖሮት ባይሰጥ እውቀት ኖሮት አክሞ ባያድን የሚተካውን ደም በመስጠት የማይተካውን ህይወት መታደግ ከደስታ በላይ ደስታ እርካታ የሚሰጥ ነው ብለዋል፡፡ ወ/ሮ ታጋይቱ አባቡ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ እንደገለጹት የባለስልጣኑ አመራሮችና ሰራተኞች ማህበራዊ ሃላፊነታቸውን ከመወጣት አንጻር በደም እጥረት ምክንያት ደም አጥተው ለሚቸገሩ ወገኖች መታደግ በመሆኑ ደም ስንለግስ ደስተኞች ነን ፡፡በቀጣይም ሰው ተኮር ተግባሮችን ተቋማዊ ሆነው እንዲቀጥሉ እንደ ባለስልጣን ባህል አድርገን ሃላፊነታችንን በዘላቂነት እንወጣለን ብለዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ያስተላለፉት መልእክት የኢትዮጵያ ማንሠራራት ጅማሮ፤ የደም ጠብታ የላብ ጠብታ የዕንባ ጠብታ የውኃ ጠብታ ድምር ውጤት መሆኑን፣ ይህ ግድብ ህያው ምልክት ሆኖ ለ
+3
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ያስተላለፉት መልእክት የኢትዮጵያ ማንሠራራት ጅማሮ፤ የደም ጠብታ የላብ ጠብታ የዕንባ ጠብታ የውኃ ጠብታ ድምር ውጤት መሆኑን፣ ይህ ግድብ ህያው ምልክት ሆኖ ለትውልድ ሲመሰክር ይኖራል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ በመርሃ-ግብሩ ላይ እንደገለጹት ውጤታማ ለመሆን ጠንክሮ መስራት ያስፈልጋል፤ዛሬ በበጀት ዓመቱ የተሻለ አፈጻጻም ላመጡ ባለሙያዎች እውቅና ስንሰጥ በቀጣይ ለሌሎች መነቃቃትን ለመፍጠር ያግዛልና ሁላችንም በቀጣይ ጠንክረን መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

ባለስልጣኑ በ2017 በጀት ዓመት የተሻለ አፈፃፀም ላመጡ ሰራተኞች እውቅና ሰጠ፡፡ (ነሀሴ 19 ቀን 2017 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በ201
+5
ባለስልጣኑ በ2017 በጀት ዓመት የተሻለ አፈፃፀም ላመጡ ሰራተኞች እውቅና ሰጠ፡፡ (ነሀሴ 19 ቀን 2017 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በ2017 በጀት ዓመት የተሻለ አፈፃፀም ላመጡ ሰራተኞች እውቅና ሰጠ፡፡ ባለስልጣኑ ቅ/ጽ/ቤቶችን እንዲሁም በማዕከል ያሉትን ዳይሬክቶሬቶችና ቡድኖችን አወዳድሮ በ2017በጀት ዓመት የተሻለ አፈጻጸም ላላቸው የእውቅና መድረክ ማካሄዱ ይታወሳል፤በመሆኑም በዛሬው ዕለት በ2017 በጀት ዓመት ጥሩ አፈጻጸም ላመጡ ሰራተኞች የእውቅና መድረክ አካሂዷል፡፡ አቶ ሰለሞን አለማየሁ የባለስልጣኑ አማካሪ እንደገለፁት የተሻለ ውጤት ያመጡትን ለማበረታታት ይበልጥ አጠናክሮ እንዲቀጥሉ ለማድርግ ደከም ያሉትን ደግሞ ለማነቃቃት መድረኩ አስፈላጊ እንደሆነ ገልጸው የውጤት ተኮር የምዘና ስርዓትን ተከትሎ የመለየት ስራ በመስራት መድረኩ የተዘጋጀ መሆኑን በመግለጽ ሌሎች ስራተኞችም የተሻለ አፈፃፀም ካላቸው ሰራተኞች በመማር ውጤታማ መሆን ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ በመርሃ-ግብሩ ላይ እንደገለጹት በስነምግባር፣በእውቀት ፣በውጤታማነት እንዲሁም ራሳችንን በማሻሻል መስራት ለስው ልጅ ስኬት አስፈላጊ እንደመሆናቸው ልናዳብራቸው ይገባል ብለዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

ባለስልጣኑ የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር አካሄደ፡፡ (ነሀሴ 19 ቀን 2017 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የወ
+5
ባለስልጣኑ የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር አካሄደ፡፡ (ነሀሴ 19 ቀን 2017 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የወርቃማ ሰኞ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር "የስኬታማነት መገለጫ ባህሪያት" በሚል ርዕስ ተካሂዷል፡፡ አቶ አለልኝ ወንዴ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ እና የምዘና ዘርፍ ሀላፊ "የስኬታማነት መገለጫ ባህሪያት" በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን ስኬት ምን ማለት ነው? ስኬታማ ለመሆን የትኞቹ መሰረታዊ ባህሪያት ሊኖሩን ይገባል? እርስዎ ስኬታማ እንዲሆኑ በግልዎ ምን አይነት ባህሪያት እንዳለዎት ያምናሉ ?ለስኬት ጎጂ የሆኑ የትኞቹ የባህሪይ መገለጫዎች ናቸው? ለህይወት ስኬት ጠቃሚ የሆኑ ባህሪያት ምንድን ናቸው ? ሌሎቹስ እንዴት ማዳበር ይችላሉ? የሚሉትን መነሻ ሀሳቦችን ያነሱ ሲሆን ስኬታማ ለመሆኑ የተለያዩ መውደቅ መነሳቶች ቢኖሩም በአላማ በመፅናት፣ስኬታማ እንዳንሆን ከሚያደርጉን ነገሮች በመራቅ ያሰብነውን እሰከምናሳካ በአላማ መፅናት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

በመርሃ-ግብሩ በቀረቡት ሪፖርቶች ላይ ሃሳብና አስተያየቶች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

የባለስልጣኑ ጠቅላላ ካውንስል የ2018 በጀት ዓመት የ45 ቀናት ክንውኑን ገመገመ፡፡ (ነሀሴ 16 ቀን 2017 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ጠ
+4
የባለስልጣኑ ጠቅላላ ካውንስል የ2018 በጀት ዓመት የ45 ቀናት ክንውኑን ገመገመ፡፡ (ነሀሴ 16 ቀን 2017 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ጠቅላላ ካውንስል የ2018 በጀት ዓመት የ45 ቀናት ክንውኑን ገመገመ፡፡ አቶ ነብዩ ዳዊት የባለስልጣኑ የእቅድ ዝግጅት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የ45ቀናት ሪፖርቱን ያቀረቡ ሲሆን በሪፖርቱ በየዘርፉ የተከናወኑ ተግባራትን ዝርዝር አቅርበዋል፡፡ አቶ ስለሺ ታደለ የባለስልጣኑ የሪፎርምና አገ/አሰ/ክ/ድ/ዳይሬክቶሬት ዳይሪክተር በበኩላቸው የሪፎርም ስራዎች አፈጻጸምን በዝርዝር አቅርበዋል፡፡ አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ በመርሃ-ግብሩ ላይ እንደገለጹት በዝግጅት ምዕራፍ የተከናወኑት ተግባራት መልካም ስራዎች መኖራቸውን ገልጸው በቀሪ ተግባራት ላይ ትኩረት በማድረግና በመረባረብ ስራዎችን መፈጸም አስፈላጊ እንደሆነ ገልጸው፤ አገልግሎት አሰጣጥን አሰመልክቶ ስራን በጥራትና በስታንዳርድ መከወን፣ መልካም አስተዳደርን ማስፈን፣ብልሹ አሰራርን ማስወገድ፣ መረጃዎችን በአግባቡ ማደራጀትና ሪፖርቶችን ወቅቱን በጠበቀ ሁኔታ ማቅረብ፣ እንዲሁም ቴክኖሎጂን በአግባቡ በመጠቀም ተቋሙን የተሻለ ደረጃ ላይ ማድረስ ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡