Ministry of innovation and technology (MinT)
Ministry of innovation and Technology (MinT) is a governmental institution ...
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام Ministry of innovation and technology (MinT)
کانال Ministry of innovation and technology (MinT) (@mintethiopia) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 12 134 مشترک است و جایگاه 4 286 را در دسته سیاست و رتبه 2 785 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 12 134 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 03 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 312 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 8 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 13.64% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 6.15% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 1 655 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 746 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 7 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“Ministry of innovation and Technology (MinT) is a
governmental institution ...”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 04 سپتامبر, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته سیاست تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 04 سپتامبر | +1 | |||
| 03 سپتامبر | +10 | |||
| 02 سپتامبر | +10 | |||
| 01 سپتامبر | +13 |
| 2 | የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ያደራጀው የፍትሕ ሙዚዬም በዛሬው እለት ተመርቋል።
=====================
ሙዝየሙን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ እና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላ መርቀውታል።
በዝግጅቱ ላይ የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ሙዚዬሙ በሀገራችን እና በክልላችን የፍትሕ እና የፍርድ ሥርዓት አሥተዳደር ከተጀመረበት ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ያለውን በግልጽ በሚያሳይ መልኩ የተደራጀ ነው ብለዋል።
ይህም በሀገራችን የፍትሕ አሥተዳደር እና የፍርድ ቤቶች አሠራር ጋር በተያያዘ ለጥናት እና ምርምር መሠረት የሚኾን ስለመኾኑም ተናግረዋል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የክልሉን ፍርድ ቤቶች አገልግሎት አሰጣጥ
ለማዘመን የሰራው ስራ የሚበረታታ መሆኑን ገልጸዋው ተግባሩ የመንግስት አገልግሎቶች በማዘመን የተገልጋዮችን እርካታ ማሳደግ የሚችል መሆኑን አንስተዋል።
ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በሚደረገው ጥረት የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰራው ስራ ለሌሎች ማሳያ ሊሆን የሚችል መሆኑን ተናግረዋል።
ከምርቃቱ በተጨማሪ የጠቅላይ ፍርድ ቤቱን የዲጅታላይዜሽን መሰረተ ልማቶች፣ ግልጽ እና የርቀት ክርክር የሚካሄድባቸው ዘመናዊ የችሎት አዳራሾች፣ የአንድ ማዕከል ዲጅታል አገልግሎት እና ባለጉዳዮች የፈለጉትን መረጃ ማግኘት የሚችሉበትን የጥሪ ማዕከል ጨምሮ በዘመናዊ መልኩ የተደራጀውን የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፍትሕ ሙዚየም ጎብኝተዋል።
ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የተገበራቸው ወረቀት አልባ የዳኝነት አገልግሎቶች እና ሌሎች የለውጥና የማሻሻያ ስራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱባቸው መሆኑ በፕሮግራሙ ላይ ተነስቷል። | 771 |
| 3 | ወጣቶች በእጃቸው የያዙትን ስማርት ስልክ ለመዝናኛ ብቻ ሳይሆን እንደ ዋና የቴክኖሎጂ ትምህርት ቤት በመጠቀም ለሚመጣው የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ዘመን ራሳቸውን ማዘጋጀት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የመንግሥት ሥራም ሆነ የአገልግሎት አሰጣጥ ለፈጠራና ለውሳኔ ሰጪነት በሚያበቃ መልኩ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ አሠራሮችን የታጠቀ መሆን እንዳለበት ሚኒስትሩ አሳይተዋል።
የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ግቦች ለማሳካት በተቋማት መካከል ያሉ የመረጃ ቋቶች እርስ በእርስ የሚናበቡበትና በሕጋዊ ማዕቀፍ መረጃ የሚለዋወጡበት ሀገራዊ ሥርዓት ይዘረጋል።
ሚኒስትሩ አክለውም፣ ትኩረታችንን በፈጠራና በሀገር ግንባታ ላይ በማድረግና እጅ ለእጅ ተያይዘን በመሥራት ለትውልድ የምትሻገር የበለፀገች ሀገር እንገነባለን ብለዋል። | 942 |
| 4 | "ስማርት ስልክ በእጃችሁ ያለ የቴክኖሎጂ ትምህርት ቤት ነው" — ዶ/ር በለጠ ሞላ።
==============
የአማራ ክልል ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ቢሮ "ኤሌክትሮኒክስ መንግሥት ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 መሠረት" በሚል መሪ ቃል የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት የፓናል ውይይት አካሄደ።
በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላ ኢትዮጵያ የዲጂታል 2025 ስትራቴጂን በመተግበር የሕዝብ አገልግሎቶችን ለማዘመን ያደረገችው የተቀናጀ ርብርብ ተጨባጭ ውጤት ማምጣቱን ገልጸዋል።
አገልግሎቶችን ከወረቀት ንክኪ ነፃ በማድረግ ረገድ ከ49 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት መሆናቸውንና በቴሌብር፣ በባንክ ዲጂታል መድረኮች እንዲሁም በመሶብ አገልግሎት ተጠቃሚነታቸው ማረጋገጡን ሚኒስትሩ አብራርተዋል።
የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን እውን ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመው፣ የተደራሽነት ማስፋፋት፣ የእኩል ዕድል ፈጠራና የተቋማት እምነት ግንባታ የዚሁ ትኩረት አካል መሆናቸውን አስገንዝበዋል።
በአማራ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ የተዘጋጀው አውደ ርዕይ የተቋማትን ዲጂታል ግንዛቤ ለማሳደግ፣ የፈጠራ ሥራዎችን ለማስተዋወቅና የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን ለማፋጠን የጎላ ሚና እንደሚያበረክት ተናግረዋል።
ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 የመንግሥት አጀንዳ ብቻ ሳይሆን በሕዝብና በመንግሥት መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያጠናክር እውነተኛ መስተጋብር እንደሆነ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
የዲጂታል መሠረተ ልማት አቅርቦት የቅንጦት ጉዳይ አለመሆኑን ያብራሩት ዶ/ር በለጠ፣ ቴክኖሎጂ ለሁሉም ዜጎች በግልጽነትና በእኩልነት የሚያገለግል አድልኦ አልባ ድልድይ መሆኑን ጠቁመዋል። | 771 |
| 5 | በባሕር ዳር ከተማ "ኤሌክትሮኒክስ ለዲጂታል 2030 መሠረት" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው ታላቅ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ዐውደ ርዕይ በይፋ ተከፈተ።
==============
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ እና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላ በጋራ በመሆን ከነሐሴ 28 እስከ 30/2018 ዓ.ም ድረስ በባሕር ዳር ከተማ የሚቆየውን ዐውደ ርዕይ በይፋ አስጀምረዋል።
ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ባለፉት ሦስት ዓመታት በክልሉ የበለጸጉና በፍትሕ፣ በትምህርት፣ በጤና፣ በሲቪል ሰርቪስ፣ በገቢወች፣ በኢንቨስትመንት፣ በግብርና፣ በቱሪዝም፣ በመሬት አስተዳደር እና በልዩ ልዩ ዘርፎች የላቀ አገልግሎት የሚሰጡ ከ35 በላይ ችግር ፈቺ ዲጂታል መተግበሪያዎችን መርቀው ወደ ሥራ አስገብተዋል፡፡
ይህ በክልሉ የተመዘገበው አስደናቂ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እመርታና አዳዲስ የቴክኖሎጂ ስኬቶች፣ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ለሀገራዊው "ዲጂታል ኢትዮጵያ" ራዕይ መሳካት የሚያደርገውን ጥረት በተግባር የሚያጠናክርና ለሌሎች ክልሎችም አርአያ የሚሆን ታላቅ ስኬት ነው።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ዶ/ር በለጠ ሞላ በፌደራልና በክልል ተቋማት መካከል ያለውን ቅንጅት በማጠናከር የተጀመሩ የቴክኖሎጂ ሽግግሮችና አዳዲስ አሰራሮች ዘላቂ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤታቸው አስፈላጊውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በዐውደ ርዕዩ በሥራ ላይ ያሉ ሲስተሞች ለጎብኝዎች ክፍት ከማድረጋቸው ባሻገር፣ በዲጂታላይዜሽን ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶችንና በቀጣይ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ የሚመክሩ የፓናል ውይይቶችም ይካሄዳሉ። | 841 |
| 6 | የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት የኢትዮጵያ መንሠራራት በሚል መሪ ሐሳብ፣ በአምስቱ የጳጉሜን ቀናት ስያሜዎች ይከበራል፡፡ | 849 |
| 7 | በመድረኩ የቀረበው የሪፎርም ጥናት የተቋሙን አሰራር ለማዘመን፣ የሙያ ብቃትን ለማሳደግ እና የሕዝብ አገልግሎት አሰጣጥን ለማሳለጥ የሚያስችሉ ቁልፍ ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎችን አመላክቷል።
ይህ ስኬታማ የሪፎርም ምዕራፍ መሸጋገር ተቋሙ ወደፊት ለሚያከናውናቸው የዲጂታልና የቴክኖሎጂ ትራንስፎርሜሽን ሥራዎች ጠንካራ መሠረት የሚጥል ነው። | 2 025 |
| 8 | የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ዘርፍ በሀገራዊ የሪፎርም ለውጥ ላይ ስኬታማ ጉዞ በማድረግ ወደ ቀጣይ ምዕራፍ ተሸጋገረ።
================
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የሙያ ምድብ፣ የሥራ ፍሰት አደረጃጀት እና የቴክኒካል ብቃት ማዕቀፍ ዝግጅት በፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች የግምገማ መድረክ ተካሄደ።
በመድረኩ ላይ የተገኙት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላ፣ መንግሥት የጀመረውን ፈጣን የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን በብቃት መፈጸም የሚችል ጠንካራ ሲቪል ሰርቫንት በመገንባት ሀገር ወደ ተሻለ ምዕራፍ የምትሸጋገርበት ሥርዓት መፈጠር እንዳለበት አስገንዝበዋል።
ሚኒስትሩ አክለውም፣ የላቀ ሀገራዊ እድገትን ለማረጋገጥና ዘመናዊ አሰራርን ለማስፈን ያለሙ የሪፎርም ሥራዎች በበለጠ ቁርጠኝነትና ጥንካሬ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
ለተደረገው ክትትልና ድጋፍ ለኮሚሽኑ ምስጋናቸውን ያቀረቡት ሚኒስትሩ፣ የተቋሙን አደረጃጀትና የሥራ ፍሰት ማሻሻል ለሕዝብ የሚሰጠውን አገልግሎት ጥራትና ቅልጥፍና ለማረጋገጥ ወሳኝ ድርሻ እንዳለው አንስተዋል።
የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነር ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በሪፎርም ትግበራው ባሳየው የላቀ ርብርብ ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ ወደ ቀጣዩ የተግባር ምዕራፍ መሸጋገሩን በግምገማ መድረኩ ላይ አብሰርዋል።
ኮሚሽነሩ ለተገኘው የላቀ ውጤት የተቋሙ ከፍተኛ አመራር ላሳየው ቁርጠኝነትና መሪነት ምስጋና አቅርበው፣ በቀጣይም ከሪፎርሙ የሚጠበቀውን ውጤት ለማምጣት ተቋማቸው አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል። | 1 921 |
| 9 | አክለውም ማዕከሉ በቀጣይም ታዳጊዎችንና ወጣቶችን በመቀበል ፕሮግራመሮችን፣ ኮደሮችን፣ ዲዛይነሮችንና መሀንዲሶችን ለማፍራት የሚያስችሉ ተግባራዊ የስልጠና መርሃ ግብሮችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በመጨረሻም፣ ከመጀመሪያ ደረጃ እስከ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተውጣጡት እነዚህ ሰልጣኞች በቡድን በመደራጀት በሮቦቲክስ፣ በፕሮግራሚንግ፣ በዲዛይንና በምህንድስና ዘርፎች ያበለጸጉዋቸውን ችግር ፈቺ የፈጠራ ሥራዎች ወደ ተግባር እንደሚቀይሩ ተመላክቷል። | 1 434 |
| 10 | በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግ እና ሒሳብ (STEM) ሮቦቲክስ ቴክኖሎጂ ፈጠራ የክረምት ሰልጣኞች ውድድር ተካሄደ።
==============
በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና በኢትዮ-ሮቦቲክስ ትምህርትና ውድድር ማዕከል ትብብር ሲሰጥ የቆየውን የክረምት ወራት ሥልጠና ያጠናቀቁ ሰልጣኞች፣ ያካበቱትን የንድፈ-ሀሳብና የተግባር እውቀት በመጠቀም ያበለጸጉትን የፈጠራ ውጤት የሚያቀርቡበት የደረጃ መለያ ውድድር በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አዳራሽ ተካሂዷል።
ይህ ውድድር በኤፕሪል 2027 በአሜሪካ ሴንት ሉዊስ ከተማ በሚካሄደው ዓለም አቀፍ የ በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግ እና ሒሳብ (STEM) ሮቦቲክስ ቴክኖሎጂ ፈጠራ ውድድር ላይ ሀገራቸውን በብቃት ወክለው የሚሳተፉ ታዳጊዎችንና ወጣቶችን ለይቶ ለማዘጋጀት ያለመ ነው።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ባይሳ በዳዳ በሥነ-ሥርዓቱ ላይ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር፣ መንግስት ለሀገሪቱ ሁለገብ እድገት በፈጠራ ሥነ-ምህዳሩ ላይ ባመቻቻቸው ምቹ ሁኔታዎች ምክንያት ወጣቶች የቴክኖሎጂ ፈጠራ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን ገልጸዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው አክለውም ወጣቶች እውቀታቸውን ወደ ተግባር በመቀየር የህብረተሰቡን ችግር የሚፈቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እንዲፈጥሩና የሀገሪቱን የዲጂታል ሉዓላዊነት እንዲያረጋገጡ ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን፣ ወላጆችም ለልጆቻቸው ዘላቂ እውቀትና ክህሎት አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።
የኢትዮ-ሮቦቲክስ ትምህርትና ውድድር ማዕከል ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ ሰናክሬም መኮንን በበኩላቸው፣ ሰልጣኞች ከስልጠናው የሚያገኙትን እውቀት ተጠቅመው የማህበረሰብ ችግሮችን መፍታት የሚችሉ ፈጣሪዎች እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል። | 1 258 |
| 11 | የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ክፍት የስራ መደብ ማስታወቂያ | 1 393 |
| 12 | ኢትዮጵያ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂው ዘርፍ ያመጣቻቸውን ስኬቶች ለአፍሪካ ሀገራት በማጋራት ለአህጉራዊ እድገት በጋራ እየሰራች ነው።
===============
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከናሚቢያ ብሔራዊ የምርምር፣ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኮሚሽን እና ከታንዛኒያ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኮሚሽን ከተውጣጡ ከፍተኛ ልዑካን ጋር የአፍሪካ የኢኖቬሽን ኤጀንሲዎች ኔትወርክ (IAA) ሴክሬታሪያት አስተባባሪነት የተዘጋጀውን የሦስት ቀን አህጉራዊ የልምድ ልውውጥ አካሂዷል።
በካናዳው ዓለም አቀፍ የልማት ምርምር ማዕከል እና በደቡብ አፍሪካው ብሔራዊ የምርምር ፋውንዴሽን የሚደገፈው የኢኖቬሽን ኤጀንሲዎች ኔትወርክ (IAA)፣ ኢትዮጵያን ጨምሮ የአባል ሀገራትን ተቋማት በማስተባበር ሁለንተናዊና ጠንካራ የፈጠራ ሥነ-ምህዳር በመገንባት ላይ ይገኛል።
በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የተገኙት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ባይሳ ባዳዳ፣ ኢትዮጵያ ሀገራዊ ኢኮኖሚዋን ለማጎልበት በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ዘርፍ በመሠረተ ልማት፣ በሕግ ማዕቀፍ እና በሰው ኃይል ልማት ላይ ባከናወነቻቸው ሰፊ ተግባራት ስኬታማ ውጤቶችን ማስመዝገቧን ገልጸዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው አክለውም ሀገሪቱ በዘርፉ ያላትን አቅም በላቀ ደረጃ ለማሳደግና አህጉራዊ ተወዳዳሪነቷን ለማረጋገጥ ከዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር ያለውን ስልታዊ ትብብር አጠናክራ የምትቀጥል መሆኑን አብራርተዋል።
በልምድ ልውውጡ የተሳተፉት የናሚቢያና የታንዛኒያ ልዑካንም በቆይታቸው ያገኙትን ተሞክሮ መሠረት በማድረግ ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ የሚተገብሯቸውን ተጨባጭ የድርጊት መርሐግብሮችና የቀጣይ የጋራ ትብብር አቅጣጫዎች እንደሚቀርፁ አመላክተዋል።
የልዑካን ቡድኖቹ የኢትዮጵያን የስታርትአፕ አዋጅ ዝግጅት፣ የሥራ ፈጠራ ፈንድ አሠራር፣ እንዲሁም በኢኖቢዝ-ኬ (InnoBiz-K)፣ ክሬቲቭ ሀብ እና በአርቲ | 1 553 |
| 13 | +2 1.JPG | 1 |
| 14 | እንኳን ለ1 ሺህ 5 መቶ 1 ኛው የነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) መውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
መልካም የመውሊድ በዓል!
ዶ/ር በለጠ ሞላ
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር | 2 052 |
| 15 | بدون متن... | 1 |
| 16 | በቴክኖሎጂ የታገዘ የመንግሥት ንብረት አስተዳደር ሥርዓት ትግበራ ላይ በትኩረት ሊሠራ እንደሚገባ ተገለጸ።
================
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ለሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች በፌደራል የመንግሥት ንብረት አስተዳደር ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ።
የሥልጠናውን መድረክ የከፈቱት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የኦዲት ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሻግሬ አለሙ፤ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን የንብረት አስተዳደር ሥርዓት በቴክኖሎጂ ለማዘመን በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ኃይል ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ሀገራዊ ሀብትን ከብክነት ለመታደግና በቁጥጥር ሥርዓቱ ላይ ውጤታማነትን ለማረጋገጥ፣ አገልግሎት ሰጪውም ሆነ ተገልጋዩ ማኅበረሰብ በፌደራል የመንግሥት ንብረት አስተዳደር ላይ በቂ ግንዛቤ ሊኖረው እንደሚገባ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ዘርፉን ለማሳለጥ የዲጂታላይዜሽን ሥራዎችን በትኩረት እያከናወነች በመሆኗ፣ የንብረት አስተዳደር ሥርዓቱን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በማደራጀት ለታለመለት ዓላማ ማዋል የሁሉም ባለድርሻ አካላት ኃላፊነት መሆኑን አንስተዋል።
በፌደራል የመንግሥት ንብረት አስተዳደር አዋጆች፣ መመሪያዎችና ደንቦች ላይ የሚፈጠር ግልጽ ግንዛቤ የሀገር ሀብትን ከአላስፈላጊ ብክነት በመጠበቅ ረገድ የጎላ ሚና ይጫወታል።
የሥልጠናው ተሳታፊዎች ያገኙት ሰፊ እውቀት ለቀጣይ ሥራቸው አጋዥ መሆኑን በመግለጽ፣ መሰል የአቅም ግንባታ መድረኮች ተጠናክረው ለሁሉም አካላት ተደራሽ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል። | 2 408 |
| 17 | በተጨማሪም ዘርፉ ወደ ሙሉ ትግበራ በሚሸጋገርበት ወቅት ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮችን ለመቅረፍ፣ የመንግሥት ሠራተኞችን የብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ሥርዓት መገንባትና የማስፈጸም አቅምን ማሳደግ የሚያስችሉ የሪፎርም ሥራዎችን በቀጣይ ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ጋር ተቀራርቦ ለማከናወን አቅጣጫ ተቀምጧል።
በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የተገኙት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላ፣ ሪፎርሙ የተመራበት ሂደት ጠንካራ በመሆኑ ተስፋ ሰጭ ውጤት ማስገኘት መቻሉን ገልጸዋል።
በተለይም በሪፎርሙ መሠረታዊ ጽንሰ-ሐሳቦችና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የተሰጠው የአቅም ግንባታ ድጋፍ ለዝግጅት ምዕራፉ ስኬት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስረድተዋል።
በግምገማ መድረኩ የተሳተፉት የዘርፉ አማካሪዎች፣ መሪ ሥራ አስፈጻሚዎች፣ የሪፎርም ቴክኒክ ኮሚቴና ንዑሳን ኮሚቴ ሰብሳቢዎች በበኩላቸው፤ የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርምን በሰባቱ መሠረታዊ የፖሊሲ ምሰሶች ከዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊና አገራዊ ሁኔታዎች ጋር ያገናዘበ የዳሰሳ ጥናት መደረጉን ገልጸው በቀሪ ሥራዎች ላይም ያላቸውን ዝግጁነት በመግለጽ ውይይቱ ተጠናቋል። | 2 533 |
| 18 | የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የመንግሥት የአገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የዝግጅት ምዕራፍ አፈጻጸም ተገመገመ።
================
በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ከአለፈው ዓመት (2018 ዓ.ም) ጀምሮ ለአንድ ዓመት ገደማ በሪፎርም ቴክኒክ ኮሚቴ ሲካሄድ የቆየው የመንግሥት የአገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የዝግጅት ምዕራፍ አፈጻጸም ግምገማና ውይይት ተካሄደ።
በግምገማው ከኢፌዲሪ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፣ ከፕላንና ልማት ሚኒስቴር፣ ከገንዘብ ሚኒስቴር እና ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የተውጣጣ የከፍተኛ ኃላፊዎች ቡድን ተሳታፊ ሆኗል።
የገምጋሚ ቡድኑ አባላት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ዘርፍ በሁለተኛው ዙር (Wave) ከተካተቱት የፌዴራል ተቋማት አንዱ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚኒስቴሩ ዋና መሥሪያ ቤት እስከ አራቱ ተጠሪ ተቋማት ድረስ ለሁለት ቀናት አካላዊ ምልከታና ግምገማ አካሂደዋል።
በዚህም በሰባቱ መሠረታዊ የፖሊሲ ምሰሶች ሥር የተቀመጡ የዝግጅት ምዕራፍ ተግባራት አፈጻጸም በቁልፍ የሥራ አፈጻጸም መለኪያዎች (KPIs) ሲገመገም ውጤታማና አበረታች መሆኑን አረጋግጠዋል።
ቡድኑ ባቀረበው የግምገማ ሪፖርትና በሰጠው አስተያየት በዘርፉ በተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎች ጥራት ያላቸው ሰነዶች መዘጋጀታቸውንና የሥራ ቦታ ምቹነት ከተጠበቀው በላይ መሆኑን በአካል ተዟዙሮ ማረጋገጡን አመላክቷል።
በተለይም ምቹ የሕፃናት ማቆያዎችና የመጸዳጃ ቤቶች መገንባታቸው፣ የአቅጣጫ መጠቆሚያዎች መዘጋጀታቸው እንዲሁም በዲጂታል ሥርዓት የተደገፈ የተገልጋይ ድጋፍ ማዕከል መዘርጋቱ በአርአያነት የሚጠቀስ ጠንካራ ጎን መሆኑ ተነስቷል። | 1 965 |
| 19 | ሀገራዊ እድገትን ለማፍጠን ትብብር ወሳኝ መሆኑን የጠቆሙት ከንቲባው፣ ከአረንጓዴ አሻራው ባሻገር በሕፃናት የትምህርት መሠረት ላይ የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ገልጸዋል።
በዕለቱ የ10 ሺህ ችግኞች ተከላ ከተከናወነበት መርሃ ግብር ጎን ለጎን፣ የመዋዕለ ሕጻናት ትምህርት ቤት የግንባታ ማስጀመሪያና ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው 200 ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል።
በመጨረሻም በጎ ፈቃደኝነት የቁሳቁስ ብቻ ሳይሆን የእውቀትና የጉልበት አስተዋጽኦ ማበርከት ጭምር በመሆኑ፣ ህብረተሰቡ የተተከሉትን ችግኞች ተንከባክቦ የማሳደግ ሀገራዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ ተላልፏል። | 1 747 |
| 20 | የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በደብረ ብርሃን ከተማ የ10 ሺህ ችግኞች ተከላ እና የመዋዕለ ሕጻናት ትምህርት ቤት ግንባታ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር አካሄደ።
================
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በሰሜን ሸዋ ዞን በታሪካዊቷና የኢንዱስትሪ ማዕከል በሆነችው ደብረ ብርሃን ከተማ በመገኘት የአካባቢ ጥበቃን ለማጎልበት ያለመ የአረንጓዴ አሻራ እና የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብር አከናውኗል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ልዑል ስዩም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ችግኝ ከመትከል ባሻገር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ዘላቂ ሀገራዊ ራዕይን ለማሳካት ያለመ በመሆኑ ሁሉም ዜጋ የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ኃላፊው አክለውም የሀገራችን የነገ ተረካቢ እና የቴክኖሎጂ ልዕልና ባለቤት የሚሆኑ ሕፃናት ላይ መሠረት ለማጣጣል የሚያስችል የመዋዕለ ሕጻናት ትምህርት ቤት ግንባታ ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
የሀገራችንን ዘላቂ የኢኮኖሚ እድገትና ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ የሚከናወኑ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሽግግርና የአረንጓዴ አሻራ ልማት ስራዎች የሚፈለገውን ውጤት ያመጡ ዘንድ፣ እያንዳንዱ ዜጋ በዲጂታል ክህሎት ግንባታና በአካባቢ ጥበቃ እንቅስቃሴዎች ውስጥ በንቃት በመሳተፍ ሀገራዊ ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባም አመላክተዋል።
የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በበኩላቸው፣ ከሚኒስቴሩ ጋር የሚደረገው የጋራ እንቅስቃሴ በማህበረሰቡ ዘንድ ከፍተኛ መነሳሳትን ከመፍጠሩም በላይ ለቴክኖሎጂው ዘርፍ እድገት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ተናግረዋል። | 1 606 |
