ch
Feedback
Abu muhammed (አቡ ሙሀመድ

Abu muhammed (አቡ ሙሀመድ

前往频道在 Telegram

በዚህ ቻናል የተለያዩ ኪታቦችን የምንቀራበት የቂርአት ቻናል ነዉ

显示更多

📈 Telegram 频道 Abu muhammed (አቡ ሙሀመድ 的分析概览

频道 Abu muhammed (አቡ ሙሀመድ (@abu_mohammed_seid) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 10 879 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 8 332,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 3 032

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 10 879 名订阅者。

根据 28 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -305,过去 24 小时变化为 -10,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 2.79%。内容发布后 24 小时内通常能获得 1.13% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 304 次浏览,首日通常累积 123 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 1

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
በዚህ ቻናል የተለያዩ ኪታቦችን የምንቀራበት የቂርአት ቻናል ነዉ

凭借高频更新(最新数据采集于 29 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

10 879
订阅者
-1024 小时
-667
-30530
帖子存档
🔖‏قال الشيخ ابن عثيمين رحمه الله 🔖ሸይኽ ኢብኑ ኡሰይሚን (አላህ ይዘንላቸው) እንዲህ ብለዋል፡- « فإذا رَأَيْتَ أخاكَ مَكْرُوبًا، فَقُل لَهُ أبْشِ
🔖‏قال الشيخ ابن عثيمين رحمه الله 🔖ሸይኽ ኢብኑ ኡሰይሚን (አላህ ይዘንላቸው) እንዲህ ብለዋል፡- « فإذا رَأَيْتَ أخاكَ مَكْرُوبًا، فَقُل لَهُ أبْشِر الفَرَجُ قَرِيب ، «ወንድምህ ጭንቀት ላይ ሆኖ ባየሀዉ ጊዜ፣  አብሽር  "እፎይታ ቅርብ ነዉ" በለዉ።» « وإذا رأيْتَهُ في عُسْرَةٍ فقُل لهُ أبْشِر اليُسْرُ قريب . «በችግር ዉስጥም ሆኖ ባየሀዉ ጊዜ፣ አብሽር  "ምቾት ቅርብ ነዉ " በለዉ።»
(شرح رياض الصالحين - ١١٦/٤)
|•| t.me/Sadik_Ibnu_Heyru

አንድ ቀን እኛም ላንመለስ ከ online  እንጠፋለን ።" ዱንያ" በጣም አጭር ናት።

🔖አዲስ ተከታታይ ትምህርት 📚رياض الصالحين من كلام سيد المرسلين 🎙በአቡ ሙሀመድ 📚የሪያዱ ሷሊሒን ኪታብ ማብራሪያ - ክፍል (     4⃣9⃣ https://t.me/UstazAbuMuhammed

➡️ ተውሂድ ሺርክን ሲያጠፋ ኢስቲግፋር ደግሞ ወንጀሎችን ያብሳል። (فَاعْلَمْ أَنَّهُ لَا إِلَٰهَ إِلَّا اللَّهُ وَاسْتَغْفِرْ لِذَنْبِكَ) እነሆ ከአላህ ሌላ አምላክ አለመኖሩን እወቅስለ ስህተትህም ምህረትን ጠይቅ። 👈يَا حَيُّ يَا قَيُّومُ بِرَحْمَتِكَ أَسْتَغِيْثُ، أَصْلِحْ لي شَأْني كُلَّهُ، وَلَا تَكِلْنِي إِلَى نَفْسِي طَرْفَةَ عَيْنٍ ~አንተ ህያዉ የሆንክ አምላክ ሆይ! አንተ ራስክን የቻልክ አምላክ ሆይ! 🎈በእዝነትህ እታገዛለሁ ። 🎈ጉዳዮን ሁሉ የተስተካከለና መልካም አድርግልኝ። 🎈ለቅጽበት እንኳ እኔን ለራሴዉ ብቻ አትተወኝ። 👉ዚክርና ዱኣ የመንፈስ ቀለብ! = t.me/https_Asselfya

photo content

photo content

ገባገባ በሉ ደርስ ተጀምሯል https://t.me/+eBmwYuwue7xiZTY0

ሙሓደራ ቁጥር 239 ክፍል 4 ርዕስ= ረድ በ ሙስጠፋ አብደላህ ላይ "መስዓለቱ ዑዝር ቢል ጀሕል'' 🎤 በ ኡስታዝ ኸድር አሕመድ አል ከሚሴ (አቡ ሓቲም) https://t.me/UstazKedirAhmed

ማነው መጤው? ~ ሙስሊሙ መብቱን በጠየቀ፣ ጭቆናን በተቃወመ፣ እምነቱን ባስተማረ ቁጥር "እናንተ ሙስሊሞች ወደ ኢትዮጵያ ስትገቡ አክብረን በተቀበልን እንዴት ውለታችን ይረሳል?" እያሉ በቅጥፈት ለሚመፃደቁ አካላት "እንዴ! እኛ እኮ ኢትዮጵያውያን እንጂ መጤዎች አይደለንም" እያሉ በከንቱ መድከም አያስፈልግም ብዬ በፅኑ አምናለሁ። ሰዎቹ እንዲህ አይነት አመክንዮ የሚገባቸው አይደሉም። ድንጋይ ላይ ውሃ ማፍሰስ ነው። መፍትሔው ማጥቃት እንጂ መከላከል አይመስለኝም። በራሱ ቋንቋ አናግረው። በዚህ ድንቁ ^ ርና ላይ በሰፊው የሚታወቁት በዋናነት የአንድ እምነት ተከታዮች ናቸው። እነሱ ናቸው "የእስላም አገሩ መካ፣ የአሞራ አገሩ ዋርካ" የሚል ምሳሌያዊ አነጋገር ፈጥረው ድንቁርናቸውን ከትውልድ ትውልድ የሚያሻግሩት። እንዴት አድርገው እንደሚጠርቧቸው እንጃ በዚህ ዘመን እንኳ አልተቀየሩም። የለውጥ ተስፋ የሚታይባቸውም አይደሉም። አስቂኙ ነገር ደግሞ ራሳቸውን የአይ^ሁድ ዘር አድርገው መኮፈሳቸው ነው። ሃገሪቱን ለሰባት መቶ ዓመታት በላይ የቦጠቦጠው ራሱን "ሰለሞናዊ መንግስት" ብሎ የሚጠራው መዥገር ስርአትኮ ባህር ተሻግሮ የሰሎሞን ዘር ነኝ የሚል ነው። መጤ ነኝ ማለት አይደል ይሄ? አፄ ምኒልክ "ዳግማዊ" ምኒልክ የተባለው ጥንት ከንጉስ ሰለሞን የተገኘ "ቀዳማዊ" ምኒልክ ነበር ብለው ስለሚያምኑ ነው። "የናዝሬቱ እየሱስ፣ የዮርዳኖስ ወንዝ፣ ቃና ዘገሊላ፣ ቤተልሄም፣ እየሩሳሌም፣ ... " እያለ እምነቱን ከባህር ማዶ ጋር የሚያይዝ አካል እንዴት ሙስሊሞችን መጤ ሊያደርግ ይዳፈራል?! የሙስሊሙን ኢትዮጵያዊነት መቀበል የከበዳቸው ጭንቅላቶች "ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴት ናት" የሚል ያረጀ ያፈጀ ተረት ዛሬም ይተርታሉ። ለመሆኑ እነሱ ዘንድ ኢትዮጵያ ማለት የቷ ናት? ለመሆኑ ኢትዮጵያ ሲሉ አፋርን፣ ሶማሊን፣ ሀረርን፣ ስልጤን፣ ከፊል ጉራጌን፣ ሰፊውን ኦሮሚያን፣ ሀላባን፣ አብዛኛው ወሎን፣ አብዛኛውን በኒሻንጉልን፣ ድሬዳዋን፣ አርጎባን፣ ... ይጨምራል ወይ? እስኪ እነዚህን አካባቢዎች ቆርጠው ያውጡና የደሴቷን ካርታ ይመልከቱ። ካርታው ላይ የሚታየው ቀዩ ክፍል ነው የሚቀራቸው። ከዚያ የቀራችሁን የክርስቲያን ደሴት ተመልከቷት! የምትዘምሩላት ኢትዮጵያ ይቺ ናት? ለማንኛውም "በቀዳማዊ ምኒልክ በኩል የሰለሞን ዘር ነን"፣ "ነገደ ይሁዳ ነን"፣ "የይሁዳ አንበሳ ነን" የሚለውን የአባቶቻችሁን ተረት የምታምኑበት ከሆነ መጤዎች እንደሆናችሁ በራሳችሁ ላይ መስክራችኋል። እኛ ሙስሊሞች ዐረቦች ነን አላልንም። ኢትዮጵያውያን ነን። እናንተ "የሁ^ዶች ነን" ካላችሁ እኛ ነን የተቀበልናችሁ። "አይ" ካላችሁ "አይ^ሁድ ነን" የሚለውን የአባቶቻችሁን ተረት ውሸት እንደሆነ አስረግጣችሁ ወርውራችሁ ጣሉ። ከዚያ በኋላ ራሳችሁን የኢትዮጵያዊነት አከፋፋይና ድርጎ ሰፋሪ አድርጋችሁ ማየታችሁን አቁሙ። የነውረኝነታችሁ ዳፋ ለደካሞች ይተርፋልና ጥፍራችሁን ሰብስቡ። በዚህ ዘመን እንዲህ አይነት የከረፋ ሃሳብ ስታንፀባርቁ ታንኩም ባንኩም በእጃችሁ በነበረበት የቀደመው ዘመን ያደረሳችሁትን ማሰብም ይሰቀጥጣል። = የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor

💫 የሴቶች መጥፊያ አራት ናቸው!! በአላህ ይሁንብኝ እነዚህ አራት ነገሮች በአንዲት ሴት ውስጥ ከተገኙ ቤቷን ያፈረሱባት፣ ሕይወቷን የገደሉባትና ከአኺራ በፊት በዱንያ ላይ ለራሷ ስቃይን የመረጠች ብትሆን እንጂ። 🥀 አንደኛው፦ ምላስን ማስረዘም ነው። የሴት ልጅ ውበት በሕይወቷ ውስጥ ያለው በዝምታዋና በመልካም ስነ-ምግባሯ ላይ ነው። ምላሷ በሐሜትና በወሬ ከረዘመ፣ እንዲሁም ባልን በመመለስ፤ ባል አንድ ቃል ሲናገር እርሷ በአራት ቃላት የምትመልስ ከሆነ ይህንን የምታደርገው የስብዕና ጥንካሬ መስሏት ነው! በአላህ ይሁንብኝ እወቂ፤ ሕይወቷን፣ ውበቷንና ቤቷን በራሷ እጅ ለማጥፋት መርጣለች ማለት ነው። 💎 ሁለተኛው፦ ውለታ መካድ ነው። ባል ዕድሜ ልኩን መልካም ቢሆንላትና ቢንከባከባት እንኳ፤ አንድ ቀን ባስቀየማት ጊዜ 'ከአንተ ምንም መልካም ነገር አይቼ አላውቅም' ብላ ያደረገውን መልካምነት በሙሉ መካድ የትዳርን ሰላም ይነጥቃታል ። 🌟 ሦስተኛው፦ ውለታ መቁጠር (መመጻደቅ) ነው። ለባሏ ያደረገችለትን ነገር ወይም ለቤቱ የዋለችውን ውለታ ደጋግማ በማንሳት እሱን የምታሳንሰውና የምታሳቅቀው ከሆነ ይህ ተግባር በትዳር ውስጥ ያለውን ፍቅር ይገላል። 🌿 አራተኛው፦ የቤት ምስጢርን ማውጣት ነው። በመካከላቸው ያለውን የግል ወሬ፣ ችግር ወይም ምስጢር ለሌላ ሰው አሳልፎ መስጠት የቤቱን ክብርና ታማኝነት ያፈርሳል፤ ይህም የትዳር ውድቀት መጀመሪያ ይሆናል። ስለዚህ እህቶቼ እነዚህን ባህሪዎች ተጠንቀቁ⁉️ t.me/Abu_hibetillah_Asselfiy t.me/Abu_hibetillah_Asselfiy

ወደ ፊት ብቻ! ~ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሁሉም አይነት ሰው አለ። ሞቅ ያለ ተሳትፎ ካለን በተለያዩ አካላት እንገመታለን። እንገመገማለን። እንተመናለን። በአቋም የሚመስለን እንዳለ ሁሉ የሚቃረነንም ብዙ ነውና ዋጋችንና ቦታችን ከሰው ሰው ይለያያል። * ከፊሉ የምትፅፈው/ የምትናገረው ነገር አይጥመውም። ከፊሎቹ ጋር ደግሞ እውነታው ይለያል። * ከፊሉ ቀድሞ በጥላቻ ስለተሞላ የኔ የሚለው ሰው ቢናገረው የሚደግፈውን ብትናገር እንኳ ሰበብ ፈልጎ ያብጠለጥልሃል። * ከፊሉ ዘንድ ሚዛናዊ ነህ። ሌላው ዘንድ ደግሞ ፅንፈኛ፣ ፍርደ ገምድል ነህ። * ከፊሉ ዘንድ አስተዋይና በሳል ነህ። ሌላው ዘንድ የሃገርና የወቅት ተጨባጭ ያልገባህ ጥሬ ነህ። * ከፊሉ ዘንድ አዛኝ ነህ። ከፊሉ ዘንድ ጨካኝ ነህ። * ከፊሉ ዘንድ እየበሰልክ ነው። ሌላው ዘንድ እየባሰብህ ነው። * ከፊሉ ዘንድ ቡድንተኛ ነህ። ሌላው ዘንድ ውግንናህ ለሐቅ ብቻ ነው። የሚርቅህ ብቻ ሳይሆን የተሻለ የሚቀርብህ ራሱ የበለጠ ሊጠላህ እና ንግግርህንም ዝምታህንም ያላሰብከውን ትርጉም እየሰጠ ሊያጣጥልህ ይችላል። ቢሆንም ታገስ። ሞራልህ ሳይጎዳ ወደፊት ገስግስ። የተራራቁ አመልካከቶች በበዙበት፣ ከዒልምና ተርቢያ የራቀ ትውልድ እንደ አሸን በፈላበት፣ በሺርክና መልከ ብዙ ቢድዐዎች ላይ የተዘፈቀው ወገን በበዛበት፣ ይሄ ሁሉ ወፈ ሰማይ በነፃነት የሚናገርበት መድረክ አግኝቶ ከየትኛውም አካል ጉንተላ ሳያገኘኝ ሰላም እጓዛለሁ ማለት ዘበት ነው፣ አጉል ምኞት። ስለዚህ ደዕዋ ላይ ያለኸው ወገኔ ሆይ! በደዕዋህ ላይ ትችትና ዘለፋ አያስደንብርህ። ቲፎዞና ጭብጨባም አያቅልጥህ። ሰዎች የሚሰጡህ ደረጃም አይድነቅህ። ሁሉም አላፊ ነው። ይልቅ አላህን ብቻ አስብ። በኢኽላስ ተጓዝ። በኢኽላስ ለካ! በኢኽላስ ቁረጥ። ጫጫታ ሳይበግርህ ወደፊት ብቻ። እልህ እንዳይሾፍርህም ሚዛንህን ጠብቅ። ዝቅ ብለህ ጀምር። ወርደህ ስራ። ተግተህ ጣር። መስመር ይዘህ፣ አላህን እያሰብክ እስከተጓዝክ ድረስ መንናቅ አያሳምምህ። ዝናም አያንጠባርህ። በየትኛውም ሁኔታ ከደዕዋ እንዳትርቅ። እንዳትርረታ። * ያያያዝኩት ግጥም የኔ አይደለም። = የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor

«አንዳንድ ዑለማዎች እንዲህ ብለዋል፦ አንድ ሰው ኻቲማው(የሂወቱ መጨረሻ) እንዲበላሽ ከሚያደርጉ ታላላቅ ምክንያቶች አራት ናቸው፦ 1.ለሰላት ግድየለሽነት ማሳየት። 2.የሚያሰክር መጠጥ (ኸምር) መጠጣት። 3.ወላጆችን መበደልና አለመታዘዝ። 4.ሙስሊሞችን አዛ ማድረግ።» — አስ-ሱዩጢ رحمه الله

https://t.me/merkez_ibnu_kesir       ይህን ቻናል  ሸር ያደረገ  አላህ ጀዛዉን ይክፈለዉ