471
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+47 روز
+1230 روز
آرشیو پست ها
የግንዛቤ ማስጨበጫ
አማራ ባንክ የማን ነው?
አማራ ባንክ ፕሮጀክት መዘጋጀት ከጀመረበት መስከረም 2011 ዓ.ም ጀምሮ ባንኩ ዕውን ሆኖ ማየት የሚፈልገው ህዝብ ለአሃዝ የሚያታክት ነው።
የቢዝነስ ሃሳቡን በማፍለቅ እና የባንኩን የቢዝነስ ሞዴል ከመቅረፅ ጀምሮ፥ስያሜውን መወሰን፥ ስሙን ማስመዝገብ፥ ለአክሲዮን ሽያጭ ማስፈቀድ፥ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ማደራጀትና በቀን ከአንድ ሽህ በላይ የአክሲዮን ገዥዎችን የስልክ ጥሪ በማስተናገድ.. ያለምንም ክፍያ ታሪካዊ ተግባር ያበረከቱት የአማራ ባንክ ፕሮጀክት አስተባባሪዎች ወደር የሌለው አስተዋጽኦ እንዳለ ሆኖ፥ የህዝቡ ተሳትፎ እና ጉጉት ግን የተለዬ ነው።
የአማራ ባንክ ፕሮጀክት አስተባባሪዎች(Promoters ) ከተለያዩ የሙያ መሥክ እና ከሁሉም አካባቢዎች በአላማው የተሰባሰቡ፥ በልህቀ ምጣኔ ሃብት ላይ ተፅኗዊ ለውጥ ( IMPACT) ለማምጣት ወስነው የተነሱ ሙሁራን ናቸው።
የባንኩ መሥራቾችስ እነማን ናቸው? (Founders)
የባለቤትነት ጥያቄ ነው!!
በርካታ ሰዎች በፊት ለፊት፥ በመልዕክት ወይም በስልክ የሚጠይቁት ጥያቄ፦
“አማራ ባንክ የማን ነው?” የሚል ነው። ከፖለቲካና ከፖለቲከኞች ነፃ ስለመሆኑ ይጠይቃሉ።
ለመሆኑ አክሲዮን ገዝተዋል?
መልስዎ “አዎ” ከሆነ፥ እርስዎም በገዙት የክሲዮን መጠን ልክ ባለቤት ነዎት!!!
በገዙት የአክሲዮን መጠን ድምፅ በመሥጠት፥ የባንኩን ዋና የበላይ አመራር አካላት(ቦርድ) የመምረጥ፥ የመመረጥና የመሻር መብት አለዎት።
ምሳሌ፦ የ 10,000 ብር(አስር እጣ) አክሲዮን የገዛ ግለሰብ/ድርጅት 10(አስር) ድምፅ አለው ማለት ነው።
በአማራ ባንክ አንድ እጣ 1000 ብር ነው። ይህ እጣ(ድምፅ) በጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጊዜ ቦርድ አባላትን ለመምረጥ፥ የትርፍ ድርሻ ለመካፈልና ለተለያዩ ውሳኔዎች የምንጠቀምበት አይነተኛ መሳሪያ ይሆናል።
ባንኩ የትርፍ ክፍፍል ሲያደርግ፥ እርስዎም በገዙት የአክሲዮን መጠን ተሰልቶ፥ የትርፍ ድርሻ የመውሰድ ጥቅምዎ የተጠበቀ ነው።
ተጨማሪ አክሲዮን ለገበያ ቢቀርብ፥ የባንኩ መሥራች እንደመሆንዎ መጠን፥ ሸር የመግዛት ዕድልዎ ባለዎት የአክሲዮን ድርሻ መጠን ይወሰናል።
የገዙት አክሲዮን ድርሻ መጠን፦ ድምፅዎ፤ የውሳኔ ጉልበትዎ፥ የትርፍ መጠን መለኪያ፥እና የባለቤትነት ማረጋገጫ ካርድዎ ነው።
እስከአሁን አክሲዮን ካልገዙስ?
ባለቤት መሆን የሚችለው ማን ነው?
ማንኛውም ኢትዮጵያዊ የሆነ ግለሰብ(ህፃናትን ጨምሮ) ወይም ህጋዊ ድርጅት አክሲዮን በመግዛት የአማራ ባንክ ባለድርሻ(ባለቤት) መሆን ይችላል። ነጋዴ፥ ተማሪ፥ ሾፌር፥ ፖለቲከኛ፣የባንክ ሰራተኛ፥ ወታደር፥ ቤተ ዕምነት፣ ህጋዊ ማህበራት፥ NGO, የመንግስት ድርጅቶች፣ ......አክሲዮን በመግዛት፥ ባለድርሻ (ባለቤት)መሆን ይችላል።
አማራ ባንክ ባለቤትነቱ የህዝብ ነው። ለዚህም ነው ማንኛውም ግለሰብ አቅሙ በሚፈቅድለት ልክ የአክሲዮን ድርሻ በመግዛት ባለቤት እንዲሆን በጊዜ ገደብ ተወስኖ ሽያጬ ለህዝብ የቀረበው።
ከጥልቁ የቢዝነስ ፍልስፍና እይታ አንፃር ደግሞ፥ ደንበኛ፥የባንኩ ሰራተኞች፥ከባንኩ ጋር ማንኛውም የቢዝነስ ዝምድና ያለው አካል ሁሉ ባለቤት ነው። ስለሆነም፥ በተለያዬ አጋጣሚ አክሲዮን ያልገዙ ግለሰቦች ከባንኩ ጋር በመሥራትና አገልግሎቱን በማግኘት ጥብቅ ዝምድና መፍጠር ይችላሉ።
በጥቅሉ፥ በንግድ ህጉ የተፈቀደውን፥ የብሄራዊ ባንክ ደንብ በሚያዝዘው መሠረት እና ወደፊት በጠቅላላ ጉባኤው የሚወሰነውን ማንኛውም የመሥራችነት ጥቅማ ጥቅም በማግኘት፥ የባለቤት መብትዎ ይረጋገጣል።
የቦርድ አመራርና በተዋረድ የሚደራጀው ዋና ስራ አስፈፃሚ አካላት ምርጫ!!
ዋናው ጥያቄ፥ የባለቤት ብቻ ሳይሆን የአመራሩ ብቃትና ሚዛናዊ ስብጥር ስለሆነ፥ በዘርፉ ጥርሱንና ጥፍሩን የነቀለ፥ የፀጉሩን ከለርም በዚሁ ስራ ላይ እንዳለ የቀየረ፥ “ጥይት የማይበሳው” (Bullet Proofed) ሆኖ የአዞ ቆዳ የለበሰ የባለሙያ ስብስብ መሆን እንዲኖርበት ሁላችንም ሃላፊነት ሊኖረን ይገባል።
የባንክ ስራ አለማቀፋዊ ነው። ወደፊትም ቴክኖሎጅ የበለጠ ያቀራርበዋል። ስለሆነም በውጭ ሃገራት ባሉ ባንኮች ልምድ ያላቸው የፋይናንስና ቴክኖሎጅ ኤክስፐርቶች በባትሪ ተፈልገው ቤታቸውን አማራ ባንክ ግቢ ውስጥ መገንባት አለባቸው።
ሌላው የትምህርት ዝግጅት(Educational Background) ነው።
እያንዳንዱ የቦርድ አመራር አባላት በተለያየ የትምህርት ዝግጅት የበቁና ሚዛናዊ ስብጥሩን የጠበቀ፥ አብረው እንዲሰሩ የሚያስችል፥ የመደጋገፍና ክፍተት የመሙላት ባህሪና ባህል ኖሯቸው፥ ብቃት ያለው የጋራ ውሳኔ የሚያስተላልፉ ሊሆኑ ይገባል።
ማሳሰቢያ!
አማራ ባንክ የስራ ማስታወቂያ አላወጣም።
አክሲዮን ሽያጭ እንደቀጠለ ነው።
አክሲዮን ለመግዛትም ሆነ ለመመሥረት የታደሠ መታወቂያ ወይም የመንጃ ፈቃድ ወይም ፓስፖርት ያስፈልጋል።
በውክልና መግዛት ይቻላል።
ለህፃናት መግዛት ይቻላል።
በቅርቡ ባንኩን ለመመሥረት የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ሲተላለፍ፥ አክሲዮን የገዙት ሁሉ በአካል ወይም በወኪል መገኘት አለባቸው።
የመሥራችነት ቀነ ገደቡ ሳያልቅ ድጋሜ መግዛት ይቻላል።
የግዢ ሂደቱን ውክልናው ከተሰጣቸው 10 ባንኮች በአንደኛው ቅርንጫፍ በመቅረብ መጨረስ ይቻላል።
መልካም የስራ ቀን ይሁንላችሁ!
ሌላ የምስራች!
የአማራ ምጣኔ ሃብት አብዮተኛ ቡድን ሁለተኛውን ፕሮጀክት አጥንቶ አክሲን ለመሸጥ ዝግጅቱን አጠናቀቀ።
አማራ ሜዲካል አ.ማ
(በምስረታ ላይ ያለ)
1) የአደራጅ ኮሚቴው መልዕክት፦
እንደሌሎች የሳይንስና የምርምር ዘርፎች ሁሉ የህክምና ጥበብ በየጊዜው የሰፋና የጠለቀ : ቀደም ባሉት ዘመናት ሊታሰቡ የማይችሉ : ተአምራዊ እድገቶች እያሳየ ባለበት በአሁኑ ዘመን በቢሊዮን ሚቆጠሩ በተለይም የታዳጊ ሀገር ዜጎች በመሰረታዊ የጤና መረጃና አገልግሎት መጏደል ምክንያት ለስቃይ :ለአካል ጉዳት እና ለሞት ተጋልጠው ይገኛሉ:: ጤና ለአንድ ሀገር እድገት መሰረታዊ ከሆኑት የልማት ዘርፎች አንዱ እንደመሆኑ : የተሻለ የጤና ስርአት ማደራጀትና የዜጎችን የጤና ሁኔታ ማበልፀግ የሚቻለው የየሀገሩ መንግስት: የአለም አቀፍ ልማት ተባባሪወች : ዜጎች: የሲቪል ማህበረሰቡ:የጤና ባለሙያው: የግሉ ክፍለ ኢኮኖሚ እና ሌሎችም አግባብነት ያላቸው አካላት በሚያደርጉት የተቀዳጀ የጋራ ጥረት ነው::
የኢትዮጵያ ጤና ፖሊሲ ከዚህ መርህ በመነሳት የግሉ ክፍለ ኢኮኖሚን ጨምሮ ለበርካታ ባለድርሻ አካላት እውቅና ይሰጣል::
አማራ ሜዲካል አክሲዮን ማህበር የጤና ፖሊሲው ለግሉ ሴክተር አስተዋፅኦ የሚሰጠውን ድርሻና ሀላፊነት በተገነዘቡና በዘርፋ የተለያየና ሰፊ ልምድ ያላቸው ባለሙያወች የሚያደራጁት ተቋም ነው::
የተቋሙ መሰረታዊ አላማወች ጥራት ያለውና በህክምና ስነ-ምግባር የሚገዛ የጤና ጥበቃና የህክምና አገልግሎት: ተመጣጣኝ በሆነ ክፍያ ማቅረብ ነው:: እነዚህ አላማወች ከምኞት አልፈው ወደ ተግባር የሚሸጋገሩበትን መንገድ ለማጥናት እና ለማቀድ አደራጅ ኮምቴው ለበርካታ ወራት በጋራ ሲሰራ ኑሯል::
አሰራራችን ሁልጊዜም በመረጃ ላይ የተመሰረተ ፥ተለዋዋጭ ሁኔታወችን ያገናዘበና አሳታፊ ስለሚሆን እቅዶቻችንም እየሰራን የምንማርባቸው አገልጋዮቻችን ናቸው:: በመንግስትና በግል: በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ ካሉ የህክምና ተቋማት መልካም ተሞክሮወችን ሁሌም እንማራለን።
በአደራጅ ኮሚቴው እምነት የጤና አገልግሎቶች ጥራትና መሻሻል መጀመሪያ እንጂ መጨረሻ የለውም:: ስለዚህም እቅዶቻችን ስራው እስኪጀመርም ሆነ ከተጀመረ በሗላ ይሻሻላሉ ፥ ይከለሳሉ::
የአማራ ሜዲካል አ.ማ የሀገሪቱን የጤና ፖሊሲ መሰረት ያረገ፥ የተገልጋዩን ህብረተሰብ እንዲሁም የጤና ሙያተኛውን ፍላጎት ተረድቶ ፥ለነዚህም ፍላጎቶች መሟላት የበኩሉን አስተዋፅኦ ለማድረግ የተደራጀ ተቋም ነው:: የአደራጅ ኮሚቴው አባላት አማራ ሜዲካል አ.ማ ሁሉም " የኔ ነው" የሚለው አገልጋይ እንዲሆን ተግተን የምንሰራ መሆኑን ያረጋገጥን፥ አግባብ ያላቸው የመንግስት አካላት ፥ ተገልጋዩ ማህበረሰብ፥ በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ የምትኖሩ ኢትዮጵያዊያን የጤና ሙያተኞች፥ የግል የጤና ተቋማት፥ የልማትና የበጎ አድራጎት ድርጂቶች እንዲሁም ሌሎች ግለሰቦችና ተቋማት ለድርጂቱ ምስረታና እድገት ለምታደርጉት ድጋፍ የከበረ ምስጋናችን ከወዲሁ እናቀርባለን::
2) ስለ አክሲዮን ሽያጭ አጭር መግለጫ፦
250,000 የተመዘገቡ መደበኛ አክሲዮኖችን ለመሸጥ፥ ዝርዝሩ እንደሚከተለው ቀርቧል::
⁃ አንድ አክሲዮን መደበኛ ዋጋ - 1000 ብር
⁃ የሚከፈለው የአገልግሎት ክፍያ-
5%
⁃ የአክሲዮን ግዢ የአከፋፈል ሁኔታ፦
አማራጭ ሀ)፦ መግዛት የሚፈልጉትን አክሲዮን መጠን 100%በመክፈል፥
አማራጭ ለ)፦50% ክፍያ በግዢ ወቅት የሚፈፀም ሆኖ፥ቀሪ 50% በስድስት ወር ውስጥ ከፍሎ ማጠናቀቅ።
⁃ የሚፈቀደው ዝቅተኛ የኢንቨስትመንት መጠን - 10 አክሲዮን(10,000 ብር)
⁃ የሚፈቀደው ከፍተኛ የኢንቨስትመንት መጠን- 12, 500
(12,500,000 ብር)
⁃ ሽያጭ የሚጀምርበት ቀን- ህዳር 19 ቀን 2012 ዓ.ም
⁃ ሽያጭ የሚያበቃበት ቀን - የካቲት 16 ቀን 2012 ዓ.ም
3) የባንክ ሂሳብ ቁጥሮች፦
- የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ዝግ ሂሳብ ቁጥር- 1000305684663
የአገልግሎት ክፍያ -1000305685128
የአቢሲኒያ ባንክ :
ዝግ ሂሳብ ቁጥር- 21445673
የአገልግሎት ክፍያ - 21445908
የዳሽን ባንክ :
ዝግ ሂሳብ ቁጥር- 5079154404011
የአገልግሎት ክፍያ - 5079154404021
የአባይ ባንክ :
ዝግ ሂሳብ ቁጥር- 201 1111019711013
የአገልግሎትክፍያ-2012111019711028
4) የድርጅቱ ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት አድራሻ:
ፖፒረስ ሆቴል ፊትለፊት፦
ሲግናል ሞል፥አራተኛ ፎቅ፥
ባህር ዳር
የስልክ አድራሻዎች፦
-+251941466607
-+251900780225
-+251904390018
- +251927594284
- +251946431020
- +251902593359
አማራ ሜዲካል አ.ማ
የግርጌ ማስታወሻ!
1) Amhara Real Estate S.C
2) Amhara Hotel Service
3) Amhara Insurance
4) Amhara Transport and
Aviation Service
5) Amhara Investment
Investment Consulting
and 5 more others!
የሁሉም ፕሮጀክቶች ምዝገባ ያለቀና ጥናቶች እየተካሄደ ይገኛል።
ሁሉም ተራ በተራ ወደ መሬት ይወርዳሉ።
ገፃችንን ይወዳጁት፤ ይከተሉት፤ ያጋሩት!!
የአማራ ባንክ አክሲዮን ሽያጭ መጨረሻ ቀናት ላይ ነው!!!
የመስራችነት እድል የሚፈቅደው የአማራ ባንክ አክሲዮን ሽያጭ ሊያበቃ ጥቂት ቀናት ቀርተዋል።
አክሲዮኖች በፍጥነት እየተሸጡ ይገኛሉ። ከ23,000 ግለሰቦች እና ድርጅቶች ፥ ከ900 ሚሊዮን ብር በላይ የተከፈለ ሸር፥ከአማራ ባንክ ገዝተው የባንኩን ምስረታ(የጠቅላ ጉባኤ ስብሰባ )በመጠባበቅ ይገኛሉ።
አያሌ ግለሰቦችም ለሁለተኛ ጊዜ ተጨማሪ አክሲዮኖችን በመግዛት የተሰጣቸውን ጊዜ በአግባቡ ተጠቅመውበታል።
የተፈረመው ገንዘብ(ቃል ከተገባው) 2 ቢሊዮን ብር ካፒታል ውስጥ፥ ከብር 1.3 ቢሊየን በላይ አልፏል። ይህ የሚያሳየው፥ አማራ ባንክ ለሽያጭ ያቀረበው ጠቅላላ አክሲዮን በቅርብ ቀን ሊያልቅ እንደሚችል ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ፥ ከስልክ ጥሪዎችና ጥያቄዎች እንደተረዳነው፥ በርካታ ሰዎች አክሲዮን እንዳልገዙ ነው።
ይህ እንዳለ ሆኖ፥ የመስራችነት ዕድል የሚሰጠው የአክሲዮን ሽያጭ ጊዜ ገደብ ለመጠናቀቅ የቀሩት ጊዜያት ከሶስት ሳምንታት ያነሰ ስለሆነ(በዕቅድ ደረጃ እስከ ህዳር 30)፥ በዚህ ጊዜ ውስጥ ፈጥኖ መግዛትና የአማራ ባንክ መሥራች፣ ባለድርሻ እና ባለአሻራ መሆን ይቻላል።
ተጨማሪ ሸር መግዛት ለሚፈልጉም ከዚህ በፊት በገዙበት አግባብ፥ ፎርሙን እንደ አዲስ በመሙላት መጨመር ይችላሉ።
ለልጆች፥ ለጓደኛ፣ ለባል/ ሚስት ወዘተ በመግዛት ወዳጅዎን መሥራች ማድረግ እና ለገና ስጦታ በማበርከት ቋሚ ትውስታ ያስቀምጡ።
ዲያስፖራ (ትውልደ ኢትዮጵያዊ ሆነው የውጭ አገር ዜግነት ያላቸው) መግዛት የሚችሉት ተቀባይነት ባለው በውጭ ሃገር ገንዘብ ብቻ ቢሆንም ፥ ገንዘቡን እና ተዛማች ሰነዶችን እንዴት መላክ እንዳለባቸው ከብሄራዊ ባንክ ሙሉ እና ዝርዝር የአፈፃፀም ደንብና መመሪያ እንደደረሰን ይዘን እንቀርባለን። የአማራ ባንክ ምስረታ እንዲመሩ የተመረጡ ግለሰቦች፥ ጉዳዩን ትኩረት ሰጥተው በመከታተል ፥ ዲያስፖራው አክሲዮን ይገዛ ዘንድ ሂደቱን በማመመቻቸት እንደሚያቀላጥፉላቸው ይጠበቃል።
በተለያዩ ምክንያቶች ሃገር ውስጥ የሌሉ ኢትዮጵያዊያን ፥ ባሉበት ሃገር ሆነው፥ አቅራቢያቸው በሚገኘው የኢትዮጵያ ቆንፅላ ፅ/ቤት ቀርበው፥ ሃገር ቤት ለሚገኘው ታማኝ ወዳጃቸው ውክልና መስጠትና፥ የታደሰ የኢትዮጽያ ቀበሌ መታወቂያ /መንጃ ፈቃድ/EP Passport/ ኮፒ በመላክ፥ አክሲዮን ማስገዛት ይችላሉ።
ለተጨማሪ መረጃ ከዚህ በታች በተጠቀሱት የአማራ ባንክ አደራጅ ቁጥሮች በመደወል ማግኘት ይቻላል።
0911600388
0900780225
0941466607
0912001819
0911248160
0911133014
Amhara Economic Think Tank በመከተል(Follow)፥ በመዉደድ (Like) እና በማጋራት(Share) ለወዳጆዎ ትክክለኛና ወቅታዊ መረጃ እንዲደርሳቸው በማድረግ ከፍተኛ ሃላፊነት አለባችሁ።
አደራጅ ኮሚቴው ሌሎች ተመሣሣይ ፕሮጀክቶችን ቀርጾ ለምስረታ ዝግጅት ላይ ይገኛል።
አማራ ባንክ እስካሁን ድረስ ምንም አይነት የስራ ማስታወቂያ አላወጣም።
ሰላምና ክብር ለናንተ ይሁን!!
ከአማራ ባንክ አክሲዮን ለገዛችሁ፥
ከዚህ ጊዜ ጀምሮ የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ እስከሚካሄድ ድረስ፥ የግንዛቤ ማስጨበጫ ይሆናሉ ያልናቸውን የብሄራዊ ባንክ ዳሬክቲቭስ እና ተመሳሳይ መረጃዎች እንለጥፋለን።
በአንባቢያን ጥያቄ መሠረትም ተገቢና የተረጋገጡ መረጃዎችን ለመስጠት ዝግጁ ነን።
ለዛሬ ስለባንክ ኮርፖሬት አስተዳደር መሥፈርቶች የሚናገረውን መመሪያ እንዳለ ለጥፈናል። ወይም ቀጥሎ ያለውን ማስፈንጠሪያ ተከትላችሁ እንድታነቡት በአክብሮት ጋብዘናል።
https://www.nbe.gov.et/pdf/directives/bankingbusiness/Bank%20Corporate%20Government.pdf
https://www.nbe.gov.et/pdf/directives/bankingbusiness/thired%20amendment%20of%20bank%20opening.pdf
Amhara bank s.c
ሰላም ሰላም ቤተሰቦች እንዴት ናችሁ?
ሳምንቱስ እንዴት አለፈ?
መልካም እለተ ቅዳሜ ይሁንላችሁ!!!!
Amhara bank s.c
https://www.facebook.com/አማራ-ባንክ-አማAmahara-bank-sc-124827542252667/
Together We Can 💪💪💪
Amhara bank s.c
Don't forget Like, share &follow this page
https://www.facebook.com/አማራ-ባንክ-አማAmahara-bank-sc-124827542252667/
ክቡራን የአማራ ባንክ አክሲዮን ገዥዎች፦
የአማራ ባንክ አክሲዮን ማህበር የአክሲዮን ሽያጭ ዛሬም በፍጥነት እየተሸጠ ይገኛል።
እስካሁን ድረስ ከ2 ቢሊዮን የተፈቀደ ካፒታል ውስጥ፥
1,077,000,ዐዐዐ ብር የተፈረመና 725,000,000 የተከፈለ ገንዘብ
(Paid up Capital) ደርሷል።
የመሥራችነት አክሲዮን ሽያጭ ሂደቱም እንደቀጠለ ነው። እስካሁን አክሲዮን ያልገዙ ግለሰቦችም ይሁን ድርጅቶች የመሥራችነት ዕድሉ ከማለቁ በፊት በአቅራቢያቸው በሚገኙት ባንኮች በመሄድ ፈጥነው መግዛት ይችላሉ።
ከዚህ ቀደም አክሲዮን የገዙና አሁንም ተጨማሪ መግዛት የሚፈልጉ፥ እንደ አዲስ የአክሲዮን ግዥ ማመልከቻ ቅፁን በመሙላት መግዛት እንደሚችሉ ተገልጿል።
በፊት የገዙበትን እና አዲሱን ደረሰኞች በጥንቃቄ በመያዝ የሸር ምስክር ወረቀታቸውን በሁለቱ ድምር እንዲሰራላቸው ክትትል ማድረግ ተገቢ ነው።
ትውልደ ኢትዮጵያዊ የሆኑ የውጭ ሃገር ዜግነት ያላቸው ግለሰቦችም የባንክ አክሲዮኖች መግዛት እንደሚችሉ በነጋሪት ጋዜጣ ተገልጿል። በአማራ ባንክ በኩል፥ ዝርዝር አፈፃፀሙን ለማውጣት በዝግጅት ላይ ስለሆነ እንደጨረሰን ይፋዊ መግለጫ በቅርቡ እንሰጣለን።
የአማራ ባንክ አ.ማ በፈረንጆች 30 Nov. 2019 የጠቅላላ ባለአክሲዮኖች ጉባኤና ምስረታ ለማድረግ በዕቅድ አስቀምጦ በዝግጅት ላይ ነው።
ትክክለኛውን ቀን እና ቦታ በቅርቡ በዚሁ ገፅ እንገልፃለን ።
ስለባንኩ ተጨማሪ መረጃ ማዎቅ ለምትፈልጉ ሁሉ ፥ አደራጅና አስተባባሪ ኮሚቴዎችን በቀጥታ በመደወል ትክክለኛ መረጃ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን።
ስልክ ቁጥሮች:
0911600388
0900780225
0941466607
0911133014
0911248160
0912001819
ከአክብሮት ጋር
https://www.facebook.com/አማራ-ባንክ-አማAmahara-bank-sc-124827542252667/
ሪከርድ ሰባሪው ባንክ!
አማራ ባንክ ‼️❗️
✅ የተፈቀደ ካፒታል ብር 2,000,000,000.00 (ሁለት ቢሊየን ብር)፤
✅ እስካሁን የተፈረመ (subscribed) አክስዮን፦ ከብር 900,000,000.00 (ዘጠኝ መቶ ሚሊየን ብር) በላይ፤
✅ እስካሁን በጥሬ ገንዘብ የተከፈለ ካፒታል (paid up) አክስዮን፦ ከብር 700,000,000.00 (ሰባት መቶ ሚሊየን ብር) በላይ፤
✅ አክስዮኑ አሁንም በሽያጭ ላይ ይገኛል፣ ህዳር 30 ቀን ሽያጩ የሚዘጋበት ቀን ይሆናል።
✅ ሽያጩ በይፋ እስከሚዘጋበት ቀን ድረስ አክስዮን ለሚገዙ ባለአክስዮኖች፣ የመስራችነት መብት የተጠበቀ ነው፤ ከዚህ በፊት አክስዮን የገዙ ባለአክስዮኖች ድጋሜ መግዛት ይችላሉ።
✅ ትውልደ ኢትዮጵያውያን የውጭ ሀገር ዜጎች አክስዮን መግዛት የሚችሉት በውጭ ምንዛሬ ብቻ ነው።
✅ ትውልደ ኢትዮጵያውያን የውጭ ሀገር ዜጎች በትዕግስት እንድትጠብቁ ተጠይቃችኋል፣ የብሄራዊ ባንክ መመሪያ እንደወጣ ክፍያ የምትፈጽሙባቸው የውጭ ምንዛሬ የባንክ ሂሳቦች እና ማሟላት ያለባችሁ መመዘኛዎች ይለቀቃሉ።
የባንኩ አደራጆች የባንኩን ምስረታ የሚያበስረውን ጠቅላላ ጉባኤ ለማከናወን በዝግጅት ላይ ናቸው። ዝግጅታቸውን እንደጨረሱ የጠቅላላ ጉባኤውን ጥሪ በሚዲያ የሚያሳውቁ ይሆናል።
Amhara bank s.c
@amharabank
Don't forget like, share & follow this page
https://www.facebook.com/አማራ-ባንክ-አማAmahara-bank-sc-124827542252667/
እስከአሁን የአማራ ባንክ አክሲዮን ላልገዛችሁ በሙሉ፦
የአማራ ባንክ አ.ማ የአክሲዮን ሽያጭ በፍጥነት እየተሸጠ መሆኑ ይታወቃል። እነሆ ዛሬ ደግሞ ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ ደርሷል። ባንክ ለመመስረት የሚያስችለውን ዝቅተኛ የተከፈለ ገንዘብ ብር 500 ሚሊዮን ቢያሟላም፥ ለመሥራችነት ጊዜው የሚያበቃው ጠቅላላ ጉባኤው ተገናኝቶ እና ተፈራርሞ የመመሥረቻ ሰነዱ በውልና ማስረጃ እስኪፀድቅ ድረስ በመሆኑ የመሥራችነት መብት የሚፈቅደውን የአክሲዮን ሽያጭ ክንውን እንደሚቀጥል ታውቋል። ስለሆነም እስካሁን ድረስ የአማራ ባንክን አክሲዮኖች ያልገዛችሁ ግለሰቦችም ሆናችሁ ድርጅቶች ይህንን ለጥቂት ቀናት የተራዘመ ዕድል እንድትጠቀሙበት እና በመሥራችነት እንድትሳተፉ ስንል በአክብሮት እናበስራለን።
የጠቅላላ ጉባኤ ጥሪ እስኪተላለፍ እና የባንኩ መመሥረቻ ፅሁፍ በይፋ በሰነዶች ማረጋገጫ ተፈሮሞ እስኪፀድቅ ድረስ፥ አክሲዮን በመግዛት ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የመሥራችነት መብቱ እንደተጠበቀ ነው። ስለሆነም የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ በቅርቡ ስለሚጠራ እስከ ዛሬ ድረስ አክሲዮን ያልገዛችሁ በሙሉ ፈጥናችሁ በመግዛት የባንኩ መሥራች ለመሆን መልካም አጋጣሚ ነው።
መሥራች የመሆን ጥቅም በጠቅላላ ጉባኤው የሚወሰን ቢሆንም፥ ከፖለቲካ እና ከወገንተኝነት የፀዳ፣ ብሄራዊ ባንክ የሚጠይቀውን መስፈርት የሚያሟላ ብቁ እና ጠንካራ የአማራ ባንክ ቦርድ ብሎም አመራር የመምረጥ እና የመመረጥ መብት ያስገኛል።
የአማራ ባንክ አደራጅ ቡድን ከማንኛውም የፖለቲካ እና ወገንተኝነት ነፃ የሆነ በጋራ የሚሰራ ስብስብ በመሆኑ ባንኩም ብቃት ባላቸው ባለሙያዎች እንዲመራ ሳይታክት ይሰራል።
ባንኩን ለመመሥረት ከሚያስችለው የጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔ በኋላም፥ የተፈቀደ ብር 2 ቢሊየን እስኪሞላ ድረስ የባንኩ አክሲዮን ሽያጭ የሚቀጥል መሆኑን ከወዲሁ ለማስገንዘብ እንወዳለን።
ከአማራ ባንክ መመሥረት በኋላም፥ የአማራ ኢንሹራንስ ፕሮጀክት ሂደት እና ሌሎች 10(አስር) ፕሮጀክቶች ትግበራ በዚሁ ቡድን አስተባባሪነት ይቀጥላል።
ለተጨማሪ ግንዛቤ፦
1) የአንድ አክሲዮን ዋጋ ብር 1000 ( አንድ ሽህ ብር ) ሲሆን መግዛት የሚቻለው ዝቅተኛ የአክሲዮን ብዛት 10 (አስር) ወይም 10,000 ( አሰር ሽህ ) ብር ነው።
2) አንድ ግለሰብ ወይም ድርጅት መግዛት የሚችለው ከፍተኛ የአክሲዮን መጠን ብዛት 100,000 (አንድ መቶ ሽህ) ወይም 100,000,000 (መቶ ሚሊዮን ብር) ነው።
3) የአገልግሎት ክፍያው ቃል የተገባውን ጠቅላላ አክሲዮን መጠን 5% ነው፡፡
4) የአማራ ባንክ አክሲዮን ማህበር ባለቤት መሆን የሚፈልግ ግለሰብ/ ድርጅት፥ ከዚህ በታች በተራ ቁጥር 6 ስር ስማቸው በተገለፁት ባንኮች በኩል በመቅረብ የተዘጋጀውን የአክሲዮን ሽያጭ ማመልከቻ ቅፅ በሁለት ኮፒ መሙላትና የተጠየቁትን መረጃዎች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል፡፡
5) የሚገዙትን ጠቅላላ የአክሲዮን መጠን በዝግ ሂሳብ እና ቃል የገቡት የአክሲዮን መጠን 5% የአገልግሎት ክፍያ ደግሞ በተንቀሳቃሽ ሂሳብ ገቢ ይደረጋል።
6) አክሲዮን ግዢ የሚፈፀምባቸው ባንኮች ዝርዝር፦
6.1. አቢሲንያ ባንክ አ/ማ
6.2. አንበሳ ኢንተ. ባንክ አ.ማ.
6.3. ዳሽን ባንክ አ.ማ.
6.4. አዋሽ ኢንተ ባንክ አ.ማ.
6.5. ኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ
6.6. ህብረት ባንክ አ.ማ.
6.7. ንብ ኢንተ.ባንክ አ.ማ.
6.8. የኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
6.9. ቡና ኢንተ ባንክ አ.ማ፣
6.10. ዓባይ ባንክ አ/ማ ናቸው።
7). መሟላት የሚገባቸው መረጃዎች፦
ሀ) የታደሰ መታወቂያ/ ፓስፖርት/መንጃ ፈቃድ
ለ) በልጆች ስም ለመግዛት የሚፈልግ የልደት ካርድ እና የአባት/እናት/ ወይም የአሳዳጊ መታወቂያ
ሐ) በውክልና ከሆነ፦ ህጋዊ ወክልና፣ የተወካይ የታደሰ መታወቂያ/ፖስፖርት/መንጃ ፈቃድ፤ የወካይ መታወቂያ ኮፒውን..
መ) አክሲዮን ለሚገዙ ድርጅቶች/ ኩባንያዎች
የድርጅቱ የታደሰ ንግድ ፈቃድ/ የንግድ ምዝገባ/ ግብር ክፍያ መለያ ቁጥር
አክሲዮን ለመግዛት የሚያስችል ህጋዊ ውክልና
ማህበራትና እድሮች የተመሰረቱበትን የፈቃድ ሰርተፍኬት፤
8) የአክሲዮን ሸያጭ አከፋፈል በሁለት አማራጮች የቀረበ ሲሆን፤ ከቀረቡት አማራጮች በአንዱ ግዢ መፈፀም ይቻላል፡፡
አማራጭ-1. የአክሲዮን ግዥ ፎርም እንደተሞላ የጠቅላላ አክሲዮኖችን ዋጋ ሙሉ በሙሉ መክፈል።
አማራጭ-2 . የአክሲዮን ግዥ ፎርም እንደተሞላ የጠቅላላ አክሲዮኖችን ዋጋ 50 % በመክፈል ቀሪውን 50% ገንዘብ በአንድ ወይም በሁለት ጊዜ ክፍያ በስድሰት ወር ጊዜ ውስጥ ከፍሎ ማጠናቀቅ፡፡
9) የተዘጋጀውን ቅጽ በሁለት ኮፒ ሞልተው ዋናውን የአክሲዮን ግዥ ገንዘብም ሆነ አሰተዳደራዊ ወጪ መሸፈኛ 5% ገንዘብ፥ ከላይ በተጠቀሱት ባንኮች ማስገባት ይችላሉ።
10) የአማራ ባንክ ፕሮጀክት ጽ/ቤት
አድራሻ፦
አዲስ አበባ፥ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ፣ወረዳ 08፣ ካዛንቺስ ብሎምቴክ ሕንፃ ( ጁፒተር ኢንተርናሽናል ሆቴል ጎን) 2ኛ ፎቅ ነው።
11) ከ 5 ሚሊዮን በላይ ለመግዛት ፍላጎት ያላቸው ግለሰቦች / ድርጅቶች/ ገንዘቡን ገቢ ከማድረጋቸው በፊት በቅድሚያ አዲስ አበባ የሚገኘውን ፕሮጀክት ጽ/ቤት ማነጋገር አለባቸው ።
12) በውጭ ሃገር ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያንም ከታች የተጠቀሱ ስልክ ቁጥሮችን በመደወል፥ በቂና ትክክለኛ መረጃ በማግኘት በውክልና መግዛት ይችላሉ።
ለበለጠ መረጃ አዲስ አበባ የሚገኘውን የፕሮጀክት ጽ/ቤት አስተባባሪ ስልክ ቁጥሮች፦
0900780225
0912001819 / 0911248160 / 0911600388 / 0911133014 / 0941466607
በመደወል ማብራሪያ ማግኘት ይችላሉ።
#Key_Notes፦
ይህን ገፅ በመከተል (Follow) ከአማራ ባንክ ጋር የተያያዙ ወቅታዊ መረጃዎችን፣ ክፍት የስራ ቦታዎችን፣ የጠቅላላ ጉባኤ ጥሪዎችን እና ሌሎች በቅርቡ የሚጀመሩ (የአማራ ኢንሹራንስን ጨምሮ) 10 ፕሮጀክቶች በተመለከተ ወቅታዊ እና ትክክለኛ መረጃዎች ያገኛሉ።
Amhara bank s.c
Together we can!!
አማራ ባንክ/Amhara Bank s.c.
አማራ በሁሉም መስኮች ማለትም በትምህርት፣ በኢኮኖሚውም፣ በጤናውም በኩል ከአማራ ባንክ በተጨማሪ በምስረታ ላይ ነው።
Amhara university, Amhara medical and Amhara insurance
✅coming soon
Amhara bank s.c
Together we can!!
@amharabank
https://www.facebook.com/አማራ-ባንክ-አማAmahara-bank-sc-124827542252667/
ሰበር መረጃ/braking news
የአማራ ባንክ አክሲዮን ማህበር በሚቀጥለው ህዳር ወር ሥራ ይጀምራል፤ ይሄ ትልቅ ስኬት ነው፤ የኢኮኖሚ እድገት የጀርባ አጥንት ሆኖ የሚያገለግል ትልቅ የፋይናንስ ተቋም ነው፤ ብዙ የተደከመበትም ነው፤ በእርግጥም ውጤት አሳይቷል፤ ባንክ ሥራ ለመጀመር የሚያሽትለውን 500 ሚሊዮን ብር አክሲዮኖችን በአጭር ጊዜ ውስጥ መሸጥ ችሏል። ባንኩ ሥራ የሚጀምረው በአገሪቱ 30 ቅርንጫፎችን በመክፈት ሲሆን 5000 ለሚሆኑ ዜጎችም የሥራ እድል ይፈጥራል። ይሄ ትልቅ እርምጃ ነው፤ ሌሎች ፕሮጀክቶችም ተጠናክረው ለውጤት እንዲበቁ መረባረብ አለብን። ይሄ ወቅት የሚጠይቀው መሬት የሚነካ ስራ መሥራትን ነው፤ የችግራችን ሁሉ መፍቻ ቁልፍም ይሄው መንገድ ነው።
Amhara bank s.c
https://www.facebook.com/አማራ-ባንክ-አማAmahara-bank-sc-124827542252667/
⏩ የአማራ አቢዮት በኢኮኖሚውም እንዲሁም በለሌሎች ችቦውን ለኩሷል። በኢኮኖሚና በምጣኔ ሐብት ያልተደገፈ አቢዮት ለአሸናፊነት አይበቃም። የአማራ ባንክ የአክሲዎን ሽያጩ በሚገርም ፍጥነት እየተቀጣጠለ ነው። እስከ አሁን ድረስ 800,000,000/ስምንት መቶ ሚሊዮን ደርሷል።
እናመሰግናለን!!!!
✅አክሲዮን ያልገዛችሁ አሁኑኑ ሸሩን በመግዛት መስራች አባል ይሁኑ። የበለፀገ አማራን እንዲሁም የበለፀገች ኢትዮጵያን ኑ አብረን እንገንባ!
✅Share ስላደረጋችሁት እናመሰግናለን!!!🙏
Facebook address :https://www.facebook.com/አማራ-ባንክ-አማAmahara-bank-sc-124827542252667/
Amhara bank s.c
@amharabank
Together We Can!!!
ትብብር‼️
የአማራ ባንክ አ.ማ ቻናል ለወዳጅ ዘመድዎ #ሼር በማድረግ ግዴታዎን ይወጡ!!
⏩ የአማራ ባንክ አክሲዮን ገዝተሻል/ገዝተሀል?
✅መልክትዎን
@Nafkote4me
@Nafkote4me
@Nafkote4me
👆ላይ ይላኩልን👆
_________
ቻናላችንን ያልተቀላቀላችሁ አሁን ተቀላቀሉ ሊንኩን ይንኩ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@amharabank
@amharabank
@amharabank
@amharabank
Facebook: https://www.facebook.com/አማራ-ባንክ-አማAmahara-bank-sc-124827542252667/
