Ministry of Urban and Infrastructure 🇪🇹🇪🇹
رفتن به کانال در Telegram
This is the official Telegram page of Ministry of Urban and Infrastructure
نمایش بیشتر9 932
مشترکین
+524 ساعت
+67 روز
+11330 روز
آرشیو پست ها
የፕሬስ መግለጫ
ኢትዮጵያ ነገዋን ዛሬ እየሠራች ነው!
ነገ የሚወሰነው ዛሬ በምንሠራው ሥራ ነው! የነገ ስኬታችን የሚቀረጸው በዛሬው ጥረታችን ነው። ከትናንት መልካም ልምዶችን በመቅሰም፣ ዛሬን በትክክል አጢኖ የነገን ራዕይ ዛሬ ላይ ሆኖ መገንባት የመንግሥታችን ጽኑ እምነትና መለያ ባህሪ ነው።
ሀገር በቀል ዕውቀትን ከዘመኑ ቴክኖሎጂ ጋር አስተሳስሮ ነገን ለመዋጀት መዘጋጀት ከዚህ ትውልድ የሚጠበቅ ትልቅ ኃላፊነት እንደኾነ መንግሥት በፅኑ ያምናል፡፡ ለዚህም ነው ዲጂታላይዜሽንን እንደ አስቻይም እንደ ኢኮኖሚ ዘርፍም በመውሰድ ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ ያለው፡፡
ኢትዮጵያ ለቀጣዩ ትውልድ ምንዳን እንጅ ዕዳን አታወርስም፡፡ ጊዜ በየአንጓዉ ለሚጠይቀዉ ጉዳይ ምላሽ መስጠት አለመቻል የትውልድ ዕዳ ነው፡፡ ለዚህም ነው ሀገራችን በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ታዳጊዎችን በትምህርት ቤት እየመገበች የምታስተምረው፤ ለዚህም ነው በሚሊዮን የሚቆጠሩ ወጣቶችን በነፃ የኮደርስ ሥልጠና እያበቃች ያለችው፤ ለዚህም ነው የመጀመሪያውን የሰው ሠራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲ እያቋቋመች ያለችው ፡፡ ነገ ያለቴክኖሎጂ ዕውቀት፣ ነገ ያለሳይበር ደኅንነት፣ ነገ ያለመረጃ ሉዓላዊነት የሕልውና አደጋ አንደኾነ መንግሥታችን ይገነዘባል፤ ትውልዱን ለዚያ ያዘጋጃል፡፡
ለዘመናት ኋላቀር ሲባል የነበረዉ የኢኮኖሚ ዘርፍ ግብርና ነገ ያለቴክኖሎጂ ሕልውናዉ አደጋ ላይ ነው፡፡ ለተፈጥሯዊ እና ሰው ሠራሽ አደጋዎች ቅድመ ጥንቃቄ እና ምላሽ አሰጣጥ ዲጂታላይዜሽን ወሳኝ ነው፡፡ የመንግሥት አገልግሎቶችን በጥራት እና በፍጥነት ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ ያለፉት ዘመናት አሠራሮች አይደለም ነገ ዛሬም አዋጭ አይደሉም፡፡
በዓለማቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እና ሥራ ፈጣሪ ወጣቶችን ለማፍራት ዲጂታል ክሕሎት በእጅጉ አስፈላጊ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ለእነዚህ ኹሉ ጉዳዮች ትኩረት ሰጥታ እየሠራች ስለምትገኝ ነው “ኢትዮጵያ ነገዋን ዛሬ እየሠራች ነው” የምንለው፡፡
የጳጒሜን አምስተኛ ቀን የነገ ቀን ብለን ማክበራችንም መጪዉ ዘመን የቴክኖሎጂ ተወዳዳሪነትን የሚጠይቅ፣ መረጃ ትንተና ላይ የተመሠረተ ውሳኔ የሚሰጥበት፣ ከግብርና እስከ ሕዋ ሳይንስ ምርምሮች በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዙ የሚኾኑበት ዘመን ዋዜማ ላይ ስለምንገኝ ለዚያ የሚመጥን ትውልድ ለማፍራት እንደምንሠራ ለማስገንዘብ ነው፡፡
ጳጉምን 5 የነገ ቀን በሚል ስያሜ መከበሩ ዲጂታላይዜሽን ለነገዋ ኢትዮጵያ ግንባታ እና ሉዓላዊነት መከበር ሀገራችን ወደ ዲጂታላይዜሽን ሽግግር ምዕራፍ ላይ እንደምትገኝ ለማብሰር ነው፡፡
+1
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት
የነገው ቀን
ሀገራዊ የቴክኖሎጂ ሽግግር
ከወረቀት ወደ ዲጂታል፤ ከተጠቃሚነት ወደ ፈጣሪነት! ትናንትን በመማርና በማረም ዛሬን በላቀ ትጋት በመገንባት ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን የዕለት ተዕለት ባህላችን እየሆነ ነው። ንግድና አገልግሎትን ያቀላጥፋል፣ መረጃዎችን ተደራሽ ያደርጋል፣ ዘርፎችንም ያዘምናል! የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያ ኮደሮች ንቅናቄ ወጣቶችን የሰው ሰራሽ አስተውሎት ፈጣሪ በማድረግ ወደ 7 ሚሊዮን ግባችን እያመራ ሲሆን የዲጂታል አገልግሎት ተደራሽነትና ጥራትን አረጋግጧል። በሀገር በቀል አቅም የበለጸገው የሳይበር ሉዓላዊነታችን ደግሞ የማንቆጣጠራቸው ቴክኖሎጂዎችን ጥገኝነት አላቆ በዲጂታል ኢኮኖሚ በራስ አቅሟ የምትቆም አዲሷ ኢትዮጵያ በታላቅ ምዕራፍ ላይ መሆኗን በኩራት ያበስራል!
+7
የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ጳጉሜን-4 የህብር ቀንን ምክንያት በማድረግ ለአቅመ ደካሞች ማዕድ አጋራ
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜ 4 ቀን 2018 ዓ/ም (ከመልሚ) የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የህብር ቀንን ምክንያት በማድረግ በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 አቅመ ደካሞችን የእንኳን አደረሳችሁ እና የአዲስ አመት መልካም ምኞት መግለጫ ማእድ አጋርቷል፡፡
በልደታ ክፍለ ከተማ የወረዳ 7 ድጋፍ የተደረገላቸው በወረዳው ውስጥ በሴፍቲኔት የታቀፉ፣ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው የማህበረሰብ ክፍል ናቸው።
የፕሬስ መግለጫ
ብዝኃነታችን የምንደምቅበት ጌጥ፣ የተደመረ ዐቅማችን ማሳያ ነው!
ኢትዮጵያ የብዝኃ ማንነቶች ድምር ናት፡፡ ኢትዮጵያውያን ከሚኖሩበት የአየር ንብረት እስከ አመጋገባቸው፤ ከአመራረታው እስከ አለባበሳቸው፤ ከሃይማኖታቸው እስከ ፖለቲካዊ አመለካከታቸው በርካታ ብዝኃነቶች ያስጌጧቸዋል፡፡ የእነዚህ ብዝኃነቶች ድምር ደግሞ የኢትዮጵያ የማድረግ ዐቅም ነው፡፡
የኢትዮጵያውያን ብዝኃነት ለዘመናት የማይታረቁ የልዩነትና ግጭት ምንጭ ተደርጎ እንዲታይ ታሪካዊ ጠላቶቻችን ያለመታከት ሠርተዋል፡፡ በዚህም በየዘመኑ የታዩ ስኬታማ ድሎችን በአጭር እየቀጩ ኢትዮጵያን የማይገባት ደረጃ ላይ እንድትገኝ ለማድረግ ጥረዋል፡፡ ይህ ትውልድ ግን የጠላቶቻችን ምኞትና የብዝኃነትን ዐቅም የተረዳ፣ የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን የሚያደርግ ባለታሪክ ለመኾን የልዩነት ሰንኮፎቹን በምክክር ለመንቀል ወስኗል፤ የጋራ ዕጣ ፋንታዉን በጋራ ተልሟል፡፡
ዛሬ ላይ ኢትዮጵያውያን የከፍታ ጉዞን ነጠብጣብ እንዳይኾን መሥመር አስይዘነዋል፡፡ ችግሮቻችንን እና የግጭት ምንጭ ኾነዉ ለባዕዳ መግቢያ ቀዳዳ፣ ለባንዳ መሹለኪያ የነበሩ ክፍተቶችን ለመድፈን በጋራ መክረናለ፡፡ ኢትዮጵያውያን በሰላማዊ ትግል ያነበሩት የለውጥ መንግሥት ባለፉት የለውጥ ዓመታት እየደረጀ መጥቶ ኢትዮጵያን በጽኑ መሠረት ላይ መገንባት የሚያስችል ዓውድ ፈጥሯል፡፡ የመልክአ ምድር፣ የአመጋገብ፣ የአለባበስ፣ የቋንቋ፣ የሃይማኖት፣ የፖለቲካዊ አመለካከትና ሌሎች ልዩነቶቻችን የኢትዮጵያ ጌጥ እና ዐቅም እንደኾኑ የጋራ አቋም ወስደናል፡፡
ብዝኃነታችን ውበት እና የካበተ ሥልጣኔያችን ማሳያ፣ ከትናንት እስከ ዛሬ የመቻላችን ምክንያት እንደኾነ በአካታች ሀገራዊ ምክክራችን አረጋግጠናል፤ ታሪኮቻችንም ምሥክሮች ኾነው አሳይተውናል፡፡ የዓለምን ታሪክና ፖለቲካ የለወጠው የዓድዋ ድል፤ የኢትዮጵያን ጂኦ-ፖለቲካዊ ዐቅም ያሳደገዉ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፣ የኢትዮጵያን ስም በዓለም በየዓመቱ በበጎ የሚያስጠራዉ አረንጓዴ ዐሻራ ለብዝኃነታችን ዐቅምነት ሕያዉ ምሥክሮች ናቸው፡፡
ለዚህም ነው ጳጒሜን 4ን የኅብር ቀን ብለን ብዝኃነትን የኢትዮጵያ ጌጥ መሆኑን በሚያረጋግጥ መልኩ እያከበርን የምንገኘው፡፡ ኢትዮጵያ የብዙ ብዝኃነቶች ሀገር በመኾኗ የብዙ ዐቅሞች ባለቤትም ናት፡፡ የብዝኃነትን ጌጥነት እና ዐቅምነት እርስ በርስ መረዳዳት እና አንዳችን ለሌላችን ጥላ ከለላ በመኾን እንገልጸዋለን፡፡ ዛሬ እነዚህን እውነቶች ለዓለም የምንገልጽበት ድንቅ ቀን ነው፡፡
እንኳን ለጳጉሜን 4 የኅብር ቀን አደረሳችሁ!
ጳጒሜን 04 ቀን 2018 ዓ.ም
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
አዲስ አበባ
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ.ር) መልዕክት
የኅብር ቀን
ኢትዮጵያችን በሀገር በቀል እሴቶቿ፤ የነገውን ብሩህ ተስፋዋን በገዛ እጆቿ እየቀረጸች ትገኛለች!
በትውልድ ቅብብሎሽ ያገኘናቸውን ድንቅ የሀገር በቀል እሴቶቻችንን በማጎልበት እና በመደመር ፍልስፍና በመመራት፣ ለጽኑ ኅብረብሔራዊ አንድነታችን የማይናወጥ መሠረት ጥለናል። ታሪካዊውን ሀገራዊ ምክክር የመጀመር የታሪክ እጥፋት ተነስተን፣ የሁሉም ዜጎቻችንን ሕይወት ከሚለውጡ ሰው-ተኮር የኮሪደር ልማታችን፣ የበጎ ፈቃድ ስራዎቻችን እንዲሁም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃግብርን በተግባር እውን እስከማድረግ ድረስ፤ ሁላችንም በአንድነት ስንቆም የጋራ ትርክቶቻችን ወደ ጋራ ስኬት እንደሚያሻግሩን በተግባር አሳይተናል።
እኛ የምንገነባው አካታች የሆነች፣ በኢኮኖሚ ራሷን የቻለች፣ የአብሮነትና መረዳዳት ባህል የጎለበተባት ጠንካራ ሀገር ብቻ ሳይሆን የሁሉንም ኢትዮጵያውያን የጋራ ታላቅነትና እምቅ አቅም በተግባር እያረጋገጥን እንገኛለን። በአንድነት ወደ ብልጽግና ጉዟችን እንቀጥላለን።
አንድ ህዝብ፣ ታላቅ ሀገር ኢትዮጵያ!
የፕሬስ መግለጫ
እንኳን ለጳጉሜን 3 የፅናት ቀን አደረሳችሁ፣ አደረሰን!
ፅናት የኢትዮጵያውያን የትናንትም የዛሬም መገለጫ ነው፡፡ ኢትዮጵያ በኢትዮጵያውያን የጋራ ዐጥንት እና ደም ተጠብቃ የቆየች የኩራት እና ክብር ምንጭ ናት፡፡ ለዚህም ነው ከትናንት እስከ ዛሬ ከየትኛዉም አቅጣጫ፣ በማንኛዉም ኃይል የሚቃጡ ጥቃቶችን ኹሉ በጀግንነት መመከት፣ ነፃ እና ሉዓላዊ ሀገር ለትውልድ ማስረከብ የተቻለው፡፡
ጳጒሜን 3 ቀንን የፅናት ቀን በሚል ስያሜ የምናከብረዉም የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለዘመናት ያፀኑ ጀግኖችን ዕውቅና ለመስጠት፤ የዛሬ ጀግኖችን ለማበረታታት እና የነገ ጀግኖችን ለመፍጠር ነው፡፡ ኢትዮጵያ በምድር፣ በአየር፣ በባሕር እና በሳይበር ግንባሮች ሉዓላዊነቷን የሚያረጋግጡ ፅኑ ጀግኖችን አፍርታለች፡፡
ኢትዮጵያ ለዓለም ፈር በቀደደዉ የሥነ መንግሥት ታሪኳ ከጠላት ትንኮሳ የተላቀቀችበት ዘመን አልነበረም፡፡ ጡንቻዋ ሲፈረጥም ታፍራ እና ተከብራ፤ የሟሸሸ ሲመስል ደግሞ ለጥቃት ተጋልጣ ታውቃለች፡፡
ያለስስት ለኢትዮጵያ ሉዓላዊነት መረጋገጥ ዋጋ የሚከፍሉ ልጆቿም ዘወትር ታፍራ እና ተከብራ እንድትኖር በተጠንቀቅ ይጠብቋታል፡፡ የጠላቶቿ ሴራ እና ትንኮሳም የበለጠ አጠንክሯት እና ጀግንነቷን ፈልቅቆ አውጥቶት እንጅ ሉዓላዊነቷን ጥያቄ ውስጥ አስገብቶት አያውቅም፡፡
ኢትዮጵያውን በጋራ ኢትዮጵያን ለመጠበቅ በየጊዜዉ ወታደራዊ ጥበብን ተላብሰው፣ ከራስ አልፎ ለሌሎች ነፃነት ዋጋ እየከፈሉ ከዚህ ዘመን ደርሰዋል፡፡ ዘመኑ የሚጠይቀውን ሰብእና፣ ወታደራዊ ዲስፕሊን እና ሥልጠናም በበቂ ተላብሰዋል፡፡ ጠላት ከትንኮሳ በፊት ደጋግሞ እንዲያስብ የሚያስገድድ ሰብአዊ ልማት እና የቴክኖሎጂ ዐቅም ተፈጥሯል፡፡
በየግንባሩ የተገነባዉ ሠራዊት ከኢትዮጵያ የብልጽግና ትልም ፊት ለመቆም የሚውተረተር ደንቃራን ኹሉ የማጽዳት፤ የተረከባትን ነፃ ሀገር በነፃነት ለቀጣዩ ትውልድ የማስረከብ፣ ኢትዮጵያ መሻቷን ኹሉ በግዛቷ ውስጥ በነፃነት የማድረግ ዐቅም እንዲኖራት የማገዝ ተልእኮን ያነገበ ነው፡፡
ኢትዮጵያን ማፍረስ የሚሹ ጠላቶች ነበሩ፤ ይኖራሉም፡፡ ነገር ግን በሠራዊታችን የማድረግ ዐቅም ማደግ፤ በተገነባበት የማሸነፍ ሥነ ልቦና እና በታጠቀዉ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ እንዲሁም በተካሄደዉ አካታች ሀገራዊ ምክክር የተላላኪ ባንዳዎች የማኩረፊያ ቀዳዳ መደፈን የጠላት የማድረግ ዐቅም ከሐሳብ የማይሻገርበት ኹኔታ ተፈጥሯል፡፡
ኢትዮጵያ አሁን የፖለቲካ ቅራኔ ያላቸው ኹሉ አኩርፈው ጫካ የሚገቡባት እና የጠላት መጠቀሚያ የሚኾኑባት ሀገር አይደለችም፡፡ ኢትዮጵያ ዛሬ ላይ የሚያሳሳ ነገን እየገነባች፤ በወል እውነት ላይ የጸናች፤ ብዝኃነትን ጌጥ ያደረገ ሕዝባዊ ሠራዊት ያላት፣ አፍሪካዊት የብልጽግና ተምሳሌት ለመኾን ወደ ከፍታ እየተስፈነጠረች ያለች ሀገር ናት፡፡ ከዚህ ጉዞዋ ሊያደናቅፋት የሚሻን መሰናክል ኹሉ ደጋግሞ እንዲያስብ፣ የአየር፣ የባሕር እና የሳይበር ተቋም እና ሠራዊት ገንብታለች፡፡
በዛሬው ዕለት የፅናት ቀንን ስናከብር የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት እና ነፃነት ለማስከበር፣ ለሕዝቦቿ ሰላም እና ደኅንነት መረጋገጥ መሥዋዕትነት የከፈሉ እና እየከፈሉ ያሉ ጀግኖችን በማክበር እና ዐሻራቸዉን አጠናክሮ ለማስቀጠል ቃል በመግባት ነው፡፡
ጳጒሜን 03 ቀን 2018 ዓ.ም
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
አዲስ አበባ
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት
"የጽናት ቀን
ኢትዮጵያን ስናስብ፣ ሌት ተቀን በጽናት በመቆም ሀገርን ከጠላት ለመጠበቅ ወጥተው ለሚያድሩት ብርቱ የፀጥታ ኃይሎቻችን ቅድሚያ ሳንሰጥ ስለ ሁለንተናዊ ከፍታ ማሰብ ፈጽሞ አይቻልም፡፡ ለዚህም ነው በዚህ የጽናት ቀን፣ ለሀገረ-መንግሥታችን ዘላቂነትና ሉዓላዊነት ሲሉ ውድ ሕይወታቸውን የከፈሉትን የጀግኖቻችንን ታሪካዊ መስዋዕትነት በከፍተኛ ሀገራዊ ክብር የምንዘክረው፡፡
ዛሬ ላይ ሀገራችን በራሷ ዕውቀትና በልጆቿ አቅም የላቀ የቴክኖሎጂ ብቃት ያላቸውን ሰው አልባ አውሮፕላኖችን፣ ዘመናዊ የታጠቁ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎችን፣ ከባድ መሣሪያዎችንና መድፎችን፣ እንዲሁም ተተኳሽ ጥይቶችን በራሷ ወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች ማምረት ችላለች፡፡ ይህ በራስ የመቆም አቅም፣ የሕዝባችን ሰላምና የሁለንተናዊ ኢኮኖሚ እድገታችን ጽኑ መሠረት በመሆኑ፣ ሀገራዊ ጽናታችንን በተጨባጭ ልማትና በጠንካራ የመጠበቅና የመከላከል አቅም እያረጋገጥን የኢትዮጵያን ዘላቂ ብልጽግና እናጸናለን!"
በሶማሌ ክልል የተከናወኑት ሜጋ ፕሮጀክቶች ለንግድና ለኢንቨስትመንት አዲስ ዕድል ፈጥረዋል
#ጳጉሜን 2 "የማንሰራራት ቀን" አስመልክቶ ለኢትዮጵያ ማንሰራራት ተምሳሌት የሆኑ ትላልቅ ፕሮጀክቶች በተለያዩ ተቋማት፣ የባለድርሻ አካላትና የሕብረተሰብ ክፍሎች ተጎበኙ፡፡ ፕሮጀክቶች ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፍ እያሳየች ያለችውን እውነተኛ ማንሰራራት በተግባር የሚያረጋግጡ መሆናቸው ተገለጸ።
የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ከከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ጋር በጂግጂጋ ከተማ ባዘጋጀው የጉብኝት መርሐግብር በከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የቤቶች ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፀጋዬ ሞሼ፤ በክልሉ የተከናወኑት የኮሪደር ልማትና ሜጋ ፕሮጀክቶች ኢትዮጵያ በማንሰራራት ላይ መሆኗን የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል።
በከተማዋ የተከናወነው የመሠረተ ልማት ግንባታ ጅግጅጋ ተወዳዳሪና ለኢንቨስትመንት የተመቸች ማድረጉን ጠቁመው፤ በገበታ ለሀገር የተገነባው የሸበሌ ሪዞርትም ቀጠናዊ ትስስርን የሚያጠናክርና የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ማንሰራራት የሚያፋጥን መሆኑን ገልጸዋል።
የጅግጅጋ ከተማ ከንቲባ አቶ ሻፊ አህመድ በጉብኝቱ ወቅትር ባስተላለፉት መልዕክት የለውጡ መንግስት ከመጣ በኮሪደር ልማት፣በቱሪዝም፣ በተለይም የሜዲካል ቱሪዝም ምሳሌ ሊሆኑ የሚችሉ የልማት ሥራዎችን ሰርቷል፡፡
ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ የመሠረተ ልማት ሥራዎች ተከናውነዋል። ባለፉት ዓመታት የማኅበረሰቡን ጥያቄ መሠረት ያደረጉ ፕሮጀክቶች ተተግብረዋል።
የባለድርሻ አካላቱ በጉብኝታቸው በክልሉ የከባድ መኪና አካል መኪና መገጣጠሚ ፋብሪካንም የጎበኙ ሲሆን ክልሉ በምሥራቅ አከባቢ ያለውን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ለማጠናከር እያደረጋቸው ያሉ ጥረቶችን ጎብኚዎቹ አድንቀዋል፡፡
የሶማሌ ክልል በቱሪዝም ዘርፍ መንግስት ከሰራቸው ኢንሼቲቮች በተጨማሪ በክልሉ አቅም በርካታ የቱሪስት መዳረሻ ሊሆኑ የሚችሉ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን በጉብኝቱ ወቅት የተገለጸ ሲሆን በምስራቅ አከባቢ ሜዲካል ቱሪዝምን ለማስፋፋት አንድ ከፍተኛ ሪፈራን ሆስፖታል በመገንባት ላይ መሆኑም በጉብኝቱ ላይ ተብራርቷል፡፡
ለአብነት በከተማዋ የንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ከ18 በመቶ ወደ 52 በመቶ ማደጉን፣ የቴሌኮም አገልግሎትም ከ2ጂ ወደ 5ጂ ደረጃ ከፍ ማለቱን ጠቅሰዋል።
በጉብኝቱ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ዋና ዳይሬክተር መስፈን ነገዎ (ዶ/ር)፤ የለውጡ መንግሥት የልማት ሃሳቦች በክልሉ ተግባራዊ ሆነው መመልከታቸውን ገልጸዋል። የንግድና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎችን በማነቃቃት ለዘመናዊ አኗኗርና ለማኅበራዊ ለውጥ መንገድ የከፈቱ መሆናቸውን አብራርተዋል።
የዚህ የጉብኝት መርሃ ግብር ዋና ዓላማ በክልሉ ያለውን የልማት እንቅስቃሴ ለግሉ ዘርፍ ማስተዋወቅና ባለሀብቶች በልማት አጋርነት የሚሳተፉበትን ዕድል መፍጠር እንደሆነ ተመልክቷል።
በከተማዋ የተገነቡ የ52 ኪሎሜትር የመንገድ ሥራዎችን፣ የኮሪደር ልማትና የመሠረተ ልማት ዝርጋታዎችን፣ የሜጋ መኪና መገጣጠሚያ ኢንዱስትሪንና የሌማት ትሩፋት ፕሮጀክቶችን አስጎብኝተዋል።
በሶማሌ ክልል የተከናወኑት ሜጋ ፕሮጀክቶች ለንግድና ለኢንቨስትመንት አዲስ ዕድል ፈጥረዋል
#ጳጉሜን 2 "የማንሰራራት ቀን" አስመልክቶ ለኢትዮጵያ ማንሰራራት ተምሳሌት የሆኑ ትላልቅ ፕሮጀክቶች በተለያዩ ተቋማት፣ የባለድርሻ አካላትና የሕብረተሰብ ክፍሎች ተጎበኙ፡፡ ፕሮጀክቶች ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፍ እያሳየች ያለችውን እውነተኛ ማንሰራራት በተግባር የሚያረጋግጡ መሆናቸው ተገለጸ።
የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ከከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ጋር በጂግጂጋ ከተማ ባዘጋጀው የጉብኝት መርሐግብር በከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የቤቶች ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፀጋዬ ሞሼ፤ በክልሉ የተከናወኑት የኮሪደር ልማትና ሜጋ ፕሮጀክቶች ኢትዮጵያ በማንሰራራት ላይ መሆኗን የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል።
በከተማዋ የተከናወነው የመሠረተ ልማት ግንባታ ጅግጅጋ ተወዳዳሪና ለኢንቨስትመንት የተመቸች ማድረጉን ጠቁመው፤ በገበታ ለሀገር የተገነባው የሸበሌ ሪዞርትም ቀጠናዊ ትስስርን የሚያጠናክርና የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ማንሰራራት የሚያፋጥን መሆኑን ገልጸዋል።
የጅግጅጋ ከተማ ከንቲባ አቶ ሻፊ አህመድ በጉብኝቱ ወቅትር ባስተላለፉት መልዕክት የለውጡ መንግስት ከመጣ በኮሪደር ልማት፣በቱሪዝም፣ በተለይም የሜዲካል ቱሪዝም ምሳሌ ሊሆኑ የሚችሉ የልማት ሥራዎችን ሰርቷል፡፡
ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ የመሠረተ ልማት ሥራዎች ተከናውነዋል። ባለፉት ዓመታት የማኅበረሰቡን ጥያቄ መሠረት ያደረጉ ፕሮጀክቶች ተተግብረዋል።
የባለድርሻ አካላቱ በጉብኝታቸው በክልሉ የከባድ መኪና አካል መኪና መገጣጠሚ ፋብሪካንም የጎበኙ ሲሆን ክልሉ በምሥራቅ አከባቢ ያለውን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ለማጠናከር እያደረጋቸው ያሉ ጥረቶችን ጎብኚዎቹ አድንቀዋል፡፡
የሶማሌ ክልል በቱሪዝም ዘርፍ መንግስት ከሰራቸው ኢንሼቲቮች በተጨማሪ በክልሉ አቅም በርካታ የቱሪስት መዳረሻ ሊሆኑ የሚችሉ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን በጉብኝቱ ወቅት የተገለጸ ሲሆን በምስራቅ አከባቢ ሜዲካል ቱሪዝምን ለማስፋፋት አንድ ከፍተኛ ሪፈራን ሆስፖታል በመገንባት ላይ መሆኑም በጉብኝቱ ላይ ተብራርቷል፡፡
ለአብነት በከተማዋ የንጹህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ከ18 በመቶ ወደ 52 በመቶ ማደጉን፣ የቴሌኮም አገልግሎትም ከ2ጂ ወደ 5ጂ ደረጃ ከፍ ማለቱን ጠቅሰዋል።
በጉብኝቱ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ዋና ዳይሬክተር መስፈን ነገዎ (ዶ/ር)፤ የለውጡ መንግሥት የልማት ሃሳቦች በክልሉ ተግባራዊ ሆነው መመልከታቸውን ገልጸዋል። የንግድና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎችን በማነቃቃት ለዘመናዊ አኗኗርና ለማኅበራዊ ለውጥ መንገድ የከፈቱ መሆናቸውን አብራርተዋል።
የዚህ የጉብኝት መርሃ ግብር ዋና ዓላማ በክልሉ ያለውን የልማት እንቅስቃሴ ለግሉ ዘርፍ ማስተዋወቅና ባለሀብቶች በልማት አጋርነት የሚሳተፉበትን ዕድል መፍጠር እንደሆነ ተመልክቷል።
በከተማዋ የተገነቡ የ52 ኪሎሜትር የመንገድ ሥራዎችን፣ የኮሪደር ልማትና የመሠረተ ልማት ዝርጋታዎችን፣ የሜጋ መኪና መገጣጠሚያ ኢንዱስትሪንና የሌማት ትሩፋት ፕሮጀክቶችን አስጎብኝተዋል።
+9
የጳጉሜ 2 የማንሰራራት ቀንን አስመልክቶ የፎቶ አውደ-ርዕይ ተካሄደ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 29 ቀን፣ 2018 ዓ.ም (ከመልሚ) የጳጉሜ 2 የማንሰራራት ቀንን አስመልክቶ 6 ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች በጋራ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ቅጥር ግቢ ውስጥ የፎቶ አውደ-ርዕይ አካሂደዋል፡፡
በአውደ-ርኢይው በየሴክተራቸው የተከናወኑ አበይቲ የመሠረተ-ልማት ስራዎችን ያቀረቡት የከተማና መሠረተ-ልማት ሚኒስቴር፣ የማዕድን ሚኒስቴር፣ የግብርና ሚኒስቴር፣ የቱሪዝም ሚኒስትር እና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሮች ናቸው፡፡
አውደ-ርዕይው በዋናናት ትኩረት ያደረገው ባለፉት የለውጥ ዓመታት በሁሉም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች በሀገር አቀፍ ደረጃ ተገንብተው የተጠናቀቁ ሜጋ ፕሮጀክቶችና አጠቃላይ የመሠረተ-ልማት ሀገሪቱ የደረሰችበትን የዕድገት በጉልህ የሚያመላክቱና የሀገሪቱን የከፍታ ደረጃ ማሳያ ናቸው ሲሉ አስጎብኚዎች በዝረዝር ገልጸዋል፡፡
በአውደ-ርዕይው ከቀረቡት መካካል በተለያዩ ከተሞች የተከናወኑ የኮሪድር ልማቶች፣ በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው የተመዘገቡ ዕምርታዊ ለውጦች፣ በአረንጓዴ አሻራ፣ በሌማት ትሩፋት፣ በማዕድን ዘርፍ፣ በቱሪዝም መዳረሻዎች የተከናወኑ የፎቶ ማሳያዎች ቀርበው ተጎብኝተዋል፡፡
በአውደ-ርዕይው አስጎብኚዎች እንደገለጹት በተከናወኑት የመሠረተ-ልማቶች ምክንያት ከውጭ ሀገራት ሲገቡ በነበሩ ግብዓቶች በሀገር ውስጥ በማምረት ከፍተኛ የሆነ የውጭ ምንዛሬ ከማስገኘቱም ባሻገር ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል ማስገኘታቸውንና ለዘላቂ የሀገር ኩራት፣ ለትውልዱ ተስፋ፣ ሀገሪቱ የመለወጧን ትንሳዔ አብሳሪ ነው ሲሉ አስጎብኝዎች ገልጸዋል፡፡
የጳጉሜ 2 የማንሰራራት ቀንን አስመልክቶ የፎቶ አውደ-ርዕይ ተካሄደ
አዲስ አበባ፣ነሐሴ 29 ቀን ፣2018 ዓ.ም (ከ.መ.ል.ሚ)
የጳጉሜ 2 የማንሰራራት ቀንን አስመልክቶ ሚኒስቴር መስሪያ ቤታችንና ሌሎች 5 ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች በጋራ በመቀናጀት በኢትዮጵያ አየር መንገድ ቅጥር ግቢ ውስጥ የፎቶ አውደ-ርዕይ አካሂደዋል፡፡
በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አስተባባሪነት በአውደ-ርኢይው በየሴክተራቸው የተከናወኑ አበይቲ የመሠረተ-ልማት ትሩፋታቸውን ያቀረቡት ሚኒስትር መ/ቤቶች የከተማና መሠረተ-ልማት ሚኒስትር፣ የማዕድን ሚኒስቴር፣የግብርና ሚኒስቴር፣የቱሪዝም ሚኒስትር እና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሮች ናቸው፡፡
አውደ-ርዕይው በዋናናት ትኩረት ያደረገው ባለፉት የለውጥ ዓመታት በሁሉም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች በሀገር አቀፍ ደረጃ ተገንብተው የተጠናቀቁ ሜጋ ፕሮጀክቶችና አጠቃላይ የመሠረተ-ልማት ሀገሪቱ የደረሰችበትን የዕድገት ማማ በጉልህ የሚያመላክቱና የሀገሪቱን የከፍታ ደረጃ ማሳያ ናቸው ሲሉ አስጎብኚዎች በዝረዝር ገልቷል፡፡
በአውደ-ርዕይው ከቀረቡት መካካል በተለያዩ ከተሞች የተከናወኑ የኮሪድር ልማቶች፣በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው የተመዘገቡ ዕምርታዊ ለውጦች፣በከተሞች የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ ረገድ፣በአረንጓዴ አሻራ፣በሌማት ትሩፋት፣በክረምት በጎ አድራጎት ስራዎች፣በማዕድን ዘርፍ፣ በቱሪዝም መዳረሻዎች የተከናወኑ የፎቶ ማሳያዎች ቀርበው ተጎብኝተዋል፡፡
በአውደርዕይው አስጎብኚዎች እንደገለጹት በተከናወኑት የመሠረተ-ልማቶች ምክንያት ከውጭ ሀገራት ሲገቡ በነበሩ ግብዓቶች በሀገር ውስጥ በማምረት ከፍተኛ የሆነ የውጭ ምንዛሬ ከማስገኘቱም ባሻገር ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል ማስገኘታቸውንና ለዘላቂ የሀገር ኩራት፣ለትውልዱ ተስፋ፣ሀገሪቱ የመለወጧን ትንሳዔ አብሳሪ ነው ሲሉ አስጎብኝዎች ገልጸዋል፡፡
ጳጉሜን -2 የማንሰራራት ቀን
የኮይሻ ፕሮጀክት ኢትዮጵያ የመልማት እንጂ ሌሎችን የመጉዳት ዓላማ እንደሌላት ማሳያ ነው
- አቶ አብዱልፈታህ በደዊ የፕሮጀክቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ
የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ኢትዮጵያ የመልማት እንጂ ሌሎችን የመጉዳት ዓላማ እንደሌላት ማሳያ መሆኑን የፕሮጀክቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አብዱልፈታህ በደዊ ገለጹ።
ምክትል ሥራ አስኪያጁ የፕሮጀክቱ የግንባታ አፈጻጸም 77 በመቶ መድረሱን ጠቁመው፤ ፕሮጀክቱ በታችኛው ተፋሰስ ሀገሮች ላይ መልካም ተጽዕኖ የሚያንጸባርቅ እንጂ ምንም ዓይነት ጉዳት የማያመጣ መሆኑ በተግባር መረጋገጡን ለጋዜጣ ፕላስ አስረድተዋል።
የኮይሻ ፕሮጀክት ከታችኛው ተፋሰስ ሀገሮች በተለይም ከኬንያ ቱርካና ሐይቅ ጋር የሚያያዝ መሆኑን የጠቆሙት አቶ አብዱልፈታህ፤ ቀደም ሲል ጊቤ 3 መገደቡ በቱርካና ሐይቅ የውኃ መጠን ላይ አሉታዊ አስተዋጽኦ ይኖረዋል የሚል ትርክት ይነሳ እንደነበር አስታውሰዋል። ሆኖም ከግድቡ በኋላ የታየው እውነታ ተቃራኒ እንደሆነና ቱርካና ሐይቅ ዓመቱን ሙሉ የተመጣጠነ የውኃ መጠን እንዲያገኝ ማስቻሉን ገልጸዋል፤ በተመሳሳይ ኮይሻም ሲጠናቀቅ በአጎራባች ሀገሮች ላይ የሚያንጸባርቅ እንጂ ጉዳት የማያመጣ መሆኑ በሥራ ማረጋገጡን ተናግረዋል።
በመሆኑም ኮይሻም ሆነ ጊቤ 3 ለታችኛው ተፋሰስ ሀገሮች የተመጣጠነ ውኃ በመልቀቅና ሊደርስባቸው የሚችለውን የጎርፍ አደጋ በመከላከል ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ መሆናቸው በተግባር ተረጋግጧል።
የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት እ.አ.አ በ2016 ወደ ሥራ ቢገባም እስከ ሁለት ዓመታት ያህል የሚታይ ሥራ እንዳልነበረ ያነሱት ምክትል ሥራ አስኪያጁ፤ በዚህ ወቅት የተከናወኑት ሥራዎች በዋናነት የመጠነኛ ቁፋሮ፣ የሳይት ዝግጅት እና የካምፕ ግንባታዎች ብቻ እንደነበሩ ገልጸዋል።
ሆኖም ከለውጡ ወዲህ በተሰጠው ልዩ ትኩረት የግንባታ ሥራው በከፍተኛ ሁኔታ ተፋጥኖ በአሁኑ ሰዓት 77 በመቶ አፈጻጸም ላይ ደርሷል። ፕሮጀክቱ ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በመቀጠል ሁለተኛው ትልቅ የኃይል ማመንጫ ሲሆን፤ የማመንጨት አቅሙም 1,800 ሜጋ ዋት ነው ብለዋል።
ኮይሻ ከላይኛው ተፋሰስ በኩል የጊቤ 3 ኃይል አመንጭቶ የሚለቀቀውን ውኃ በድጋሚ በመያዝ የሚጠቀም በመሆኑ፣ የዝናብ ወቅቶችን ሳይጠብቅ ዓመቱን ሙሉ ውኃ ይዞ የሚጠቀምና በፍጥነት የሚተካ የውኃ ምንጭ ያለው ብቸኛ ፕሮጀክት ነው ተብሏል።
በኦሞ ወንዝ ላይ ከተገነቡት ግድቦች መካከል አራተኛው የሆነው ይህ ፕሮጀክት በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ውስጥ ተጠናቆ በሙሉ አቅሙ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ተመልክቷል።
