ch
Feedback
Ministry of Urban and Infrastructure 🇪🇹🇪🇹

Ministry of Urban and Infrastructure 🇪🇹🇪🇹

前往频道在 Telegram

This is the official Telegram page of Ministry of Urban and Infrastructure

显示更多
9 584
订阅者
+324 小时
+467
+10130
帖子存档
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ለአየር ንብረት ጥበቃ ከሚያበረክተው መሠረታዊ አስተዋፅዖ ባለፈ፣ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የማር ምርት ላይ ተጨባጭ ውጤቶችን እያስመዘገበ ይገኛል። ተፈጥሮንና አካባቢያች
+9
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ለአየር ንብረት ጥበቃ ከሚያበረክተው መሠረታዊ አስተዋፅዖ ባለፈ፣ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የማር ምርት ላይ ተጨባጭ ውጤቶችን እያስመዘገበ ይገኛል። ተፈጥሮንና አካባቢያችንን በመጠበቃችን፣ ደኖች እየተስፋፉ በመምጣታቸው፣ የንብ ዝርያዎችን የሚያግዙና የማር ምርትን የሚያሳድጉ ምቹ ከባቢዎች ምክንያት የምግብ ምንጮች ሊፈጠሩ ችለዋል። ‎ተስፋን እንትከል!

የመሠረተ-ልማት ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች በሠው ሠራሽ አስተውሎት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሠጠ አዲስ አበባ፣ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም(ከ.መ.ል.ሚ) የመሠረተ-ልማት ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪውን ዲጅታላይዝ ለማድረግ ታስቦ በሠው ሠራሽ አስተውሎት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሠጥቷል፡፡ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ዲጅታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም እየተራቀቀና እየዘመነ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ የተቋሙ አመራሮችና ባለሙያዎች ከዘመኑ ጋር ራሳቸውን ፈጥነው በእውቀትና በክህሎት ቀድመው በመገኘት በሀገራችን የሚከናወኑ የመሠረተ-ልማቶች በሁሉም ክልሎች ተግባራዊ እንዲሆኑ ስልጠናው እጅግ የጎላ ነው ያሉት በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የመሠረተ-ልማት ዘርፍ አማካሪ አቶ ቃሲም ጃቢር መድረኩን በከፈቱበት ወቅት ነው፡፡ የሰው ሠራሽ አስተውሎት ያለው ፈፈዳ በዓለማችንና በኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ዘርፍ እጅግ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ የሚገኝ መሆኑን የጠቀሱት ባለሙያው የዕለት ተዕለት ሥራዎችን በማቀላጠፍ አዳዲስ ፈጠራዎችን እውን እያደረገ ይገኛል ብለዋል። በተለይ በከተማ ልማት እና መሠረተ ልማት ዘርፍ የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ያለው ጠቀሜ ባለሙያው እንዳብራሩት ዘመናዊ የከተማ ፕላን (Smart City Planning): ሳተላይት እና ድሮኖች የሚሰበስቡትን መረጃ በመጠቀም ከተሞች እንዴት እንደሚያድጉ አስቀድሞ መተንበይ ይቻላል። ይህም መሬትን በአግባቡ ለመጠቀምና ህገ-ወጥ ሰፈራዎችን ለመቆጣጠር ይረዳል። የትራንስፖርትና መንገድ አስተዳደር (Traffic Optimization): በትራፊክ መብራቶችና ካሜራዎች አማካኝነት የትራፊክ መጨናነቅን መቆጣጠር እና ተሽከርካሪዎች ያለ ምንም እንከን እንዲንቀሳቀሱ ማድረግ ይቻላል። የአገልግሎት አሰጣጥ ዘመናዊነት (E-Governance): እንደ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ያሉ አካላት የነዋሪዎችን መረጃና አገልግሎት (ለምሳሌ የሲቪል ምዝገባ) ለማቀላጠፍ በ AI የተደገፉ ዲጂታል ሲስተሞችን እንደምጠቀሙ በስልጠናው ተገልጿል።

What we do now will inform how far our transformation goes

Ethiopia Delivers - This review demonstrates how coordinated efforts are driving tangible change where it matters most.

በገንዘብ ሚኒስቴር ከፍተኛ አማካሪ የሆኑት ትዕግሥት ፍስሀ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ አዲስ የከተማ ልማት ምዕራፍ ውስጥ እየገባች ሲሆን፥ ትኩረቱም ከተሞችን ማሰፋፋት ላይ ብቻ ሳይሆን ምርታማነታቸውን ማ
በገንዘብ ሚኒስቴር ከፍተኛ አማካሪ የሆኑት ትዕግሥት ፍስሀ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ አዲስ የከተማ ልማት ምዕራፍ ውስጥ እየገባች ሲሆን፥ ትኩረቱም ከተሞችን ማሰፋፋት ላይ ብቻ ሳይሆን ምርታማነታቸውን ማሳደግ እንዲሁም ምቹ፣ ተወዳዳሪ፣ ሁሉን አቀፍና ዘመናዊ ከተሞች ለሥራ ዕድል ፈጠራና ለጋራ ብልፅግና ቀጣይ ሞተር እንዲሆኑ ማድረግ ነው። #PMOEthiopia #EthiopiaDelivers ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/FDREGovermentCommunication

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ‎“ኢትዮጵያ ታከናውናለች” በተሰኘው ብሔራዊ ጉባኤ ላይ በመገኘቴ ታላቅ ክብር ይሰማኛል። ‎ ‎ “ከለውጥ ወደ ዘላቂ ሽግግር” በሚል መሪ ቃል እየተ
+3
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ‎“ኢትዮጵያ ታከናውናለች” በተሰኘው ብሔራዊ ጉባኤ ላይ በመገኘቴ ታላቅ ክብር ይሰማኛል። ‎ ‎ “ከለውጥ ወደ ዘላቂ ሽግግር” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ባለው ጉባኤ ላይ፣ በየደረጃው የተጓዝንበትንና አሁን የደረስንበትን መንገድ መለስ ብዬ እንድቃኘው አድርጎኛል። ሀገራችን በራሷ አቅም ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በመገንባት፣ ያልተሞከሩ ግዙፍ ልማቶችን በማከናወን በየጊዜው ወደ ላቀ ደረጃ እየተሸጋገረች ትገኛለች። እነዚህ ሁሉ በአጋጣሚ የተገኙ ድሎች ሳይሆኑ በመደመር መንፈስ ላይ ተመስርተው፣ ዘላቂ ለውጥ የሚመጣው በጋራ በመቆም ነው፤ በሚል ጽኑ እምነት የተወሰዱ፣ በቆራጥ ውሳኔዎች የተገኙ ውጤቶች ናቸው። ‎ ‎የጀመርናቸው ለውጦች በራሳቸው የመጨረሻ ግብ አይደሉም፤ ይልቁንም ከእኛ በኋላ ለሚመጡት ተከታታይ ትውልዶች የምንጥለው ጠንካራ መሠረት ነው። ‎ሀገርን መገንባት በአንድ ትውልድ ብቻ የሚያበቃ ሳይሆን የሁላችንም የጋራና ቀጣይነት ያለው ሥራ በመሆኑ፤ በዚህ ጽኑ እምነት እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ይህንን መንፈስ ይዞ ወደፊት እንዲጓዝ፣ የተቀበለውን ወረት አግዝፎ ይበልጥ ወደ ላቀ ከፍታ እንዲያመራ ጥሪዬን አቀርባለሁ!"

በአገልግሎት ማዘመን እና በስታንዳርድ ትግበራ የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ከተሞች እውቅና ተሰጠ አዳማ፣ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ/ም(ከመልሚ) በከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የከተማ አመራር፣ ፋይና
+9
በአገልግሎት ማዘመን እና በስታንዳርድ ትግበራ የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ከተሞች እውቅና ተሰጠ አዳማ፣ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ/ም(ከመልሚ) በከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የከተማ አመራር፣ ፋይናንስ አገልግሎት መሪ ሥራ አስፈፃሚ የመዘጋጃቤታዊ አገልግሎት ስታንዳርዳይዜሽንና ማዘመን ዴስክ በ2018 በጀት አመት የመዘጋጃቤታዊ አገልግሎት አፈጻጸም መሰረት በማድረግ የእውቅና ፕሮግራም አካሄዷል። በመድረኩ ኦሮሚያ፣ አማራ፣ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጰያ፣ ሲዳማ እና ደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች ተሳትፈዋል። የእውቅና መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት በከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የከተማ አመራር፣ ፋይናንስ አገልግሎት መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደሳለኝ ገመቹ እንደተናገሩት ከተሞች የፓለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ የእድገት ማዕከላት እንደመሆናቸው መጠን ከጊዜ ወደ ጊዜ የህዝብ ቁጥር በመጨመሩ ምክንያት በርካታ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ይነሳሉ። የህዝቡን ጥያቄ ለመመለስ አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን እና ስታንዳርድን ተግባራዊ በማድረግ ረገድ የአመራሩ ቁርጠኝነት የማይተካ ሚና አለው ብለዋል። እንዲሁም ስታንዳርድን ተግባራዊ ካደረጉ ከተሞች ልምድ በመውሰድ አገልግሎትን በማዘመን በቀጣይ 2019 በጀት ዓመት አገልግሎት አሰጣጥን በኦንላይን ለማድረግ እንሰራለን ብለዋል። በዕለቱ የአፈጻጸም ምዘና ግብረ መልስ ሪፓርት  የምዘና ምንነት፣ የአገልግሎት አቅርቦት አፈጻጸም ምዘና ዝንባሌ፣ የአገልግሎት አፈጻጸም ጠቋሚዎች፣ የ2018 የአፈፃፀም ምዘና ማሳያዎች፣ የተስተዋሉ ጥንካሬዎች እና ድክመቶች እና የምዘና ውጤት የሚሉ  ነጥቦች በዝርዝር ቀርበዋል። በመጨረሻም የላቀ አፈጻጸም ላሳዩ ከተሞች እውቅና ተሰጥቷል።

የዘርፉ የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በማኔጅመንት አካላት ተገመገመ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 15/ 2018 ዓ.ም፣ (ከመልሚ) የከተማና መሠረተ-ልማት ሚኒስቴር የማኔጅመንት አካላት የዘርፉ
+9
የዘርፉ የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በማኔጅመንት አካላት ተገመገመ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 15/ 2018 ዓ.ም፣ (ከመልሚ) የከተማና መሠረተ-ልማት ሚኒስቴር የማኔጅመንት አካላት የዘርፉን አጠቃላይ የ2018 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ገመገሙ፡፡ ክብርት ሚኒስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ የመሩትና ክቡራን ሚኒስትር ዴኤታዎችና ሁሉም የስራ ክፍል ኃላፊዎች የተሳተፉበት የማኔጅመንት አካላት የግምገማ መድረክ  ተካሄዷል፡፡ በስድስት ስትራቴጂክ ግቦች ላይ ትኩረቱን አድርጎ የተዘጋጀውና የተጠቃለለው የዘርፉ የበጀት ዓመቱ የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚው በአቶ አብርሃም ዘነበ ከቀረበ በኋላ በተደረገ የጋራ ውይይት በዕቅዱ ሊካተቱ ይገባቸዋል በተባሉ ጉዳዮችና የግልጽነት ማብራሪያ በተጠየቀባቸው ጉዳዮች ላይ ሀሳብና አስተያየቶች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡ በመጨረሻም ከመድረክ በተሰጠ የማጠቃለያ አስተያየት አጠቃላይ በሪፖርቱ የቀረቡ ሀሳቦች በሀገራችን ከተሞች እየተከናወኑ ያሉ የከተማ ልማትና የኮንስትራክሽን ስራዎችን አፈጻጸም በትክክል የገመገመ መሆኑ ተነስቷል፡፡ በቀጣይ የሚዘጋጀው ዕቅድም ዘመኑ የከተሞች ዘመን መሆኑን የከተሞችን አጠቃላይ ገጽታና ዕድገት በማየት ብቻ መመስከር የሚቻል በመሆኑ በዚያው ልክ ያደገ መሆን እንዳለበት የገለጹት ክብርት ሚኒስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ የተጀመሩ የኮሪደር ልማትና የስራ ዕድል ፈጠራ ስራዎች፣ የአረንጓዴ አሻራ፣ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ፣ የደቀቁ አካባቢዎችን መልሶ የማልማትና የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ስራዎችን የማዘመን ስራ ትኩረት ተሰጥቷቸው በስፋት መሰራት እንዳለባቸው አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ‎ '‘ዲጂታል ለልህቀት'’ በሚል ስያሜ በተዘጋጀው ጉባኤ ላይ፣ በተለያዩ ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን በአንድ መድረክ የሚያጣምረውን፣ በአፍሪካ ቀ
+8
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ‎ '‘ዲጂታል ለልህቀት'’ በሚል ስያሜ በተዘጋጀው ጉባኤ ላይ፣ በተለያዩ ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን በአንድ መድረክ የሚያጣምረውን፣ በአፍሪካ ቀዳሚ የተቀናጀ የዲጂታል አገልግሎት መተግበሪያ ዛሬ በይፋ መርቀናል። ‎ ‎ ይህ ታላቅ ስኬት ለሀገራችን ከፍተኛ ኩራት ከመሆኑም በላይ በቴክኖሎጂ የሚመራ እና  ዓላማ ተኮር ኢንቨስትመንት ምን ሊያስገኝ እንደሚችል ማረጋገጫ ነው። የኢኮኖሚ ወሳኝ መሠረተ ልማት የሆነው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፤ የዜጎችን ጊዜ ይቆጥባል፣ የሙስና ቀዳዳዎችን ይደፍናል፣ እንዲሁም በመንግሥት በኩል የተቋማትን ታማኝነትና ጥንካሬ ያጎለብታል። ‎ ‎ከሁሉም በላይ የኢትዮጵያ ትልሞች ተራ ምኞት ሳይሆኑ፣ በራሳችን እጆችና አቅም የምንገነባቸው እውነታዎች መሆናቸውን በግልጽ የሚያሳይ ምስክር ነው። ይህን ስኬት እንድናጠናክር፣ ተሞክሯችንን ለአፍሪካውያን ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን እንድናካፍል፣ እንዲሁም ከዚህ የበለጠ ውጤት ለማስመዝገብ በቁርጠኝነት እንድንጓዝ ጥሪዬን አቀርባለሁ!"

በ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ሂደት ስኬት እና ድህረ-ምርጫ ተግባራት ላይ ውይይት ተካሄደ አዲስ አበባ ሰኔ 10/2018 ዓ.ም(ከመልሚ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር አመራር እና ሰራተኞች በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሂደት፣ ስኬት እና ድህረ-ምርጫ ተግባራት ላይ ውይይት አካሂደዋል። ውይይቱን በንግግር ያስጀመሩት የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒሰትር ዲኤታ ክቡር አቶ ፈንታ ደጀን እንደተናገሩት በስኬት የተጠናቀቀው ሀገራዊ ምርጫው ነጻ ፍትሐዊ እና ሠላማዊ መሆኑ መንግስትና ፈጻሚው አካል የነበራቸውን አበርክቶ ላይ ለመምከር የተዘጋጀ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል። በምርጫ ሂደት መንግስት ከተመሠረተ በኋላ ደግሞ የጋራ ሀገርን ለመገንባት ብርቱ ትብብር ከመላው ሕዝብ እንደሚጠበቅ ክቡር አቶ ፈንታ ገልጸዋል። የሃሳብና የፖለቲካ ልዩነቶች ቢኖሩም ሀገርንና ብሄራዊ ጥቅምን በማስከበር ረገድ በጋራና በትብብር ለአንድ ሀገራዊ አላማ መቆም እንደሚያስፈልግም ደግሞ የገለፁት የውይይት ሰነድ ያቀረቡት ክቡር ሚኒስትር ደኤታ የትምጌታ አስራት (ዶ/ር) ናቸው። ምርጫ በባህሪው የውድድር እና የፉክክር ጉዳይ ቢሆንም ለአንድ ሀገር ግንባታ እስከሆነ ድረስ ወደ ትብብር መቀየር ይገባል፡፡ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እና ተጠሪ ተቋማት ምርጫው የተሳካ እንዲሆር በርካታ ስራዎች እንደተሰሩም ክቡር ሚኒስትር ደኤታ ገልጸዋል፡፡ የድህረ ምርጫ ተግባራትን በውጤታማነት በማከናወን ጠንካራ ስርዓተ መንግስት የመገንባት ሀገራዊ ግብን ማሳካት ዓላማ ያደረገ ውይይት እንደሆነና የጋራ ግንዛቤ መፍጠር፣ ህገ ወጥ ድርጊቶችን መከላከል እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል ፡፡ በመጨረሻም የመወያያ ሰነዱን አስመልክቶ የተለያዩ አስተያየቶች እና ጥያቄዎች ተነስተው ክቡር አቶ ፈንታ  ደጀን ምላሽ እና የቀጣይ አቅጣጫ ሰጥተዋል፡፡

የሚሰራ እጅ፣ የሚናገር አፍ፣ የሚያስብ አእምሮ ሲሰናሰሉ ነው ልማት እና ለውጥ የሚመጣው።

የክረምቱ ወቅት ሲደርስ፣ እኛም ለወገኖቻችን የምንዘረጋው የደግነት እጅ አብሮ ይጀግናል! ‎በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን፣ ጎሮ ወረዳ የዘንድሮውን የክረምት የበጎ ፈቃድ ዘመቻ ዛሬ በይፋ አስጀምረናል። የገ
+9
የክረምቱ ወቅት ሲደርስ፣ እኛም ለወገኖቻችን የምንዘረጋው የደግነት እጅ አብሮ ይጀግናል! ‎በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን፣ ጎሮ ወረዳ የዘንድሮውን የክረምት የበጎ ፈቃድ ዘመቻ ዛሬ በይፋ አስጀምረናል። የገጠር ኮሪደር ልማት መርሃ-ግብራችን አካል በሆነው ዲዛይን መሠረት 20 ቤቶች በአካባቢው ይገነባሉ። ‎ ‎ሀገራችንን በጋራ ማንሳት የምንችለው አንዳችን ለሌላችን እጃችንን ስንዘረጋ ብቻ ነው! ስለሆነም እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በዚህ ሥራ እንዲሳተፍ ጥሪዬን አቀርባለሁ።

በኢትዮጵያ በበርካታ ከተሞች ዕውን እየሆነ ያለው የፕሪፋብ ቴክኖሎጂ የቤት ግንባታ ጥበብ ዱከም፣ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ/ም (ከመልሚ) ለሰው ልጆች መሠረታዊ ፍላጎቶች ከሆኑት ከምግብና አልባሳት ቀጥሎ መጠለያ አንዱ ነው፡፡ መንግስት መሠረታዊ ፍላጎት የሆነውን የቤት ልማት አቅርቦትን ለማሳደግ በርካታ የቤት ልማት አማራጮችና ቴክኖሎጂዎችን ለማላመድ ዘርፈ-ብዙ ስራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ ከእነዚህ ስራዎች መካከል አንዱ የሆነውን የፕሪፋብ ቴክኖሎጂ የቤት ልማት ግንባታን ማፋጠን ደግሞ የተፈለገውን ውጤት ለማምጣት ያስችላል፡፡ ይህም ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ ለመጣው የህብረተሰብ ክፍል የመኖሪያ ቤት አቅርቦትን ለማሻሻል በአጭር ጊዜ ተመርተው የሚገጣጠሙ ቤቶችን መስራት ተገቢ ነው፡፡ በእነዚህ የተገጣጣሚ የህንጻ አካላት የሚገነቡ ቤቶች የሀገር ውስጥ ግብአቶችን በብዛት የሚጠቀሙ፤ ብክነትንና ብክለትን የሚከላከሉ፤ ወጪ ቆጣቢ እና የዜጎችን የመክፈል አቅም ያገናዘቡ ከመሆናቸው ባሻገር ባለሙያዎችን በአጭር ጊዜ አሰልጥኖ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ መሆናቸው ተመራጭ ያደርጋቸዋል፡፡ ከእነዚህ የመፍትሄ አማራጮች አንዱ ደግሞ የፕሪፋብ ቴክኖሎጂ ነው፡፡ ከዚህ አንጻር በከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የኮንስትክሽን ኢንዱስትሪ ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ያዘጋጀውና በዱከም ከተማ መግቢያ ላይ በፕሪፋብ ቴክኖሎጂ የተገነባው 48 የመማሪያ ክፍሎች ያሉት የቤት ግንባታ ለዚህ ማሳያ ነው፡፡ በቅርቡ በኢትዮጵያ በተለያዩ ከተሞች የተገነባውን የኮሪደር ልማት ተከትሎ የገጠሩን ነዋሪ የኑሮ ዘይቤ ለማሻሻል እየተሰሩ ካሉ ስራዎች መካከል አንዱ በሆነው የገጠር ኮሪደር እየተተገበረ ያለው የፕሪፋበ ቴክኖሎጂ የቤት አሠራር ጥበብ በይበልጥ ከታወቁት በብረት፣ በሲሚንቶ እና በብሎኬት ከሚገነቡ ቤቶች በተለየ በቃጫ፣ በጠጠር፣ በአሸዋ እና በሲሚንቶ ብቻ ተመርቶ የሚገነባው ቤት በቀላሉ ተመርቶ አገልግሎት ላይ ለማዋል የሚቻልበትን ዘዴ ያስተዋወቀ ነው፡፡ ቴክኖሎጂውን ወደ ኢትዮጵያ በማምጣት ያላመዱት ኢንጂ.ብርሃኑ ካሣ በጉብኝቱ ሂደት እንደገለጹት ከዛሬ 8 ዓመት በፊት የባለቤትነት መብት ዕውቅና ያገኘው የፕሪፋብ ቴክኖሎጂ በአሁኑ ሰዓት ስታንዳርድ ወጥቶለት በሀገራችን ከተሞችና የገጠር ቀበሌዎች በስፋት እየተተገበረ በመሆኑ የቴክኒክና ሙያ ተማሪዎችን ለማሰልጠን ካሪኩለም ተቀርጾለት ቴክኖሎጂውን በስፋት መጠቀም የሚቻልበትን ዕድል ለማስፋት ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የጉብኝቱ ተሳታፊዎች ቴክኖሎጂው በተግባር ተፈትኖ በስፋት እየተሰራበት ያለ በመሆኑ ባዩት ነገር መደሰታቸውን ገልጸው ቴክኖሎጂው እያደገ የሚሄድ በመሆኑ ጅምሩ መስፋት እንዳለበትና በየጊዜው ማሻሻያዎች ሊደረጉበት እንደሚገባ፤ የህንጻ አካሉ የሚመረትበት የተለየ የማምረቻ ቦታ ቢኖረው፤ የላቦራቶሪ ፍተሻ የሚረጋገጥበት ሁኔታ ቢፈጠር፤ የገበያ ትስስር ቢኖር፤ በጋራ አብሮ ለመስራት የሚቻልበት ዕድል ቢፈጠር እና በዘርፉ ከተቋቋሙ ማህበራት ጋር ተቀናጅቶ ለመስራት የሚያስችሉ ሁኔታዎች ቢመቻቹ የሚሉ ምክረ-ሀሳቦችን ለግሰዋል፡፡