fa
Feedback
Addis Ababa City Manager Office

Addis Ababa City Manager Office

رفتن به کانال در Telegram
1 474
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-37 روز
-2130 روز
آرشیو پست ها
wps_wid.cid-1315061244.1758003295.exe5.52 MB

The government is working hard to ensure food freedom by increasing productivity and productivity. · See original · Rate this translation

የሕዝብን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2018 በጀት ዓመት መጀመሪያ ሩብ ዓመት የሕዝብን ተጠቃሚነት ይበልጥ ያረጋገጡ ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል አሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 በጀት ዓመት አንደኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እየተካሄደ ነው፡፡ ከንቲባ አዳነች በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ በክረምቱ ወራት ማሕበረሰቡ ላይ የኑሮ ጫና ሊያሳድሩ የሚችሉ ተግባራትን በመለየት ሕዝቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ሥራዎች ተከናውነዋል፡፡ በዚህም የኑሮ ውድነት ጫናን ከመቀነስ አኳያ የገበያ ማረጋጋት፣ ምርት በብዛት እንዲገባ የማድረግ፣ ገበያ ላይ ሊደርሱ የሚችሉ ብልሽቶችን የመቆጣጠር እና የሕዝቡን የኑሮ ጫና ለማቃለል ያስቻሉ ሥራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል። የክረምት ወቅት ተጽዕኖ በተለይም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ወገኖች ላይ ጫና እንዳያሳድር ከተማ አስተዳደሩ ውጤታማ ሥራዎችን በማከናወን ለሕዝቡ ያለውን ወገንተኝነት በተግባር ማረጋገጥ መቻሉን ጠቅሰዋል። የሀገር ባለውለታዎችን፣ አቅመ ደካሞች እና ለማህበራዊ ችግር የተጋለጡ ወገኖችን በመለየት በሰው ተኮር ሥራዎች ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል። በዓላት እሴታቸውን ጠብቀው በድምቀት እንዲከበሩ ብሎም የሕዝብ አብሮነት እንዲጠናከርባቸው መደረጉን ነው ያስረዱት፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ የኮንፈረንስ ቱሪዝም የስበት ማዕከል እንድትሆን በማድረግ በርካታ ሀገር እና ዓለም አቀፍ ሁነቶችን ማስተናገድ መቻሉን ጠቁመዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ መካሄድ ጀምሯል። በሩብ ዓመት ሪፖርቱ ከተካተቱ ቁልፍ ተግባራት ውስጥ አገልግሎትን ቀልጣፋ፣ አስተማማኝ፣ ተደራሽና ፍትሃዊ በማድረግ የተገልጋይን ወጪና ጊዜ ለመቀነስ የአዲስ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት በማስመረቅ በማዕከል እና በቦሌ ቅርንጫፍ ወደ ተግባር ተገብቷል። በዚህ ማዕከል ውስጥ 13 የማዕከል ተቋማት፣ 3 የፌደራል እና 2 የፋይናንስ ተቋማት ተሳታፊ ሲሆኑ በማዕከል [107] እና በቦሌ ቅርንጫፍ [96 ] አገልግሎቶች ተለይተው አገልግሎት በመስጠት ላይ ሲሆኑ 157የአገልግሎት ካውንተሮች በማዕከል (101) እና በቦሌ ቅርንጫፍ (56) መዘጋጀታቸው ተጠቅሷል::

ዛሬ ማለዳ የከተማችንን የ2018 በጀት ዓመት 1ኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ማካሄድ ጀምረናል ። በግምገማ መድረኩ በሩብ ዓመቱ የታቀዱ እና የ90 ቀን አበይት ተግባራት የደረሱበት የአፈፃፀም ደረጃ ይገመገማል። መድረኩ የተገኙ ዉጤታማ አፈፃፀሞችን ይበልጡን አልቀን በማስቀጠል እና የታዩ ጉድለቶችን በማረም እንዲሁም ትኩረት እና የተለየ ርብርብ የሚሹ ተግባራትንም ለይተን ቀጣይ አቅጣጫ የምናስቀምጥበት ይሆናል ። ፈጣሪ ኢትዮዽያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ ከንቲባ አዳነች አቤቤ

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የመሠረተ ልማት እና ማዘጋጃቤታዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የአዲስ አበባ ከተማ ፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ሩብ አመት ዕቅድ አፈፃፀም ገመገመ።… See more

የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የ2018 ዓ.ም 1ኛ ሩብ ዓመት እቅድ አፈጻጻሙ በአዲስ አበባ ም/ቤት መሠረተ ልማትና ማዘጋጃ ቤታዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ዛሬ ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም ተገምግሟል። የኮሚሽኑ ኮሚሸነር አህመድ መሀመድ የ2018 ዓ.ም 1ኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምን ሪፖርት ያቀርቡ ሲሆን ሌሎች አስረጂ ሰንዶችም ቀርበው በቋሚ ኮሚቴ አባላት ተገምግ ሟል ። ኮሚሽኑ በ1ኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጻሙ የተለየዩ ሚዲያ አግባቦችን በመጠቀም ያከናወናቸው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችና በክረምቱ ጊዜ አደጋን ለመቀነስ የተደረጉ ጥረቶችና የመ ጡ ለውጦች እንዲሁም በአደጋ ምላሽ ዘርፍ የተሰጡ ፈጣን ምላሾች የሚበረታቱና ለውጦች መመዝገባቸውን በምልከታቸው ማረጋገጣቸውን ጠቅሰው የኮሚሽኑን እቅድ አፈጻጸምን አስመልክቶ የቀረበው ሠነድ የነባራዊ ሁኔታ ትንተና ጉድለት ያለበት በመሆኑ በቀጣይ ማስተካከያ እንዲደረግ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። የግምገማ መድረኩን የመሩት የአዲስ አበባ ም/ቤት መሠረተ ልማትና ማዘጋጃ ቤታዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሰቢ ዶ/ር ግዛቸ ው አይካ እንደተናገሩት በአዲስ አበባ በመስከረም ወር የተከበሩ በዓላት ያለምንም አደጋ ክስተት እንዲጠናቀቁ የኮሚሽኑ አመራርና ባለሞያዎች ላደርጉት ከፍተኛ አስተዋጾኦ ምስጋናቸው አቅርበዋል ። አያይዘውም የከተማዋን እድገት የሚመጥን አገልግሎት ለመስጠት እንዲቻል በኮሚሽኑ ቴክኖሎጂ ዘርፍ የተጀመሩ ውጤታማ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉና በአደጋ ቅነሳ ሰራም እየተከናወኑ ያሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች በልዩ ትኩረት እንዲከናወኑ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

ታማኝ ግብር ከፋዮች አዲስ አበባ እንደገና እንድትሰራ ማድረጋቸውን አቶ አገኘሁ ተሻገር ገለፁ ታማኝ ግብር ከፋዮች አዲስ አበባ እንደገና እንድትሰራ ማድረጋቸውን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ገልፀዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር "ግብር ለሃገር ክብር" በሚል መሪ ቃል ለታማኝ ግብር ከፋዮች የእውቅና እና ሽልማት መርሃ ግብር አካሂዷል፡፡ በመርሃ ግብሩ በክብር እንግድነት የተገኙት የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር፤ መንግስት ሃገሪቱ መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሃገራት ተርታ እንድትሰለፍ የተለያዩ ዕቅዶችን ነድፎ እየተገበረ መሆኑን በመጥቀስ፤ ለዚህም የገቢ ሰብሳቢ ተቋማት ኢኮኖሚው ከሚያመነጨው ሀብት በቂ ገቢ ለመሰብሰብና ሀገራዊ የልማት ዕቅዶችን ለማሳካት እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። መንግስት በሃገር ውስጥ ከሚፈጠረው ሃብት የከተሞች ዕድገት እና የዜጎች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን እያረጋገጠ መሆኑን አቶ አገኘሁ ተሻገር ተናግረዋል፡፡ በቀጣይም የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተለይ የአዲስ አበባ ከተማን የዕድገት ፍላጎት ለማሟላት የመንግስት እና የግብር ከፋዩ ማህበረሰብ ይበልጥ ተቀናጅቶ መስራት እንደሚያስፈልግ ጠቅሰዋል፡፡ የሃገራችንን ዕድገት ለማረጋገጥ እና የከተማ አስተዳደሩን ገቢ የመሰብሰብ ዓቅም ይበልጥ ለማሳደግ ሊሰራ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በአዲስ አበባ ከተማ የሚታየው ሁለንተናዊ ለውጥ ያለ ታማኝ ግብር ከፋዮች ተሳትፎ አይሳካም ያሉት አቶ አገኘሁ አዲስ አበባ ከተማ እንደገና እንድትሰራ አድርጋችኋልና ለዚህም ከፍተኛ ምሰጋና ይገባችኋል ሲሉ አድናቆታቸውን ችረዋል ፡፡ የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች፤ በተለይ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለከተማዋ ዕድገት እንዲሁም አዲስ አበባ የአፍሪካ ምሳሌ እንድትሆን ለሚያደርጉት ጥረት መንግስት ከፍተኛ አድናቆት አለው ያሉት አፈ-ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር፤ የተጀመረው የለውጥ ጉዞ እንዲቀጥል ለግብር ከፋዩ መሰረታዊ የአገልግሎት አሰጣጥ እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በየጊዜው እየፈተሹ መሰራት ሁሌም የትኩረት ማዕከል ሊሆን ይገባዋል ሲሉ አሳስበዋል፡፡

ግብር ለሀገር ክብር ! ዛሬ የከተማችንን ታማኝ ግብር ከፋዮች በታላቅ ድምቀት ሸልመናል ፤ ተሸላሚ ግብር ከፋዮቻችን እንኳን ደስ አላችሁ ! ዉድ ታማኝ ግብር ከፋዮች መዲናችን ከእናንተ በምትሰበስበዉ ገቢ በከተማችን በአስደናቂ ሁኔታ የተገበርናቸዉ ሜጋ ፕሮጀክቶች፣ የወንዝ ዳርቻና የኮሪደር ልማት ፣ የህዝቡን የኑሮ ጫና ያቀለሉ ስራዎች ፣ የተማሪዎች ምገባ፣ ከተማችንን ለቢዝነስ እና ለመኖር የተመቸች ንፁህ ፣ ጤናማ አካባቢ እና በአለም አቀፍ ደረጃም ተመራጭና ተወዳዳሪ እየሆነች ይገኛል ፤ ይህ ለዉጥ በርግጥ ለእናንተም ተጨማሪ አሴት፣ለቢዝነስ ማህበረሰቡ ተጨማሪ የሀብት መፍጠሪያ ምንጭ ነዉ። በቀጣይ በግብር አሰባሰብ ዙሪያ የአገልግሎት አሰጣጣችንን ይበልጡን ዲጂታላይዝ በማድረግ ፣ በማዘመን እና ተጠያቂነትን በማስፈን ክፍተቶችን እየሞላን ፣ እፀፆችን እያረምን የሁለንተናዊ ብልፅግና ተምሳሌት የሆነች ከተማን እየገነባን እንሄዳለን ። በዛሬዉ የእዉቅና እና የሽልማት መርሃ ግብር ለእዉቅና የበቃችሁ ግብር ከፋዮቻችን ለታማኝነታችሁ ምስጋናዬ የላቀ ነዉ ፣ በተለይም የወርቅ እና የፕላቲኒየም ደረጃ ግብር ከፋዮች የዘርፉ አምባሳደሮቻችን በመሆናችሁ በከተማችን በየትኛዉም መንግስታዊ አገልግሎት እና ኩነት የቅድሚያ ቅድሚ እንድትስተናገዱ እና VIP ፕሮቶኮል እንዲሰጣችሁ መወሰናችንን ስገልፅ ሌሎችም የእናንተን አርአያነት እንደሚከተሉ በማመን ነዉ ። ግብር ለሀገር ክብር ! ፈጣሪ ኢትዮዽያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ

የአዲስ አበባ ከተማ የስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ሩብ አመት የእቅድ አፈፃፀም ከሠራተኞች ጋር ገመገመ። የከተማ ስራ አስኪያጅ ፅ/ቤት የ2018በጀት አመት የመጀመሪያ የሩብ አመት የእቅድ አፈፃፀም በተለይም ከዝግጅት ምዕራፍ ስራዎች ክንውን፣ከበዓላት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች አንፃር፣ምቹ የስራ አካባቢን ከመፍጠር፣ብልሹ አሰራርን ከመከላከል፣ቅንጅታዊ አሰራርን ከመዘርጋት፣የመልካም አስተዳደር ችግርን ከመፍታት ፣ከበጀት አጠቃቀም ፣የግንዛቤ ስራዎችን ከመስራት አንፃር የተከናወኑ ተግባራትን የያዘ ዝርዝር ሪፖርት ቀርቦ ዉይይት ተካሂዶበታል። በዉይይት መድረኩም በቢሮ ሀላፊ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ስራ አስኪያጅ እና የጥናትና ልማት ትግበራ ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ ይመኙሻል ታደሰ በዚሁ ወቅት የፅ/ቤቱ የመጀመሪያዉ የ2018 በጀት አመት የሩብ አመት አፈፃፀም አመርቂ የሚባል ውጤት ማስመዝገቡን ገልፀዋል:: ፅ/ቤቱ የማዘጋጃ ቤታዊ የአገልግሎት አሰጣጥን በቴክኖሎጂ የታገዘ ፈጣንና ቀልጣፋ ለማድረግ ለተሰሩ የሪፎርም ተግባራት የመምራትና የማስተባበር ሚናውን በብቃትና በውጤታማነት በሩብ አመቱ ሲያከናውን መቆየቱን አስገንዝበዋል:: ወ/ሮ ይመኙሻል አክለውም በፅህፈት ቤቱ በዝግጅት ምእራፍ ስራዎች የተጀመረው የተቋም ግንባታና የተለዩ የሪፎርም ስራዎች ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ጠቅሰው በፅ/ቤቱ ስራዎችን በፍጥነት ለማከናወን የሠራተኛውን የመፈፀም አቅም የሚገነቡ ፍላጎቶችን በመለየት አስፈላጊ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች በተከታታይነት መስጠት ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው ገልጸዋል። የዘርፉን ስራዎች በቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ እና የአገልግሎት አሰጣጣችንን በከተማዋ እድገት ልክ ለማድረግና ወቅታዊ አገልግሎት ለመስጠት በቀጣይ በተግበራ ምዕራፋችን ላይ ተግባራዊ ለማድረግ ሁሉም ባለሙያና አመራር የበኩሉን ሚና መወጣት እንደሚኖርበት አቅጣጫ አስቀምጠዋል:: ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

በሀሰተኛ መሸኛ ለመገልግል የሞከረች ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለች በሀሰተኛ መሸኛ አገልግሎት ለማግኘት የሞከረች ግለሰብ በቁጥጥር መዋሏን የአዲስ አበባ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አስታውቋል፡፡ ግለለሰቧ ከአስር ቀን በፊት ከኦሮሚያ ክልል መልቀቂያ (መሸኛ) አምጥተው የሶስት ወር ቆይታ እየጠበቀች ባለችበት ሂደት በተጨመሪ ከልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 የተዘጋጀ የአዲስ አበባ ነዋሪነት ሀሰተኛ መሸኛ በመያዝ ከአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 መታወቂያ ለማውጣት ሲሞከሩ ለክፍለ ከተማው የሲቪል ምዝገባ ጽ/ቤት በደረሰው ጥቆማ ግለሰቧ በቁጥጥር ስር እንድትውል መደረጉን ገልጿል። በተጨማሪም በግለሰቧ ተይዘው የተገኙ ሁለቱ መልቀቂያ (መሸኛ) ላይ ግለሰቧ በሁለት ብሔር ተገልፆ የተዘጋጀ መሆኑ ማየት መቻሉን አመልክቷል። ግለሰቧ አሁን ሀሰተኛ መሸኛ ይዘው በመገኘታቸው በህግ ጥላ ስር ሆነው ጉዳያቸው በአራዳ ክፍለ ከተማ የወረዳ 9 ፖለሲ በመጣራት ላይ እንደሚገኝ ኤጀንሲው አያይዞ ገልጿል። ለበለጠ መረጃ፣ ጥቆማ ወይም ማብራርያ በነፃ ስልክ መስመር 7533 ይደውሉ። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች