fa
Feedback
Abu muhammed (አቡ ሙሀመድ

Abu muhammed (አቡ ሙሀመድ

رفتن به کانال در Telegram

በዚህ ቻናል የተለያዩ ኪታቦችን የምንቀራበት የቂርአት ቻናል ነዉ

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Abu muhammed (አቡ ሙሀመድ

کانال Abu muhammed (አቡ ሙሀመድ (@abu_mohammed_seid) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 10 887 مشترک است و جایگاه 8 332 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 3 032 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 10 887 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 28 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -305 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -10 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 2.79% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 1.13% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 304 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 123 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 1 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
በዚህ ቻናል የተለያዩ ኪታቦችን የምንቀራበት የቂርአት ቻናል ነዉ

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 29 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

10 887
مشترکین
-1024 ساعت
-667 روز
-30530 روز
آرشیو پست ها
አንድ ቀን እኛም ላንመለስ ከ online  እንጠፋለን ።" ዱንያ" በጣም አጭር ናት።

🔖አዲስ ተከታታይ ትምህርት 📚رياض الصالحين من كلام سيد المرسلين 🎙በአቡ ሙሀመድ 📚የሪያዱ ሷሊሒን ኪታብ ማብራሪያ - ክፍል (     4⃣9⃣ https://t.me/UstazAbuMuhammed

➡️ ተውሂድ ሺርክን ሲያጠፋ ኢስቲግፋር ደግሞ ወንጀሎችን ያብሳል። (فَاعْلَمْ أَنَّهُ لَا إِلَٰهَ إِلَّا اللَّهُ وَاسْتَغْفِرْ لِذَنْبِكَ) እነሆ ከአላህ ሌላ አምላክ አለመኖሩን እወቅስለ ስህተትህም ምህረትን ጠይቅ። 👈يَا حَيُّ يَا قَيُّومُ بِرَحْمَتِكَ أَسْتَغِيْثُ، أَصْلِحْ لي شَأْني كُلَّهُ، وَلَا تَكِلْنِي إِلَى نَفْسِي طَرْفَةَ عَيْنٍ ~አንተ ህያዉ የሆንክ አምላክ ሆይ! አንተ ራስክን የቻልክ አምላክ ሆይ! 🎈በእዝነትህ እታገዛለሁ ። 🎈ጉዳዮን ሁሉ የተስተካከለና መልካም አድርግልኝ። 🎈ለቅጽበት እንኳ እኔን ለራሴዉ ብቻ አትተወኝ። 👉ዚክርና ዱኣ የመንፈስ ቀለብ! = t.me/https_Asselfya

photo content

photo content

ገባገባ በሉ ደርስ ተጀምሯል https://t.me/+eBmwYuwue7xiZTY0

ሙሓደራ ቁጥር 239 ክፍል 4 ርዕስ= ረድ በ ሙስጠፋ አብደላህ ላይ "መስዓለቱ ዑዝር ቢል ጀሕል'' 🎤 በ ኡስታዝ ኸድር አሕመድ አል ከሚሴ (አቡ ሓቲም) https://t.me/UstazKedirAhmed

ማነው መጤው? ~ ሙስሊሙ መብቱን በጠየቀ፣ ጭቆናን በተቃወመ፣ እምነቱን ባስተማረ ቁጥር "እናንተ ሙስሊሞች ወደ ኢትዮጵያ ስትገቡ አክብረን በተቀበልን እንዴት ውለታችን ይረሳል?" እያሉ በቅጥፈት ለሚመፃደቁ አካላት "እንዴ! እኛ እኮ ኢትዮጵያውያን እንጂ መጤዎች አይደለንም" እያሉ በከንቱ መድከም አያስፈልግም ብዬ በፅኑ አምናለሁ። ሰዎቹ እንዲህ አይነት አመክንዮ የሚገባቸው አይደሉም። ድንጋይ ላይ ውሃ ማፍሰስ ነው። መፍትሔው ማጥቃት እንጂ መከላከል አይመስለኝም። በራሱ ቋንቋ አናግረው። በዚህ ድንቁ ^ ርና ላይ በሰፊው የሚታወቁት በዋናነት የአንድ እምነት ተከታዮች ናቸው። እነሱ ናቸው "የእስላም አገሩ መካ፣ የአሞራ አገሩ ዋርካ" የሚል ምሳሌያዊ አነጋገር ፈጥረው ድንቁርናቸውን ከትውልድ ትውልድ የሚያሻግሩት። እንዴት አድርገው እንደሚጠርቧቸው እንጃ በዚህ ዘመን እንኳ አልተቀየሩም። የለውጥ ተስፋ የሚታይባቸውም አይደሉም። አስቂኙ ነገር ደግሞ ራሳቸውን የአይ^ሁድ ዘር አድርገው መኮፈሳቸው ነው። ሃገሪቱን ለሰባት መቶ ዓመታት በላይ የቦጠቦጠው ራሱን "ሰለሞናዊ መንግስት" ብሎ የሚጠራው መዥገር ስርአትኮ ባህር ተሻግሮ የሰሎሞን ዘር ነኝ የሚል ነው። መጤ ነኝ ማለት አይደል ይሄ? አፄ ምኒልክ "ዳግማዊ" ምኒልክ የተባለው ጥንት ከንጉስ ሰለሞን የተገኘ "ቀዳማዊ" ምኒልክ ነበር ብለው ስለሚያምኑ ነው። "የናዝሬቱ እየሱስ፣ የዮርዳኖስ ወንዝ፣ ቃና ዘገሊላ፣ ቤተልሄም፣ እየሩሳሌም፣ ... " እያለ እምነቱን ከባህር ማዶ ጋር የሚያይዝ አካል እንዴት ሙስሊሞችን መጤ ሊያደርግ ይዳፈራል?! የሙስሊሙን ኢትዮጵያዊነት መቀበል የከበዳቸው ጭንቅላቶች "ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴት ናት" የሚል ያረጀ ያፈጀ ተረት ዛሬም ይተርታሉ። ለመሆኑ እነሱ ዘንድ ኢትዮጵያ ማለት የቷ ናት? ለመሆኑ ኢትዮጵያ ሲሉ አፋርን፣ ሶማሊን፣ ሀረርን፣ ስልጤን፣ ከፊል ጉራጌን፣ ሰፊውን ኦሮሚያን፣ ሀላባን፣ አብዛኛው ወሎን፣ አብዛኛውን በኒሻንጉልን፣ ድሬዳዋን፣ አርጎባን፣ ... ይጨምራል ወይ? እስኪ እነዚህን አካባቢዎች ቆርጠው ያውጡና የደሴቷን ካርታ ይመልከቱ። ካርታው ላይ የሚታየው ቀዩ ክፍል ነው የሚቀራቸው። ከዚያ የቀራችሁን የክርስቲያን ደሴት ተመልከቷት! የምትዘምሩላት ኢትዮጵያ ይቺ ናት? ለማንኛውም "በቀዳማዊ ምኒልክ በኩል የሰለሞን ዘር ነን"፣ "ነገደ ይሁዳ ነን"፣ "የይሁዳ አንበሳ ነን" የሚለውን የአባቶቻችሁን ተረት የምታምኑበት ከሆነ መጤዎች እንደሆናችሁ በራሳችሁ ላይ መስክራችኋል። እኛ ሙስሊሞች ዐረቦች ነን አላልንም። ኢትዮጵያውያን ነን። እናንተ "የሁ^ዶች ነን" ካላችሁ እኛ ነን የተቀበልናችሁ። "አይ" ካላችሁ "አይ^ሁድ ነን" የሚለውን የአባቶቻችሁን ተረት ውሸት እንደሆነ አስረግጣችሁ ወርውራችሁ ጣሉ። ከዚያ በኋላ ራሳችሁን የኢትዮጵያዊነት አከፋፋይና ድርጎ ሰፋሪ አድርጋችሁ ማየታችሁን አቁሙ። የነውረኝነታችሁ ዳፋ ለደካሞች ይተርፋልና ጥፍራችሁን ሰብስቡ። በዚህ ዘመን እንዲህ አይነት የከረፋ ሃሳብ ስታንፀባርቁ ታንኩም ባንኩም በእጃችሁ በነበረበት የቀደመው ዘመን ያደረሳችሁትን ማሰብም ይሰቀጥጣል። = የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor

💫 የሴቶች መጥፊያ አራት ናቸው!! በአላህ ይሁንብኝ እነዚህ አራት ነገሮች በአንዲት ሴት ውስጥ ከተገኙ ቤቷን ያፈረሱባት፣ ሕይወቷን የገደሉባትና ከአኺራ በፊት በዱንያ ላይ ለራሷ ስቃይን የመረጠች ብትሆን እንጂ። 🥀 አንደኛው፦ ምላስን ማስረዘም ነው። የሴት ልጅ ውበት በሕይወቷ ውስጥ ያለው በዝምታዋና በመልካም ስነ-ምግባሯ ላይ ነው። ምላሷ በሐሜትና በወሬ ከረዘመ፣ እንዲሁም ባልን በመመለስ፤ ባል አንድ ቃል ሲናገር እርሷ በአራት ቃላት የምትመልስ ከሆነ ይህንን የምታደርገው የስብዕና ጥንካሬ መስሏት ነው! በአላህ ይሁንብኝ እወቂ፤ ሕይወቷን፣ ውበቷንና ቤቷን በራሷ እጅ ለማጥፋት መርጣለች ማለት ነው። 💎 ሁለተኛው፦ ውለታ መካድ ነው። ባል ዕድሜ ልኩን መልካም ቢሆንላትና ቢንከባከባት እንኳ፤ አንድ ቀን ባስቀየማት ጊዜ 'ከአንተ ምንም መልካም ነገር አይቼ አላውቅም' ብላ ያደረገውን መልካምነት በሙሉ መካድ የትዳርን ሰላም ይነጥቃታል ። 🌟 ሦስተኛው፦ ውለታ መቁጠር (መመጻደቅ) ነው። ለባሏ ያደረገችለትን ነገር ወይም ለቤቱ የዋለችውን ውለታ ደጋግማ በማንሳት እሱን የምታሳንሰውና የምታሳቅቀው ከሆነ ይህ ተግባር በትዳር ውስጥ ያለውን ፍቅር ይገላል። 🌿 አራተኛው፦ የቤት ምስጢርን ማውጣት ነው። በመካከላቸው ያለውን የግል ወሬ፣ ችግር ወይም ምስጢር ለሌላ ሰው አሳልፎ መስጠት የቤቱን ክብርና ታማኝነት ያፈርሳል፤ ይህም የትዳር ውድቀት መጀመሪያ ይሆናል። ስለዚህ እህቶቼ እነዚህን ባህሪዎች ተጠንቀቁ⁉️ t.me/Abu_hibetillah_Asselfiy t.me/Abu_hibetillah_Asselfiy

ወደ ፊት ብቻ! ~ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሁሉም አይነት ሰው አለ። ሞቅ ያለ ተሳትፎ ካለን በተለያዩ አካላት እንገመታለን። እንገመገማለን። እንተመናለን። በአቋም የሚመስለን እንዳለ ሁሉ የሚቃረነንም ብዙ ነውና ዋጋችንና ቦታችን ከሰው ሰው ይለያያል። * ከፊሉ የምትፅፈው/ የምትናገረው ነገር አይጥመውም። ከፊሎቹ ጋር ደግሞ እውነታው ይለያል። * ከፊሉ ቀድሞ በጥላቻ ስለተሞላ የኔ የሚለው ሰው ቢናገረው የሚደግፈውን ብትናገር እንኳ ሰበብ ፈልጎ ያብጠለጥልሃል። * ከፊሉ ዘንድ ሚዛናዊ ነህ። ሌላው ዘንድ ደግሞ ፅንፈኛ፣ ፍርደ ገምድል ነህ። * ከፊሉ ዘንድ አስተዋይና በሳል ነህ። ሌላው ዘንድ የሃገርና የወቅት ተጨባጭ ያልገባህ ጥሬ ነህ። * ከፊሉ ዘንድ አዛኝ ነህ። ከፊሉ ዘንድ ጨካኝ ነህ። * ከፊሉ ዘንድ እየበሰልክ ነው። ሌላው ዘንድ እየባሰብህ ነው። * ከፊሉ ዘንድ ቡድንተኛ ነህ። ሌላው ዘንድ ውግንናህ ለሐቅ ብቻ ነው። የሚርቅህ ብቻ ሳይሆን የተሻለ የሚቀርብህ ራሱ የበለጠ ሊጠላህ እና ንግግርህንም ዝምታህንም ያላሰብከውን ትርጉም እየሰጠ ሊያጣጥልህ ይችላል። ቢሆንም ታገስ። ሞራልህ ሳይጎዳ ወደፊት ገስግስ። የተራራቁ አመልካከቶች በበዙበት፣ ከዒልምና ተርቢያ የራቀ ትውልድ እንደ አሸን በፈላበት፣ በሺርክና መልከ ብዙ ቢድዐዎች ላይ የተዘፈቀው ወገን በበዛበት፣ ይሄ ሁሉ ወፈ ሰማይ በነፃነት የሚናገርበት መድረክ አግኝቶ ከየትኛውም አካል ጉንተላ ሳያገኘኝ ሰላም እጓዛለሁ ማለት ዘበት ነው፣ አጉል ምኞት። ስለዚህ ደዕዋ ላይ ያለኸው ወገኔ ሆይ! በደዕዋህ ላይ ትችትና ዘለፋ አያስደንብርህ። ቲፎዞና ጭብጨባም አያቅልጥህ። ሰዎች የሚሰጡህ ደረጃም አይድነቅህ። ሁሉም አላፊ ነው። ይልቅ አላህን ብቻ አስብ። በኢኽላስ ተጓዝ። በኢኽላስ ለካ! በኢኽላስ ቁረጥ። ጫጫታ ሳይበግርህ ወደፊት ብቻ። እልህ እንዳይሾፍርህም ሚዛንህን ጠብቅ። ዝቅ ብለህ ጀምር። ወርደህ ስራ። ተግተህ ጣር። መስመር ይዘህ፣ አላህን እያሰብክ እስከተጓዝክ ድረስ መንናቅ አያሳምምህ። ዝናም አያንጠባርህ። በየትኛውም ሁኔታ ከደዕዋ እንዳትርቅ። እንዳትርረታ። * ያያያዝኩት ግጥም የኔ አይደለም። = የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor

«አንዳንድ ዑለማዎች እንዲህ ብለዋል፦ አንድ ሰው ኻቲማው(የሂወቱ መጨረሻ) እንዲበላሽ ከሚያደርጉ ታላላቅ ምክንያቶች አራት ናቸው፦ 1.ለሰላት ግድየለሽነት ማሳየት። 2.የሚያሰክር መጠጥ (ኸምር) መጠጣት። 3.ወላጆችን መበደልና አለመታዘዝ። 4.ሙስሊሞችን አዛ ማድረግ።» — አስ-ሱዩጢ رحمه الله

https://t.me/merkez_ibnu_kesir       ይህን ቻናል  ሸር ያደረገ  አላህ ጀዛዉን ይክፈለዉ

💥*የብቸኝነት ቤት ይሄ ሰው ሁሉ ቤተሰቡንና ወዳጆቹን ተለይቶ ሚኖርበት ቦታ ነው አጫዋቹ መልካም ስራው ብቻ ሆኖ የሚያገኝበት ቦታ ነው።
💥*የብቸኝነት ቤት ይሄ ሰው ሁሉ ቤተሰቡንና ወዳጆቹን ተለይቶ ሚኖርበት ቦታ ነው አጫዋቹ መልካም ስራው ብቻ ሆኖ የሚያገኝበት ቦታ ነው።

ኹጥባ የ ዝናብን ፀጋ ወደአላህ ማስጠጋትhttps://t.me/UstazAbuMuhammed