fa
Feedback
GLOW KG AND PRIMARY SCHOOL ADDIS ABABA ETHIOPIA.

GLOW KG AND PRIMARY SCHOOL ADDIS ABABA ETHIOPIA.

رفتن به کانال در Telegram

Always strive for Excellence❤!!

نمایش بیشتر
1 431
مشترکین
+824 ساعت
+127 روز
+730 روز
آرشیو پست ها
ቀን 1/7/2015 ዓ.ም ማስታወቂያ! በ2015 የትምህርት ዘመን 6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ እና ሀገራቀፍ ፈተና ተፈታኝ ለሆናችሁ ተማሪዎች በሙሉ ቀደም ሲል በቀጥታ / ኦላይን መመዝገባችሁ ይታ
ቀን 1/7/2015 ዓ.ም ማስታወቂያ! በ2015 የትምህርት ዘመን 6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ እና ሀገራቀፍ ፈተና ተፈታኝ ለሆናችሁ ተማሪዎች በሙሉ ቀደም ሲል በቀጥታ / ኦላይን መመዝገባችሁ ይታወቃል፡፡ ከዚህ ጋርም በተያያዘ የተመዘገባችሁበትን መረጃ ትክክለኛነት ለማረጋገጥ እንዲቻል ለ6ኛ ክፍል https://aa6.ministry.et እና ለ8ኛ ክፍል https://aa.ministry.et ሊንኮችን በመጫን View Result የሚለውን በመጫን የመለያ ቁጥራችሁን እና ስም / Registration Number and First Name በማስገባት ማየት የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ስህተት ካለበት ለትምህርት ቤታችሁ በስቸኳይ እንድታሳውቁ እናሳስባለን፡፡ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ! Blog: - https://aacaebc.blogspot.com You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ... TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/

ውድ የትምህርት ቤታችን የተማሪ ወላጆች በሙሉ የቦረናን ድርቅ ምክንያት በማድረግ ካለን ላይ ቀንሰን እንደከዚህ በፊቱ ለቦረና ህዝብ የሚሆን መኮሪኒ፣ ፓስታ ወይም ሩዝ በልጆት እንዲልኩልን በትህትና እንጠይቃለን :: 👏 ስለሚደረጉት በጎነትና ትብብር ሁሉ በግሎው ትምህርት ቤት አስተዳደር ስም ከፍ ያለ ምስጋናችንን በቅድሚያ እናቀርባለን!! ት/ቤቱ

በደቡብ ኢትዮጵያ በተለያዩ አከባቢዎች በተለይም በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን እና ሶማሌ ክልል ደቡባዊ ክፍሎች የከፋው ድርቅ አሁንም መቋጫ አላገኘም፡፡ በነዚህ አከባቢዎች በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አርብቶ አደሮች ለድጋፍ እጃቸውን ያዘረጋው ድርቁ በሚሊየኖች የሚቆጠሩ የቀንድ እና የጋማ ከብቶችንም ጭምር ገድሏል አስከፊነቱም ቀጥሏል፡፡ በተለይም በቦረና በርካታ ከብቶችን በማርባት ለሌሎች ይተርፉ የነበሩት አርብቶ አደሮች አሁን ለድጋፍ ፍለጋ እጃቸውን ሰጥተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሜትሮሎጂ እንደሚለው ግን ለአምስት ተከታታይ የዝናብ ወቅቶች በድርቅ የቀጠሉት የደቡብ ኢትዮጵያ አከባቢዎች እየመጣ ባለው የዘንድሮ የበልግ ወቅት ለመደበኛ የቀረበ ዝናብ በማግኘት ድርቁ መቋጫ ሊያገኝ ይችላል፡፡

ነገ ሐሙስ የካቲት 23/2015 ዓ.ም በሚከበረው 127ኛው የዓደዋ ድል በዓል ምክንያት ት/ት የማይኖር መሆኑን እየገለፅን ግሎው ት/ቤት መልካም የድል በዓል ለሁሉም ኢትዮጲያዊ ይመኛል !!! ማሳሰቢያ ፦ ዓርብ የካቲት 24/2015 ዓ.ም መደበኛው የሙሉ ቀን ት/ት የሚቀጥል መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

grade 8 sb.pdf4.55 MB

grade 7 sb.pdf4.54 MB

+5
grade 1 sb.pdf16.85 MB

Amharic grade 1-8 student book

+1
Performing and visual art Grade 7 student text book.pdf5.50 MB

+1
CTE Grade 7 TextBook.pdf7.36 MB

IT Grade 8 Student's Textbook.pdf10.46 MB

IT Grade-7-Student Text-Last Edition-Confirmed writers 2 (1).pdf9.81 MB

#ለሁሉም የት/ቤታችን ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች #እንደሚታወቀው ሰኞ የካቲት 06/2015 ዓ.ም የሦስተኛው  ሩብ አመት /ሁለተኛው ሴሚስተር/ ትምሀርት ይጀምራል። #ስለሆነም ውድ ወላጆች፦ 1. ትምህህርት ሙሉቀን ይሰጣል። ጥናት ለሚያጠኑ ተማሪዎች ጥናት አለ። 2. ተማሪዎች በፕሮግራም መሰረት ደብተር እና የሚያስፈልጉ የመማሪያ ቁሳቁሶችን ማምጣት/መያዝ/ አለባቸው። 3. ተማሪዎች  ወደ ትምህርት ቤት ሲመጡ ሴቶች ፀጉራቸውን ተሰርተው/ወደ ኋላ አስይዘው/ ፣ወንዶች በአጭሩ ተቆርጠው/ተስተካክለው/፣ ጥፍራቸውን ተቆርጠው፣ ንፁህ የሆነ የት/ቤቱን የደንብ ልብስ/Uniform/ ለብሰው በተለመደው ወደ ግቢ መግቢያ ስዓት ሳያረፍዱ መምጣት ይኖርባቸዋል። 4. ተማሪዎች ለ2 ሳምንት ያክል ከትምህርት ጋር ተለያይተው በመቆየታቸው ወላጆች ልጆችን ለትምህርት ዝግጁ እንዲሆኑ እና ለቀጣይ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ እንዳለባቸው በመምከር የማነቃቃት ስራ መስራት ይጠበቅባችኋል። 5. ወላጆች ልጆቻችሁን የት/ቤቱን ህግና ደንብ ማክበር እንዳለባቸው፣ ታዛዥና በስነ-ምግባር የተመሰገኑ መሆን እንዳለባቸው ፣ መምህራን የሚሰጧቸውን ምክርና ትምህርት በአግባቡ መቀበል እንዳለባቸው፣ የሚሰጣቸውን ስራ በአግባቡ መስራት እንዳለባቸው መምከር ከሁሉም ወላጅ/ህጋዊ አሳዳጊ/የሚጠበቅ ነው። 6. በመጨረሻም ተማሪዎች የእጅ ፅሁፋቸውን፣ የማንበብና የንግግር ክህሎታቸውን ማዳበር እንዳለባቸው በመምከር እንዲሁም አመርቂ ውጤት እንዲያስመዘግቡ በማበረታታት ወደ ትምህርት ገበታቸው በአዲስ መንፈስና በሞራል እንዲመለሱ በማድረግ የበኩላችሁን የወላጅ ሀላፊነት እንድትወጡ ሲል ት/ቤቱ ያሳስባል። #ማሳሰቢያ፦ ትምህርት ተጀምሮ ለቀረ ተማሪ ማንኛውም ለሚያልፈው/ለሚያመልጠው/ ነገር ሁሉ ት/ቤቱ ሀላፊነት የማይወስድ መሆኑን ቀድመን ለማሳወቅ እንወዳለን።                                  ት/ቤቱ

FIRST SEMESTER EXAM SCHEDULE
FIRST SEMESTER EXAM SCHEDULE