fa
Feedback
Adventist information አድቬንቲስት መረጃ

Adventist information አድቬንቲስት መረጃ

رفتن به کانال در Telegram

ሰላም ለሁላችሁም! የዚህ ቻናል አላማው ለ7ተኛ ቀን አድቬንቲስት አባላት ብቻ ሳይሆን ለሁሉም ሰው የሚሆን መንፈሳዊ መልዕክቶችን ማካፈል። የ7ተኛ ቀን አድቬንቲስት አለም አቀፋዊ እና ሀገር አቀፋዊ መረጃዎችን እንዲሁም ሌሎች ጠቃሚ መረጃዎች ከታማኝ ምንጮች በማረጋገጥ ማድረስ ነው። የቻናሉ መቀላቀያ @AdventistEthio ለጥያቄ እና ለጥቆማ @metagesy 0923943365

نمایش بیشتر
2 001
مشترکین
+224 ساعت
+67 روز
+3630 روز
آرشیو پست ها
Repost from ጉርሻ Tube
ቅዳሜ ከሰዓት ሌላ ቀጠሮ እንዳይዙ! 261 የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች በሕፃናትና በታዳጊዎች አንደበት በቃል ሊቀርቡ፤ * ሐምሌ 18፣ ከ 8፡30 ጀምሮ * በወመዘክር ቅጥር ግቢ * በብላቴን ጌታ ኅሩይ ወ
ቅዳሜ ከሰዓት ሌላ ቀጠሮ እንዳይዙ! 261 የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች በሕፃናትና በታዳጊዎች አንደበት በቃል ሊቀርቡ፤ * ሐምሌ 18፣ ከ 8፡30 ጀምሮ * በወመዘክር ቅጥር ግቢ * በብላቴን ጌታ ኅሩይ ወ/ሥላሴ አዳራሽ ተቀጥሯል። በዕለቱም በጥንታዊ የብራና ጥቅልል ላይ በጥንቃቄ ከመከ'ተብ ጀምሮ አሁን በዘመናችን ስማርት ስልኮች ላይ በቀላሉ እስከመገኘት ድረስ መጽሐፍ ቅዱስ ያለፈበት የብዙ ዘመናት ታሪክ በረዳት ፕሮፌሰር መስፍን ማንደፍሮ አማካኝነት ትንታኔ ይሰጥበታል። መግቢያ በነጻ ነውና ኪስዎን አንድም ሳይዳብሱ ጊዜዎትን ብቻ አመቻችተው ከወዳጆችዎ ጋር በመምጣት ይህንን መልካም ይጠቀሙ! ©️ፍኖተ ብራና አገልግሎት ጉርሻ page 🌴🌴🌴 https://www.facebook.com/share/p/18xps9X3qA/?mibextid=wwXIfr

የአቃቂ አድቬንቲስት ት/ቤት በተለያየ የስራ መስክ ክፍት የስራ ቦታ አለው፡፡ መስፈርቱን የምታሟሉ የትምህርታ እና የስራ በማቅረብ መወዳደር የምትችሉ መሆን ለመግለፅ እንወዳለን፡፡ @AdventistEt
የአቃቂ አድቬንቲስት ት/ቤት በተለያየ የስራ መስክ ክፍት የስራ ቦታ አለው፡፡ መስፈርቱን የምታሟሉ የትምህርታ እና የስራ በማቅረብ መወዳደር የምትችሉ መሆን ለመግለፅ እንወዳለን፡፡ @AdventistEthio @metagesy

አንዳንዴ የተባረኩ ሰዎች ሲያገለግሉ ወይም ሲተጉ አብረን ብንገኝ መልካም ነው፡፡ ቅዳሜ ሀምሌ 18/2018ዓ.ም ከ ረ/ፕ መስፍን ማንደፍሮ ጋር ጥሩ ጊዜ ይኖራል፡፡ አትቅሩ፡፡ @AdventistEthio
አንዳንዴ የተባረኩ ሰዎች ሲያገለግሉ ወይም ሲተጉ አብረን ብንገኝ መልካም ነው፡፡ ቅዳሜ ሀምሌ 18/2018ዓ.ም ከ ረ/ፕ መስፍን ማንደፍሮ ጋር ጥሩ ጊዜ ይኖራል፡፡ አትቅሩ፡፡ @AdventistEthio @metagesy

📌 "ሰው ከቸርች ለመጥፋቱ ምክንያት አትኹኑ!" ሰዎች ወደ ቤተክርስቲያን የሚመጡት ጌታን ለመስማትና ለማምለክ ብቻ ሳይኾን፣ ቅዱስ ኅብረት ለማድረግም ጭምር መኾኑ የታወቀ ነው። ከሰው ልጆች መሠረታዊ ፍላጎቶች አንዱ "የእኔ" የሚሉትና "የእኛ" ተብለው የሚታቀፉበትን ማኅበረሰብ ማግኘት ነው። ለዚኽ መሠረታዊ ፍላጎት ደግሞ ቤተክርስቲያን አንዷና ዋነኛዋ መጠለያ ናት። ነገር ግን ሰው በዚኽ ንጹሕ ልብ ኾኖ ሲመጣ፣ ተመልሶ እንዲኼድና በቤተክርስቲያን እንዳይቆይ ምክንያት የሚኾኑ አሰናካይ ሰዎች ያጋጥሙታል። በኖኅ መርከብ ውስጥ እባብም እርግብም፣ ጅብም አህያም፣ ፍየልም ነብርም አብረው እንደነበሩት ኹሉ፤ በጌታ ቤትም (በቤተክርስቲያን) ውስጥ የዋሆች ብቻ ሳይኾኑ አሰናካዮችም አሉ። በዚህም ምክንያት ዐዳዲስ አማኞችና ወደ ቤተክርስቲያን የመጡ ምስኪን ሰዎች የእነዚኽ አሰናካዮች ሰለባ ይኾናሉ። አንዳንዶች ቸርች ሲቀይሩ፣ አንዳንዶች ግን ሙሉ በሙሉ ተስፋ ቆርጠው ወደ ቀደመ ሕይወታቸው ይመለሳሉ፤ ወይም የትም ሳይሄዱ በቤታቸው ይቀመጣሉ። ለመኾኑ ሰዎችን ከቤተክርስቲያን የሚያስወጡትና ማሰናከያ የሚኾኑት እነዚህ ሰዎች ምን ዓይነቶች ናቸው? ⚠️ ሰዎችን ከቸርች የሚያጠፉ 9 አሰናካይ ምክንያቶች፡- 1. ዘረኝነት (ወገንተኝነት)፦ ዘረኝነት ትልቁና ዋነኛው አሰናካይ ጉዳይ ነው። የአንድ አካባቢ ልጆች ወይም የአንድ ብሔር ሰዎች ብቻ ከፊት ኾነው መድረኩንና ቤቱን በበላይነት በያዙ ጊዜ ሌላውን ያገለላሉ። ይኼን ጊዜ ቤቱን የጌታ ቤት ሳይኾን የ"ሰው ቤት" ያደርጉታል፤ በዚህም ምክንያት መጤው ሰው በብሔሩ ምክንያት ወደ ማይገለልበት ስፍራ ለመሄድ ወይ ተሰናክሎ ለመቅረት ይገደዳል። 2. ሐሜተኞች፦ ሰው በተለያየ ድካምና ውጣ ውረድ ውስጥ ያልፋል። ከጀርባ ኾነው የሚያሾከሹኩ ሐሜተኞች ግን የዚያን ሰው ነጻነት ይነጥቃሉ። ይልቁንም ሰውየው ከወደቀበት ውድቀት ይልቅ በወሬና በሐሜት ሕይወቱን ስለሚያስመርሩት ከቸርች እንዲቀር ምክንያት ይኾናሉ። 3. አድመኞችና ምቀኞች፦ አድመኝነት ማለት የታሰበበት ዐመፅና ሴራ ማለት ነው። ይኽም ምዕመኑ በአገልጋዮች ላይ፣ ወይም አገልጋዮች እርስ በርስ በአገልጋዮች ላይ የሚሸርቡት ሊኾን ይችላል። ይኽ ስውር ደባ መገለጡ ስለማይቀር፣ ይኽንን ድራማ የሚያዩ ምስኪን ምዕመናንና ጌታን የሚፈሩ አገልጋዮች ሳይቀሩ ተሰናክለው ከቸርች ይቀራሉ። 4. ዝሙት (የግብረገብነት መበላሸት)፦ ልክ እንደ ዔሊ ልጆች ያሉ አገልጋዮች ዛሬም አሉ። ለጸሎትና ለትምህርት የሚመጡ እኅቶችን የሚያሰናክሉ፣ ለብዙዎች ልብ ስብራትና ለእምነት መርከስ ምክንያት የኾኑ ወንድሞችና እኅቶች በቤቱ ውስጥ መኖራቸው ሰዎችን ያሰናክላል። 5. አጭበርባሪዎችና ስግብግቦች፦ ገንዘብን የሚወዱና ያገኙትን አጋጣሚ ኹሉ ለዚኽ ከንቱ ምድራዊ ረብ የሚጠቀሙ ሰዎች አሉ። በቸርች ውስጥ እንዲኽ ዓይነት ሰው ይኖራል ብለው የማይጠረጥሩ የዋህ ክርስቲያኖች በቀላሉ ይታለላሉ፤ በዚኽም ማጭበርበር ምክንያት ተስፋ ቆርጠው ከቸርች ይቀራሉ። 6. ልዩነትን አለማስተናገድ፦ በአለባበስ፣ በባሕል፣ ወይም በተለያዩ ማኅበራዊ ዳራዎች (Background) ምክንያት ሰዎችን ማግለልና "እኛን አይመስሉም" በሚል መንፈስ ማራቅ ሰዎችን ገፍቶ ያስወጣል። 7. የስልጣንና የጥቅም ሽኩቻ፦ በቤተክርስቲያን መሪዎች ወይም አገልጋዮች መካከል የሚፈጠሩ የአስተዳደር ግጭቶች፣ የገንዘብ አያያዝ ጉድለቶችና የስልጣን ፉክክሮች የምዕመናንን እምነት ሙሉ በሙሉ ያጠፋሉ። 8. በሰዎች ውጫዊ ገጽታ ላይ ማተኮር (ፈራጅነት)፦ ሰዎችን በውጫዊ ማንነታቸው፣ በአለባበሳቸው ወይም ካለፉበት የሕይወት ታሪክ (ለምሳሌ ሱሰኝነት ወይም ደካማ ታሪክ) በመነሣት የመኮነንና የማግለል ዝንባሌ ሲኖር፤ ግለሰቦች እረፍት ፍለጋ የመጡበት ቦታ "የፍርድ ወንበር" ኾኖ ስለሚያገኙት ይርቃሉ። 9. የዶክትሪን ወይም የስርዓት ግጭቶች፦ በአንዳንድ መሰረታዊ ባልኾኑ፣ ለድነት ወሳኝ ባልኾኑ ስነ-መለኮታዊ አመለካከቶችና ሥርዓቶች ላይ የሚደረጉ መከፋፈሎችና አላስፈላጊ ክርክሮች ሰዎችን ያሰልቻሉ፣ ያርቃሉም። 📌 ማጠቃለያ በእነዚኽ ኹሉ ሰዎችና አስከፊ ምክንያቶች የተነሣ ብዙዎች ከቸርች ይቀራሉ። ከዚኽ ሲከፋ ደግሞ ከራሱ ከጌታም ይርቃሉ። ስለኾነም፣ እንደዚኽ ባሉ ክፋቶችና ዐመፆች ተካፋይ ባለመኾን፣ በእኛም ስውርም ኾነ ግልጽ ጠባይ ምክንያት ማንም እንዳይሰናከል እያንዳንዳችን ልንጠነቀቅ ይገባል። ​ቤተክርስቲያን ለማንም ሰው ክፍት የኾነች የፍቅርና የደኅንነት ማዕከል እንጂ፣ ፍጹማን ነን ባዮች ብቻ የሚደሰቱባት የተመረጡ ሰዎች ክበብ መኾን የለባትም!" ጌታ በነገር ኹሉ ማስተዋልን ይስጠን። አሜን። © ከማህበራዊ ሚዲያ ላይ ካነበብኩት

ትክክለኛ ውሳኔ፡፡ የምዕራብ ኬንያ ዩኒየን በቅዳሜ( በሰንበት አምልኮ ሰዓት) ምንም አይነት የገንዘብ ማሰባሰብ ስራ እንዳይከናወን አዘዘ፡፡ ምን ትላላችሁ፡፡ AdventistEthio @metagesy
ትክክለኛ ውሳኔ፡፡ የምዕራብ ኬንያ ዩኒየን በቅዳሜ( በሰንበት አምልኮ ሰዓት) ምንም አይነት የገንዘብ ማሰባሰብ ስራ እንዳይከናወን አዘዘ፡፡ ምን ትላላችሁ፡፡ AdventistEthio @metagesy

መልካም ሰንበት! "..ልጆች የእግዚአብሔር ስጦታ ናቸው..."።መዝሙር 127፡3 አዲሶቹን የHope Channel Ethiopia የዩቲዩብ ቻናሎች subscribe, share, Like ማድረግ አይርሱ! እ
መልካም ሰንበት! "..ልጆች የእግዚአብሔር ስጦታ ናቸው..."።መዝሙር 127፡3 አዲሶቹን የHope Channel Ethiopia የዩቲዩብ ቻናሎች subscribe, share, Like ማድረግ አይርሱ! እናመሰግናለን!

📌መልካም ዜና!📌 ለ2018 ዓ.ም. የአድቬንቲስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራቂዎች በሙሉ! SEAL (Society of Ethiopian Adventist Lay-members) ለአራተኛ ጊዜ ባዘጋጀው
📌መልካም ዜና!📌 ለ2018 ዓ.ም. የአድቬንቲስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራቂዎች በሙሉ! SEAL (Society of Ethiopian Adventist Lay-members) ለአራተኛ ጊዜ ባዘጋጀው ዓመታዊ የምርቃት መሰናዶ ላይ እንዲገኙ በአክብሮት አድመንዎታል:: ቦታ:- አቃቂ አድቬንቲስት ቤ/ክርስቲያን (ት/ቤት ግቢ ውስጥ) ቀን:- ሰኔ 27/2018 ዓ.ም.  (July/04/2026) ሰዓት፦ ሙሉ ቀን ከጠዋት 2፡30 ጀምሮ  📌ውድ ተመራቂያን 300 ብር ብቻ የመመዝገቢያ በመክፈል ድምቅ ባለ የምርቃት ሥነ-ስርዓት ጌታን ለማመስገን ባዘጋጀነው ድግስ ላይ ለመሳተፍ አሁኑኑ ይመዝገቡ::  📌ምዝገባው ተጀምሯል እስከ ሰኔ 20 ይቆያል::  📌ለምዝገባ የተዘጋጀውን የGoogle Form በመሙላት ስትመዘገቡ ላላችሁ የትኛውም ጥያቄ የሚከተሉትን ስልኮች ተጠቀሙ።  መታገስ የኔነህ:- +251923943365 ኤባ ደከቦ:- +251948154603 ዶ/ር ዳዊት ካሳ +251 91 343 7865 👇🏼 ለምዝገባ የተዘጋጀውን የGoogle Form በመጫን ይመዝገቡ  https://forms.gle/MhueadFSDXjXUh1o8 ማሳሰቢያ‼️ ላልተመዘገበ ቦታ አይኖረንም፡፡

የማይቀርበት የአምልኮ ቀን ስለዚህ ምክንያት በሰማይና በምድር ያለ አባትነት ሁሉ ከሚሰየምበት ከአብ ፊት እንበረከካለሁ ኤፌሶን 3:15 በቃሊቲ 7ኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተ-ክርስቲያን ግንቦት 15,201
የማይቀርበት የአምልኮ ቀን ስለዚህ ምክንያት በሰማይና በምድር ያለ አባትነት ሁሉ ከሚሰየምበት ከአብ ፊት እንበረከካለሁ ኤፌሶን 3:15 በቃሊቲ 7ኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተ-ክርስቲያን ግንቦት 15,2018 ኑ የተለየ የአምልኮ ጊዜ አብረን እናሳልፍ፡፡ 🧎‍♂‍➡️ ፀሎት 🎤 ዝማሬ 📖 የእግዚአብሔር ቃል ( ስብከት ) https://t.me/AdventistEthio @metagesy

በሁላችንም ዘንድ እጅግ የተወደደው ወንድማችን ፋሲካው አዲስ የመዝሙር አልበም አስመርቋል። ሊንኩን በመጫን ሙሉ አልበሙን መስማት ትችላላችሁ። ሁላችንም ቻናሉን በመቀላቀል፣ ላይክ በማድረግና ለሌሎች በማጋራት መንፈሳዊ ግዴታችንን እንወጣ!!! Blessings!!!

ድልን ሰጠው "እግዚአብሔርም ዳዊትን በሄደበት ሁሉ ድልን ሰጠው።" (2 ሳሙኤል 8፥6) ዳዊት ጎበዝ ተዋጊና መሪ ቢሆንም፣ የድሉ ባለቤት ግን እግዚአብሔር እንደሆነ ያውቅ ነበር። በሕይወታችን ውስጥ የምናገኛቸው ስኬቶች፣ የምናልፋቸው ፈተናዎችና የምናገኛቸው ድሎች ሁሉ የራሳችን ጥረት ውጤቶች ብቻ አይደሉም፤ ከእግዚአብሔር የተሰጡ የጸጋ ስጦታዎች ናቸው። እግዚአብሔር ዳዊትን ያሸነፈው በአንድ የተወሰነ ስፍራ ወይም በአንድ ውጊያ ላይ ብቻ አልነበረም፤ "በሄደበት ሁሉ" እንጂ። ይህ የሚያሳየው የእግዚአብሔር አብሮነት ወሰን የሌለው መሆኑን ነው። እኛም በሕይወት ጉዟችን በትምህርት፣ በሥራ፣ በቤተሰብ ኑሮ ወይም በአገልግሎት በምንሰማራበት በማንኛውም መስክ እግዚአብሔርን ስናስቀድም፣ እርሱ በሄድንበት አቅጣጫ ሁሉ መንገዳችንን ያቀናልናል፤ በነገሮቻችንም ላይ ድልን ያጎናጽፈናል። ዳዊት ድልን ያገኘው ዝም ብሎ ተቀምጦ ሳይሆን "በሄደበት" ማለትም በሠራበት፣ በተንቀሳቀሰበትና በታገሉበት የሕይወት ውጣ ውረድ ውስጥ ነው። እግዚአብሔር ሰነፎችን ሳይሆን የሚተጉትንና በእምነት የሚራመዱትን ይባርካል። እኛ የበኩላችንን እምነትና ጥረት ይዘን ስንነሳ፣ እግዚአብሔር ደግሞ መለኮታዊ ኃይሉን በመጨመር ጉድለታችንን ይሞላል፤ ፍጻሜያችንንም በድል ያደርገዋል። ጌታ ሆይ!  ለእኔና ይሄን ለሚሰሙትን ሁሉ የሕይወታችን ድልና ስኬት አንተ ብቻ ነህ። በዕለት ተዕለት ውሎአችን፣ በሥራችንና በምንሄድበት መንገድ ሁሉ በአብሮነትህ ድልን እንድትሰጠን እጸልያለሁ። 🙏🙏 @Adventist Ethio @metagesy

የአዲስ አበባ ዞን መዘምራን ህብረት በሌስፔራንስ 7ኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተ-ክርስቲያን ከግንቦት 7-8/2018ዓ.ም የምትችሉ ሁሉ ኑ የበረከቱ ተካፋይ ሁኑ፡፡ በህብረት እግዚአብሔርን እናምልክ @Adv
የአዲስ አበባ ዞን መዘምራን ህብረት በሌስፔራንስ 7ኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተ-ክርስቲያን ከግንቦት 7-8/2018ዓ.ም የምትችሉ ሁሉ ኑ የበረከቱ ተካፋይ ሁኑ፡፡ በህብረት እግዚአብሔርን እናምልክ @AdventistEthio @metagesy

🔹ግንቦት 4/2018 በያሬድ ሙዚቃ ት/ቤት በተደረገው የመዝሙር ድግስ በርካታዎች እጅግ ተደንቀዋል   🔹ከተሰጡት አስተያየቶች ጥቂቶቹ፤ “መዝሙር እንደዚህ ሲዘመር ሰምቼ አላውቅም” “በብዙ ድካምና ልፋት የተዘጋጀ እንደሆነ ያስታውቃል” የሚሉት ጥቂቶቹ ናቸው   🔹የፍኖተ ብራና ቡድንም የተለያዩ መጽሐፍትን በቀላሉ ለታዳሚው ማድረስ ችሏል 🔹ሁሉም መጽሐፍቱን የተቀበሉ በታላቅ ደስታና ምስጋና ነበር   🔹“ባለፈው ፋሲካ የሰጣችሁኝ የክርስቶስ ምሳሌያዊ ትምህርቶች መጽሐፍ እጅግ ጠቅሞኛል፣ ብዙ ተምሬበታለሁ፤ አሁንም እያነበቡት ነው” ያለ ታዳሚም ነበር   🔹“ቤተክርስቲያን ፕሮግራም አለ ተብለው ቢጠሩ የማይመጡ ዓይነት ሰዎችን ለመድረስ” የተቻለበት የተዋጣለት ዝግጅት ግሩም ነበር   🔹ፕሮግራሙ እንደሚገባው በቤተ ክርስቲያኗ አለመተዋወቁ እርምት እንዲወሰድበት አስተያየት ተሰጥቷል   🔹የመዘምራን ቡድኑ ቀጣይ ፕሮግራሞችን በሌሎችቦታዎችም ያቀርባል   🙏🏽ስብሐት ለአምላካችን ይሁን!🙏🏽   ተጨማሪ መረጃና ድንቅ ፎቶዎች እዚህ ላይ ይገኛል   https://livingparchment.org/choral-performance-and-book-distribution-at-yared-music-school/ ————————— YouTube | Telegram | Facebook | Instagram

ትንታግ ትውልድ የወጣቶች የህብረት ቀን በ CMC አድቬንቲስት ቤተ-ክርስቲያን ግንቦት 19 @AdventistEthio @metagesy
ትንታግ ትውልድ የወጣቶች የህብረት ቀን በ CMC አድቬንቲስት ቤተ-ክርስቲያን ግንቦት 19 @AdventistEthio @metagesy

📌መልካም ዜና!📌 ለ2018 ዓ.ም. የአድቬንቲስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራቂዎች በሙሉ! SEAL (Society of Ethiopian Adventist Lay-members) ለአራተኛ ጊዜ ባዘጋጀው ዓመታዊ የምርቃት መሰናዶ ላይ እንዲገኙ በአክብሮት አድመንዎታል:: ቦታ:- አቃቂ አድቬንቲስት ቤ/ክርስቲያን (ት/ቤት ግቢ ውስጥ) ቀን:- ሰኔ 27/2018 ዓ.ም.  (July/04/2026) ሰዓት፦ ሙሉ ቀን ከጠዋት 2፡30 ጀምሮ  📌ውድ ተመራቂያን 300 ብር ብቻ የመመዝገቢያ በመክፈል ድምቅ ባለ የምርቃት ሥነ-ስርዓት ጌታን ለማመስገን ባዘጋጀነው ድግስ ላይ ለመሳተፍ አሁኑኑ ይመዝገቡ::  📌ምዝገባው ተጀምሯል እስከ ሰኔ 20 ይቆያል::  📌ለምዝገባ የተዘጋጀውን የGoogle Form በመሙላት ስትመዘገቡ ላላችሁ የትኛውም ጥያቄ የሚከተሉትን ስልኮች ተጠቀሙ።  መታገስ የኔነህ:- +251923943365 ኤባ ደከቦ:- +251948154603 ዶ/ር ዳዊት ካሳ +251 91 343 7865 👇🏼 ለምዝገባ የተዘጋጀውን የGoogle Form በመጫን ይመዝገቡ  https://forms.gle/MhueadFSDXjXUh1o8 ማሳሰቢያ‼️ ላልተመዘገበ ቦታ አይኖረንም፡፡

📌መልካም ዜና📌 ለ2018 ዓ.ም. የአድቬንቲስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራቂዎች በሙሉ! SEAL (Society of Ethiopian Adventist Lay-members) ለአራተኛ ጊዜ ባዘጋጀው ዓመታዊ የምርቃት መሰናዶ ላይ እንዲገኙ በአክብሮት አድመንዎታል:: ቦታ:- አቃቂ አድቬንቲስት ቤ/ክርስቲያን (ት/ቤት ግቢ ውስጥ) ቀን:- ሰኔ 27/2018 ዓ.ም.  (July/04/2026) ሰዓት፦ ሙሉ ቀን ከጠዋት 2፡30 ጀምሮ  📌ውድ ተመራቂያን 300 ብር ብቻ የመመዝገቢያ በመክፈል ድምቅ ባለ የምርቃት ሥነ-ስርዓት ጌታን ለማመስገን ባዘጋጀነው ድግስ ላይ ለመሳተፍ አሁኑኑ ይመዝገቡ::  📌ምዝገባው ተጀምሯል እስከ ሰኔ 20 ይቆያል::  📌ለምዝገባ የተዘጋጀውን የGoogle Form በመሙላት ስትመዘገቡ ላላችሁ የትኛውም ጥያቄ የሚከተሉትን ስልኮች ተጠቀሙ።  መታገስ የኔነህ:- +251923943365 ኤባ ደከቦ:- +251948154603 ዶ/ር ዳዊት ካሳ +251 91 343 7865 👇🏼 ለምዝገባ የተዘጋጀውን የGoogle Form በመጫን ይመዝገቡ  https://forms.gle/MhueadFSDXjXUh1o8 ማሳሰቢያ‼️ ላልተመዘገበ ቦታ አይኖረንም፡፡

በእግዚአብሔር ደስ ይበልህ፤ የልብህንም መሻት ይሰጥሃል። መንገድህን ለእግዚአብሔር ዐደራ ስጥ፤ በእርሱ ታመን፤ እርሱም ያከናውንልሃል፤ ጽድቅህን እንደ ብርሃን፣ ያንተን ፍትሕ እንደ ቀትር ፀሓይ ያበራዋል። በእግዚአብሔር ፊት ጸጥ በል፤ በትዕግሥትም ተጠባበቀው፤ መንገዱ በተቃናለት፣ ክፋትንም በሚሸርብ ሰው ልብህ አይሸበር። ከንዴት ተቈጠብ፤ ቍጣንም ተወው፤ ወደ እኵይ ተግባር እንዳይመራህ አትከፋ። ክፉ ሰዎች ይጠፋሉና፤ እግዚአብሔርን ተስፋ የሚያደርጉ ግን ምድርን ይወርሳሉ። ለአፍታ እንጂ፣ ክፉ ሰው አይዘልቅም፤ ስፍራውንም ብታስስ አታገኘውም። ገሮች ግን ምድርን ይወርሳሉ፤ በታላቅ ሰላምም ሐሤት ያደርጋሉ። ክፉዎች በጻድቃን ላይ ያሤራሉ፤ ጥርሳቸውንም ያፋጩባቸዋል። እግዚአብሔር ግን ይሥቅባቸዋል፤ቀናቸው እንደ ደረሰ ያውቃልና። መዝ 37:4-13 መልካም ሰንበት happy sabbath @AdventistEthio @metagesy