HUHCSF ✞
رفتن به کانال در Telegram
Haramaya University, Harar Health Campus Christian Students Fellowship Worship Center: @ Me'erab Harar MKC Meet Leaders: @Gutewr
نمایش بیشتر291
مشترکین
+124 ساعت
+17 روز
+130 روز
آرشیو پست ها
291
ሰላም ለእናንተ ይሁን የተወደዳችሁ ቅዱሳን ✋
ዛሬ በተለመደው ሰኣታችን የህብረት/የትምህርት ግዜ ስለሚኖረን ሁላችንም #ማስታወሻ እና #መጽሓፍ ቅዱስ ይዘን እንምጣ ተባረኩ።👐
291
👋ሰላም የተወደዳችሁ እንደምን ቆያችሁ በሀረር የሺ እመቤት ት/ቤት ላሉ ተማሪዎች የደብተር እና እስክሪብቶ ድጋፍ እንድናደርግ ስለተጠየቅን የቻልነውን አንዳንድ እስክሪብቶ
ወንዶች ለ ታሪክ(psycha) እና ለቃል(pc2)
ሴቶች ለ ሀና(pc2) እና ገነት(psycha) እንድትሰጡ በጌታ ፍቅር እንጠይቅለን።
ሰኞ ስለሚሰጣቸው እስከ ቅዳሜ እንድንሰጥ እና ቅዳሜ ፌሎ ስንመጣ ይዘን እንድንመጣ።🙏❤️
2ኛ ቆሮንቶስ 9
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹¹ ሁል ጊዜ በልግስና መስጠት እንድትችሉ በሁሉ ነገር ያበለጽጋችኋል፤ ልግስናችሁም በእኛ በኩል የሚደርሳቸው ሰዎች እግዚአብሔርን ለማመስገን ምክንያት ይሆናቸዋል።
¹² ይህ የምትሰጡት አገልግሎት የቅዱሳንን ጒድለት የሚያሟላ ብቻ ሳይሆን፣ ብዙ ምስጋና ለእግዚአብሔር የሚቀርብበት ነው።
From Rehobot team
291
7ቱ እኔዎች በዮሀንስ ወንጌል
በመጋቢ ማቲ
ቀን ሁለት ክፍል 1፡ እግዚአብሔር ራሱን በብሉይ ያስተዋወቀበትን ስም ኢየሱስ ለምን መዋስ አስፈለገው?
291
ሰላም ለእናንተ የተወደዳችሁ
ባለፉት አራት ተከታታይ ሳምንታት ከመጋቢ ማቲ ጋር በቅዳሜ የጋራ የህብረት ጊዜ የተማርነውን "7ቱ እኔዎች በዮሀንስ ወንጌል" ተከታታይ ትምህርት የድምፅ ቅጅ በቴሌግራም በዚህ ሳምንት በየዕለቱ እናጋራለን። ቅጅውን በመከታተል ና በማዳመጥ እንጠቀም።
📖 መዝሙር 65፥4📖
“አንተ የመረጥኸው በአደባባዮችህም ለማደር የተቀበልኸው ምስጉን ነው፤ ከቤትህ በረከት እንጠግባለን።”
ለበረከት ሁኑ!
291
ሰላም ለእናንተ የተወደዳችሁ
ዛሬ ቅዳሜ በህብረታችን የሚሰበሰበው መባ ለወንድማችን ዘላለም ህክምና የሚውል በመሆኑ ሁላችንም ተዘጋጅተን እንድንመጣ ለማሳሰብ እንወዳለን።
📖 መዝሙር 65፥4📖
“አንተ የመረጥኸው በአደባባዮችህም ለማደር የተቀበልኸው ምስጉን ነው፤ ከቤትህ በረከት እንጠግባለን።”
ለበረከት ሁኑ!
291
# አስቸኳይ የእርዳታ ጥሪ ‼️
ገላትያ 6፡9-10
" ባንዝልም በጊዜው እናጭዳለንና መልካም ሥራን ለመሥራት አንታክት።
እንግዲያስ ጊዜ ካገኘን ዘንድ ለሰው ሁሉ ይልቁንም ለሃይማኖት ቤተ ሰዎች መልካም እናድርግ። "
የበሌ ሐዋሳ ከተማ ታዳጊ ወጣት ዘላለም ዘፍኔ የዩኒቨርስቲያችን ሁለተኛ ዓመት የጤና ተማሪ እንዲሁም የህብረታችን አባል ሲሆን ወደግቢ ለመመለስ በመንገድ ላይ እያለ ከአዳማ ወደ 20 ኪ/ሜ ርቀት በሚትገኝ ወላንጭት ተብሎ በሚጠራ አከባቢ ያልታሰበ የመኪና አደጋ ደርሶ በጭንቅላት ላይ ከፍተኛ ጉዳት በሕክምና ቋንቋ #Diagonosis = severe TBI + increcaed ICP + Aspiratio pneumonia በሪፈር አዳማ ስፔሻላይዝድ ሆሲፒታል ተኝቶ ይገኛል ።
ስለዚህም አስፈላጊውን ህክምና እንዲያገኝ ሁላችንም በልባችን ባሰብነው ልክ እንድንተባበር በጌታ ፍቅር እንጠይቃችኋለን። 🙏
የተረጋገጠ የባንክ አካውንት ስላስፈለገን ከይቅርታ ጋር ለጊዜው በዚህ የባንክ አካውንት 👉 #1000301395667 እንድንልክ ይሁን።
ለበረከት ሁኑ
291
ሰላም ይብዛላችሁ
ዓመታትን በቸርነቱ የሚያቀዳጅ ቅዱስ አምላካችን ስሙ የተመሰገነ ይሁን እያልን አዲስ ዓመትን አስመልክቶ በ FOCUS ህብረት ልዩ የበዓል ዋዜማ የህብረት ጊዜ ዛሬ ከ ምሽቱ 12:00-4:00 ተዘጋጅቷል። በስፍራው በመገኘት ፀጋ እንድንካፈል ተጋብዘናል።
ለበረከት ሁኑ 🙌
"አንተ የመረጥኸው በአደባባዮችህም ለማደር የተቀበልኸው ምስጉን ነው፤ ከቤትህ በረከት እንጠግባለን።"
📖📖መዝሙር 65፥4📖📖
291
ሰላም ለእናንት ይሁን
ከነገ ጳጉሜ 01 ጀምሮ እስከ መስከረም 01 ባሉት ተከታታይ ቀናት የጋራ የፃም ፀሎት ጊዜ በማለዳ ፀሎት አስተባባሪዎች ተዘጋጅቷል። በጋራ የምንፀልይበት ጊዜም በመደበኛው የማለዳ የፀሎት ጊዜ ከ12:30-1:30 ይሆናል ።
ሁላችንም በአንድነት በመምጣት እነዚህን ቀናት አብረን በፃም በእግዚአብሄር ፊት እንቅረብ።
291
የዛሬው የህብረት ጊዜያችን ይሄን ይመስል ነበር።
በኛ መካከል የተገኘው መንፈስ ቅዱስ ይባረክ🙏
ቀጣይ ሳምንት እስክንገናኝ ጌታ ከናንተ ጋር ይሁን🙌
291
ቡራኬ🙌
📖 ዘዳግም 32:3-4 📖
በጌታ በኢየሱስ ስም
በእግዚአብሔር ፍፁም ስራ እየተደነቃችሁ ስሙን የምታወድሱበት ጊዜ ይሁንላችሁ!
እግዚአብሔር በትክክለኛው መንገዱ ይምራችሁ!
በስራው የማይሳሳተውን ፃድቅ እርሱ እግዚአብሔርን የሚያረካ ህይወትን ይስጣችሁ !
ስለ ሁሉ የሚያስመካ የምትደገፉበትና የምጠሩት አለታችሁ እግዚአብሔር ይሁንላችሁ!
የእግዚአብሔርን ትክክለኝነት በድርጊቱም እንከን አልባነቱን እንዲሁም የእውነት ወጋኝነቱን ተራኪ ያድርጋችሁ!
በ ዕዝራ 9፥15 ተብሎ እንደተፃፈ
አግዚአብሔር ከነበደላችሁ ፊቱ በቀረባችሁበት ቀን እግዚአብሔር መመለሻን መንገድ ያሳያችሁ!
የእግዚአብሔር የፅድቅ ረሀብ ያረካው ኢየሱስ የህይወታችሁ ምሳሌ ይሁናችሁ !
መቅረብ በማይቻልበት በእግዚአብሔርና ህልውናውን ውስጥ ያከረማችሁ ኢየሱስን በሚያከብር የህይወት አቋም እግዚአብሔር ይግለጣችሁ!
ማንም መቆምም የሀጥያትንም ሀይል ማሸነፍ በራሱ አይችልምና እግዚአብሔር ግን በልጁ ወደ መንገዱ መመለስን ያድርግላችሁ!
እግዚአብሔር ወደ ራሱ የመመለስን ጉልበትና አቅም ይስጣችሁ !
በ መዝሙር 16፥11ተብሎ እንደተፃፈ
እግዚአብሔር የህይወትን መንገድ ያሳያችሁ !
የደስታችሁን ስፍራ እግዚአብሔር በፊቱ ውስጥ ይደብቅላችሁ!
በእግዚአብሔር ቀኝ ባለው መንገድ መመላለስ ይሁንላችሁ !
እግዚአብሔር በማይለዋወጠው የዘላለም ፍትሀዊነት አካሄዳችሁን ይቅረፀው!
እግዚአብሔር በምሕረትህ ብዛት በምድረ በዳ አይተዋችሁ!
በመንገድም ይመራችሁ ዘንድ የደመና ዓምድ በቀን፥ የምትሄዱበትንም መንገድ ያበራላችሁ ዘንድ የእሳት ዓምድ በሌሊት ከእናንተ አይራቅ!
ያስተምራችሁም ዘንድ መልካሙን መንፈሱን ይስጣችሁ!
እግዚአብሔር በምድረ በዳ ይመግባችሁ! ምንም አትጡም!
ተባረኩ!
🙌 አሜን 🙌
