cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

️🌙ኢስላም የሰላም መንገድ🌙️

🕌🕌🕌🕌🕌🕌🕌🕌🕌🕌 ወደ አላህ ከጠራና መልካምን ከሰራ <<እኔ ከሙስሊሞች ነኝ>> ካለም ሰው ይበልጥ ቃሉ ያማረ ማነው? አል–ፉሲለት ምዕ41:33 t.me/MuslimNegnEneSul t.me/MuslimNegnEneSul 🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟 🕌🕌🕌🕌🕌🕌🕌🕌🕌🕌

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
315
مشترکین
+124 ساعت
-17 روز
-330 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

ለመኖር አዲስ ቀን በተሠጠኝ ቁጥር ከራሴ ተስፋ የቆረጥኩበት ሁኔታ ዳግም ይለመልማል። ከትናንት ወዲያ አጠፋሁ ብዬ ዕድሜ ልኬን ስቆዝም አልኖርም ። ትናንት ወደቅኩ ብዬ ዘላለሜን ስተክዝ አልገኝም። አቧራዬን አራግፌ ጭቃዬኔ ተጣጥቤ እስቲ ልነሳና ዛሬን ልየው ደግሞ። አልሐምዱ ሊላህ ዐላ ኩሊ ሓል። የእስትንፋሴ ጌታ አላህ ሆይ አጠንክረኝ። ሶባሐል ኸይር ወዳጆቼ ! https://t.me/MuhammedSeidAbx
نمایش همه...
ቁርአን ውስጥ የተጠቀሱ 7 ከንቱ ምኞቶች‼ ============================= ①) «ዋ ምኞቴ! ምነው አፈር በሆንኩ!» [አ-ን'ነበእ: 40] ②) «ዋ እኔ! ምነው በሕይወቴ (መልካምን ሥራ) ባስቀደምኩ ኖሮ!» [አል-ፈጅር: 24] ③) «ዋ ጥፋቴ! ምነው መጽሐፌን ባልተሰጠሁ!» [አል-ሐቀህ: 25] ④) «ዋ ጥፋቴ! እገሌን ወዳጅ አድርጌ ባልያዝኩ ኖሮ እመኛለሁ!» [አል-ፉርቃን: 28] ⑤) «ዋ ምኞታችን! አላህን በተገዛን፤ መልክተኛውንም በታዘዝን ኖሮ!» [አል-አሕዛብ: 66] ⑥) «ዋ ምኞቴ! ከመልክተኛው ጋር ቀጥተኛን መንገድ ይዤ በሆነ!» [አል-ፉርቃን: 27] ⑦) «ወይ ምኞቴ! ታላቅ ዕድልን አገኝ ዘንድ ከነሱ ጋር በሆንኩ!» [አ-ን'ኒሳእ: 73] ሁሉም የሟቾች ምኞቶ ናቸው። ቀብር ውስጥ ያሉት ሰዎች ምኞታቸው ወደ ዱንያ አንዴ መጥተው ለአኺራቸው ጥሩን ነገር መስራት ነው። ግን ምን ዋጋ አለው! አልፏል ተቀድሟል! ቀብር ገብተህ አንተም ይህን ከምትመኝ ነፍስህ አካልህ ውስጥ እስካለች ድረስ ለአኺራህ አስቀድም።  ብልህ የሆነ ሰው ከመጸጸቱ በፊት ሥራውን ይሥራ አላህ ሆይ! ከነዚህ ከንቱ ምኞቶች በእዝነትህ ጠብቀን።
نمایش همه...
አሥ ሠላሙ ዐለይኩም ወራሕመቱላሂ ወበረካቱሁ ያ ጀመዓህ! "የተደበቀው እውነት" የሚለው ስድስተኛው መጽሐፌ በገበያ ላይ ውሏል። "የተደበቀው እውነት" የሚያውጠነጥነው ስለ ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" መምጣት በተውራት እና በኢንጂል ተነግሮ የመጽሐፉ ሰዎች ይህንን እውነት እንዴት እንደደበቁት የሚገልጥ እና የሚያጋልጥ ነው። ዝርዝሩን መጽሐፉ ላይ ያንብቡ እና ለሎች የሂዳያህ ሠበብ እንዲሆን አስነብቡ! መጽሐፉን መርካርቶ አንዋር መሥጂድ ኢሥላማዊ መጻሕፍት መደብር ውስጥ ያገኙታል፥ የበለጠ ለመረጃ +251920781016 ዐብዱ ብለው ይደውሉ! መጽሐፉ ተደራሽነት እንዲኖረው ባለው የማኅበራዊ መገናኛ ብዙኃን ሼር በማድረግ ሠበቡል ሂዳያህ ይሁኑ! ወጀዛኩሙላህ ኸይራ! ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom
نمایش همه...
እሷ ያን ሁሉ መስመር ጽፋልህ አንተ "እሺ" ብቻ ብለህ የምትመልስ ከሆነ ቀጥሎ የሚመጣዉን ጦርነት ጠብቅ። ምን እንደሚያናድደኝ ታውቃላችሁ ? ብዙዎቻችሁ ከሴት ልጅ ጋር እንዴት መኖር እንዳለባችሁ አታውቁም ። ትን ይበልህ አቦ https://t.me/MuhammedSeidAbx
نمایش همه...
ABX

ወደ ቤታችሁ እንኳን መጣችሁ!!

ሁሉም ቢሞላለት ደስ ይለዋል፣ ሁሉም ሀብታም መሆን ይፈልጋል፣ ሁሉም መዝናናት ይፈልጋል፤ ሁሉም ገንዘብ ማግኘት ይፈልጋል፣ ሁሉም ጥሩ ኑሮ መኖር ይፈልጋል፣ ሁሉም ሰኞ በደስታ ማሳለፍ ይፈልጋል፡፡ ይህ ሀሳብ ያንተ ብቻ አይደለም፡፡  ስለዚህ ብቻህን አይደለህም አትፍራ ለማለት ነው እሺ፡፡ መልካም ዉሎ ሶባሐል ኸይር! https://t.me/MuhammedSeidAbx
نمایش همه...
እንደ ቅሬታ ማቅረብ Complain ማብዛት ዝምድናን የሚበጥስ፣ ጓደኝነትን የሚሸረሽር፣ ወዳጅነትን የሚያደበዝዝ ... ነገር ይኖር ይሆን! በተለይ ሰው ከኑሮው እና ከሐጃው እየታገለ፣ ሕይወት ነፍስ ዉጪ ነፍስ ግቢ በሆነችበት በዚህ የትንቅንቅ ዘመን፡፡  አልደወልክልኝም፣ አልጠየቅከኝም፣ ምን ደረስክ አላለልከኝም …  እያሉ ነገር ማጋነን። ዛሬ ላይ ሰው ብዙ ነገር ጭንቅላቱን ይዞታል፡፡  ዛሬዉኑ ወደፊቱ፣ ኢማኑ፣ ሥራው፣ ኑሮው፣ ቤተሰቡ፣ ልጆቹ፣ አኺራው … ዛሬ ላይ ሰዎች የራሣቸው ችግርና አጀንዳ ራሱ በቂ ነው፡፡ ተጨማሪ ሀሳብና ሸክም አትሁኑባቸው፡፡ ወቀሳ አታብዙባቸው፣ ጥፋት አትቁጠሩባቸው፣ ምክንያት ፈልጉላቸው፣ ከሀሳብና ጭንቀት ነፃ ሆነው ይኖሩ ዘንድ ምክንያት ሁኗቸው፡፡ ሶባሐል ኸይር! https://t.me/MuhammedSeidAbx
نمایش همه...
መልካም ስራህ ብቻውን በቂ አይደለም… ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿لَا يُدْخِلُ أَحَدًا مِنْكُمْ عَمَلُهُ الْجَنَّةَ، وَلَا يُجِيرُهُ مِنَ النَّارِ، وَلَا أَنَا، إِلَّا بِرَحْمَةٍ مِنَ اللَّهِ﴾ “ከናንተ አንዳችሁ በመልካም ስራው ብቻ ጀነት አይገባም፤ ከእሳትም አይጠበቅም። እኔም ብሆን። በአላህ ራህመት (እዝነት) ቢሆን እንጂ።” 📚 ሙስሊም ዘግበውታል 2817
نمایش همه...
አስቂኝ ክስተት ፈገግ በሉበት‼️ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ✍የመን ውስጥ ዘማር የተባለ ቦታ ላይ አንድ መስጂድ ውስጥ የተከሰተ በጣም አስቂኝ ክስተት ነው አንብበው ሳይጨርሱ በሳቅ ሟቋረጥ ግን አይቻልም¡ || ይህ ክስተት እዚያው መስጂዱ ውስጥ ሶ'ፈል አወል (የመጀመሪያው ሰፍ) ላይ ቆሞ ሲሰግድ የነበረ አንድ ሰጋጅ ነው የሚያስተላልፍልን... * እናም ይህ ሰው እንዲህ ይለናል:- «አንድ ሰው ይሞትና ተሰግዶበት ተቀበረ ከዚያም ከኢሻ ሶላት በኋላ ነእሹ (ጀናዛ መሸከሚያው) ሊመልሱት ይዘውት ወደ መስጂድ ሲመጡ ሰአት ሄዶ ስለነበር መስጂዱ ተዘግቷል። ስለዚህ ኻዲሞች ለፈጅር ሶላት ሲመጡ እንዲያነሱት በሚል ጀናዛ መሸከሚያው ከመስጂዱ በር ከደረጃ ላይ ያስቀምጡታል። : ነገር ግን ሌሊት 9:30 ሰአት አካባቢ አንድ ሰውዬ ወደ መስጂድ ሲመጣ መስጂዱ ዝግ ሆኖ እና በረንዳው ተከፍቶ አገኘው የተወሰነ ቢጠብቅም መስጂዱን የሚከፍተው አጣ  ብርዱ በጣም ሲበረታበት ዞር ብሎ ሲያይ ጀናዛ መሸከሚያው ከአጠገቡ አገኘ በውስጡም ብርድልብስ ነገር አለ። : እና ይህ ሰው አገኘሁ ብሎ ጀናዛ መሸከሚያው ውስጥ ብርድ-ልብሱን ለብሶ ለጥ ብሎ እንቅልፉን ተኛ አባቴ! በብርድ ደንዝዞ የነበረው ሰውነቱ ትንሽ ምቾት ሲያገኝ ነፍሱንም አያውቅ ለጥ ብሎ ተኝቶልሀል... ሃሃሃ! ትንሽ እንደቆየ የመስጂዱ ኻዲም መጥቶ መሲጂዱ ሊከፍት ሲል በረንዳ ላይ ከነእሹ (ጀናዛ መሸከሚያው) ላይ የተኛ ሰውዬ ይመለከታል ከፈጅር በኋላ ሊሰገድበት ያመጡት ጀናዛ መሰለው... : ከኋላውም ሌሎች ሰዎች መጥቶ ግማሹ ሽንት ቤት ሌላው ውዱእ ሊያደርግ ይሄዳሉ ይህ በረንዳ ላይ ተኝቶ የሚያዩት ሰውዬ (ጀናዛ) ደግሞ ሁሉም ቀድመውኝ የመጡ ሰዎች ሊሰገድበት ያመጡት ጀናዛ ነው ብሎ ያስባል በውስጡ... (ያዝ እንግዲህ¡) በዚያ ላይ ፈጅር ነው ሰው ከእንቅልፉ ተነስቶ እየመጣ ነው ያለው ገና በደንብ ያልነቃ ህዝብ ነው። ሊሰገድበት የመጣ ጀናዛ ይሆናል በማለት ተጋግዘው ወደ መስጂድ ኢማሙ ጋር ወደ ሚህራብ አስገቡት። ሃሃ! : ብ ር ድ የቀጠቀጠው ሰውዬ ሲሸከሙት አያውቅ ተኝቷል¡ ህእ! ሰዎቹም የማን ይሁን ብለው አይጠይቁ ገና ከእንቅልፋቸው በደንብ አልነቁም እና ተሸክመው መስጂድ ውስጥ አስገቡት። ፈጅር አዛን ብሎ ለመስገድ ወደ 50 የሚሆኑ ሰዎች ተሰበሰቡ። ይህንን ታሪክ የሚያስተላልፍልን ሰው እኔም ከሰጋጆቹ አንዱ ነኝ የመጀመሪያው ሶፍ ላይ ነበርኩ ይላል። ከፈርድ በኋላ ልንሰግድበት ጀናዛው ከፊት ተደርጎ የፈጅር ሶላት እየሰገድን ነው። እህእ! : ልክ ለሁለተኛው ረከአ ስንነሳ ጂናዛው ሲንቀሳቀስ አየሁ እንዴዴዴ አይኔ ነው ወይስ ምንድ ነው¿ ብዬ አይኔን አበስኩ ጨፍኜም ገለጥኩ መንቀሳቀሱን ግን አልተወም በቃ እንቅልፍ አለቀቀኝም ይሆናል ብዬ አሰብኩ። ነገር ግን ነእሹ በደንብ መንቀሳቀስ ጀመረ ያኔ መረባበሽና መፍራት ጀመርኩ። ይህ የተኛው ሰውዬ ከብርድ ልብሱ ውስጥ ድንገት አንገቱ  አውጥቶ ሰገዳችሁ? ብሎ ጠየቀ። : ያኔ! ሁሉም ሰጋጆች ደንግጦ መተረማመስና መሮጥ ጀመሩ  እኔም አጠገቤ ከነበረው በር ወጥቼ በባዶ እግሬ ሮጥኩኝ ወደ 1 ኪ.ሜ ያክል የሚርቀውን ቤቴን በትንሽ ደቂቃዎች ደረስኩ ደግሞ ባዶ እግሬ መሆኔም የማውቀው ነገር የለም። ኢማሙ (አሰጋጁም) ሲያየው ደንግጦ መሬት ላይ ይወድቋል ሌሎች ሰዎች ግማሹ ከግድግዳ ጋር ይጋጫል ሌላው ደግሞ ልክ እንደኔው በባዶ እግሩ ይሮጣል መስጂድ ውስጥ አንድ ሰው አልቀረም። : አሁንም ሌላኛው በጣጣጣም የሚያስቀው ክስተት ተከሰተ ያ ከሬሳ መሸከሚያ(ከነእሹ) ላይ ተኝቶ የነበረው ሰውዬ ሲነሳ ሰዎች ሲሸሹ ሲሮጡ ሲያይ ከኋላቸው ተከትሎ መሮጥ ጀመረ። እናንተ ምን ሆናችሁ ነው ? ቂያማ ቆሞ ነው እንዴ? እያለ ከኋላ ኋላቸው መሮጥ ጀመረ። ሃሃሃ! : ሰዎቹ ደግሞ ወደ ኋላቸው ሲዞሩ ይህ ሰውዬ እየተከተላቸው  መሆኑ ያያሉ ያኔ ይብስባቸዋል ባለ በሌለ ሀይላቸው ይሮጣሉ። በዚህ መልኩ ሁሉም  ሰላታቸውን አቋርጠው ሮጡ...» ይለናል ቦታው ላይ የነበረ አንዱ ሰጋጅ።
نمایش همه...