1 474
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-37 روز
-2130 روز
آرشیو پست ها
ከጀርመን አደባባይ - ጋርመንት - ሐጫሉ ጎዳና - ሐጫሉ አደባባይ እየተሰራ ያለው የኮሪደር ልማት የቀንና የምሽት ገፅታ!!
በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሩብ አመት ከደረቅ ቆሻሻ መልሶ መጠቀም ( Recycling) ከ515 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል።
በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አስተማማኝ የገበያ ትስስር በመፍጠር እና 27,133 ቶን ደረቅ ቆሻሻን ወደ ሀብት በመቀየር ከ515 ሚሊዮን ብር በላይ በዘርፉ የተሰማሩ ማህበራት ገቢ ማግኘታቸው ተገልጿል።
በአሁኑ ወቅት በመዲናችን የደረቅ ቆሻሻ ቆሻሻ መልሶ መጠቀም ተግባር ለበርካታ ወጣቶች የስራ እድል እየፈጠረ መሆኑን ከፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
በኢትዮጵያ ለጥበብ ልዩ ትኩረት በመስጠት ድንቅ ስራ እየተሰራ ነዉ፡፡ " የባህል እና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ
ሚንስተሯ ይህን የተናገሩት በትላንትነው እለት ጥቅምት 4/2018 በመዲናዋ የተገነባው አዲስ ሲኒማ ኮምፕሌክስ ህንጻ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት መሆኑን በገለፁበት ወቅት ነዉ፡፡
በመዲናዋ የተገነባው አዲስ ሲኒማ ኮምፕሌክስ ህንጻ ከፍተኛ የመንግስት ባልስልጣናት በተገኙበት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆን ተደርጓል፡፡
የባህል እና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ በምርቃት ስነ ስረዓቱ ላይ እንደተናገሩት የጥበባት ዘርፍ የሀገር ገጽታን የሚገነቡ፤ የማህበረሰብ ቢያኔን የሚሰጡ፣ ለባህል ልውውጥና ዲፕሎማሲ ዕድገት ቁልፍ ሚና የሚጫወት ዘርፍ በመሆኑ መንግስት የሃገራችን ጥበብ እንዲያድግ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
አያይዘውም በአዕምሯዊ ልማትና ብልጽግና ላይ ጥበባት ያላቸውን ፋይዳ በመረዳት መንግስት በልዩ ሁኔታ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ ሁለት ትላልቅ የጥበብ ማዕከላትን አስመርቆ ወደተግባር እንዲገቡ መደረጉን ጠቁመዉ ከተማ አስተዳደሩ ላደረገዉ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ለክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤና ለአመራራቸዉ ከፍ ያለ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
መንግስት በየደረጃዉ ከጥበብ ባለሙያዎች ጋር ዉይይቶችና ምክክሮችን ማድረጉ ገልፀዉ የኪነጥበብ ሙያተኞች የሚያነሷቸው ጥያቄዎች በህግ ማእቀፍ፤በፖሊሲና በአሰራር እየተፈተሹ ምላሽ እንዲያገኙ እየተሰራ ይገኛል ሲሉም ገልፀዋል፡፡
በመጨረሻም በኢትዮጵያ ለጥበብ ልዩ ትኩረት በመስጠት ድንቅ ስራ እየተሰራ በመሆኑ በዘርፉ ያሉ ባለሙያዎች ኪነጥበብ ለሀገር ግንባታ እና ለህብረብሄራዊ አንድነት ጉልህ ሚና እንዲያዉሉት መልእክታቸዉን አስተላልፈዋል፡፡
ዛሬ ያስመረቅነው ባለ 15 ወለል ዘመናዊ የሲኒማ ማዕከል በአይነቱ ልዩና ለኪነጥበብ እድገት አዲስ ምዕራፍ ከፋች መሆኑን ሳበስር በደስታ ነው !
መንግስት የኪነጥበብን ወሳኝ ሚና በመረዳትና ልዩ ትኩረት በመስጠት በቢሊዮኖች በጀት መድቦ በአይነታቸው ልዩና ዘመናዊ ለሲኒማ ፣ለቲያትር ራሳቸውን የቻሉ ትልልቅ ማዕከላት ሲገነባ ፤ በኪነጥበብ ዘርፈ የተሰማራችሁ ከያኒያንና የጥበብ ቤተሰቦች ሁሉ፣ ለአገራችን ሁለንተናዊ ብልጽግና መረጋገጥ መሰረት የሚሆኑ የጥበብ ስራዎችን በማበርከት፣ ታሪክ የማይዘነጋው ዘመን ተሻጋሪ አስተዋጽኦ እንደምታበረክቱ በማመን ነው ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
የረዳን ፈጣሪ የተመሰገነ ይሁን!
ዛሬ ለኪነጥበብ ቤተሰቦች እና ለከያኒያን ተጨማሪ ብስራት የሆነውን አዲሰ እና እጅግ ዘመናዊ አዲስ ሲኒማ ኮምፕሌክስ ህንፃ ግንባታ አጠናቅቀን መርቀን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል።
በአይነቱ የመጀመሪያ እና እጅግ ዘመናዊ የሆነውን የህፃናትና ወጣቶች ቴአትርና ሲኒማ ኮምፕሌክስ መርቀን ብዙም ሳንቆይ፣ ዓለም በፊልም ኢንዱስትሪው የደረሰበት ደረጃ ለመድረስ በያዝነው ዕቅድ መሰረት፣ ለኪነጥበብና ለከያኒያን ትልቅ የምስራች የሆነውን አዲስ እና እጅግ ዘመናዊ ሲኒማ ኮምፕሌክስ ህንፃ በዛሬው ዕለት ስራ አስጀምረናል።
አዲስ ሲኒማ ኮምፕሌክስ ህንፃ፣ ባለ 15 ወለል ሲሆን የህንፃው አጠቃላይ ስፋት 24,000 ካ.ሜ ሆኖ ባለ አራት ወለል የመኪና ማቆሚያ የያዘ ነው። 592 ህፃናትንና 887 አዋቂዎችን የመያዝ አቅም ያላቸው ሁለት የሲኒማ አዳራሾችን ጨምሮ በቂ የሆነ የድምፅ ማስተላለፊያ ሲስተም፣ ዘመናዊ የመብራት ስርጭት፣ የአየር መቆጣጠሪያ መሳሪያዎችን አካቷል።
በተጨማሪም፤ ለቢሮዎች፣ ለእስቱዲዮ፣ ለሥዕል እና አርት ጋለሪ፣ ለቤተመፃሕፍት እና ለተለያዩ ተያያዠ አገልግሎቶች፣ ለካፍቴሪያ፣ ለሱፐርማኬት፣ ለምግብ ቤት፣ ለሱቆች፣ ለውበት ሳሎን፣ ለባንክ አገልግሎት፣ የትኬት መሸጫ ቢሮዎች እና ለጉብኝት አገልግሎት የሚውሉ ክፍሎችንም አሟልቷል።
በቅጥር ጊቢውም የልጆች መጫወቻ የስፖርት ሜዳ፣ የመኪና ማቆሚያና አረንጓዴ ስፍራዎችን ጨምሮ ለማስታወቂያ የሚሆኑ ስክሪኖች እና ዘመናዊ ሊፍቶች እንዲሁም የፓርኪንግ ቴክኖሎጂዎች ተገጥመውለታል።
በዚህ አዲስና ዘመናዊ ለትውልድ ተሻጋሪ የሆነ ስራ ላይ የተሳተፋችሁ አማካሪዎች፣ ተቋራጮች እና የኪነጥበብ ባለሙያዎች፣ አመራሮች እና ሰራተኞች፣ ደከመን ሰለቸን ሳትሉ የተሳተፋችሁትን በሙሉ በከተማ አስተዳደሩ እና በራሴ ስም ላመሰግናችሁ እውዳለሁ፡፡
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
የኮሚሽኑ የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች ለሚከፍሉት መስዋዕትነት ክብር እንዳላቸው በመልካም አስተዳደር ውይይት ላይ የተገኙ ተሳታፊዎች ገለጹ ።
የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን በሚሰጣቸው አገልግሎቶችና በመልካም አስተዳደር ዙሪያ ከሁሉም ክ/ ከተሞች ከተወጣጡ የህብረተሰብ ተወካዮች ጋር ዛሬ ጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ውይይት አካሂዷል ።
በውይይት መድረኩ ኮሚሽኑ በሁሉም ዘርፎች እየሰጣቸው የሚገኙ አገልግሎቶችን መሠረት ያደረገ የመነሻ ሪፖርት የቀረበ ሲሆን በኮሚሽኑ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የታዩ የመልካም አስተዳደር ጉድለቶች ካሉ እንዲቀርቡ ለተሳፊዎች ዕድል ተሰጥቶ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል፡
የውይይት መድረኩ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት ኮሚሽን
መ/ቤቱ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች በተመለከተ ያላቸው መረጃ ውስን መሆኑን ጠቅሰው ኮሚሽኑ አደጋን ከመቀነስ አንጻር ወደ ህብረተሰቡ በስፋት በመቅረብ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራዎችን በልዩ ትኩረት እንዲያከናውንና በአደጋ ጊዜ የአደጋ ተሽከርካሪዎችን በማያስገቡ አካባቢዎች ምቹ ሁኔታን ከመፍጠር አንጻር እንደዚሁም በአደጋ ጊዜ በቅንጅት ከሚሰሩ ተቋማት ጋር የተቀናጀና የተናበበ ተግባር እንዲኖር ያስፈልጋል የሚሉና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን በስፋት አቅርበዋል ።
አያይዘውም የኮሚሽኑ የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች የሠውን ህይወትና ንብረት ለማዳን በሚያደርጉት ጥረት ለሚከፍሉት መስዋዕትነት ክብር እንዳላቸው ጠቅሰው በተለይም አደጋን ለመቀነስ በሚደረገው ጥረት ሁሉ ከኮሚሽኑ ጋር በቅርበትና በትብብር እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።
የውይይት መድረኩን የመሩት ም/ኮሚሸነርና የአደጋ ምላሽ ዘርፍ ኃላፊ ኮማንደር መስፍን አያሌውና የኮሚሽኑ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ መላኬ አለማየሁ በሰጡት ማብራሪያ ኮሚሽኑ የሠውን ህይወትና ንብረት ከማናቸውም አደጋ ለመጠበቅና ከተማዋን ከአደጋ ስጋት ነጻ ለማድረግ መስዋዕትነት በመክፈል ጭምር እየሠራ መሆኑን ጠቅሰው ከተሳታፊዎች የተነሱ ገንቢ አስተያየቶችን በ2018 ዓ.ም እቅድ አፈጻጸም ላይ ተጨማሪ ግብዓት ሆነው እንደሚካተቱ ገልጸዋል::
አያይዘውም ከከተማው ነዋሪ ጋር የሚካሄዱ መሰል የውይይት መድረኮች ኮሚሽኑ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ውጤታማ የሚያደርጉ በመሆናቸው በተለያዩ አግባቦች ተጠናከረው የሚቀጥሉ መሆኑን ተናግረዋል።
ከተሳታፈዎች ለተነሱ ጥያቄና አስተያየቶች በየደረጃው ባሉ የኮሚሽኑ አመራሮች ምላሽና ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን በውይይት መድረኩ ከአስራ አንዱም ክፍለ- ከተሞች የተወጣጡ 600 ተወካዮች ተሳትፈዋል።
ድሮ ከግለሰብ ግቢ መብራት ማውጣት ብርቅ ነበረ።የአዲስ አበባን ውበት በይበልጥ የገለጠው በመንገድ መብራት ላይ የተሰራው ስራ ነው።የመብራት መሠረተ ልማቶቻችን ከጉዳትና ከስርቆት መጠበቅ የሁሉም ዜጋ ሃላፊነት ነው።"
በም/ከንቲባ ማ… See more
